የኛ አርኪዮሎጂስቶች ‹‹ጦጣ›› ከሚፈልጉ…
አርኪዮሎጂስቶች
ተግተው የሚፈልጉት ነገር ቢኖር ቅሪተ አጽም ነው፡፡ ከቻሉ የሰው ለማግኘት ይሞክራሉ፤ ካልሆነላቸው የእንስሳ
አጽም፤ ካጡ ደግሞ የዕጽዋት ቅሪት፤ በጣም ከተቸገሩ ደግሞ የጥንት ሰው መገልገያ ሊሆኑ ይችላሉ ያሏቸውን ስለታም
ድንጋዮችና ሸክላዎች ይፈልጋሉ፡፡
ሰው ከጦጣ ሊመጣ አይችልም ብዬ ለመሞገት አልፈልግም፡፡ ምን አገባኝ! የሚያምን ይመን፤ የማያምንም አለማመኑን ይመን፡፡ እኔን የሚያሳስበኝ! ጦጣ ስንፈልግ እንደ ጦጣ ማሰብ የመጀመራችን ነገር ነው?
ያ
ጦጣ፤ የመጀመሪያው ጦጣ፤ ኢትዮጵያ ብቻ መገኘቱ ነገር ለምን ጥሩ ዜና እንደሚሆን ግን አይገባኝም!፡፡ ለምን
አሜሪካ አይገኝም? ለምን ዩሮፕ አይገኝም? …..አረ… ኢትዮጵያ የሰው ልጅ ምንጭ ስለሆነች ነው! አይደል?፡፡ የሰው
ልጅ ምንጭ ጦጣ ከሆነ፤ ያ ጦጣም ኢትዮጵያ ብቻ ከተገኘ…ኢትዮጵያውያን ከሌላው የሰው ዘር ሁሉ ተለይተን ለጦጣ
የቀረብን መሆናችን አይደል? እና ይሄ ምን ያኮራል? ያሳፍራል እንጂ፡፡ እንኳንም ዘንቦብን ...