1ኛ የጴጥሮስ መልእክት5:8
| ||
"በመጠን ኑሩ ንቁም፥ ባላጋራችሁ ዲያብሎስ የሚውጠውን ፈልጎ እንደሚያገሣ አንበሳ ይዞራልና" እንዳለው በመጠን አልኖርም ብሎ የታበየው ማቅ በትዕቢቱ ሊጠፋ ተቃርቧል።
|
የጽሁፍ ምንጭ፤ ዐውደምህረት ብሎግ
· ማኅበረ ቅዱሳን የመፍረስ አደጋ ያሰጋዋል
· ውግዘቱ ሥርአተ ቤተክርስቲያንን ያልተከተለ ነው፤ ይወገዛሉ የተባሉት ግለሰቦች ተጠርተው አልተጠየቁም
· አባ ሠረቀብርሃንና ዲ/ን በጋሻው ስማቸው ይወገዙ ከተባሉት ውስጥ የለም
ቅዱስ
ሲኖዶስ ትናንትና በነበረው የስድስተኛ ቀን ውሎው ሁለት ዋና ዋና ጉዳዮችን ያነሳ ሲሆን የጠዋቱ የማኅበራት ጉዳይ ነው። ከሰዓት በኋላ ደግሞ የተነሳው የሃይማኖት ህጸጽ አለባቸው ስለተባሉ ግለሰቦችና ማኅበራት ጉዳይ ነው።
በጠዋቱ
ውሎ በማኅበራት ጉዳይ ላይ የተሰናዳው ጥልቅ ጥናት የቀረበ ሲሆን ጥናቱም በሃይማኖት ጸሎት ላይ ያለውን “ወነአምን በአሐቲ ቅድስት ቤተክርስቲያን እንተ ላዕለ ኩሉ ጉባኤ ዘሐዋርያት” በሚለው መሰረት ጉባኤ የሚለው አንዲት ቤተክርስቲያንን ነውና ሌሎች ማኅበራት አያስፈልጉም። አንዲቷ ቤተክርስቲያን ራስዋ ማኅበር ናትና የሚል ጥቅል ይዘት ያለው ጥናት ቀርቦዋል። ጥናቱ ሁሉንም አባቶች ያስደሰተ ሲሆን፣ አንዳንድ አባቶች ከውሳኔ በፊት ጥናቱ ለሁላችንም ይሰጠንና እናንብበው ብለው ሲጠይቁ አቡነ ቄርሎስ ጥናቱ በጥሩ ሁኔታ ቀርቦአል። ትክክል የምንለውን ውሳኔ መወሰን ነው እንጂ ጽሁፉን እንደገና ወስደን የምናነበው ለምንድን ነው? ብለው በመጠየቃቸው ተባዝቶ ይሰጠን የሚለው ሀሳብ ቀርቶ በጉዳዩ ላይ ዛሬ ለመወሰን ቀጠሮ ተይዟል። ማኅበሯን ትልቅ ስጋት ውስጥ የከተታትም ይኸው ውሳኔ ነው ተብሏል።