Saturday, April 7, 2012

ሆሣዕና በአርያም እያሉ ይጮኹ ነበር ማቴ ፳፩፣፱




«ሆሳዕና» ቃሉ ከሁለት አረማይክ ቃላት የተሰራ ሲሆን ትርጉም «እባክህ እርዳ፣ አሁን አድን» ማለት ነው። እብራይስጡም  ይህንኑ ቃል ወርሶ «הושענא » ሆሻአና ሲል ይገኛል። አዎ «አሁን አድን፣ እባክህ እርዳን» ብሎ የአዳም ዘር ያጣውን ልጅነትና የደረሰበትን ሞት ለመላቀቅ የሚያሰማው የጩኸት ድምጽ ነው፣ «ሆሳዕና»!!!
ዳዊት ነቢይ በመንፈስ ቅዱስ ተመልክቶ ማዳኑን ሲጣራና አሁን ናልን ሲል ከዘመናት በፊት አድምጠነዋል። የውስጥ ዓይኖቹ ሩቅ አይተዋል። ማዳኑንም ሽተው እንዲህ ሲል ዘምሮለታል።
«አቤቱ፥ እባክህ፥ አሁን አድን አቤቱ፥ እባክህ፥ አሁን አቅና» መዝ ፻፲፰፣፳፭ 
ያ ማለት ደግሞ « אָנָּ֣א  יְ֭הוָה  הֹושִׁ֘יעָ֥ה  נָּ֑א  אָֽנָּ֥א  יְ֝הוָ֗ה  הַצְלִ֘יחָ֥ה  נָּֽא   » አና ያኽዌ ሆሳአና አና ያኽዌ ሆስሊኻ  ና» የሚለው የእብራይስጡ ቃል ነው።
አበው የማዳኑን ነገር አስቀድመው አይተው በተስፋ «ሆሳዕና» እያሉ ዘምረዋል። የእግዚአብሔር የማዳን ሥራ በክርስቶስ ኢየሱስ እስኪገለጥ ዘወትር በእንባና በዝማሬ ወደ ተስፋው ፍጻሜ ድምጻቸውን ያሰሙ ነበር።
አዎ ንጉሥ ክርስቶስ ከዘጠና ዘጠኙ በጎች መካከል የጠፋውን አንዱን በግ ፍለጋ ንጉሥ ሆኖ ሳለ እንደንጉሥ ያይደለ በአህያ፣ ለዚያውም በውርንጫ ተቀምጦ «የአሁን አድን (ሆሳዕና)»  ጩኸት ሊመልስ በጽዮን ከተማ ይመጣል፤ ይህንንም ዘካርያስ ከዘመረው ዘመናት ተቆጥረው ነበር።
«አንቺ የጽዮን ልጅ ሆይ፥ እጅግ ደስ ይበልሽ አንቺ የኢየሩሳሌም ልጅ ሆይ፥ እልል በዪ እነሆ፥ ንጉሥሽ ጻድቅና አዳኝ ነው ትሑትም ሆኖ በአህያም፥ በአህያይቱ ግልገል በውርጫይቱ ላይ ተቀምጦ ወደ አንቺ ይመጣል» ዘካ ፱፣፱
ምንኛ ይደንቅ? ምንኛስ ይረቅ? ንጉሥ ስለመምጣቱ አስቀድመው የተናገሩለትና  ከዘመናት በፊት ማዳኑን አይተው በእልልታ የዘመሩለት!!
ሰማያዊ ንጉሥ ክርስቶስ ከቅድስት ድንግል ማርያም ያለዘርዓ ብእሲ ከስጋችን ተዛምዶ ማዳኑን ሲጠብቁ፤ ከሩቅ አይተው ሲጣሩ፣ ሲዘምሩለትና አንድ ቀን ማዳኑ እንደሚሆን ተስፋ ሲያደርጉት የነበረው ሰዓቱ ደርሶ በመካከላቸው ሲገኝ ይጠብቁት የነበረው ዓይነት ሳይሆን  ውበት የሌለውን ንጉሥ  ለመቀበል የገዛ ወገኖቹ ተቸግረው ነበር።
አዎ የደም ግባት ብቻ ሳይሆን የንጉሥ ወግ የሌለው፣ በአህያ ለዚያውም በውርንጫ የሚመጣ ንጉሥ እንዴት ይቀበሉት?

አለ በየቦታው ዋሾና ቀጣፊ!

 
                      ዋሾ፤ ቀጣፊ
                                           (ከደጀብርሃን)
እንዲያው ቅጥፍ አርጎ የነገር አበባ
ሳይሸተው የሚያበን የዲስኩር ገለባ
የሰው አረማሞ የሆነ ፍሬ አልባ
መጎንጎን ማፍተልተል፣ተንኮልና ደባ
ሳይጠሩት የሚጮህ ፣ጣልቃ የሚገባ
በከቸቸ ዓይኑ፤ እንደአዞ የሚያነባ
ነጩን የሚያጠቁር ክፋት የሚቀባ
ሰው መሳይ በሸንጎ ፣ለብሶ የእድሜ ካባ
 አለ በሰፈሩ፣ አለ በሀገሩ፣
በዋሾ የተወጋ፣ አለ በመንደሩ፣
                        ያለቀሰም አለ፣ እንባን የፈሰሰ፣ ኑሮን ያመረረ
                        ተወግቶ የደማ ፣ ውስጡ የጠቆረ፣
                        ትዳሩ የፈረሰ፣ ሜዳ ላይ የቀረ
                     ተሰርቶበት ነገር፣ ውድቀት የቆጠረ፣
                     ጓደኛን የጠላ፣ ጸብን ያከረረ፣
                     አለ የተወጋ፣ አለ የተነካ በዋሾ ቀጣፊ
                     በሀሰት ዲስኩሩ፣ በነገር ፈልሳፊ
                   በሃይማኖት ስፍራ፣ አለ መስቀል ይዞ፣
                   እያለቃቀሰ ልክ ፣ እንደአዞ፣
                   ጸብን እየዘራ፣ በሀሰት ደንዝዞ፣
                   አለ በየቢሮው፣ ወንበር ተደግፎ፣
                   አብስሎ ሚያበላ፣ የተንኮልን ገንፎ፣
                   አለ በአስኳላው፣ ደብተር ተሸክሞ፣
                  አጋጭቶ የሚስቅ፤ በክፋት አላትሞ፣
አለ በየቦታው ዋሾና ቀጣፊ
በምታልፈው እድሜ፣ ሳይመስለው አላፊ።
በምታልፈው እድሜ ሳይመስለው አላፊ፣
                        ዛሬም ገና አለ
 ዋሾና ቀጣፊ........

Friday, April 6, 2012

ዘሪሁን ሙላቱ ከቡታጀራ፣ ዳንኤል ግርማ ከደሴ፣ "ቀኝ ኋላ ዙር" ተባሉ

                             የጽሁፉ ምንጭ፣ dejeselaam-dejeselaam.blogspot.com
በረጅም ምላስ እና በፈሪሳዊ ፍልስፍና ከሚታወቁት የ"ማኅበረ ቅዱሳን" ቀንደኛ ነውጠኞች መካከል ዘሪሁን ሙላቱ እና ዳንኤል ግርማ የተባሉት ግለሰቦች ከቡታጀራ እና ደሴ ከተሞች በመጡበት እግራቸው እንዲመለሱ መደረጉን ከየሥፍራው የደረሰን መረጃ ያመለክታል፡፡

ዘሪሁን ሙላቱ ከቡታጀራ የተባረረው ማንም ሳይወክለውና ሳይልከው ዓመታዊውን የመድኃኔዓለም በዓለ ንግሥ ተደግፎ ለራሱ ዝናና እና መልካም ገፅታ ግንባታ በማሰብ ዐውድ ምሕረት ላይ ለመስበክና "ኦርቶዶክስ መልስ አላት" በሚል ርዕስ ያሳተመውን ቪሲዲ ቸብችቦ ኪሱን በብር ለመሙላት አስልቶ ወደ ስፍራው በመሄዱ መሆኑን ውስጥ ዐዋቂ ምንጮቻችን አስታውቀዋል፡፡

ዘሪሁን ከወንድወሰን ጋር በመሆን "ሀገር-አማን" ብሎ ወደ ቡታጀራ የገሰገሰ ሲሆን፣ በትላንትናው ዕለት (መጋቢት 27 ቀን 2004 ዓ.ም) በቡታጀራ ደብረ ሠላም መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን ተገኝቶ ዐውደ ምሕረት ላይ ወጥቶ ለመስበክ ዕድል እንዲሰጠው ጠይቋል፡፡ በሥፍራው የነበሩ የሀገረስብከቱ ሠራተኞች፣ የደብሩ አለቆችና የልዩ ልዩ ክፍል የሥራ ኃላፊዎች ማንነቱን ይጠይቁታል፡፡ ዘሪሁንም፣ "እኔ መምህር ዘሪሁን ሙላቱ" እባላለሁ በማለት ይጀምርና ስለ ራሱ ማንነትና አስተዋጽዖ አጉልቶና አግዝፎ መተንተን ይጀምራል፡፡ ካህናቱም "ለመሆኑ ይህንን ስትለን ተዘዋውረህ ለመስበክ የሚያስችልህ ፈቃድ አለህ ወይ"? ይሉታል፡፡ እርሱም በቀጥታ "የለኝም" ሳይላቸው ታዋቂ ሰባኪ ነኝ፤ ብዙ ቦታ ተገኝቼ አስተምሬአለሁ በማለት ቀጥተኛ መልስ መስጠት ሳይችል ይቀራል፡፡ "እሺ ወደዚህ ስትመጣ ማን እንደላከህ ልትነግረን ትችላለህ? ለዛሬ እዚህ መጥተህ እንድትሰብክ የተመደብክበት ወይም የታዘዝክበት ደብዳቤ ልታሳየን ትችላለህ"? ብለው ጠየቁት፡፡ እርሱም አንዱንም ጥያቄ በአግባቡ ሳይመልስላቸው ይቀራል፡፡