Thursday, April 19, 2012

«አንድ ጌታ አንድ ሃይማኖት አንዲት ጥምቀት»ማለት ምን ማለት ነው?

በአንድ ወቅት መጠሪያ ስሙ «ማሞ» የሚባል ሰው የፍተሻ ኬላ ላይ ጠባቂ ያስቆመውና የይለፍ ወረቀት እንዲያሳይ ይጠይቀዋል። አቶ ማሞም በፎቶግራፍ የተደገፈ ማንነቱን ገላጭ መታወቂያ ከኪሱ መዘዝ ያደርግና ለኬላ ጠባቂው ያሳያል። ኬላ ጠባቂውም በአካለ ሥጋ ከፊቱ የቆመውን አቶ ማሞንና የመታወቂያው ላይ የማሞን ፎቶ ቢያስተያይ ጨርሶውኑ የሚመሳሰሉ አልሆን ይለዋል።
 ኬላ ጠባቂ ቢቸግረው ጊዜ ስማ ሰውዬው ስምህ ማነው? ብሎ ይጠይቀዋል።
አቶ ማሞም « ማሞ» እባላለሁ በማለት መልስ ይሰጣል።
 ኬላ ጠባቂውም እንደገና- ይኼ መታወቂያ እኮ ማሞ የሚል ስም የለውም! ይለዋል።
አቶ ማሞም አዎ ልክ ነው። «ማሞ» የሚል ስም የለውም ይላል እያረጋገጠ።
አንተ ማሞ የምትባል ከሆነ ማሞነትህን የሚያረጋግጥ መታወቂያ ማሳየት ሲገባህ ለምን ማሞ ያልሆነ መታወቂያ ታሳየኛለህ? ይላል ኬላ ጠባቂው በንዴት።
እውነተኛው ማሞም ስለማንነቱና እውነተኛ ስላልሆነው የማሞ መታወቂያ ማስረዳት ጀመረ።
እኔን ለማወቅ የፈለጉ ኬላ ጠባቂዎች  የምላቸውን እንዲሰሙኝ እኔ እስከነ ሕይወቴ ቆሜ ለማስረዳትና፣ መታወቂያ ማየት ሲያምራቸው ደግሞ ይህንን የኔን ማንነት የማይገልጸውን የወንድሜን መታወቂያ ይዣለሁ ብሎ እብደት ቀመስ ማብራሪያውን አቀረበ።
ያኔም ኬላ ጠባቂው እንደእብድ ሳይሆን ሆን ብሎ እንደሚያምታታ ገብቶት፣ «ማሞ ሌላ መታወቂያው ሌላ» ብሎ ሲያበቃ ሰውዬው ማንነቱን የሚገልጽ መታወቂያ ባለመያዙና የራሱ ያልሆነ መታወቂያ አላግባብ ይዞ በመገኘት ወንጀል እንዲጠየቅ ወደማረፊያ እንዲሄድ የመደረጉን ታሪካዊ ወግ ከዓመታት በፊት አዳምጠናል።
ይህንን ገላጭ ወግ እዚህ ላይ ያነሳነው ያለምክንያት አይደለም። በትናንትናው ምሽት የሀገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ስለ «ኢስላማዊው ሰለፊና ስለኦርቶዶክሱ ማቅ ሰለፊ» ማንነት  የተነተኑበት የመንግሥታቸውን አቋም ተንተርሶ «አንድ አድርገን» ብሎግ ምሬቱን ሲገልጽ አግኝተነዋል።

Wednesday, April 18, 2012

ሀልዎተ እግዚአብሔር



ርእስ፤ ሀልዎተ እግዚአብሔር/Existence of God/
ደራሲ፤  ካሳሁን ዓለሙ
መግቢያ

20ኛው // ከየትኛውም የታሪክ ጊዜ በበለጠ ሳይንሳዊ ዕውቀት የመጠቀበት ክፍለ ዘመን እነደነበር ይታወቃል፡፡ ዘመኑ ሳይንሳዊ አስተሳሰብ የመጠቀበት ብቻ አልነበረም፤ በተቀራኒውም ዓለም በጦርነት የታመሰችበትና በኢ-ሞራል አስተሳሰብ የዘቀጠችበትም እንጂ፡፡ በተለይ -ሞራላዊነት ያደረሰው ጥፋት ወደርና ልክ የለውም ሊባል ይቻላል፡፡ ለዚህ ደግሞ የዘመኑ ፍልስፍናዊ አስተሳሰብ በቁሳዊ አመለካከት ላይ መመሥረቱና መንፈሳዊ የሚባሉትን የሰው ልጆች ሀብታት መሰረዙ ትልቅ ሚና ተጫውቷል፡፡ ይህ መንፈሳዊ አመለካከትን በሐሣባዊነት ቅርጫ አጉሮ የተመሠረተ ፍልስፍናም የሣይንስን ዕድገት በቁሳዊነት መርህ ብቻ እንዲመራ አድርጎታል፡፡ በዚህ የተነሣ ሃይማኖትም ተጠራርጎ በሐሣባዊነት መርህ በመፈረጅ የሳይንስ ፀር ተደርጎ ሊወሰድ ችሏል፡፡ ይህ መርህ በተለይ 2ኛው የዓለም ጦርነት በኋላ ዓለም በሶሻሊዝም አስተምህሮ ተጠምቃ አዲስ እግዚአብሔር የለምትምህርትንክርስትናእንድትነሣ አድርጓታል፤አዲስ ክርስቲያን ከጳጳስ ይበልጣልእንደሚባለውም በአዲሱ አስተሳሰብ ተጠምቀው ሳይንቲስት የኾኑት የቁሳካላዊያን ልጆችም እግዚአብሔር የለምአስተምህሯቸው ውጥንቅጧን አውጥተዋታል፡፡

ሀገራችን ኢትዮጵያም የገፈቱ ቀማሽ በመኾን አዲሱን ሃይማኖት ተቀብላ እንዲትጠመቅ የተማሩትምሁር ልጆቿበግልፅም በሥውርም ጥረውላታል፡፡ በዚህ ጥረታቸውም የሀገሪቱን ትምህርት በቁሳዊ ሳይንስ የአስተምህሮ መርህ በመቅረጽ፣ የሃይማኖትን የሥልጣኔ ፀርነት በሥርዓተ-ትምህርቱ በማራገብና የመንግሥት ተቋማትን ተቆጣጥረው በማስተማር ወትውተዋል፡፡ በዚህም ያልገባቸውን አዲስ የቁስአካላዊ አስተምህሮ በትውልዱ አዕምሮ አጭቀው አጭቀው ግራ ገብ ስላደረጉት ጭራሽ ለባሰው ምንፍቅና እኔ አምላክነትትምህርተ ዕምነት ሰለባ አድርገውታል፡፡ በዚህ የተነሣ እነ ኦሾ እንኳን እንደፈጣን ሎተሪበነፃነት እየፋቁት ይገኛሉ፡፡ ከዘመኑ ትውልድም ብዙ ወጣትኒቼ እንዲህ ብሏልሲሉት የእሱ አቀንቃኝ፣ ኦሾን ሲሰማም የእሱ ደቀ መዝሙር፣ ሪቻርድ ዳዊኪንምእግዚአብሔር ቅዠት ነውሲለው ቅዠታም፣ የእስጢፋኖስ ሃውኪንግን አዲስ የሳይንስ ግኝት ሲሰማ ወይም ሲያይም -አማኝ ሳይንቲስ ይኾናል፡፡ ይህ ብቻ ሳይኾን የቁሳካላዊ ዝግመተ ለውጥ አስተምህሮ የፈጠረበት የሥነ ምግባር አልባነት ተፅእኖም -ሞራላዊሙሱንእንዲኾን አድርጎታል፡፡

ከፈጣሪ አይደለም

        እግዚአብሔር ፍቅር ነው!
ሲለጉን ተደፋን፣ ሲገርፉንም ጮኽን
ሲስቡን ተሳብን፣ ሲገፉን ተገፋን
ሲመቱን አመመን፣ ሲጥሉን ወደቅን
ሲሰብሩን፣ደቀቅን፣ሲገድሉንም ሞትን
እንደሆነው ሆነ፣ የሆነው ሆነብን፣
 ከቶ ምንም የለም፣ ያልሆነው የሚሆን።
                 ከሆነውም ሁሉ፤ የሆነብን ነገር፣
                ሥረ መሠረቱ፣ የኩነቱ ምስጢር
               የክስተት እንግዳ፣ ድንገት የሚፈጠር
               ከፀሀይዋ በታች ከቶ አዲስ ነገር
             አምላክ ያላወቀው የለም በዚህ ምድር።