Showing posts with label ዜና. Show all posts
Showing posts with label ዜና. Show all posts

Tuesday, August 9, 2016

ተገቢ ትኩረት የሚያሻው የአዲስ አበባ ሀ/ስብከት ካህናት አቤቱታ!



በአዲስ አበባ ሀ/ስብከት ውስጥ ያሉ አጠቃላይ ማኅበረ ካህናቱ በአቤቱታ ድምጻቸው  ወቅታዊ፤ ትክክለኛና አፋጣኝ ምላሽ የሚያስፈልገው አቤቱታ አቅርበዋል የሚል እምነት አለን። ይህንን አቤቱታ ዝም ብሎ ማለፍ በቤተክርስቲያኒቱ አጠቃላይ ውድቀት ላይ ከኤጲስቆጶሳት አስመራጭ ኮሚቴ ስህተቶች ጋር ተባባሪ መሆን ብለን እናምናለን።
ዘረኝነት፤ ጉቦና የኃጢአት ገመና እንዲህ እንደዘንድሮው ታይቶም፤ ተሰምቶም አይታወቅም። ማኅበረ ቅዱሳን በትክክል ቤተ ክርስቲያኒቱን መቆጣጠሩን ያስመሰከረበት ጊዜ ቢኖር በዚህ የኮሚቴ ምርጫ የታየው የኩነኔና የፍርድ መዝገብ በአደባባይ መነገሩ ነው። ዘረኝነት ቦታውን ተረክቧል። ሙስናው በግልጽ ይታያል። ድሮም ቢሆን በእነጉድ ሙዳይ የሚመራ ኮሚቴ ከዚህ ዓይነቱ ቆሻሻ ተግባር የራቀ ሊሆን እንደማይችል የነበረን ግምት ትክክለኛ ነበር።
የኛም ግምት ስህተት እንዳልነበር የሚያሳየው የአዲስ አበባ ሀ/ስብከት ካህናት ድርጊቱን በመመልከት ቀጥተኛ አቤቱታ ማቅረባቸው ሲሆን ለካህናት ጩኸት ጆሮ ሊሰጠው ይገባል እንላለን። ፓትርያርክ ማትያስም ለራሳቸው ክብርና ስም፤ ታላቂቱ ቤተክርስቲያኒም ከተደቀነባት ውርደት ማዳን ካለባቸው ጊዜው አሁን ነው። የካህናቱን አቤቱታ እዚህ ያንበቡ!








Friday, April 22, 2016

የከፍያለው ቱፋ ጥፋቱ "ኢየሱስ፣ ኢየሱስ"ማለቱ!!



 ከፍያለው ቱፋ ወጣት መንፈሳዊ ተማሪና ሰባኪ ነበር። በዚህ ለጋ እድሜው ከስሞች ሁሉ በላይ ስም የሆነውን "ኢየሱስ ክርስቶስን" ከአፉ አይለይም።  በእርግጥም ያንን ማለት እንደጥፋት ከተቆጠረ ለጉባዔ ቀርቦ ቢቻል እውነቱን ነግሮ ወደሚፈለገው እውነት እንዲመለስ ማድረግ አለያም እኔ የያዝኩት እውነት ሌላ መልክ የለውም ካለም የራሱን ምርጫ አድርጎ ማሰናበት ሲቻል በበለው በለው ዘመቻ አስፈንጥሮ ማስወጣት አሳዛኝ ነው።  ከታች የቀረበው ጽሑፍ የሚያስረዳን ነገር በየቦታው የተደራጁ የዚያ ማኅበር ሰዎች ረጅም እጅና ቅብብሎሽ ምን ያህል የረዘመ ብቻ ሳይሆን የሰዎችን የኃጢአት ሸክም ለራሱ ፍላጎት መሳካት እንዴት መጠቀም እንደሚችል ያሳያል። ያንብቡ!

‹መንፈሳዊ ጉባኤ አዘጋጅተህ፥ ሰዎችን ሰብሰበሃል›› በሚል ተቃውሞ ክስ ተመስርቶበት፥ ከሰሞኑ 18 ከሚደርሱ ቅዱሳን ጋር መታሰሩን ሐራ ዘተዋህዶ መዘገቧ የሚታወቅ ነው፡፡ አሁን በደረሰን መረጃ መሰረት ደቀመዝሙር ከፍያለው ቱፋ የተከሰሰበት ክስ ፍሬ ከርስኪ መሆኑን ተረድቶ፥ ትላንት ማለትም 12/08/2008 ዓ/ም በአንድ ሺህ ብር ዋስ ፍርድ ቤቱ ሊለቀው ችሏል፡፡ ፍርድ ቤቱም አክሎም “የማንንም ሃይማኖት መስደብ፣ መንቀፍና መዝለፍ በሕግ ፈጽሞ የተከለከለ ነው፤ ደግሞም ማንም ሰው ያማነበትን እውነት መመስከርና መስበክ እንደሚችል” ገልጿል፡፡ በቦታው ላይ ፖሊስ ደርሶ ነገሩን ባይቆጣጠር ኖሮ ደም በማፍሰስ የሚያምነው ማህበሩ፥ የወንድሞችንና የእህቶችን ደም ከማፍሰስ እንደማይቦዝን የታወቀ ነው፡፡ ኽረ ለመሆኑ ለሃይማኖት የተደባደበ ሐዋርያ ማን ነው?

         አሁን አሁን በእናት ቤተክርስቲያናችን ውስጥ ባሉ አንዳንድ ጽንፈኛ ግለሰቦች ምክንያት ወንድሞች በጋራ ተሰባስበው መጽሐፍ ቅዱስን ከተማማሩ፣ በአንድነትም በመዝሙር በቅኔ ለአምላካቸው ከተቀኙ እንደ ምንፍቅና መታየት ከተጀመረ ሰነባብቷል፡፡ ይሁንም እንጂ ቅድስት ቤተክርስቲያን፥ የጌታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ቀዳሚ ትምህርት መሰረት አድርጋ ወንጌል ለፍጥረት ሁሉ በየትኛውም ሥፍራ መሰበክ እንዳለበት ታስተምራለች፡-

· “እንግዲህ ሂዱና አሕዛብን ሁሉ በአብ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ስም እያጠመቃችኋቸው፥ ያዘዝኋችሁንም ሁሉ እንዲጠብቁ እያስተማራችኋቸው ደቀ መዛሙርት አድርጓቸው፡፡” ማቴ 28፡-19፡፡

         ደቀመዝሙሩና ከእርሱ ጋር የታሰሩ ወገኖች፥ ይሄንን የሐሰት ክስ ያቀነባበሩባቸውን ግለሰቦች መልሳችሁ መክሰስ ትችላላችሁ ቢባሉም እንኳ “በቀል የእግዚአብሔር ነው” በማለትና “ከአባታችን ከእግዚአብሔር የተማርነው ይቅርታና ምህረት ማድረግ ነው” በማለት አንዳችም አጸፋ ለማድረስ እንዳልፈለጉ ውስጥ አዋቂዎች ይናገራሉ፡፡ ይሄ ደግሞ የአሰበ ተፈሪ ሐገረ ስብከት ሠራተኞችን ትዝብት ውስጥ የሚጥልና በቤተክርስቲያንም ወንጌል ለምን ተማማራችሁ በማለት የሚያሳስርና የሚከስ አባት የላትም፡፡ ይህንን ያደረጉት “የገባውን እውነት ቀብሮ ልጆቼን በምን አሳድጋለሁ ብሎ በግልጽ ወንጌልን የሚቃወመው ላዕከ ወንጌል ምንዳ ጉታ፥ ትዳሩን አያከብርም በሚባለው ሊቀ ብርሃናት ከሀሊ በቃሉ፥ እና በፀያፍ ቅጽል ስም የሚጠራው መልአከ ጸሐይ ዮሐንስ፣ ቀሲስ የማታ ወርቅ በተባሉ ግለሰቦች ሲሆኑ እነዚህ ሰዎች በዓመጻ ተነሳስተው ከማህበሩ በሚያገኙት. ድጋፍ ተነሳስተው  መሆኑ ታውቋል፡፡

“ወጥመድ ተሰበረ እኛም አመለጥን” እንዲል መጽሐፍ ክብር ሁሉ ለእግዚአብሔር ብቻ ይሁን! አሜን!

በዲሲ ቅ/ማርያም ቤተክርስቲያን የሥልጣንና የገንዘብ ጦርነቱ ተባብሶ ቀጥሏል!


በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ እየተለመደ የመጣ ችግር አለ። በተለያዩ አብያተ ክርስቲያናት ውስጥ በሁለትና ሦስት ጎራ ተከፋፍሎ የመጣላት፤ የመደባደብና ፍርድ ቤት ድረስ የመካሰስ አደጋ ከመቼውም ጊዜ በላይ እየሰፋ መጥቷል። መሠረታዊው የግጭቱ ምክንያት ሲገመገም በሁለት ነጥቦች ላይ ያጠነጥናል።


                       የሴራው መነሻ፤
1/ በተለያየ መንገድ ገንዘብ ለመዝረፍ እና

2/ በቤተ ክርስቲያኒቱ ውስጥ የማይነቃነቅ ባለሥልጣን  ለመሆን ነው።


                      የሴራው ተሳታፊዎች፤
የተወሰኑ ምዕመናንና ምዕመናት ግን በሴራው ተዋናዮች ዓላማ ተጠልፈው በቅንነት ቤተ ክርስቲያናቸውን ከአደጋ ለመከላከል ሲሉ ወደጦርነቱ ይገባሉ። የፖለቲካ ክፍፍሉም የራሱ ሚና ይኖረዋል። የሁለት ጎራ ሴረኞች ሕዝቡን የሚቀሰቅሱት ለቤተክርስቲያን ያለነሱ የተሻለ አሳቢ የሌለ በማስመሰል እንጂ ሁለቱም ጎራዎች ድብቅ ዓላማቸው አንዱ አንዱን በመንቀል በቦታው ላይ ራሳቸውን ለመትከል ነው። ይህ ሲባል በቅን አስተሳሰብ የተነሱ የለም ማለት አይደለም። ነገር ግን ቅኖቹ «ከነገሩ ጦም እደሩ» ብለው ራሳቸውን ስለሚያገሉ በመፍትሄው ላይ ተሳታፊ አይደሉም። ሁከቱና ብጥብጡ በውጪው ዓለም ባሉ አብያተክርስቲያናት ማለትም በለንደን፤ በሮም፤ በደቡብ አፍሪካ፤ በሰሜን አሜሪካ እየከፋ ሄዷል።


                            የሴራው ተዋናዮች
የሴራው ተዋናዮች ዓይነት ደግሞ የተለያዩ ናቸው። በአብዛኛው በየአኅጉረ ስብከቱ የሴራው ባለቤቶች ሊቃነ ጳጳሳት ሲሆኑ በየአድባራቱ ደግሞ አስተዳዳሪዎች፤ ቦርዶች፤ የሰበካ ጉባዔ አባላትና ማኅበረ ቅዱሳን  ናቸው።  ከታች የተመለከተው ቪዲዮ ጦርነቱ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ሲካሄድ ያሳያል።
«ነገር ግን እርስ በርሳችሁ ብትነካከሱና ብትበላሉ እርስ በርሳችሁ እንዳትጠፋፉ ተጠንቀቁ» ገላ 5፤15




Tuesday, April 5, 2016

ደቀ መዝሙር ከፍያለው ቱፋ ወደኮሌጁ እንዲመለስ ተወሰነለት!



ሰበር ዜና
       ደቀመዝሙር፥ ዲያቆን፥ ዘማሪ፥ መምህር ከፍያለው ቱፋ ‹‹በሰዋሰወ ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ መንፈሳዊ ኮሌጅ›› በነጻነት እየወጣ እየገባ እንዲማር የኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ ምድብ አንድ ፍ/ብሔር ችሎት ወሰነ!!
       የሞት ጣር የሚያቅረው ማህበረ ቅዱሳን የተባለ የባንዳ ስብስብ፥ ባሳለፍነው ሳምንት ደቀመዝሙር ከፍያለው ቱፋ ከሰዋሰወ ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ መንፈሳዊ ኮሌጅ፥ ከትምህርት ገበታው እንዲነሳ በላካቸው ጀሌዎቹ በኩል ተሟግቶ ‹‹እንዲታገድ›› ማድረጉ የሚታወስ ነው፡፡ ይህችም እንደትልቅ ድል ተቆጥራ ‹‹ሐራ ዘተዋህዶ›› በተባለችው የደከመች ብሎጋቸው ላይ ሁለት ጊዜ ዜና ሰርተው ማናፈሳቸውም የሚታወስ ነው፡፡ የሚገርመው ግን ደቀመዝሙሩ እንዲታገድ በተወሰነው ‹‹ውሳኔ›› ላይ የኮሌጁ የበላይ ኃላፊ ‹‹ብጹዕ አቡነ ሕዝቅኤልና የኮሌጁ ዋና ዲን ሊቀ ኀሩያን ሰርጸና ብዛት ያላቸው የኮሌጁ አመራሮች›› አለመፈረማቸውን ሸሽገዋል፡፡ ያልፈረሙበት ምክንያት ደግሞ ደቀመዝሙሩን ከኮሌጁ የሚያስወጣ የሃይማኖት ሕጸጽ ባለማግኘታቸው ነው፡፡ የማህበሩ ጀሌዎች ግን ኃላፊነቱን በመውሰድ፥ ያልስልጣናቸው የኮሌጁን ማህተም ተጠቅመው፥ ደቀመዝሙሩን ያሰናበቱት፡፡ ይህ ደግሞ ወንጀል በመሆኑ ምክንያት ደቀመዝሙር ከፍያለው ቱፋ ለሚመለከታቸው የቤተክርስቲያናችን አባቶች በማሳወቅ፥ ጉዳዩን ‹‹ወደ ኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ ምድብ አንድ ፍ/ብሔር ችሎት›› ለመውሰድ ተገድዷል፡፡
        ከታች ለማስረጃነት ያቀረብነው የፍርድ ቤት ትዕዛዝ፥ በቀን 23/07/2008 ዓ/ም፥ የፌ/መ/ደ/ፍ/ቤት/ኮ/ቀ ምድብ 1ኛ ፍ/ብሔር ችሎት፥ በቁጥር የኮ/መ/ቁ 50074 ያሳለፈው ውሳኔ ሲሆን፥ ደቀመዝሙር ከፍያለው ቱፋ ላይ በኪራይ ሰብሳቢነት የማህበረ ቅዱሳን ጀሌዎች በኮሌጁ ስም ያሳለፉትን ውሳኔ፥ ከመሰረቱ ያፈረሰ ‹‹አጭርና ግልጽ›› ትዕዛዝ ነው፡፡ ትዕዛዙም እንዲህ የሚል ነው፡-
“ሌላ ተለዋጭ ትዕዛዝ እስከሚሰጥ ድረስ ተከሳሽ በከሳሽ ላይ ትምህርቱን እንዳይማር የሰጠው ውሳኔ እንዳይፈጸም ታዟል፡፡ ለሚመለከተው አካል ይጻፍ፡፡ ማለትም በደብዳቤ ቁጥር 399/2/233/08 በ19/07/2008 ዓም የተጻፈው እንዳይፈጸም ታዟል፡፡”
       እንግዲህ ሽንፈት ለማን ነው? ለጠላት፥ ለዲያብሎስ አይደለምን? አሸናፊውስ፥ የልባችን ንጉስ፥ ጌታችን ኢየሱስ አይደለምን? እነሆ መስፋትና ማሸነፍ ለእግዚአብሔር ልጆች ሲሆን በአንጻሩ ደግሞ መክሰር ለዲያብሎስ ሆኗል!!
      ይህ በእንዲህ እንዳለ ደቀመዝሙር ከፍያለው ቱፋ ከትምህርት ገበታው እንዲነሳ ውሳኔ በማሳለፍ ሥራ ላይ የተጠመደው፥ በሙስና የኮሌጁ ምክትል ዲን የሆነው አቶ ማሞ ከበደ፥ የፍርድ ቤቱን ውሳኔ አልፈጽምም በማለቱ ምክንያት እስራት ይጠብቀዋል፡፡ በተጨማሪም አቶ ማሞ ከበደ በማህበሩ የተሰጠውን አጀንዳ ለማስፈጸም ሲል ብቻ፥ ብጹዕ አቡነ ሕዝቅኤልና የኮሌጁ ዋና ዲን የሆኑት ሊቀ ኀሩያን ሰርጸ ፊርማቸውን ሳያስቀምጡ፥ ካለስልጣኑ በኮሌጁ ስም በወሰነው ወንጀል ሌላ ዘብጥያ ይጠብቀዋል፡፡ ሲጀመር አቶ ማሞ ከበደ የኮሌጁ ሠራተኛ ነው እንጂ የሃይማኖት ህጸጽ መርማሪስ ማን አደረገው? የሃይማኖት ህጸጽ ቢኖር እንኳ ሊጠይቀው የሚገባው፥ ቤተክርስቲያን ሥልጣን የሰጠችው አካል የሊቃውንት ጉባኤ ነው እንጂ፥ አንድ ጤና የጎደለው ሠራተኛ አይደለም፡፡ ሲኖዶስ ያልወሰነውን፥ ሊቃውንት ጉባኤ ያልወሰነውን ግለሰቡ የማሕበረ ቅዱሳንን አጀንዳ ተሸክሞ ለማስፈጸም መድከሙ ነውረኛነቱን የሚሳይ ነው፡፡ ሲቀጥልም ግለሰቡ የሃይማኖት ሕጸጽ የመመርመር ሥልጣንም ይሁን ብቃት የለውም፡፡ በርግጥ አቶ ማሞ ከበደ በደቀመዝሙሩ ላይ የእግድ ደብዳቤ የጻፈው ‹‹የሃይማኖት ህጸጽ›› ተመልክቶ ሳይሆን፥ ከማኀበሩ በሚያገኘው የኪራይ ሰብሳቢነት ልክፈት በመለከፉ ምክንያት እንደሆነ የቅርብ ወዳጆቹ ይመሰክሩለታል፡፡
ይህን ጉዳይ እየተከታተልን የምናቀርብ መሆኑን ከወዲሁ እንገልጻለን፡፡

Sunday, December 6, 2015

“የሊቀ ጳጳሱ ልጅ ነኝ” በሚል የቀረበን ጥያቄ ውድቅ አደረገው።

(መማሌት ኪዳነወልድ)
የፍርድ ቤት ክርክሩ ከ3 ዓመት በላይ ፈጅቷል      የሽሬ እንዳሥላሴ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የነበሩት አቡነ ሚካኤል፤ በነሐሴ ወር 2003 ዓ.ም ከሞቱ በኋላ ነው፤ “የሊቀ ጳጳሱ ልጅ ነኝ” የሚል የወራሽነት አቤቱታ ለፍ/ቤት የቀረበው፡፡ “የሟች ልጅ ነኝ” የሚል አቤቱታ ያቀረቡት አቶ ዮሐንስ ተክለሚካኤል፤ ጳጳሱ እንዳሳደጓቸው በመግለጽና ተወላጅነቴን ያስረዱልኛል ያሏቸውን ሰነዶች በማያያዝ፣ የሰዎችን ምስክርነት ለፍ/ቤት አሰምተዋል፤ ፍ/ቤቱም ኅዳር 23 ቀን 2004 ዓ.ም የልጅነት ማረጋገጫ ውሳኔውን አሳወቀ፡፡ ጉዳዩ ግን በዚሁ አልተቋጨም፡፡ የሊቀ ጳጳሱ እኅት፤ የፍ/ቤቱን ውሳኔ በመቃወም ይግባኝ ጠይቀዋል፡፡ በአቶ ዮሐንስ የቀረበው የልደትና የጥምቀት ወረቀቶች በአግባቡ የተረጋገጡ አይደሉም፤ ልጅነቱ በሳይንሳዊ መንገድ በዲኤንኤ መረጋገጥ አለበት በማለት መቃወሚያ አቅርበዋል - የጳጳሱ እኅት ወ/ሮ በላይነሽ ዓባይ፡፡ “ሊቀ ጳጳሱ አሳድገውኛል ከማለት ውጪ፣ ሊቀ ጳጳሱ በልጅነት እንደተቀበሉት የሚያሳይ ማስረጃ አልቀረበም፤” ያሉት ወ/ሮ በላይነሽ፤ በተጨማሪም በቀረበው የጥምቀትና የልደት ካርድ ላይ የአባት ስም የተቀየረው ሊቀ ጳጳሱ ከሞቱ በኋላ ነው፤” ብለዋል፡፡ አቶ ዮሐንስ በሰጡት መልስ፣ “ወ/ሮ በላይነሽ የጳጳሱ እኅት መሆናቸውን አላውቅም፡፡ በሕይወት እያሉ እኅት አለኝ አላሉኝም፤” ብለዋል፡፡ “የአባቱን ስም ቀይሯል” ለሚለው ተቃውሞ አቶ ዮሐንስ ምላሽ ሲሰጡም፤ በሟች አባቴና በእናቴ ስምምነት፤ እናቴ ቤተሰቦችጋ ነው ያደግሁት፡፡ በዚህ ምክንያት፣ በእናቴ አባት ስም ስጠራ ቆይቻለሁ፤” ብለዋል፡፡ “ከልደትና ከጥምቀት ወረቀት ውጭ፤ የሰው ምስክሮች አስደምጫለሁ፡፡ ከምስክሮቹ አንዷም እናቴ ናት፤” በማለትም ተከራክረዋል፡፡ የይግባኝ ክርክሩን የዳኘው ከፍተኛ ፍ/ቤት፤ በአቶ ዮሐንስ ቀረበው የልደት የምስክር ወረቀት ሕጋዊነት እንደሌለው ገልፆ፤ በክሊኒክ የተመዘገበ የወሊድ መረጃዎችንም ጠቅሷል፡፡ በክሊኒኩ የተመዘገበው የወላጅ እናት አድራሻ የተሳሳተ እንደሆነ ፍ/ቤቱ ጠቅሶ፤ የወላጅ እናት ዕድሜ ተብሎ የተመዘገበው መረጃም፤ ከዮሐንስ እናት ዕድሜ ጋር በሰፊው ይራራቃል፤ ብሏል፡፡ ከፍተኛው ፍርድ ቤት እስከ መስከረም 4 ቀን 2008 ዓ.ም ጉዳዩን ሲመረምር ከቆየ በኋላ በሰጠው ውሳኔ፣ አቶ ዮሐንስ “የሊቀ ጳጳሱ ልጅ አይደሉም፤” በማለት የሥር ፍ/ቤትን ውሳኔ ሽሯል፡፡ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሕግ፣ ለማዕርገ ጵጵስና የሚመረጡት በሥርዓተ ምንኩስና በድንግልና መንኩሰው በክህነት ቤተክርስቲያኒቱን የሚያገለግሉ ሲሆኑ ቤተ ክርስቲያኒቱም ይህንኑ በማረጋገጥ በጣልቃ ገብ መከራከሯን የፍርድ ሐተታው ያመለክታል፡፡