Friday, May 4, 2012

«አሁን ደግሞ ገፍተው፤ ገፍተው ማንን ይሆን የሚወረውሩት?»

                                                                      (by dejebirhan)
አንድ ሰሞን የዘመድኩን በቀለ ትኩሳት  «በደጀሰላምና አንድ አድርገን» እንዲሁም በሌሎቹ ውርንጭላ ብሎጎች ሳይቀር፤  ይሄ ነው የተዋህዶ ልጅ፣ ሲኦልም ቢሆን ግባ፤ ውረድ ፣ ዘመድኩን  የአባ ቢላዋ ልጅ፣ ቆራጡ፤ እሳቱ፤ አንድ ለእናቱ፤ ጀግናው ፣ ሰማእቱ ምኑ ቅጡ፤ ያልተባለ፣ ያልተወራ ነገር አልነበረም። ከወሬ አቀባባዮቹ ብሎጎች አንስቶ፤ የወሬ አቀባባዮቹ አስተያየት ሰጪዎች ሁላቸውም በአንድነት፤ በአንድ ጀምበር ዘመድኩንን አጽድቀው፣ እነሱንም የሰማእትነት ሲቃ በሚተናነቃቸው  አስተያየቶች ተዥጎድጉደው ድረ ገጾቹን በእንቶ ፈንቶ አቆሽሸው ዘመድኩንን ከእርቅ አጣልተው ሲያበቁ ለተመኙለት   የእነሱ  ሲኦል (በኛ በኩል ግን እስር ቤት) ዱለውት ሲያበቁና  ፋይሉ ተዘግቶ ወደ መዝገብ ቤት መልስ  ሲሆን አንድም አጨብጫቢ ቃሊቲ አብሮት ሳይወርድ ያ ሁሉ ጯሂ የራሱን ኑሮ ወደማሞቁ መመለሱን ታዝበን ተገርመናል፣ ምናልባትም ዘመድኩን ዛሬ ላይ ሆኖ የያኔውን ግፋ በለው ፤ዓይኑን ገልጦ ሲመለከት  ያን ሁሉ ጆፌ አሞራ እንደእኛው ታዝቦ  ምን እንደሚሰማው ስንገምት «ሰውን ማመን ቀብሮ ነው» በተለይም ማቅን ማመን ውሃ መጨበጥ ነው፤ ይል ይሆናል። ያም ሆነ ይህ ጥሩ የትምህርትና ነገሮችን የማመዛዘን ጊዜ እንደሚሆንለት አይጠረጠርም። በዚያ መጠቀም ሳይችል ቀርቶ በከሰሱኝ  ሰዎች ላይ ቂሜ አይበርድም በሚል  ስሜት  በቀል አርግዞ የሚወጣ ከሆነም ከርቸሌ ውስጥ በችግር ተወልውሎ በተዘጋጀ የልቡ አዳራሽ፤ ከደጅ ቆመው የሚጠብቁት የቂም መናፍስት ወዲያው ገብተው የከፋ ችግር ከሚያመጡበት በቀር እሱ የሚጎዳው ወይም የሚያመጣው አንዳች ነገር እንደማይኖር ከወዲሁ ማስገንዘቡ ተገቢ ነው። ለማንኛውም ቃሊቲ የማስተዋል፣ የመማርና የማገናዘብ ጊዜ እንዲሆንለት ምኞታችን ነው።

አንዳንድ የማቅ አባላት የሲ. አይ. ኤ. ሰላዮች ሆነው ተገኙ

በዋናነት ቤተ ክህነት አካባቢ “የቀን መጋኛ” የሚባለው ባያብል ሙላቱ የሰጠውን መረጃ ዊኪሊክስ ይፋ አድርጓል።   በዲ/ን ሙሉጌታ ወ/ገብርኤል
 

በይበልጥም የኬብል ቁጥር 
ADDIS ABAB 00000451  002 OF 003  የሚለውን ይመልከቱ!!

 
በርካታ የማኅበረ ቅዱሳን አባላትና ሌሎች ወገኖች ማኅበረ ቅዱሳንን በተመለከተ ያላቸው አመለካከት የተለያየ ነው። ማኅበሩ እውነተኛ ማንነቱን ደብቆ በቅድሚያ ቤተክርስቲያንን ከዚያም የመንግስትን ሥልጣን ለመያዝ በግልጾቹም በስውሮቹም አመራሮች እየተደገፈ የሚያደርጋቸው እንቅስቃሴዎችን አባላቱ በቅጡ አልተረዱም። ቤተክርስቲያን እኛ ባንኖር ኖሮ ጠፍታ ነበር። ያለንላት እኛ ነን። ቤተክርስቲያን ሰው ስለሌላት አስራታችሁን ለማኅበረ ቅዱሳን አውጡ በማለት የሚያሰወራውን ወሬ  እና በአካፋ ተቀብሎ በማንኪያ የሚሰጠውን ስጦታ በማመን የተታለሉ ወገኖች ይገኛሉ። እውነቱን ከማህበሩ ጋር ለበርካታ አመታት በቅርብ የሰሩ ወገኖችና እንቅስቃሴውን በሙላት የተረዱ የቤተክርስቲያን ልጆች ያውቁታል።

Thursday, May 3, 2012

አዎ ኢትዮጵያ ውስጥ በትክክል አሸባሪነት አለ!

ሙስሊሞች ሁሉ አክራሪዎች ወይም ክርስቲያን የተባሉ ሁሉ ክርስቲያኖች ናቸው ብለን አናምን። ከሁለቱም ወገን ሃይማኖቱን ተጠግቶ የራሱን ገበያ የሚያደራና ስውር አጀንዳውን በሰው ላይ ለመጫን የሚፈልግ እንዳለ የአደባባይ እውነታ ነው።
በቅርቡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሰጡት የፓርላማ መግለጫ ላይ በሁለት ወገን ስላሉት ሃይማኖታዊ ታዛውን የተጠለሉትን ኢትዮጵያውያን ችግር ፈጣሪዎችን ቀድሞውኑ ያወቅናቸው ቢሆንም የየግላችንን ጩኸት ከረፈደ በኋላም ቢሆን በግልጽ አውጀው ነግረውናል።
የሚገርመው ነገር ከእስላሞቹ አሸባሪዎች ወገን የጠቅላይ ሚኒስትሩን ድምጽ ከንቱ ስሞታ ለማለት ጊዜ ያልፈጀባቸው ሲሆን እውነታው ግን በኢትዮጵያ ውስጥ አሸባሪነት ስለመኖሩ የኢትዮጵያው ጠቅላይ ሚኒስትር ዲሞክራት ይሆኑ አምባ ገነን ከእሳቸው ሥርዓት ጋር ሊያያዝ የማይገባውን ነገር ለማያያዝ በመሞከር ግራና ቀኝ የተቃውሞ ጅራፍ ማስጮህ በምድሪቱ ላይ ያለውን እውነታ የሚለውጠው አይደለም።