Tuesday, February 14, 2012

የይስሙላ ድርድር እንዳይሆን እንሰጋለን!


የይስሙላ ድርድር እንዳይሆን!
ሰሞኑን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የ20 ዓመት የሁለት ሲኖዶስ ክፍፍል ለማቆም ድርድር እንደተጀመረ ከሚዲያው ሰምተናል። ምንም ይሁን ምንም እርቅና ስምምነት ከልብ ከሆነ መልካም ነው። እነዚህ ሁለት ወገኖች የራሳቸው ጥቅምና መብት የማስከበር ዓላማ እንዳላቸው ሁሉ ለስምምነቱ እልባት አለመድረስም ያንን በማስጠበቅ ላይ የተመሰረተ ስለሆነ የከዚህ በፊቶቹ ድርድሮች ውጤታማ ሳይሆኑ ቀርተዋል። ያሁኑን የተለየ የሚያደርገው ምን እንደሆነ በግልጽ የተነገረ ነገር ባይኖርም እኛ ግን ያለፈው ነገር እንዳይደገም ከመስጋት አንጻር የግላችንን ሃሳብ ከታች በአጭሩ ለማቅረብ ሞክረናል።

ድርድር የእርቅ መነሻ ምእራፍ ነው። ተደራዳሪዎች ግራና ቀኝ ሆነው ይሄንን ማግኘት ወይም ማስጠበቅ አለብኝ ብለው ይዘው የሚቀርቧቸው የድርድር ጭብጦች ይኖራቸዋል። ጭብጡ የሚወሰነው ተደራዳሪው ወገን በሚያመጣው ነጥብ ላይ ነው። የትኛውም ተደራዳሪ ወገን አስቀድሞ እነዚህን አምስት ነጥቦች አስወግዶ ወደ ድርድሩ ጠረጴዛ ካልመጣ ድርድሩ ውጤታማ አይሆንም።
የተደራዳሪዎች ውስጣዊ ሁኔታዎች፥
1/ ለድርድር የሚያቀርባቸው ነጥቦች ከተደራዳሪው ወገን የሚጠብቀው በነባራዊ ሁኔታ ያልተመሰረተ ጥያቄ ከሆነ፣
2/ ከምፈልጋቸው ነጥቦች ምንም አላጎድልም ወይም ሁሉም ይጠበቁልኝ ብሎ ከተዘጋጀ፣
3/ ከሁለቱ ተደራዳሪዎች ውጪ የሚያግባባ የሶስተኛ ወገን አደራዳሪን ሃሳብ ለመቀበል ካልፈቀደ፣
4/ ተደራዳሪው ወገን ለሚያቀርበው ሃሳብ «ምን እያለ ነውብሎ ከማጣጣል «እያለ ያለው ለምንድነውብሎ ለመረዳት ካልፈለገ፣
5/ ነገሮችን በሰከነ መንፈስ ለመገንዘብ ከመሞከር ይልቅ ከተደራዳሪው ወገን ምንም ላይገኝ ብሎ እልህ በመጋባት የሚያከር ከሆነ፣ የሁለት ወገን ተደራዳሪዎች ድርድር ውጤታማ ላይሆን ይችላል።
የተደራዳሪዎች ውጫዊ ሁኔታዎች፣
የትኛውም ተደራዳሪ ወገን ከጎኑ በድጋፍ የቆሙ ወይም በእጅ አዙር የሚደግፉ ወይም ሃሳቡን የሚመሩ ወገኖች ድርድሩን ሊያከሩበት ወይም ተደራዳሪው በማይፈልጋቸው የኃይል ውጫዊ አሰላለፎች ድርድሩን ውጤታማ እንዳይሆን ሊያደርጉት ይችላሉ።
1/ ተደራዳሪውን ከኋላ የሚነዱት ኃይሎች፣ በተደራዳሪያቸው ሳቢያ የሚደርስባቸውን ጉዳት ለመከላከል ድርድሩን ከፍጆታ ባለፈ የማይፈልጉት ሆኖ ሲገኝ፣
2/ ተደራዳሪውን የሚደግፉ አባላት፣ በተደራዳሪያቸው ምክንያት የአባልነት ወይም የደጋፊነት መብታቸው የማይጠበቅ ከሆነ ወይም ካልተከበረ፣ ድርድሩ በውጪያዊ ተጽእኖ ሊስተጓጎል ይችላል።
በተደራዳሪዎቹ ውስጣዊ የድርድር አቋምና ዓላማ እንዲሁም ድርድሩ በቀጥታ ባይመለከታቸውም ከድርድሩ የሚጠቀሙ ወይም የሚጎዱ አካላት በድርድሩ ላይ ተጽእኖ በማሳረፍ ውጤታማነት እንዲጎድለው ሊያደርጉ ይችላሉ።
ከነዚህ ነጥቦች ተነስተን በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የውጪና የሀገር ውስጥ ሲኖዶስ መካከል ያለውን የእርቅ ድርድር መገምገም ይቻላል።
በሀገር ውስጥና በውጪው ሲኖዶስ አንጻር፣
1/ የኢትዮጵያ መንግሥት፣ በግዛቱ ያለውን ሲኖዶስ በራሱ ሕግ ጥላ ሥር እስካለ ድረስ እንደሕጋዊ ሲኖዶስ ስለሚቆጥር በድርድሩ ላይ በውጪ ካለው ሲኖዶስ የሚቀርቡ የድርድር መልኮች ሁሉ የእሱን(የመንግሥትን) ሉዓላዊነት የማይነኩ እንዲሆኑ ይፈልጋል።
2/ በሀገር ውስጥ ያለው ሲኖዶስ ድርድሩ በስደተኝነት ወይም በሁለተኛ ሀገር የሚኖር ባለመሆኑ ከውጪ ያለውን ሲኖዶስ እንደአቻ ሳይሆን እንደመብት ጠያቂና ተቀባይ ወገን አድርጎ የመመልከት ሁኔታ ሊኖር ይችላል።
3/ በውጪ ያለው ሲኖዶስ በድርድሩ መነሻ እርቁ ፍጻሜ ቢኖረው የሚያጣው ነገር ሊኖር እንደሚችል ከገመተ ወይም ድርድሩ የነበረውን ሁኔታ ቀይሮ ፍጹም ሊያደርገው አይችልም ብሎ ካመነ ድርድሩን ውጤታማ ላያደርገው ይችላል።
ስለሆነም በሁለቱ ሲኖዶስ ወገኖች በኩል ያሉትን ነባራዊ ሁኔታዎች ገምግመውና አስቀድመው ለሲኖዶሱ ድርድር መልካምነት በየራሳቸው መንገድ ጠርገው በዚያ ላይ እየተረማመዱ ወደድርድሩ ጠረጴዛ ካልመጡ በስተቀር ስምምነቱ ፍጻሜ ይደርሳል ማለት አስቸጋሪ ነው።
እስካሁን የተደረጉ ግንኙነቶች ሁሉ ውጤታማ ያልሆኑበት ምክንያት ይህንን መሠረት ያደረጉ ናቸው።
እኛም እነዚህን ነጥቦች ያነሳነው ቤተክርስቲያንን እንደክርስቶስ አካልነቷ ሳይሆን እንደፖለቲካ መሳሪያነቷ እየተጠቀሙ በሚገኙት የውጪና የሀገር ውስጥ ሲኖዶስ አመለካከት ላይ ተንተርሰን እንጂ እንደመንፈሳዊ ተቋም ሰዎች አይተናቸው አይደለም። ሥልጣንንና ኃይልን (Authority & Power) ስለመካፈል እንደፖለቲካው የድርድር መሳሪያነት (Negotiation tools) ከላይ ያየናቸው ነጥቦች ጠቃሚ ናቸው። ከሃዲና ከሃዲ ተባብለው ተወጋግዘው ሲያበቁ አሁን ስለክህደቱ ጉዳይ ጉባዔ ለመጥራት ሳይሆን ስለሥልጣኑ ጉዳይ ሼር ለመነጋገር እንደሆነ ስንመለከት ቀድሞውኑ የተጣሉት ስለክርስቶስ ቤተክርስቲያን እንዳልነበረ ያረግጥልናል። ስለሆነም ፖለቲከኞቹ የሃይማኖት ሰዎች ድርድራችሁን አለዝባችሁ ስምምነት ላይ በድርድር መርህ ለመድረስ ሞክሩ!
ለዚህም የድርድሩ መርህ ይርዳችሁ እንላለን!

Monday, February 13, 2012

የአቡነ ገብርኤል ተልዕኰ!


በሲዳማ፣ ጌዴኦ፣ አማሮና ቡርጂ ዞኖችና ልዩ ወረዳዎች ሀገረ ስብከት በተለይም በሀዋሳ ለአንድ ዓመት ከስምንት ወራት ያህል የቆየው ውዝግብ እስካሁን መቋጫ አለማግኘቱን መረጃዎች ያመለክታሉ፡፡ ለውዝግቡ መባባስ የአቡነ ገብርኤል አንዱን አቅርቦ አንዱን የማራቅ አድሏዊ አመራር ትልቁን ድርሻ ሲወስድ፣ ቅዱስ ሲኖዶስ፣ የመንበረ ፓትርያርክ ልዩ ጽ/ቤትና ጠቅላይ ቤተክህነት ጽ/ቤት ተገቢውን እርምጃ ባለመውሰዳቸው የምዕመናኑ ሰቆቃ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መምጣቱን ከተለያዩ ምንጮች ለመረዳት ችለናል፡፡

አቡነ ገብርኤል በሁለንተናዊ የስብዕና ቀውስ ውስጥ ያሉ ሰው ናቸው ያሉ ታዛቢዎቻችን እንዳስረዱን፣ ሊቀጳጳሱ የሚናገሯቸውና የሚፈጽሟቸው ድርጊቶች የትላንቱ ከዛሬው፣ የዛሬው ከነገ የማይጣጣሙ ርስ በርሳቸው የሚምታቱ ናቸው ብለዋል፡፡ በተከበረውና በተቀደሰው ዐውደ ምሕረት ላይ አንድ ጊዜ በድያለሁ ይቅርታ ሲሉ፣ ሌላ ጊዜ ደግሞ በግል መጽሔት ጭምር በአምሳለ ሥላሴ የተፈጠሩትን ምዕመናንንና ምዕመናትን ቀበሮዎች እያሉ የሚሳደቡ መሆናቸው ተገልጿል፡፡  ሰውየው በዚህ ብቻ ሳያበቁ በቅዱስ ሲኖዶስ ፊት ከቤተክርስቲያን የተለየ እና የተከፈለ ሕዝብ የለም ጥቂት ተሃድሶአውያን ናቸው እያሉ የ"ማኅበረ ቅዱሳን"ን የውሸት አሉባልታ ያስተጋባሉ፡፡ ሌላ ጊዜ ደግሞ አዎን የተሰደደ ሕዝብ አለ፡፡ ዕድሉ ይሰጠኝና ሁለቱንም አስማማለሁ እያሉ ሲማጸኑ ይታያሉ፡፡

አቡነ ገብርኤል በግል ቀርቦ ለሚያነጋግራቸው አሁን ያለው የቤተክርስቲያን ቀውስ በዋነኛነት በ"ማኅበረ ቅዱሳን" የተንኮልና የጥፋት ዕቅድ እንደሚመራ፣ እንዲሁም አገልጋዮች ያለ ጥፋታቸው እንደሚሰደቡና በግላቸውም አገልጋዮቹን እንደሚያደንቋቸው ሲመሰክሩ፣ በአደባባይ ሲሆን ግን ከማኅበሩ ብሰው ሽንጣቸውን ገትረው ይራገማሉ፡፡ አቡነ ገብርኤል የማስመሰል ድርጊታቸው ከውስጥ ባህርያቸው የሚመነጭ ነው ያሉ እነዚህ ወገኖች፣ እንደማሳያ የሚሆነን በዕድሜ ያረጁ ሆነው ሳለ ወጣት ለመምሰል ጥቁር ሂና (የፀጉር ቀለም) መቀባታቸው ራሳቸውን በወጣትነት ውስጥ ደብቀው ከሁኔታዎች ጋር ለመመሳሰል መሞከራቸው ነው ብለዋል፡፡ ቤተክርስቲያንንም የሚያጠቁት የዋህና ምንም የማያውቅ ቅን ክርስቲያን በመምሰል ነው ብለዋል፡፡

ምክራችሁን እሻለሁ!

 ጥያቄ፦

እባካችሁ ወገኖች ምክራችሁን እሻለሁ!

በጌታ የተወደዳችሁ ወገኖቼ ሰላም ለናንተ ይሁን!

ባለትዳርና የልጆች እናት ነኝ፡፡ ባለቤቴ እጅግ የሚወደድና ምስጉን ባህርይ ያለው ሰው ነው፡፡ ስራው የግሉ ንግድ ላይ ሲሆን ብዙውን ጊዜ ለስራው ሲሮጥ ከወዲህ ወዲያ ሲል ለስኬቱም ሲለፋ ነው የሚውለው፡፡ ለኔም ሆነ ለልጆቹ ያለው ፍቅር ሰው የሚቀናበትና እጅግ የሚገረምበት ነው፡፡ ትልቁ ህልሙ ልጆቹን ውጤታማ አድርጎ ለማየት ሲሆን ብዙውን ጊዜም እኔ ባለፍኩበት ልጆቼ እንዲያልፉ አልፈልግም ብሎ ይናገራል፡፡

እኔ ደግሞ በስነ ጥበብ ስራ ላይ ስገኝ ከስራዬ ባህርይ የተነሳ ከብዙ አለማውያን ወንዶች ጋር እገናኛለሁ፡፡ በስራዬ ደግሞ ስኬታማና ስም ያለኝ ሴት ነኝ፡፡ በሃገር ውስጥም ሆነ ከሃገር ውጪ የተለያዩ ግለሰቦችም ሆኑ ድርጅቶች እያዘዙኝ እሰራለሁ፡፡ ከዚህ በተጨማሪ በአንድ የውጪ ድርጅት ውስጥም ተቀጠሬ እየሰራሁ ነው፡፡

ከኢትዮጵያ ውጪ ካሉት አሰሪዎቼ ውስጥ አንደኛው ግለሰብ ብዙውን ጊዜ ወደሃገር ቤት ይመላለሳል፡፡ የስራ ትእዛዞችን ሰጥቶኝና የተሰሩትንም ይዞ ለመሔድ እዚህ በመጣ ጊዜ በተደጋጋሚ እንገናኛለን፡፡ ይሄ ሰው ዳጎስ ያለ ክፍያ የሚከፍለኝ ሲሆን ከውላችን ውጪም ተጨማሪ ገንዘብ በስራዬ መደሰቱን በመግለጽ አልፎ አልፎ ይሰጠኛል፡፡ ባለበት ሃገር ሆኖም ለሰላምታ ይደውልልኛል አልያም ኢሜይል አልፎ አልፎ እንጻጻፋለን፡፡

ከቅርብ ጊዜ ውዲህ ደግሞ በፌስቡክ ላይ ተገናኝተን ቻት እየተደራረግን ቀረቤታችን ለየት ያለ ወሬን ወደማውራት እና ወደመነፋፈቅ ተሸጋገረ፡፡ በወሬያችን እንደሚወደኝ እና ለኔ ለየት ያለ ስሜት እንዳለው ሲገልጽልኝ ባለትዳርና የልጆች እናት መሆኔን እያወቀ እንዲህ አይነቱን ነገር ማሰብ እንደሌለበት ደጋግሜ እናገረዋለሁ አኩርፎኝ እንለያያለን፡፡ (ሳልገልፀው የማላልፈው ጉዳይ ቢኖር እርሱ ትዳሩን ከጥቂት አመታት በፊት የፈታ ሲሆን የልጆች አባትም ነው)፡፡

የሄንን ሰው በስራየ ማጣት የለብኝም ባይሆን ረጋ ብዬ አስረዳዋለሁ እልና በሌላ ጊዜ ኦን ላይን ሳገኘው ረጅም ሰዓት ወስጄ ሃሳብ እንለዋወጣለን፡፡ በሃላም የተረዳኝ መስሎ ለጥቂት ጊዜ ተወኝ፡፡ የምናወራውም እነዴት ነህ እንዴት ነሽ ብቻ ሆነ፡፡ መጻጻፉንም እንደድሮው ሳይሆን ቀነስ አደረገ፡፡

እኔም በራሴ ወስኜ ፌስ ቡክ የሚባለውን ነገር ከስንት አንዴ ከመጠቀም በቀር በአብዛኛው ተውኩት፡፡ የምከፍተውም ከሃገር ውጪ ያሉ አብሮ አደጎቼን ለማግኘትና ከክርስቲያን ወገኖቼ ጋር መንፈሳዊ ነገሮችን ለመዋወጥ ብቻ ነው፡፡ እርሱንም ሊያገኘኝ የማይችልበትን ሰዓት እየተጠቀምኩ ነበር፡፡


በቅርቡ በግል ኢሜይሌ የተላኩልኝን መልእክቶች በማየትና ምላሽ በመስጠት ላይ እያለሁ በዚያም ቻት ማድረጊያው ላይ መልእክት መጣልኝ፡፡ ከዚህ በፊት በዚህ ተጠቅሜ ስለማላውቅ በመገረም ሳነበው የእርሱ እንደሆነ ገባኝ፡፡ በመጥፋቴ እንደተጨነቀና እንዳጋጣሚ እንዳገኘኝ ገልጾልኝ ተቀይሜው እንደሆነ ጠየቀኝ፡፡ በፍጹም ቅያሜ በኔ ልብ ውስጥ እንደሌለ ገልጬለት ስለ ስራችን አውርተን ተለያየን፡፡

በሳምንቱ ይመስለኛል ስልክ ደውሎ ለየት ላለ ስራ እንደሚፈልገኝ ገልጸልኝ ስለሁኔታውም አስረድቶኝ ለኔ ቀላልና ልሰራው የምችለው መሆኑን ገለጽኩለት፡፡ እግረ መንገዱንም ስለነበረው ያለፈው ሁኔታ አንስቶብኝ ፈጽሞ እንዲረሳውና ግንኙነታችን እንደቀድሞ እንዲሆን ገልጨለት በዚሁ ተለያየን፡፡ በማግስቱ ኢሜይል አድርጎልኝ አገኘሁ፡፡ ለኔ የተለየ ልብ እንዳለው፤ ፈጽሞ ሊያጣኝ እንደማይፈልግ ፤የሚያጣኝ መስሎት ተጨንቆ እንደነበርና አሁን ግን እረፍት እንዳገኘ የሚገልጽ ነበር፡፡ ምላሽ ግን አላኩለትም፡፡