Thursday, April 5, 2012

የአባ ፋኑኤልን ጵጵስና የሚሽር ደብዳቤ የኦርቶዶክስ ወሀቢዝም ብሎግ በሆነው «ደጀሰላም» ላይ ወጣ


 አባ ፋኑኤልን ከጵጵስና ሽረናል የሚለው የኦርቶዶክስ ወሀቢያዎችን ደብዳቤ ለማንበብ እዚህ ይጫኑ
አባ ፋኑኤል ወደምድረ አሜሪካ እንዳይገቡ በደብዳቤ ለቅዱስ ሲኖዶስ ያመለከተው የኦርቶዶክስ ወሀቢዝም ማኅበር አባላት በጥቅምቱ ሲኖዶስ ከዳር ዳር በየብሎጋቸው ሲንጫንጩ እንደነበር ያስቀረናቸው መረጃዎች የሚያረጋግጡልን የቅርብ ጊዜ ትዝታችን ናቸው።
እንግዲህ አባ ፋኑኤል ወደአሜሪካ እንዳይገቡ አስቀድሞ በመዋጋት፤ ያ ሳይሆን ሲቀርና ምድረ አሜሪካ መግባታቸው ሲታወቅ ደግሞ ወደ ሀገረስብከቱ እንዳይመጡ አንድም የወፍ ዘር ዝር ሳይልና ሳይቀበላቸው ከመቅረቱም በላይ በአባ አብርሃምና በአንዲት ሴት ስም የግል ንብረትነት እንደተመዘገበ በሚነገርለት ሀገረ ስብከት መሄድ  ባይችሉና  በሩ ሁሉ ቢዘጋባቸው፣ በሰላም ጊዜ ወደተከሉት ቤተክርስቲያን ሄደው በዚያ ቢያርፉ ደግሞ በግላቸው ቤተክርስቲያን ውስጥ መሽገዋል ብሎ ስም በማጥፋት፤ ሥራ የተጠመዱት የኦርቶዶክስ ወሀቢዝም ማኅበር (ማቅ) አባላት ይህንንም እንደኃጢአት በመቁጠር የከሳሽነት ድርሻቸውን በደብዳቤ ለቅዱስ ሲኖዶስ የላኩ መሆናቸውም የሚዘነጋ አይደለም። የቆዩ ደብዳቤዎችን ለማየት ከፈለጉ ይህንን ይጫኑ
ከነዚህ የኦርቶዶክስ ወሀቢዝም ማኅበር (ማቅ) አቀንቃኞችና አሸርጋዶች አንዱ ይኼው ቄስ ነኝ የሚለው ዶ/ር የተሰጠውን የአገልግሎት ድርሻ እየተወጣ ወደቤቱ ወይም ወደእንጀራ መብያ ስፍራው በመመለስ ትህትናን ገንዘብ ማድረግ ሲገባው እንደወሀቢዝም ዓላማ(ማቅ) የአስተሳሰብ ሱሪውን አሳጥሮ ሁከት፤ብጥብጥ፣ የሥራ እንቅፋትና አባ ፋኑኤልን የማደናቀፍ ተልእኰውን ለመወጣት ሲባትል ሊቀጳጳሱ በምክር፣ በተግሳጽ፣ እና በጽሁፍ ማስጠንቀቂያ ከእኩይ ኢ-ቅስና ተግባሩ እንዲታቀብ ቢያስታምሙትም እሱ እንደፍርሃትና እጅን እንደመስጠት ስለቆጠረው በተለመደው ወሀቢያ አገልግሎቱ ቀጥሎበት ስላገኙት «ሰይፍ ዘክልዔ አፉሁ» በሆነው ስልጣናቸው በዐመጽ ያደፈ ልብሱን ከላዩ ላይ ቀደው ቢጥሉለት ሊያመሰግን ሲገባው በሌለው አቅምና ስልጣን «ረስጠብ» እንደዚህ እያለ እንደሚጠቅሰው የእርስዎም ስልጣን ተገፏል ሲል እስከ ግንቦት ሲኖዶስ የሚያደርሰንን አስቂኝ ደብዳቤ በኦርቶዶክስ ወሀቢዝም ድረ ገጽ ላይ አድመኛ ተባባሪዎቹን አሰልፎ አሰንብቦናል።
እዚህ ላይ ልናነሳ የሚገባን ጥያቄዎች፣
1/ አባ ፋኑኤል በቤተክርስቲያናችን አሠራር በየደረጃው መወሰድ የሚገባቸውን የእርምት እርምጃ በመውሰድ አግባብነቱን የጠበቀ አካሄድ መከተል ይቅርና በተገቢው መንገድ ያልሆነ እግድ ፈጽመው ቢሆን ኖሮስ ተበደልኩ ወይም እርምጃው ትክክል አይደለም የሚል ወገን የቤተክርስቲያኒቱ አካል ነኝ የሚል ከሆነ አቤቱታውን ማቅረብ የሚገባው ለማነው?
2/ አንድ ቄስ ነኝ የሚል ዶ/ር እርምጃ ከተወሰደበት እርምጃውን ለመከላከልና መብቱን ለማስከበር የሚችለው በህግ አግባብና መንገድ ብቻ ነው ወይስ አብያተ ክርስቲያናትን ወይም አባላትን በማሰለፍና በማሳደም?
3/ ዶ/ሩ ቄስ አላግባብ ተወሰደብኝ ለሚለው እርምጃ አድማውን ወደ ሁሉን አቀፍ የቤተክርስቲያን እንቅስቃሴ ለመውሰድ ከመፈለግ ባሻገር «ረስጠብ»ን በመጥቀስ አላግባብ ክህነትን የሚያግድ ጳጳስ ከጵጵስናው ይሻር! ብሏል በማለት ምንጭ ማጣቀሱ ጳጳሱ አሁን በነቄስ ዶ/ር ተሽረዋል ማለት ነው? ይህንን ለማለት ሥልጣኑን ከየት አገኙት?
4/ ለአባ ፋኑኤል እርምጃ አጸፋዊ ምላሽ የሆነው ደብዳቤ የተጻፈው በዋሽንግተን ዲሲና በአካባቢው አህጉረ ስብከት ጽ/ቤት ማኅተም ሲሆን የአህጉረ ስብከቱ ጽ/ቤት ኃላፊ ማነው? የስልጣነ ክህነትን እግድ ለማየት የተሰየመው ጉባኤ የት ያለው? እነማን ናቸው?
ሀገረስብከቱ ይህንን ደብዳቤ ስለ ዶ/ሩ ቄስ ጉዳይ የመመልከት ውክልናን ያገኘው ከማነው?
5/ የአብያተክርስቲያናቱ የአቋም መግለጫ በምን ስሌት ነው የስልጣነ ክህነትን ጉዳይ መመልከት የጀመረው? በአቋም መግለጫ የሚቀለበስ ወይም የሚከበር የክህነት ሥልጣን የት ሀገር ነው ያለው? ምናልባትም የሚያስቸግርህን በለው በሚለው የወሀቢዝም ፍልስፍና ይሰራ ይሆናል። ምክንያቱም ወሀቢዝም የምትቀበል ከሆነ ትቀበላለህ፣ እምቢ ካልክ ትመታለህ ፖሊሲው ስለሆነ ነው።
ስናጠቃልለው
ይህ ወሀቢያ ኦርቶዶክስ አቀንቃኝ ቡድን አባ ፋኑኤል ነገ ወደ ጅማ ሀገረ ስብከት ተዛውረዋል የሚል ዜና ቢሰማ ጅማ ባሉ ተላላኪዎቹ አድማውንና ሴራውን ይተዋል ወይም የከሳሽነት አፉን ዘግቶ ዝም ይላል ብሎ ማሰብ የወሀቢያነቱን እንቅስቃሴ አለማወቅ ብቻ ሳይሆን በዚህ ዘመን ለጥፋት የተላከ የጥፋት መሳሪያ መሆኑን አለመረዳትም ይሆናል።
የኦርቶዶክስ ወሀቢዝም ብሎጎች አባ ፋኑኤልን ለማጥፋት የወሀቢያ ተግባራቸውን እንደማያቆሙ ቢታወቅም ትግላቸው ሁሉ ውሃ ወቀጣ ከመሆን ውጪ እስካሁን የፈየደው ነገር አለመኖሩን ስንመለከት የያዛቸው የዘመቻ አባዜ ግን መቼም ቢሆን ሳያጠፋው እንደማይለቀው አስረግጠን መናገር እንችላለን። በህውከት ቤቱን የሰራ መቼም አይኖርም። 
 «ክፉ ሰው ዓመፃን ብቻ ይሻል ስለዚህ ጨካኝ መልአክ ይላክበታል» ምሳ 17፣11
ለዚህም ጊዜ ይስጠን ሁሉን እናየዋለን።
የራሳቸውን የኦርቶዶክስ ወሀቢያ አገልግሎታቸውን እንደቅድስና ስራ በመቁጠር የአባ ሰላማ ብሎግ የዶ/ሩን ቄስ እግድ ደብዳቤ ስላወጣ የተሃድሶ ብሎግ ብለው በመጥራትና አባ ፋኑኤልን ወደተሀድሶ ለማጣበቅ መፈለጋቸውን ስንመለከት «ይሉሽን ባልሰማሽ፣ ገበያ ባልወጣሽ» የተባለውን ተረት እንድናስታውስ ያስገድደናል። ቤተክርስቲያኒቱ የምትታወከው በኦርቶዶክስ ወሀቢዝም ማኅበር (ማቅ) መሆኑን የማያውቅ ቢኖር ራሱ ማቅ ብቻ ነው። ከዚያ ውጪ ጳጳሱን ሽረንሃል የሚል ደብዳቤ በብሎጉ ላይ ያወጣ ኦርቶዶክሳዊ ሆኖ የሚታየው  ከየትኛው የኦርቶዶክስ  ፍርድ በተገኘ መብት ነው?
በኦፊሴል የጻፉትን ደብዳቤ ያገኘና ድረ ገጽ ላይ ባወጣ ክፍል የተነሳ አባ ፋኑኤል የሚሰደቡበት ምክንያት ምንድነው? አባ ፋኑኤል ጽፈው ያሳወቁትን የእግድ ደብዳቤ እነማን እጅ መግባት እንዳለበትና እንደሌለበት ሲጠብቁ መኖር አለባቸው ወይ? በወሀቢዝም ደጀ አፍ ብሎግ ላይ ሲወጣ የኦርቶዶክስ የሚሆነውና ካልወጣ ደግሞ የተሃድሶ ነው የሚባለው በምን ስሌት ነው? እናንተ በተሃድሶ ብሎግ ላይ ወጣ ስትሉ  እኛ ግን እንደዚህ ልንላችሁ ስለመቻላችን አትገነዘቡም ማለት ነው?
የአባ ፋኑኤልን ጵጵስና የሚሽር ደብዳቤ የኦርቶዶክስ ወሀቢዝም ብሎግ በሆነው «ደጀሰላም» ላይ ወጣ!



ጌታ ኢየሱስ የመገበው ስንት ሰው ነው? 4ሺ ወይስ 5ሺ ሰዎችን?

የማቴዎስ ወንጌል
14፥21
ከሴቶችና ከልጆችም በቀር የበሉት አምስት ሺህ ወንዶች ያህሉ ነበር።
የማቴ ወንጌል 15፥38
የበሉትም ከሴቶችና ከልጆች በቀር አራት ሺህ ወንዶች ነበሩ።
በማርቆስ ወንጌል ላይም እንደዚህ የሚል ተጠቅሷል።

የማርቆስ ወንጌል
6፥44
እንጀራውንም የበሉት ወንዶቹ አምስት ሺህ ነበሩ።
8፥9
የበሉትም አራት ሺህ ያህል ነበሩ።
8፥19
አምስቱን እንጀራ ለአምስት ሺህ በቈረስሁ ጊዜ፥ ቍርስራሹ የሞላ ስንት መሶብ አነሣችሁ? እርሱም፦ አሥራ ሁለት አሉት።
8፥20
ሰባቱን እንጀራስ ለአራት ሺህ በቈረስሁ ጊዜ፥ ቍርስራሹ የሞላ ስንት ቅርጫት አነሣችሁ? እርሱም፦ ሰባት አሉት።
ታዲያ የተመገቡት ትክክለኛው የሰዎች ቁጥርና የተነሳው የቁርስራሽ ቁጥር ስንት ነው? ወንጌላውያኑስ ለምን ቁጥሮቹን አበላልጠው ዘገቡ? አልገባኝምና መልስ እሻለሁ
መልስ
(ከደጀብርሃን)
ጥቅሶቹን አበዛሃቸው እንጂ ጥያቄህ በማቴ 14፤21 እና በማቴ 15፣38 ላይ የተመገቡት ሰዎች ቁጥርና የተነሳው ቁርስራሽ መጠን የተለያየው ለምንድነው? የሚል ይመስለኛል።
ከዚህ አንጻር በአጭሩ ስመልስልህ አዎ፤ 4 ሺህ ሰዎችና 5 ሺህ ሰዎች መግቦ አንዴ 7 ቅርጫት፣ አንድ ጊዜ ደግሞ 12 ቅርጫት አትረፍርፏል። ይህንንም በአጭሩ ላብራራ።
1/ በማቴ 14፣20-21 ላይ የተመለከተው 5 ሺህ ሰዎችና 12 ቅርጫት ቁርስራሽን በተመለከተ፣
ነገሩን ለመረዳት እንድንችል ከማቴዎስ ምእራፍ 13 እንጀምር። ማቴዎስ 13 የምሳሌዎች ምዕራፍ ተብሎ በነገረ መለኰት ምሁራን ይጠራል። ምክንያቱም የዘሪው ምሳሌ ማቴ 13፣3 ፣ የሰናፍጭ ምሳሌ ማቴ 13፣31 የእንቁ ምሳሌ ማቴ 13፣44፤ የመረብ ምሳሌ ማቴ 13፣47 ፤ የተነገረበት ምዕራፍ ነው። እዚህ ላይ የምሳሌዎችን ምዕራፍ ማንሳት ያስፈለገበት ምክንያት ምሳሌዎችን ለመተንተን ሳይሆን ምሳሌዎቹ የተነገረበት ቦታና ሁኔታ በነገረ ጭብጥነት እንድንይዝ በማስፈለጉ ነው። በዚሁ መሰረት ይህ የምሳሌ ምዕራፍ ታሪክ በኢየሱስ የተነገረው ከቤቱ ወጥቶ በባህር ዳሩ አጠገብ መሆኑን ነው።
«በዚያን ቀን ኢየሱስ ከቤት ወጥቶ በባሕር አጠገብ ተቀመጠ፤እርሱም በታንኳ ገብቶ እስኪቀመጥ ድረስ ብዙ ሰዎች ወደ እርሱ ተሰበሰቡ፥ ሕዝቡም ሁሉ በወደቡ ቆመው ነበር» ማቴ 13፣1-2
ይህም ከቤቱ ሲል ከናዝሬት (ሉቃ 4፣16) ሲሆን የባህሩ ዳር ደግሞ ገሊላ (ማር 1፣16) መሆኑን ጥቅሶቹ ያረጋግጡልናል። ያም ማለት ከናዝሬት ወደ ገሊላ ሄዶ «የምሳሌዎቹን ታሪክ» ከባህሩ ዳር አስተማረ ማለት ነው። ከዚያስ በኋላ ወደየት ሄደ? የሚለውን ስንከተል ደግሞ ይህንን እናገኛለን። ማቴ 13፣53 ላይ ተቀምጦልናል።


Wednesday, April 4, 2012

የባቢሎን ግንብ

በመጽሐፍ ቅዱስ ኦሪት ዘፍጥረት ምዕራፍ 11 ዘንድ፣ የባቢሎን ግንብ ሰማይን እንዲደርሱ የተባበሩት ሰው ልጆች የሠሩ ግንብ ነበር። ያ ዕቅድ እንዳይከናወንላቸው ለመከልከል፣ እግዚአብሔር እያንዳንዱ በተለየ ቋንቋ እንዲናገርበት ልሳናታቸውን አደባለቀ። መግባባት አልተቻላቸውምና ስራው ቆመ። ከዚያ በኋላ፣ ሕዝቦቹ ወደ ልዩ ልዩ መሬት ክፍሎች ሄዱ። ይህ ታሪክ ብዙ የተለያዩ ዘሮችና ቋንቋዎች መኖሩን ለመግለጽ እንደሚጠቅም ይታስባል።

የባቢሎን ግንብ (ዘፍ. 11፡1-9)

       ምድርም ሁሉ በአንድ ቋንቋና በአንድ ንግግር ነበረች። ከምሥራቅም ተነሥተው በሄዱ ጊዜ በሰናዖር ምድር አንድ ሜዳ አገኙ፤ በዚያም ተቀመጡ። እርስ በርሳቸውም፦ ኑ፣ ጡብ እንሥራ፣ በእሳትም እንተኲሰው ተባባሉ። ጡቡም እንደ ድንጋይ ሆነላቸው፤ የምድርም ዝፍት እንደ ጭቃ ሆነችላቸው። እንዲህም፦ ኑ ለእኛ ከተማና ራሱ ወደ ሰማይ የሚደርስ ግንብ እንሥራ፤ በምድር ላይ ሳንበተንም ስማችንን እናስጠራው አሉ። እግዚአብሔርም የአዳም ልጆች የሠሩትን ከተማና ግንብ ለማየት ወረደ። እግዚአብሔርም አለ፡ - እነሆ፣ እነርሱ አንድ ወገን ናቸው፣ ለሁሉም አንድ ቋንቋ አላቸው፤ ይህንም ለማድረግ ጀመሩ፤ አሁንም ያሰቡትን ሁሉ ለመሥራት አይከለከሉም። ኑ፣ እንውረድ፤ አንዱ የአንዱን ነገር እንዳይሰማው ቋንቋቸውን በዚያ እንደባልቀው። እግዚአብሔርም ከዚያ በምድር ሁሉ ላይ በተናቸው፤ ከተማይቱንም መሥራት ተዉ። ስለዚህም ስምዋ ባቢሎን ተባለ፣ እግዚአብሔር በዚያ የምድርን ቋንቋ ሁሉ ደባልቋልና፤ ከዚያም እግዚአብሔር በምድር ሁሉ ላይ እነርሱን በትኖአቸዋል።
በትንተና
የሰው ልጆች ሁሉ አንድ ኅብረተሰብ ሆነው የሠፈሩባት አገር ሰናዖር ለኤፍራጥስ ወንዝ ቅርብ ነበረች። ባቢሎን በጥንታዊ አሦር ቋንቋ ምንጭ በተገኘ ባቢሉ (ባብ-ኢሉ) ማለት «የአማልክት በር» ለማለት ነው። በዕብራይስጥ ትርጉም ግን የ«ባቤል» ስም «መደባለቅ» ለማለት ለሚለው ቃል ይመስላል። ከውድቀቱ በፊት የተናገረው ቋንቋ አንዳንዴ «የአዳም ቋንቋ» መሆኑ ይባላል። በታሪክ አንዳንድ ሰው በግምት ያም ሆነ ይህ ቋንቋ መጀመርያው ቋንቋ እንደ ነበር የሚለው ክርክር አቅርቧል። ለምሳሌ ቋንቋው ዕብራይስጥ ወይም ባስክ እንደ ነበር ተብልዋል።
በኦሪት ዘፍጥረት ምዕራፍ 10 ባቢሎን ከተማ የናምሩድ ግዛት መጀመርያ እንደ ነበር ይላል።