Sunday, April 29, 2012

ማኅበረ ቅዱሳን እና ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ካልእ አይተዋወቁም!

  To read in PDF ( Click Here )
                            A source from: www.abaselama.org
አክራሪውና ወግ አጥባቂው የሰለፊያ የግብር ወንድም ማኅበረ ቅዱሳን የተመሰረተበትን 20 ዓመት ሰባት ያህል ወራትን አሳልፎ ሚያዝያ 27 በእግር ጉዞ ሊያከብር መሆኑን ሲገልጽ የቆየ ቢሆንም፣ የተመዝጋቢ ቁጥር በማነሱና በሌላም ምክንያት መራዘሙ እየተወራ ነው። ይሁንና ማስታወቂያው ላይ በትልቁ የብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ፎቶ ተሰቅሏል። የእርሱ የጉዞ መርሀ ግብርና አቡነ ጎርጎርዮስ፣ የእርሱ 20 ዓመትና አቡነ ጎርጎርዮስ ምን እንዳገናኛቸው ለጊዜው ባይታወቅም ብቻ ፎቷቸው በትልቁ የማስታወቂያው ማዳመቂያ ሆኗል።
1980 ብፁዕነታቸው እስካረፉበት እስከ 82 . ድረስ ወደ ዝዋይ የካህናት ማሰልጠኛ ገብተው የተማሩ አንዳንድ የዩኒቨርሲቲና የኮሌጅ ተማሪዎች መካከል አንዳንዶቹ በኋላ ላይ የማኅበረ ቅዱሳን መስራቾች እንደነበሩ ይነገራል። ይህን አጋጣሚ መነሻ በማድረግ ነው ማኅበሩና የማኅበሩ ሰዎች ብፁዕነታቸውን የማኅበሩ መስራች አባት አድርገው ይቆጥራሉ።
ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስን በቅርብ የሚያውቋቸው እንደሚናገሩላቸው ግን ቤተ ክርስቲያን በለውጥ ጎዳና ላይ እንድትራመድ የሚፈልጉ ሰው ነበሩ። ይሁን እንጂ ከሕዝቡ ወግ አጥባቂነትና ንቃተ ህሊና አንጻር ለውጡ አዝጋሚ መሆን እንዳለበት ነበር የሚያምኑት ይባላል። ከላይ እንደገለጽኩት ይህ የብፁዕነታቸው ዓላማ ባይገባቸውም አንዳንድ የማኅበረ ቅዱሳን ቀደምት ሰዎች ዝዋይ ከርመው ተመልሰዋል። ምክንያቱም እነዚህ የማኅበሩ ሰዎችና ማኅበሩም እንደማኅበር ከብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ውጪ መሆናቸውን እየታዘብን ነው። ዛሬ የማህበሩ ሰዎች በስፋት የሚቃወሙት ብፁዕነታቸው በጽሁፍ ያስተላለፏቸውን ትምህርቶች ነው። የማኅበሩ መሠረት ወንጌል ሳይሆን ተረት ነውና።

Saturday, April 28, 2012

16 ክርስቲያኖች ታሰሩ!

ታቸው ዶኒ አስቸጋሪና ለቤተክርስቲያን የማይመች ሰው መሆኑን እናውቃለን። አጥማቂ ነኝ እያለ ቅብዓ ቅዱስና እምነት ነው፤ እያለ አፈር እንደሚሸጥም ይታወቃል። በሽሮ ሜዳ ሥላሴ፣ በቃሊቲ ማርያምና በአቃቂ መድኃኔ ዓለም በሺናሻ ቅጠል ብዙዎችን ሲያጮህ የነበረ ሰው ነው። ሌላም ሌላም ነገር.....! ሰውዬው ለቤተክርስቲያን ሸክምና እንቅፋት ከመሆን ባለፈ መፍትሄ መሆን የሚችል ሰው አይደለም። ደጀ ብርሃን ብሎግም ከሰውዬው ጠባይ የተነሳ በባቦ ጋያ መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን አካባቢ ምስቅልቅል ከመፍጠር አይመለስም ብሎ ስለሚገምት በዓላማና በአቋም ባንመሳሰልም የቤተክርስቲያን ችግር የእኛም ችግር ስለሆነ ከአንድ አድርገን ብሎግ ላይ የወጣውን መረጃ እንዳለ አቅርበነዋል።
(አንድ አድርገን ሚያዚያ 19 ፤ 2004ዓ.ም)፡- የባቦጋያ መድሀኒአለም ቤተክርስትያን የቦታ ጉዳይ ለያዥ ለገናዥ እያስቸገረ ይገኛል ፤  ጌታቸው ዶኒ እንዳሰበው ነገሮች እየሄዱ አለመሆናቸውን ሲረዳ የቤተክርስትያኒቱን ቄሰ ገበዝ ትላንት አመሻሽ ላይ የመቅደሱን ቁልፍ ካለመጡ ብሎ ጠይቋቸው ነበር ፤ እርሳቸውም ‹‹አንተ ማነህና ነው የቤተክርስትያኒቱን ቁልፍ የምሰጥ ›› በማለት እምቢ ሲሉት ጉልበት ተጠቅሞ ቁልፉን እጁ ለማስገባት ሙከራ አድርጎ  ነበር ፤ ቄሰ ገበዙ የመቅደሱን ቁልፍ አልሰጥም በማለት ለአካባቢው ክርስትያኖች ስልክ ደውለው በአጭር ጊዜ ውስጥ ክርስትያኖቹ የተሰበሰቡ ሲሆኑ ከደቂቃዎች በኋላ ጌታቸው ‹‹አመጽ ለማስነሳት ሰዎች ተሰብስበዋል›› ብሎ በደወለላቸው ፖሊሶች አማካኝነት በጊዜው የነበሩትን 16 ክርስትኖችን  እስር ቤት ሊያስገቧቸው ችለዋል ፡፡ ከእነዚህ ውስጥም ሶቶች ጎልማሶችና ፤ ወጣቶች ይገኙበታል ፤  የእነዚህ ንጹሀን ክርስትያኖች  ተቃውሞ ‹‹ጌታቸው ዶኒ  የቤተክርስትያኒቱን ቁልፍ ለምን ይቀበላል ? ቁልፉን ተቀብሎ ከዚህ በፊት ሲናገር እንደነበረው የባቦጋያን መድሀኒአለም ቤተክርስትያን ለመዝጋት የሚያደርገውን ተግባር እንቃወማለን ፤ ›› በማለታቸው ነው ለእስር የበቁት፡፡

ደጀ ሰላም ብሎግ ኢትዮጵያ የክርስቲያን ደሴት ናት ሲል ህገ መንግሥቱ ደግሞ ኢትዮጵያ የሁሉም ሃይማኖቶች ሀገር ናት ይላል! የደሴቲቱ ገዢስ ማኅበረ ቅዱሳን ይሆን?

 ኢትዮጵያ የክርስቲያን ደሴት ናት ካልን እስላሞቹና ሌሎቹ ወደየት ይድረሱ?
ደጀ ሰላም ብሎግ- ህገ መንግሥት፣ የጠ/ሚኒስትር መግለጫ፣ ገለመሌ አይሰራም የሚል ይመስላል፤ ይህንን የሚያረጋግጠው ኢትዮጵያ የክርስቲያን ደሴት መሆኗን ከሁለት ዓመት በፊት ዘግቦ ነበር። ሌሎች ሃይማኖቶች ኢትዮጵያ ውስጥ እንዳሉና ሊኖሩ እንደሚገባ አምኖ ባለመቀበል ሀገሪቱ የአንዲት ሃይማኖት ደሴት ናት ማለት ምን ማለት ነው? ሁሉም ኦርቶዶክሳዊ ኢትዮጵያ የክርስቲያኖች ብቻ ናት እንደማይል ይታወቃል። እነዚህኞቹ ግን የክርስቲያን ብቻ ደሴት ነን እንዲል በመንፈሳዊ ታዛ ተጠልለው ይቀሰቅሱታል። ሰለፊ/ወሀቢ የሚባለው ደግሞ በሌላኛው ጽንፍ በኢትዮጵያ የሙስሊም መንግሥት መቆም ይገባዋል ይላል። ማሸበር የሚባለውስ ከዚህ ወዲያ ምን ሊሆን ይችላል? ይህንን የቲ-ሸርት ጫወታ የማኅበረ ቅዱሳን ሌላኛው አፍ እንደሆነ በሚነገርለት ከደጀ ሰላም ብሎግ ላይ ያገኘነው ስለሆነ ያንብቡትና ሚዛናዊ ግምትዎን ይውሰዱ።

(ደጀ ሰላም፤ ጃኑዋሪ 17/2010):- በዓለ ከተራ ሰኞ በመላ ኢትዮጵያ ታቦታተ ሕጉ ከየመንበራቸው ወጥተው ይከበራል። በሀገራችን ዋና ከተማ በአዲስ አበባ በዐቢይነት በጃን-ሜዳ ሲከበር፣ በመላው ሀገሪቱ ደግሞ ታቦታተ-ሕጉ ወደ ጥምቀተ-ባሕር ወደሚፈጸምባቸው ውሃዎች ይወርዳሉ። ከተራን ማክበር አዲስ አይደለም። ነገር ግን አምና በተከበረው “የከተራ” በዓል ላይ የታየው የሕዝቡ አከባበር፣ ሥነ ሥርዓቱና በጎ አርአያው ተጠቃሽ በመሆኑ ልናስታውሰው ወደድን። ወጣቶች አንድ ዓይነት ካናቴራ (ቲ-ሸርቶች) አሰርተው በመልበስ ራሳቸው የሕዝባቸውና የበዓላቸው አስተናባሪ ሆነው የታዩበት ሁኔታ ሁሉንም ያስደመመ ነበር። ከመንግሥት እስከ ቤተ ክህነት ባለሥልጣናት፣ ከኦርቶዶክሳውያን እስከ ሌሎች እምነት ተከታዮች ድረስ መነጋገሪያ መሆኑ ይታወሳል። በወቅቱም የሚከተሉትን መዘገባችን ይታወሳል።






የአባቶቻችንን ርስት ምን ያህል እንፈልገዋለን?
(በብርሃናዊት)

በዘንድሮው የጥምቀት በዓል ላይ: የተለያዩ ኢትዮጵያውያን "ኢትዮጵያ የክርስቲያን ደሴት ናት" እና "የአባቶቼን ርስት አልሰጥህም" የሚሉ ጽሑፎች የታተሙበትን ቲሸርቶች ለብሰው በዚህ ድረ-ገጽ ላይ ሳይ: ሁለት ዓይነት ስሜት ተሰማኝ::

1. የመጀመርያው ሕዝበ-ክርስቲያኑ ለእምነቱና የእምነት ሥርዓቱን በነጻነት ለማካሄዱ ምን ያህል ተቆርቋሪ እንደሆነና: ሙሉ ለሙሉ የእምነቱን ጉዳይ ችላ እንዳላለው: ምናልባትም እንደማይለውም ጭምር የተረዳሁበት ስለሆነ: አዎንታዊ ገጽታው ታይቶኛል::

2. ሁለተኛው ስሜቴ ግን: ሕዝበ-ክርቲያኑ ስሜቱ እንደሻከረና: በትንሹም በትልቁም ሊገነፍል የሚችል ስሜታዊነትን እንዲያዳብር በጽንፈኞች መደረጉን ሳይ የፈጠረኝ ስሜት ነው:: በእውነቱ መልካሙን መንፈሳዊነት የሚያደፈርስና የሚሠርቅ: የጨቅጫቃ መናፍቃንና የተንኳሽ ጽንፈኞች ፍላጻ የኢትዮጵያን ሕዝበ ክርስቲያን ወግቶ እስከዛሬ ሳይገድለው በመቅረቱ ጥበበ-እግዚአብሔርን እንዳደንቅ ተገድጃለሁ:: ሰአሊ ለነ ቅድስት የምንላት ድንግል ማርያም አሁንም በእኛ ተስፋ አልቆረጠችም::