ጠያቂ፦ አብርሃም እባላለሁ፤ በኢየሱስ ክርስቶስ ወንጌል አምናለሁ፡ ቃሉንም ዘወትር አነባለሁ፡ ነገር
ግን በአሳፋሪ የዝሙትና የስንፍና ሃጢአት ባሪያ ሆኝለሁ....ብዙ ጊዜ ለመመለስ ብሞክርም በተደጋጋሚ ወደቅኩ።
እባካችሁ ይህንን ጥያቄ ያነበባችሁ ሁሉ ባላችሁበት ቦታ ጸልዩልኝ። ምክራችሁንም ለግሱኝ።
መልስ፦
የዝሙት ኃጢአት ባሕርያት
ከሁሉ አስቀድሜ እየተለማመድክ ስላለኸው ኃጢአት ምንነትና ባህርይ የበለጠ መረዳት እንድትችል አንዳንድ ነገሮችን ለማለት እወዳለሁ።
እንደዚህ አይነት ኃጢአቶች ብዙ ጊዜ በትንሹ የሚጀመሩና ከጥቂት ጊዜ በኋላ የራሳቸው የሆነ ሕይወት አበጅተው በራሳቸው ጉልበትና ኃይል የሚንቀሳቀሱ ኃጢአቶች ናቸው። ብዙ ጊዜ የሚጀመሩት በፈተና ነው። የሚፈትኑና የፍትወት ፍላጎትን የሚያነሳሱ ሁኔታዎች ይገጥሙና የመጀመሪያውን ፈተና መቋቋም ባለመቻል ይጀመራል። ብዙ ጊዜ ይህንን አይነት ኃጢአት የሚለማመድ ሰው (ቀድሞውኑም ጤናማ የክርስትና ሕይወት የነበረው ሰው ከሆነ) ኃጢአቱን ለማሸነፍና ፈተናውን ለመቋቋም የተወሰኑ ትግሎችን ያደርጋል። የሚፈትን ነገር ይኖራል፤ እናም ያንን ለመቋቋም ይሞከራል፡ ነገር ግን ይወደቃል። እንደ ማንኛውም ኃጢአት ከመደረጉ በፊት የነበረው "ደስታ"ና ግፊት ኃጢአቱ ከተደረገ በኋላ ከመቅስበት ጠፍቶ ወደ ጸጸትና ሃፍረት ስለሚለወጥ፤ ፈተናውን ሳይቋቋሙ ቀርተው በዚህም ኃጢአት ሲወድቁ ሰዎች በመጀመሪያ አካባቢ ይጸጸታሉ፤ ሁለተኛም ደግመው ላለማደረግ ይወስናሉ። ነገር ግን ከጥቂት ጊዜያት በኋላ ተመሳሳይ ፈተና ይመጣል፤ ትንሽ ያንገራግራሉ ደግመውም ያንኑ ኃጢአት ሲለማመዱ ራሳቸውን ያገኙታል ወዘተ።
እንዲህ እንዲህ ይልና መጀመሪያ ፈተና ከዚያም ማንገራገር በመጨረሻም መውደቅ የሚለው አዙሪት እየተደጋገመ ይሄዳል። ይህ ድግምግሞሽ ግን ወደሚቀጥለው የኃጢአት ደረጃ ይሻገራል። ይህም ከጊዜ በኋላ ኃጢአቱ እየተወደደና እየተደጋገመ ስለሚሄድ በራሱ ሕይወት ያለው ልምድ ይሆናል። ልምድ ደግሞ የሕይወት አካል ከሆነ ኃጢአቱ የሚደረገው ፈተና ስላለ ብቻ ሳይሆን ደስ ስለሚልና ስለ ለመድነው ነው። ከፈተና አልፎ የራሱ የሆነ ሕይወት አበጀ ማለት ነው። ከፈተና አልፎ በየጊዜው የምንለማመደው የሕይወታችን አካል ሆነ ማለት ነው። በዚህ ደረጃ ከደረሰ ደግሞ ኃጢአቱን ለመለማመድ ግዴታ የሚፈትኑ ነገሮች መኖር የለባቸውም። እኛው ራሳችን፤ በራሳችን ተነሳሽነት እንደ ልማዳችን ኃጢአቱን መለማመድ እንጀምራለን። መጀመሪያ ላይ ፈተናው የሚመጣው ከውጪ ነበር፤ በኋላ ልምድ ሲሆን ግን ያለ ወጪያዊ ፈተና ኃጢአቱ መጥፎ ልማድ ስለሆነብን ተነሳሽነቱ ከእኛው ውስጥ ነው የሚመነጨው። ይህ አደገኛ አካሄድ ላይ እንዳለን የሚያሳይ ምልክት ነው። ኃጢአቱ በሕይወታችን ቤቱን እየሠራና የእኛ አንዱ አካል እየሆነ የሚያመልክት ትልቅ ማስጠንቀቂያ ነው።
መልስ፦
የዝሙት ኃጢአት ባሕርያት
ከሁሉ አስቀድሜ እየተለማመድክ ስላለኸው ኃጢአት ምንነትና ባህርይ የበለጠ መረዳት እንድትችል አንዳንድ ነገሮችን ለማለት እወዳለሁ።
እንደዚህ አይነት ኃጢአቶች ብዙ ጊዜ በትንሹ የሚጀመሩና ከጥቂት ጊዜ በኋላ የራሳቸው የሆነ ሕይወት አበጅተው በራሳቸው ጉልበትና ኃይል የሚንቀሳቀሱ ኃጢአቶች ናቸው። ብዙ ጊዜ የሚጀመሩት በፈተና ነው። የሚፈትኑና የፍትወት ፍላጎትን የሚያነሳሱ ሁኔታዎች ይገጥሙና የመጀመሪያውን ፈተና መቋቋም ባለመቻል ይጀመራል። ብዙ ጊዜ ይህንን አይነት ኃጢአት የሚለማመድ ሰው (ቀድሞውኑም ጤናማ የክርስትና ሕይወት የነበረው ሰው ከሆነ) ኃጢአቱን ለማሸነፍና ፈተናውን ለመቋቋም የተወሰኑ ትግሎችን ያደርጋል። የሚፈትን ነገር ይኖራል፤ እናም ያንን ለመቋቋም ይሞከራል፡ ነገር ግን ይወደቃል። እንደ ማንኛውም ኃጢአት ከመደረጉ በፊት የነበረው "ደስታ"ና ግፊት ኃጢአቱ ከተደረገ በኋላ ከመቅስበት ጠፍቶ ወደ ጸጸትና ሃፍረት ስለሚለወጥ፤ ፈተናውን ሳይቋቋሙ ቀርተው በዚህም ኃጢአት ሲወድቁ ሰዎች በመጀመሪያ አካባቢ ይጸጸታሉ፤ ሁለተኛም ደግመው ላለማደረግ ይወስናሉ። ነገር ግን ከጥቂት ጊዜያት በኋላ ተመሳሳይ ፈተና ይመጣል፤ ትንሽ ያንገራግራሉ ደግመውም ያንኑ ኃጢአት ሲለማመዱ ራሳቸውን ያገኙታል ወዘተ።
እንዲህ እንዲህ ይልና መጀመሪያ ፈተና ከዚያም ማንገራገር በመጨረሻም መውደቅ የሚለው አዙሪት እየተደጋገመ ይሄዳል። ይህ ድግምግሞሽ ግን ወደሚቀጥለው የኃጢአት ደረጃ ይሻገራል። ይህም ከጊዜ በኋላ ኃጢአቱ እየተወደደና እየተደጋገመ ስለሚሄድ በራሱ ሕይወት ያለው ልምድ ይሆናል። ልምድ ደግሞ የሕይወት አካል ከሆነ ኃጢአቱ የሚደረገው ፈተና ስላለ ብቻ ሳይሆን ደስ ስለሚልና ስለ ለመድነው ነው። ከፈተና አልፎ የራሱ የሆነ ሕይወት አበጀ ማለት ነው። ከፈተና አልፎ በየጊዜው የምንለማመደው የሕይወታችን አካል ሆነ ማለት ነው። በዚህ ደረጃ ከደረሰ ደግሞ ኃጢአቱን ለመለማመድ ግዴታ የሚፈትኑ ነገሮች መኖር የለባቸውም። እኛው ራሳችን፤ በራሳችን ተነሳሽነት እንደ ልማዳችን ኃጢአቱን መለማመድ እንጀምራለን። መጀመሪያ ላይ ፈተናው የሚመጣው ከውጪ ነበር፤ በኋላ ልምድ ሲሆን ግን ያለ ወጪያዊ ፈተና ኃጢአቱ መጥፎ ልማድ ስለሆነብን ተነሳሽነቱ ከእኛው ውስጥ ነው የሚመነጨው። ይህ አደገኛ አካሄድ ላይ እንዳለን የሚያሳይ ምልክት ነው። ኃጢአቱ በሕይወታችን ቤቱን እየሠራና የእኛ አንዱ አካል እየሆነ የሚያመልክት ትልቅ ማስጠንቀቂያ ነው።