Thursday, April 26, 2012

የጎንደር ደብረ ኀይል ወደብረ ጥበባት በዓታ ለማርያም የአቋቋም ምስክር ትምህርት ቤት ግንባታ ውል ተፈረመ፡፡


(ከደጀ ብርሃን) ጅምሩ ጥሩ ነበር። የሰበሰባችሁትን የቤተክርስቲያን ገንዘብ  ከማስወረሳችሁ በፊት ወይም  ስትነግዱብን ኖራችሁ የሚሉትን ድምጾች ለማፈንና ይህንን የመሰለ ትሩፋት እየሰራን ነው ለማለት ያደረጋችሁት ይመስላል። ባካፋ ዝቃችሁ እጣንና ጧፍ ከመበተን ያለፈ ቋሚ ስራ ስትሰሩ አልነበራችሁም። ይሁን እንጂ ገንዘባችንን ከቀበራችሁበት ስላወጣችሁና ምንም ይሁን ምንም እንጥፍጣፊው ስለደረሰን አመስግነናል።

በእንዳለ ደምስስ
Gedamate 3ማኅበረ ቅዱሳን በሰሜን ጎንደር ሀገረ ስብከት የሚገኘውን የደብረ ኀይል ወደብረ ጥበባት በዓታ ለማርያም የአቋቋም ምስክር ትምህርት ቤትን በ4.6 ሚሊዮን ብር ለመገንባት ሚያዚያ 12 ቀን 2004 ዓ.ም. የግንባታ ውል ስምምነት ከአስማማው አያሌው ሕንጻ ሥራ ተቋራጭ ጋር ተፈራረመ፡፡ በማኅበረ ቅዱሳን የማኅበራዊ ልማት ዋና ክፍል አስተባባሪነት የሚከናወነው ይኸው ፕሮጀክት ማኅበረ ቅዱሳንን በመወከል የማኅበሩ ዋና ጸሐፊ ዲ/ን ሙሉጌታ ኀ/ማርያምና የሕንፃ ሥራ ተቋራጩ ባለቤትና ሥራ አስኪያጅ አቶ አስማማው አያሌው አማካይነት የፊርማ መርሐ ግብሩ ተፈጽሟል፡፡
በማኅበረ ቅዱሳን ዋና ጽ/ቤት በተከናወነው የፊርማ መርሐ ግብር ላይ የማኅበሩ ዋና ጸሐፊ ዲ/ን ሙሉጌታ ኀ/ማርያም ባደረጉት ንግግር ‹‹ 4.6 ሚሊዮን ብር የሚፈጅ ፕሮጀክት ቀርጾ የአቋቋም ምስክር ትምህርት ቤት ለመገንባት ከዚህ በፊት አድርገነው አናውቅም፡፡ ይህ ትልቅ እድገት ነው፡፡ ምእመናንም ማኅበረ ቅዱሳንን ማመን የቻሉበት ነው፡፡ በሚሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ አውጥቶ ማኅበረ ቅዱሳን ይሥራው ለማለት መቻል ሙሉ ለሙሉ በማኅበሩ ላይ እምነት እንዳሳደሩ ነው የሚያሳየው፡፡ እኛም በታማኝነት ትኩረት ሰጥተን እንድንሠራ የሚያደርገን ነው፡፡ ጨረታውን ከብዙዎቹ የሕንጻ ሥራ ተቋራጮች ጋር ተወዳድሮ ያሸነፈው ድርጅት በማኅበሩ ውስጥ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያደረገና አብሮ የኖረ ነው፡፡ ሥራውንም በጥራትና ከተያዘለት ጊዜ ቀደም ብሎ በማጠናቀቅ ያስረክባል የሚል እምነት አለኝ፡፡ በማኅበረ ቅዱሳን በኩልም ሥራውን ለማፋጠን አስፈላጊውን ድጋፍ ሁሉ እንደሚያደርግ አረጋግጣለሁ›› በማለት ገልጸዋል፡፡

«የማኅበረ ቅዱሳን ዲግሪና የካንጋሮ እጅ አንድ ነው!»



/ን ሙሉጌታ ወልደገብርኤል
Email: yetdgnayalehe@gmail.com
ጥብቅ ማሳሰቢያ:
በቅድሚያ ጽሑፉን ለምታነቡ ወንዶችንም ሴቶችም የእግዚአብሔር ልጆች ሁሉ ሰላም ይሁን! እያልኩ በጽሑፉ ከተካተቱ እውነታዎችና ከጽሑፉ ከፊል ይዘት የተነሳ ጽሑፉ ከጸሐፊው መልእክት ዓላማና ከመልእክቱም ግብ ውጭ ሌላ አንድምታ እንዳይዝና እንዳይሰጠው ይህን ጥብቅ የሆነ ወንድማዊ ማስጠንቀቂያ ለመጻፍ ግድ ብለዋል:: ጸሐፊው በስራ ክቡርነት ያምናሉ: በየትኛውም የስራ መስክ ተሰማርተው ከራሳቸው አልፈው ለቤተሰብና ለሀገር የሚተርፉት ዜጎችንም የላቀ ክብር አላቸው:: ክብር ስለማያውቅ: ሰላሙን አጥቶ በሰላማዊያን ዜጎች የህይወት ጎዳና ላይ እየቆመ እሾክና አሜከላ ስለሚዘራ: እርግማን ቀለብ ስለሆነለት: የራሱ ያለሆነውን በማጭበርበርና በማደናገር የራሱ በማድረግ የሚታወቀው እልል ያለ ህጋዊ ሽፍታ ማህበርና አባላቶቹ ብቻ ላይ ያነጣጠረ እውነታ መሆኑን ተገንዝባችሁ ጽሑፍን በቅንነት ታነቡት ዘንድ በአክብሮት እጠይቃለሁ::

ሰበር ሰሚ ችሎት ለመንፈሳዊ ፍርድ ቤት የወረወረው የካህናት ጩኸት!

 መንፈሳዊ ፍርድ ቤቶች አቅም ግንባታ የላቸውም!
ለዚህ ጽሁፍ መነሻ የሆነው ሪፖርተር ጋዜጣ በሚያዚያ 17/2004 ዓ/ም እትሙ ያወጣውን ስለሃይማኖት ተቋማት ይልቁንም በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የወርቁ ሠፈር ማርያም ቤተክርስቲያን  አገልጋይ በነበሩት 6 ካህናት ላይ «ሰበር ሰሚ ችሎት» የሰጠውን ብይን አስመልክቶ «ደጀ ሰላም» ብሎግ ደስታውን በመግለጽና የሪፖርተርን ዘገባ በማድነቅ መልሶ መረጃውን ለማስተጋባት የሄደበት መንገድና ስለመንፈሳዊ ፍርድ ቤት በማቀንቀን የተጓዘበትን የምኞት መንገድ ስህተት ለማሳየትና መልስ መስጠት በማስፈለጉ ይህን ጽሁፍ ማቅረብ አስፈልጓል።
የሰበር ችሎት የህግ ትርጉምን በተመለከተ፣
በመዝገብ ቁጥር 18419 ግንቦት 4 ቀን 1998 ዓ.ም. የቀረበለትን የይግባኝ አቤቱታ የተመለከተው ሰበር ሰሚ ችሎት የሰጠው ብይን በስር ፍርድ ቤቶች ሁሉ አሳሪ የሆነውን ውሳኔ የሰጠው የጠቅላይ ፍርድ ቤትን ሥልጣንና ኃላፊነት ለማቋቋም በወጣው አዋጅ ቁጥር 42/97 አንቀጽ 2/4 ላይ ላይ የተሰጠውን መብት በመጠቀም መሆኑ ይታወቃል።