Friday, April 27, 2012

አዲስ አበባ በሚገኙ አንዳንድ የ"ማኅበረ ቅዱሳን" ሱቆች ላይ የማሸግ እርምጃ ተወሰደ!

ሊያደርግ ያቀደውን የእግር ጉዞ ለሌላ ጊዜ አስተላለፈ
አዲስ አበባ ውስጥ በሚገኙ የ"ማኅበረ ቅዱሳን" ሱቆች ላይ የማሸግ እርምጃ መወሰዱን የደረሱን መረጃዎች አመለከቱ፡፡ በተለይም በኡራኤልና በሜክሲኮ አካባቢ የሚገኙ የ"ማኅበረ ቅዱሳን" ሱቆች ላይ "ባልተፈቀደ የንግድ ሥራ ላይ ስለተሠማራ ሱቁ ታሽጓል" በሚል ማስታወቂያ የታሸጉት እነዚህ ሱቆች፣ "ማኅበረ ቅዱሳን" ከማንኛውም አካል የንግድ ሥራ ፈቃድ ሳይወስድ የሚሠራባቸው መደብሮች መሆናቸው ታውቋል፡፡
"ማኅበረ ቅዱሳን" በፖለቲካዊና ሃይማኖታዊ እንዲሁም በቤተክርስቲያን ስም እና በራሱ ስም እያዛነቀ ሚናው ባልለየ እንቅስቃሴ ውስጥ እዚህም እዚያም የሚነከር በመሆኑ በሰሞኑ ከሕግ ጋር ለመፋጠጥ ተገዷል ተብሏል፡፡ ከንግድ ሥራ ጋር በተያያዘም ለመንግሥትም ሆነ ለቤተክርስቲያን ተገቢውን ገቢ ሳያስገባ ዝም ብሎ የሚዘርፍ ድርጅት እንደመሆኑ መጠን ሕጋዊ መሥመር እንዲይዝ ሲደረግ ጨርሶ ፈቃደኛ ሊሆን አለመቻሉ ተገልጿል፡፡

ፍትወተ - ሥጋ


- ትንሹ እሳት (የዓለም፣ የሥጋ፣ የሰይጣን እሳት)
በመሠረቱ  ማንኛውም እሳት ኃይል ነው (አለው)፡፡ በትክክል ከሠሩበት ጠቃሚ ነው፡፡ ያለ አግባብ ከሠሩበት ደግሞ አጥፊና ደምሳሽ ነው፡፡ በዘህ ክፍል ውስጥ ከሚገኙት የእሳት ዓይነቶች ውስጥ አንዳንዶቹ ምንም ጥቅም የማይገኝባቸው፣ እንዲያውም አጥፊ ብቻ የሆኑ እሳቶች ሲሆኑ፣ አንዳንዶቹ ደግሞ በአግባቡና በእግዚአብሔር ፍቃድ መሠረት ከተሠራባቸው ለበረከት የሚሆኑ፣ በሥጋ ምሪት ከተሠራባቸው ደግሞ የኩነኔ መሰላሎች የሆኑ እሳቶች ናቸው፡፡
1. ፍትወተ - ሥጋ (Sex) - እግዚአብሔር ለሰዎች ከሰጣቸው ጠቃሚ ኃይሎች አንዱ የሆነው ፍትወተ ሥጋን በአብዛኛው ለክፋት መገልገያነት ሲውል ማየታችን መጥፎ እንደሆነ አድርገን እንድንመለከተው አድርጎናል፡፡ በእግዚአብሔር ቃል ላይ ተመርኩዘን ስለዚህ ጉዳይ ያጠናን እንደሆነ ግን መልካም ስጦታ እንደሆነ ነው የምናገኘው፡፡ ይህን ስጦታ በአግባቡ ለተጠቀመበት ሰው የበረከት ምክንያት ይሆንለታል፡፡ ከጌታ ፍቃድ ውጪ ለሠራበት ደግሞ የጥፋት መሣሪያ ይሆንበታል፡፡ "እግዚአብሔርም ሰውን በመልኩ ፈጠረ፤ በእግዚአብሔር መልክ ፈጠረው፣ ወንድና ሴት አድርጎ ፈጠራቸው፡፡ እግዚአብሔርም ባረካቸው፣ እንዲህም አላቸው፡- ብዙ ተባዙ ምድርንም ሙሉአት...." (ዘፍ. 127-28) ከሚለው የመጽሐፍ ቅዱስ የመጀመሪያው ገጽ ጥቅስ አንስቶ በመላው መጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች ውስጥ ጋብቻና የጋብቻ ውጤቶች የሆኑት ልጆች የእግዚአብሔርን ቡራኬ ሲቀበሉ እናያለን፡፡ በጋብቻ ውስጥ ውትወተ ሥጋ አለ፣ ቀጥሎም ልጆች ይገኛሉ፡፡ ስለዚህ በቃል ኪዳን መሐላ ማኅተም በታሰረ ጋብቻ ውስጥ የባልና ሚስት ግንኙነት የተቀደሰ ተግባር እንጂ፣ ርክሰት አይደለም፡፡ በዚህ መልኩ ብቻ ከተሠራበት የፍትወተ-ሥጋ እሳት ጠቃሚና ቅዱስም ይሆናል፡፡ ከዚህ ውጪ ግን የገሃነመ እሳትን የመጀመሪያ ነበልባሎች እዚህ ምድር ላይ የሚጭር እርኩስ እሳት ይሆናል፡፡ ፍትወተ-ሥጋ እሳት ስለመሆኑ ቅዱስ ጳውሎስ በተለያዩ መልእክቶቹ አመልክቷል፡፡ ለምሳሌ 1 ቆሮ. 78-9 ላይ እንዲህ ይላል - "ላላገቡና እንዲሁም ባሎቻቸው ለሞቱባቸው ሴቶች የምለው እንዲህ ነው፤ ሳያገቡ እንደ እኔ ቢኖሩ መልካም ነው፡፡ ነገር ግን ራሳቸውን መቈጣጠር ቢያቅታቸው ያግቡ፤ ምክንያቱም በሥጋ ምኞት ከመቃጠል ይልቅ ማግባት የተሻለ ነው፡፡" የሥጋ ምኞት (ፍትወት) ለምን ያቃጥላል; መልሱ ግልጽ ነው እሳት ስለሆነ፡፡ እዚህ ላይ .ጳውሎስ ስለዚህ እሳት መልካምነት ይናገራል፡፡ በሌላ ቦታ ግን ያለአግባቡ በጥቅም ላይ ስለዋለ ርኩስ እሳት ይናገራል፡፡ 

የአቡነ ገብርኤል ቡድን አጉራ ዘለል ሰባክያንን በድጋሚ በመጋበዝ ከሲኖዶስ ውጪ መንቀሳቀሱን ቀጥሎበታል


 ዘሪሁን ሙላቱ እና ፋንቱ ወልዴ እንደተጋበዙ ውስጥ ዐዋቂ ምንጮቻችን ገልፀዋል።

"ማኅበረ ቅዱሳን" የሀዋሳ ንዑስ ማዕከል አስተባባሪነት በሀዋሳ ቅዱስ ገብርኤል ገዳም ስብከተ ወንጌል ክፍል ስም ከሚያዘያ 19 እስከ 21/ 2004 . እና ከግንቦት 3 እስከ 5/2004 . የሚቆዩ ሁለት ጉባዔያት በመዘጋጀት ላይ መሆናቸው ተሰማ፡፡
የአቡነ ገብርኤል ሀገረ ስብከት ከየካቲት 25 እስከ የካቲት 27/2004 በሕገ ወጥነት ያካሄደው ጉባዔ እንዳይካሄድ የካቲት 22 ቀን 2004 . በቁጥር 221/54/2004 በወጣ ደብዳቤ የዕግድ ደብዳቤ ቢታዘዝም፣ ትዕዛዙን ባለመቀበል፣ የኢትዮጵያ ሲኖዶስን ህልውና የማይቀበለውን መምህር ዘበነ ለማን፣ ዳንኤል ክብረትንና ምሕረተአብ አሰፋን በመጋበዝ ፍጹም ለማኅበረ ቅዱሳን የወገነ ድራማን ተጫውቷል፡፡
አሁንም፣ መምህር ዘበነ ለማን በድጋሚ በመጥራት፣ ፋንቱ ወልዴን ከአሜሪካ፣ ጎረምሳውን ዘሪሁን ሙላቱንና ዘማሪ ይልማ ኃይሉን በመጋበዝ ፍጹም የሆነውን ማኅበረ ቅዱሳናዊ ግዛት ለማስፋፋት ደፋ ቀና በመባል ላይ መሆኑ ታውቋል፡፡