Wednesday, April 4, 2012

እኛ ጦጣ ነን?

የኛ አርኪዮሎጂስቶች ‹‹ጦጣ›› ከሚፈልጉ…

naodlive@gmail.com


አርኪዮሎጂስቶች ተግተው የሚፈልጉት ነገር ቢኖር ቅሪተ አጽም ነው፡፡ ከቻሉ የሰው ለማግኘት ይሞክራሉ፤ ካልሆነላቸው የእንስሳ አጽም፤ ካጡ ደግሞ የዕጽዋት ቅሪት፤ በጣም ከተቸገሩ ደግሞ የጥንት ሰው መገልገያ ሊሆኑ ይችላሉ ያሏቸውን ስለታም ድንጋዮችና ሸክላዎች ይፈልጋሉ፡፡
የብዙዎቹ ኢትዮጵያውያን አርኪዬሎጂስቶች ሕልም ግን ሉሲን የሚቀድም የጦጣ አጽም ማግኘት ነው፡፡ ሉሲን ያገኛትም ፈረንጅ ስለሆነ ደስተኛ አይደሉም ስለዚህ የ‹‹ሀበሻን ጦጣ›› ራሱ ሀበሻ እንዲያገኝ ይፈልጋሉ፡፡ በቅርቡ ሀበሻ ተመራማሪዎች ያገኙት ቅሪተ አጽምም የተሞገሰውም የሉሲን የዕድሜ ሪከርድ ስለሰበረ እና …ነው፡፡

ይሄ ሁሉ ልፋት ግን አንድ ነገር ለማረጋገጥ ነው? እኛ ሰዎች ከጦጣ መምጣታችንን!
ሰው ከጦጣ ሊመጣ አይችልም ብዬ ለመሞገት አልፈልግም፡፡ ምን አገባኝ! የሚያምን ይመን፤ የማያምንም አለማመኑን  ይመን፡፡ እኔን የሚያሳስበኝ! ጦጣ ስንፈልግ እንደ ጦጣ ማሰብ የመጀመራችን ነገር ነው?
ያ ጦጣ፤ የመጀመሪያው ጦጣ፤ ኢትዮጵያ ብቻ መገኘቱ ነገር ለምን ጥሩ ዜና እንደሚሆን ግን አይገባኝም!፡፡ ለምን አሜሪካ አይገኝም? ለምን ዩሮፕ አይገኝም? …..አረ… ኢትዮጵያ የሰው ልጅ ምንጭ ስለሆነች ነው! አይደል?፡፡ የሰው ልጅ ምንጭ ጦጣ ከሆነ፤ ያ ጦጣም ኢትዮጵያ ብቻ ከተገኘ…ኢትዮጵያውያን ከሌላው የሰው ዘር ሁሉ ተለይተን ለጦጣ የቀረብን መሆናችን አይደል? እና ይሄ ምን ያኮራል? ያሳፍራል እንጂ፡፡ እንኳንም ዘንቦብን ...

ኑሮ በአገርኛ፤ ጾም ይበዛበታል!

 በፍቄ ከአዲስ አበባ፣

ባሕር ማዶ ካሉ ሰዎችጋ ስናወራ አንዳንድ የማይገቡን ወሬዎችን እየሰማን ጭንቅላታችንን እየናጥንወቸ ጉድ!” ማለታችን አይቀሬ ነው፡፡ ለኛ ባዳ ከሆነው ከቀላሉ “GPS” ጀምሮ፣ credit card ቢሉ፣ ምን ቢሉ ሁሉም ለኛ እንቆቅልሾች ናቸው፡፡ ወጉ ቀርቶብኝ በቅጡ በኮነነኝ እንዲሉ “GPS” ቀርቶብኝ እበላው ባገኘሁ የሚለው እስኪታወሰን ድረስ እንደመማለን፡፡ እዚህ GPS የለም፣ credit card የለም፣ ባቡር (ወይም subway station ብሎ ቋንቋ) የለም፣ smart phone የለም፣ wi-fi የለም (አለ እንዴ?) ለነገሩ የዚህ ጫወታ ጉዳዮች እነዚህ ሁሉ ስላልሆኑ እንኳን ደስ ያላችሁ፡፡ በርግጥ ግን ወደጫወታው አጀንዳ ለመድረስ አሁንም ዳር፣ ዳሩን መነካካት የግድ ነው፡፡አሜሪካኖች ለምን ወፋፍራም ሆኑ? ኢትዮጵያውያኖች ለምን ቀጫጭን ሆኑ?› ብለን ብንጀምርስ!
ያልተመጣጠነ ውፍረት 75 በመቶ አሜሪካውያን የጤና እክል እየፈጠረ ነው፤ 75 በመቶ ኢትዮጵያውያን ደግሞ (ይህ ቁጥር በጥናት አልተረጋገጠም እንጂ፣) ችግራችን ቅጥነት ነው፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ obesity ሳይሆን በምግብ እጥረት፣ በጨጓራ ሕመም የሚሰቃዩ ሰዎችን ነው ማግኘት የሚቻለው፡፡ ለምን ብለን የጠየቅን እንደሆን ጠቅላይ ሚኒስትሩ በስልጣናቸው አፍላ ዘመን ቃል በገቡት መሠረትበቀን ሦስቴ መብላትባለመቻላችን ነው፡፡ በቀን ሦስቴ መብላት ማለት አሰሱን ገሰሱን ማግበስበስ ማለት አይደለም፡፡ በሦስተኛ ክፍል ሳይንስ ላይ እንደተማርነው የተመጣጠነ ምግብ መብላት ማለት ነው፡፡ የተመጣጠነ ምግብ ደግሞ ፕሮቲን፣ ካርቦሃይድሬት፣ ፋት፣ ቫይታሚኖችና ማዕድኖችን መያዝ አለበት፡፡

የኢትዮጵያውያንን አመጋገብ በጥቅሉ በአንድ መስመር መተረክ ይቻላል፡፡ ቁርስ፤ ዳቦ በሻይ (ሻይ ከተገኘ!) ምሳ፤ እንጀራ በሽሮ ወጥ፣ እራት፤ እንጀራ በሽሮ ወጥ፡፡ በዚህ የአመጋገብ ልምድ ውስጥ የሚካተቱት ጤፍ፣ ስንዴ፣ ባቄላ እና ውሃ ናቸው፡፡ በርግጥ በስንዴ ውስጥ ካርቦሃይድሬት፣ በጤፍ ውስጥ iron (ብረት ነክ ማዕድን) በባቄላ ውስጥ ፕሮቲን አለ፡፡ ፋት ግን ምናልባት እንደሽሮፕ በማንኪያ በምትጨመረው ዘይት ውስጥ ካልሆነ በቀር የለም፤ ስለዚህ የሚያወፍረን ምንም ነገር የለም፡፡ በምግብ ዝርዝራችን ውስጥ የሚያወፍር ነገር አለመኖሩ እሰዬው፣ ነገር ግን በሽታ የመከላከል አቅማችንን የሚያጎለብት÷ የፍራፍሬና የአትክልት dessert እንዳይኖር እርጥብ አገራችንን ያደረቃት ማነው?

የልምድ Vegetarians
ኢትዮጵያውያን የኑሮ ነገር ሁኖብን ከጥንትም ጀምሮ የምንመገበው የምግብ ዓይነት vegetarian የሚያሰኘን ነው፡፡ የጤፍና ባቄላ ድምር!!! በርግጥ ብዙዎቻችን የምግብ ምርጫችን ምን እንደሆነ ስንጠየቅ ቁርጥ ወይም ክትፎ ልንል እንችላለን፡፡ የምግብ ምርጫችን ግን አምሮታችን እንጂ÷ ‘የምናዘወትረው የምግብ ዓይነት ነውየሚል ትርጉም እንደሌለው ሁላችንም ይገባናል፡፡

ቬጂቴሪያንነትም ሆነ ቅጥነት ዕድሜን እንደሚቀጥል ምሁራኑ ይናገራሉ፤ ይሁን እንጂ የወፋፍራሞቹ አሜሪካውያን አማካይ ዕድሜ 70 ሲዘልቅ፣ የቀጫጭኖቹና የልምድ ቬጂቴሪያኖቹ ኢትዮጵያውያን ዕድሜ ግን ሃምሳ መድረስ አቅቶታል፡፡የዘመኑ ምርጫ፣ ምን እና ቀጫጫየተባለውን እውነታ አፈርድሜ አስበልቶ፣ ውፍረትን እንደምቾትና እንደጤነኝነት ባገራችን እንዲቆጠር ያደረገው ማነው?

ምግብ አጥቂውን ነው የሚያጠቃው
ይህች አባባል አገልግሎት ላይ የምትውለው ብዙ በሊታ ከሲታዎችን ለመተቸት ነው፡፡ ይሁን እንጂእውን በሊታ ከሲታዎች አሉ?› ብለን ከጠየቅን ውዥንብር ውስጥ መውደቃችን አይቀሬ ነው፡፡ አንዳንዴ አሰሱን ገሰሱን ማግበስበስ ሆድን ከመቆዘርና፣ ጨጓራን ለበሽታ ከመዳረግ ያለፈ ፋይዳ የለውም፡፡

ምግብ አጥቂውን ነው የሚያጠቃውየሚለው አባባል እንደየሃገሩ የተለያየ ትርጉም ይኖረዋል፡፡ ምንም እንኳን እኛጋ ብዙ የሚበሉት ናቸው የሚከሱት ብሎ ለመሳለቅ ቢያገለግልም፤ ወፋፍራሞቹ ዓለም ግን ብዙ መብላት ለውፍረት፤ ውፍረት ደግሞ ለበሽታ ወይም ሞት ይዳርጋል የሚል አንድምታ አለው፡፡ ዞሮ ዞሮ ምግብ አጥቂውን ነው የሚያጠቃው፡፡

እኛ አገር ግን ምግብ ይከበራል፡፡ገበታ ንጉሥ ነውነው ከነአባባሉ፡፡ ሁሉም ንጉሥ ከሚሊዮን አንድ ነው፤ ታዲያ ገበታን ከንጉሥ እኩል ምን አደረገው ብለን ስንጠይቅ መልስ ሊሆን የሚችለውገበታ በሃገራችን ከሚሊዮን አንድ ነውየሚል ይሆናል፡፡ ሌላው ዓለም በሌለ መልኩ ኢትዮጵያ ውስጥ ምግብ ከንጉሥ እኩል ይከበራል፣ ይዘፈንለታል፡፡ በዘፈን ክሊፖቻችን ሳይቀር ለእንቁልልጭ ይቀርባል፡፡ ለምን? ምግብ ብርቅ ነዋ! ምግብን ከጥንት እስከዛሬ በሃገራችን ብርቅ ሆኖ እንዲቀር ያደረገው ማነው?

Sunday, April 1, 2012

የአቡኑ ገዳም



ቡኑ ገዳም
ተራራ ወጥቼ፣ ቡኑ ዘንድ ሄጀ መስቀል ለመሳለም
ክረምቱ በረታ፣ ምንም  ልተቻለ፣ ያሰብኩት ሳይሞላ፣ ሳይሆንልኝ ቀረ
ዳመናው ዝናቡ፣ ጉምና ጭጋጉ፣ ይህ የዛሬ ክረምት መች ያነቃንቃል!
ደጁን ጨቀይቶት፣ ወንዙም ጐርፍ ሞልቶት፣ ጅጉን ስፈሪ፣ በጣም ያስጨንቃል
በታምር በፀሎት፣ ከተራራው ፋፍ፣ ከዳመናው በላይ የገደሙት ገዳም
ደካማው ጉልበቴ፣ ንደምን ይቻለው፣ ጭቃውን ሸርተቴ፣ የኖኁን ዝናም
ዛሬ፣ ነገ ያልኩ ሰማዩና ምድሩን ሳስስ ስመለከት፣ ስቃኝ ድማሱን
ዓይኖቼም ደከሙ፣ ለቀ ጉልበቴ፣ መቃብር ቁፋሮ፣ ሰርክ መማሱን!
ማለዳ-ማለዳ ደረትዋን ገልብጣ፣ ድምጿንም ከፍ ደርጋ የምትጮኸው ወፍ
የቀሰቀሰች  ንቅልፍ ነሳችኝ፣ ሽፍንፍን ብዬ፣ ተኝቼ በሰላም በደህና ንዳላርፍ!
ምድር-ዓለሙ ክዶኝ፣ ሁሉም ጥሎኝ ሄዷል፣ ጠያቂም የለኝም ከቶ ሚያጽናናኝ
ወፊቱስ የት ሄደች? ከጠፋች ቆይታለች፣ ድምጿንም ልሰማሁ፣ ንዳታዝናናኝ
ደጋግሞ የቆየ የሚነፍሰው ነፋስ ለው መጥፎ ጠባይ፣ ኃይለኛ ዙሪት
የጐጆየን ክዳን በትኖ ያነሳ፣ ምን ዓይነት ተንኮል ነው፣ ምን ዓይነት ብሪት!
መቸ ይኸ ብቻ! ሰማዩን ተርትሮ ስደንጋጭ ብልጭታ መብረቅ ሲፈነጥቅ
ከታትሎ ይሏል የሰማይ ነጐድጓድ ቤቱን ንቀጥቅጦ ጆሮ ስኪሰነጥቅ
ተራራ ልወጣህ፣ ታቡን ዘንድ ልደረስኽ፣ መስቀል ልተሳለምክ ብሎ ነው መሰለኝ
ከዚያ ላይ ስወጣ ገደል ከምገባ፣ ወድቄ ከምሞት፣ ወይም ንሸራትቶኝ ከሚሰባብረኝ
ከዚሁ ከቤቴ ካልጋዬ ተኝቼ፣ በንፋስ፣ በመብረቅ ነጉዶ ንጐዳጉዶ እንዳሻው ያድርገኝ!
                              
 ገ/ኢ ጎርፉ