Friday, February 17, 2012

የቤተክርስቲያን መታደስ!


.............................በአሁኑ ወቅት ማንም ሰው ሊያስተውለው እንደሚችል በቤተ ከርስትያን ውስጥ ሁለት የሚጋጩና እርስ በእርሳቸው መጠፋፋት የሚፈልጉ አካላትን እናገኛለን :: አካላት ስንልም ሃሳቦች ናቸው :: ሃሳቦች ግን ሰዎችን ይዘዋል :: ሁለቱ አካላት በእየራሳቸው ለአንድ ዓላማ ይኽውም ለቤተ ክርስቲያን ለመጥቀም እንደሚሰሩ ይናገራሉ ::

ማህበረ ቅዱሳንና ማህበረ ቅዱሳናዊ አስተሳሰብ

ማህበረ ቅዱሳናዊ አስተሳሰብ የምለው ቤተ ክርስቲያን እንከን የለሽ በመሆንዋ ምንም አይነት ትችት ማቅረብ የለብንም የሚለውን እና አብዛኛው የማህበሩ አባላት እንዲሁም ብዙ የሰንበት ትምህርት ቤት ተማሪዎችም የሚጋሩት ነው :: ይህ ሃሳብ በመሰረተ ሃሳብነት ማነኛውም ኦርቶዶክሳዊ ሊደግፈውና ሊጋራው የሚገባው ነው :: የራስን ቤት ይልቁንም መክራና ዘክራ ያሳደገችንን ቤተ ክርስቲያን እንዲህ ናት እያሉ በእየ ሜዳው ስሟን ማጥፋት ክብሯን ማጉደፍ የማይገባ ስራ መሆኑ እሙን ነው :: በሌላ በኩል ደግሞ ምእመናኑ ወደ ኑፋቄ የሚነጠቁበትን እና በሃይማኖት ያሉትም ደግሞ ወደ ቤተ ክርስቲያን አገልግሎት የማይቀርቡበትን ምክነያት አጥንቶ እነዚህ እንዲህ ይደረግ ይህ ይስተካከል ማለት አግባብ ነው ::

ማህበረ ቅዱሳን በእየ ዜናው መውጣት ከጀመረ አለፈ ከረመ እንዳንዶች አይንህን ላፈረ አይነት ጽሁፍ ሲጽፉበት አንዳንዶች ደግሞ እርሱ ከሌለ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ አትኖርም ብለው ክርር ያለ ክርክር ያደርጋሉ :: ታዲያ ሁለቱም ትክክል ሊሆኑ ስለማይችሉ ትክክለኛው የቱ ይሆን ማለቱ አስፈላጊ ነው :: የዚህ ጽሁፍ ጸሓፊ ማህበሩን በሚገባ የሚያውቅ ድክመቶቹንም የማያስተባብል ስለሆነ የማህበሩን በጎ ጎኖችን ሙሉ በሙሉ ዘርዝሮ መጨረስ ባይችልም ዋና ዋና በጎ ጎኖችንና ድክመቶቹን ይጽፋል :: የጽሁፉም አላማ ሰዎች ጥሩውንና መጥፎውን ለይተው ከመልካሙ ጋር እንዲተባበሩ ከመጥፎው ደግሞ እንዲርቁ ነው ::

Thursday, February 16, 2012

የምንገዛው ለማነው?


                        
1/ ነፍስ ሁሉ በበላይ ላሉት ባለ ስልጣኖች ይገዛ፡፡ ከእግዚአብሔር ካልተገኘ በቀር ስልጣን የለምና፤ ያሉትም ባለስልጣኖች በእግዚአብሔር የተሾሙ ናቸው፡፡
2. ስለዚህ ባለ ስልጣንን የሚቃወም እግዚአብሔርን ሥርዓት ይቃወማል፤የሚቃወሙትም በራሳቸው ላይ ፍርድን ይቀበላሉ፡
3. ገዢዎች ለክፉ አድራጊዎች እንጂ መልካም ለሚያደርጉ የሚያስፈሩ አይደሉምና፡፡ባለስልጣንን እንዳትፈራ ትወዳለህን? መልካሙንአድርግ ከእርሱም ምስጋና ይሆንልሃል፤
4. ለመልካም ነገር ለአንተ የእግዚአብሔር አገልጋይ ነውና፡፡ በከንቱ ግን ሰይፍ አይታጠቅምና ክፉ ብታደርግ ፍራ፤ ቁጣውን ለማሳየት ክፉ አድራጊን የሚበቀል የእገዚአብሔር አገገልጋይ ነውና፡፡


Wednesday, February 15, 2012

በኤርትራዊው አሸባሪ የተመራው የማኅበረ ቅዱሳን ቡድን!

ለዘማርያን የመዝሙር ግጥምና ዜማ በመቀመር የሚታወቀው ዲ/ን ጋሻዬ መላኩ ጥር 4 ቀን 2004 ዓ.ም ጋብቻውን  በሥርዓተ ተክሊል በአዲስ አበባ ደብረ ጽጌ ቅዱስ ኡራኤል ቤተክርስቲያን ፈጸመ፡፡ (ምናልባት ዲ/ን ጋሻዬን ለማታውቁት በዘማሪት ዘርፌ ከበደ እውነተኛ ታሪክ ዙሪያ በሚያጠነጥነው የ"ፓራሜራ" ፊልም ላይ ከዘማሪ ዲ/ን ሀብታሙ ሽብሩ ጋር ሆኖ ግጥምና ዜማ ሲያስጠናት የሚታየው ነው)፡፡

በዲ/ን ጋሻዬ መላኩ ሥርዓተ ተክሊል ላይ ከሌሊቱ 10፡00 ሰዓት ጀምሮ በርካታ የቤተክርስቲያናችን ሰባክያንና ዘማሪያን እንዲሁም ልዩ ልዩ አገልጋዮች የተገኙ ሲሆን እስከ ጥዋቱ 2፡30 የነበረው መርሐ ግብር የተረጋጋ እና የሰከነ እንደነበር ተገልጿል፡፡ ይሁን እንጂ፣ ሥጋ ባየበት እንደሚዞር ጆፌ አሞራ ከአገልጋዮች ሥር የማይጠፋው "ማኅበረ ቅዱሳን" ዝግጅቱን ለማደናቀፍ መሞከሩ አልቀረም፡፡

"ማኅበረ ቅዱሳን" ያዘጋጀው ይህ የረባሽ ቡድን ሦስት መታወቂያዎችን ይዞ ሲንቀሳቀስ በካራማራ ወረዳ ፖሊስ የተያዘና ጉዳዩ በፍርድ ቤት በመታየት ላይ ያለ ተስፋዬ በሚባል ኤርትራዊ አሸባሪ ግለሰብ እና ሐጂ እና እንድዬ በሚባሉ ሁለት ረዳቶቹ እንደተመራ ታውቋል፡፡ ቁጥጥር በማይደረግበት በቤተክርስቲያን አንጡራ ሀብት ከ"ማኅበረ ቅዱሳን" በወር እስከ 3500 (ሦስት ሺህ አምስት መቶ) የሚከፈላቸው እነዚህ ግለሰቦች ጥቅምት 11/2004 ዓ.ም በዲ/ን ዘማሪ ትዝታው ሳሙኤል ላይ ድብደባ የፈጸሙና በዘመድኩን በቀለ የክስ ሂደት ላይም በየችሎቱ እየተገኙ በአገልጋዮች ላይ የዛቻ እና የማስፈራራት ወንጀል የሚፈጽሙ መሆናቸው በተጨማሪ ታውቋል፡፡

እነዚህ ሦስት ግለሰቦች የተመደቡላቸውን ወደ ሰባ የሚሆኑ ወሮበሎች መርተው ወደ ተቀደሰው የቤተክርስቲያን ቅጥር ግቢ ገብተው ሁከት ለማሰነሳት የሞከሩ ሲሆን፣ በቅድሚያ መረጃ የደረሰው የፖሊስ ሠራዊት ደርሶ ሁከቱን በቁጥጥር ሥር ሊያውለው ችሏል፡፡ ይህ የወሮበላ ቡድን አገልጋዮችን በስም እየጠራ እነ እከሌ፣ እነ እከሌ ይውጡልኝ እያለ ላንቃው እስኪላቀቅ ቢጮኽም፣ በቤተክርስቲያን የሚካሄደው የዲ/ን ጋሻዬ መላኩ የጋብቻ ሥነ ሥርዓት መርሐ ግብር በስብከተ ወንጌል አዳራሹ በተሳካ ሁኔታ መካሄዱን በሥፍራው የነበሩ ታዳሚዎች ገልጸውልናል፡፡

በስብከተ ወንጌል አዳራሹ በነበረው አገልግሎት መጋቤ ሀዲስ በጋሻው ደሳለኝ ተገኝቶ ለዕለቱ የሚገባ መንፈሳዊ መልዕክት ያስተላለፈ ሲሆን፣ መምህር አሰግህድ ሣህሉ፣ መምህር ተረፈ አበራ እና ሌሎችም አገልጋዮች መታደማቸው ተገልጿል፡፡ በዕለቱ መርሐ ግብር መሠረት ከመምህር ተረፈ ቀጥሎ ትምህርቱን ያቀረበው መጋቤ ሀዲስ በጋሻው ሲሆን፣ በዚሁ ትምህርቱ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ወደ ልጇ በማማለድ የእነ ዶኪማስን ጉድለት በማሟላት የአማላጅነቷ ሚስጥር የተገለጠበት እና በጌታ ዘንድም ጋብቻ ክቡር መሆኑ የተመሠከረበት ነው በማለት በመሳጭ ስብከቱ ምዕመናንና ምዕመናትን አገልግሏል፡፡

"ማኅበረ ቅዱሳን"፣  "በሃይማኖት ጉዳይ መፍረድ የአንተ ሥልጣን አይደለም፤ አርፈህ ተቀመጥ" ቢባልም የሚሰማበት ጆሮ ስለሌለው ቤተክርስቲያንንና ሕዝብን የማወክ ተግባሩን ቀጥሎበታል፡፡

"ማኅበረ ቅዱሳን" በቤተክርስቲያንና በፍርድ ቤት ፊት እውነትን መጋፈጥ ሲያቅተው፣  በውድቅት ሌሊት እንደሚልከሰከስ ሰይጣን በየአጥቢያ ቤተክርስቲያናቱ፣ በየጎዳናውና በየቤቱ እየዞረ የሚረብሽ ተናካሽ ውሻ ወደመሆን ደረጃ ወርዷል ሲሉ ታዛቢዎቻችን ገልጸዋል፡፡ በወንጌል ብርሃን ሲፈተሽ እንደ ቅቤ የሚቀልጠው "ማኅበረ ቅዱሳን" በእግዚአብሔር ቤተመቅደስ እንደዚህ ዓይነቱን ርኩሰት እየደጋገመ መፈጸሙ የዘመኑ መጨረሻ ዓይነተኛ ምልክት መታየት መጀመሩን አንባቢ ያስተውል ብለዋል፡፡

የዝግጅት ክፍላችንም እግዚአብሔር ለወንድማችን ለዲ/ን ጋሻዬ መላኩ፣ ጋብቻው የሠመረ የአብርሃምና የሣራ እንዲያደርግለትና ቀሪው የአገልግሎት ዘመኑን እንዲባርክለት፣ እንዲሁም በሚሠራው ሥራና በሚሰጠው አገልግሎት ፀጋውን እንዲያበዛለት  ይመኛል፡፡

የእግዚአብሔር ጥበቃና ቸርነት ከሁላችን ጋር ይሁን!!!
አሜን!!!