Showing posts with label መረጃ. Show all posts
Showing posts with label መረጃ. Show all posts

Wednesday, March 9, 2022

የቤተ ክርስቲያኒቱ ጠላቶች በጉያዋ ናቸው!

ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ በሦስት መንገድ ችግር ውስጥ ናቸው። 1ኛ/ ወደው ባልተወለዱበት ዘር ትግሬ በመሆናቸው በኦሮሙማው ኃይል የሚታዩት እንደጠላት ነው። 2ኛ/ የራሳቸው የአመራርና የሥልጣን አጠቃቀም ድክመት የተነሳ የመፈራትና የመከበር አቅማቸው አናሳ መሆኑ ሌላኛው ችግር ነው። 3ኛ/ ሊቃነ ጳጳሳቱ በራሳቸው የግል ኑሮ ምቾትና ምንግዴለሽነት የተነሳ ቤተ ክርስቲያኒቱን ስለረሷት ከፓትርያርኩ ጋር መቆም አልቻሉም። ወደፊትም ቢሆን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አሁን ባለችበት መንገድ ከተጓዘች በውስጥና በውጪ ጠላቶቿ እየተገዘገዘች የመውደቋ ነገር የጊዜ ጉዳይ ካልሆነ በስተቀር መፍረሷ አይቀርም። የዚህ ፅሁፍ አቅራቢ ሦስት ምክር ያቀርባል። 1/የቀድሞው ፓትርያርክ ከዚህ ዓለም ስላረፉ አሁን ያሉት ፓትርያርክ ከእድሜ: ከህመምና ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች የተነሳ በቂ ውሳኔ እየተሰጠ ባለመሆኑ ችግሮቹ ተደራራቢ እየሆኑ በመገኘታቸው ለቤተክርስቲያኒቱ ፈጣን አመራር መስጠት የሚችል ሰው በራሳቸው በፓትርያርኩ አቅራቢነት እንደራሴ ቢሾም: 2/ አጠቃላይ የሰበካ ጉባኤ ስብሰባ በዓመት ሁለት ጊዜ መሆኑ ከድግስና ከተጋነነ ሪፖርት ውጪ ችግር ፈቺ ስላልሆነ የየአህጉረ ስብከቶቹን ችግር የሚያጠናና ለእንደራሴው ቢሮ የሚያቀርብ ቡድን ተሰይሞ በየችግሮቹ ዘርፍ ፈጣን ውሳኔ ቢሰጥባቸው: 3/ ለቤተ ክርስቲያኒቱ የሚቆረቆሩ በሙያ: በልምድና በችሎታ ከልዩ ልዩ የህብረተሰብ ክፍሎች የአማካሪ ቦርድ ቢቋቋም የተሻለ ይሆናል። ይህ አሰራር በግብፅ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያና ተግባራዊ ሆኖ ብዙ ችግር መቃለል ተችሏል። ከዚህ ውጪ አሁን ባሉት ጳጳሳት የሚፈታ የቤተ ክርስቲያን ችግር የለን። አይኖርምም። ራሳቸው የቤተ ክርስቲያኒቱ ችግሮች ናቸው። ፈሪሃ እግዚአብሔር የነበራቸውና በጥብዓት ይታገሉ የነበሩት ሁሉ በዐረፍተ ዘመን ሁሉን ትተው ሄደዋል። አሁን ካሉት ጳጳስ ተብዬ ወመኔዎች አንዱ የሆነው ቅዱስ ፓትርያርኩ ለመናገር ያሰቡትን ሃሳብ እንዳያስተላልፉ የዱርዬ ስራውን እንዴት ይሰራ እንደነበር ይህ ቪዲዮ ያሳያልና ተመልክታችሁ ፍረዱ! በፕሮቶኮል ደረጃ ከፓትርያርኩ ፊት መነጋገሪያ ማይክ አይነሳም። ማፊያው ጀነራል ሦስት መነጋገሪያ ፓትርያርኩ እንዳይነጋገሩ ሲያሸሽና ለአዳነች አቤቤ ሲሰጥ ተመልከቱ።

Friday, October 20, 2017

"ማኅበረ ቅዱሳን ኢትዮጵያዊው ሙስሊም ብራዘርሁድ"



ማኅበረ ቅዱሳንን ከግብፁ ሙስሊም ብራዘርሁድ ጋር የሚያመሳስለው ተግባራትና ሂደቶች!

ሙስሊም ብራዘር ሁድ ወይም የሙስሊም ወንድማማቾች ማኅበር የተባለው ድርጅት በ1928 ዓ/ም በግብጽ ተመሠረተ። ከሰማንያ ዐመታት በኋላ በጄኔራል አልሲሲ መንግሥት በአሸባሪነት ተፈርጆ ድምጥማጡ እስኪጠፋ ድረስ በ70 ሀገሮች ውስጥ ቅርንጫፎቹን ከፍቶ በዘመናዊና ሃይማኖታዊ ትምህርት ቤቶች፤ በገበያ ማዕከላት፤ በንግድ ሱቆች፤ በማከፋፈያ ድርጅቶች፤ በሚዲያ ተቋማት ወዘተ የሀብት ማግበስበሻ መንገዶች እየተሳተፈ ክንዱን በማፈርጠም ለእንቅስቃሴው የሚጠቅመውን የገንዘብ ምንጭ ሲፈጥር ቆይቷል። ይህ የግብጹ ሙስሊም ብራዘር ሁድ በዐረብ ሀገራት ውስጥ ተመሳሳይ የሙስሊም ወንድማማች ማኅበራትን በማደራጀትና በማሰልጠን መንግሥታቱን ሲያስጨንቅ የቆየ ሲሆን አሁንም እያስጨነቀ ይገኛል።

የሙስሊም ብራዘር ሁድ ለተባለው ሃይማኖታዊ-ፖለቲካዊ ድርጅት ዋነኛ ተቀባይነት ማግኘት ዋናው ምክንያት የሆነው በእስላሙ ሕብረተሰብ ውስጥ ቶሎ ሰርጾ እንዲገባ የሚያካሂደው ሃይማኖታዊ አስተምህሮቱና  ለዚህ እምነት መክፈል የሚገባውን ዋጋ ሁሉ በመክፈል ከአላህ ዘንድ የሚከፈለውን ምንዳ ለመቀበል ቶሎ መሽቀዳደም ተገቢ መሆኑን አበክሮ በመስበኩ የተነሳ ነው።

1/ የሙስሊም ብራዘር ሁድ መዋቅራዊ እንቅስቃሴ

 ሙስሊም ብራዘር ሁድ መዋቅሩ በሀገሪቱ የመንግሥት ሲቪላዊ መዋቅር ደረጃ የተዘረጋ ነው። ይህም ከማዕከላዊ ቢሮው ተነስቶ አባል በሆኑ በእያንዳንዱ ቤተሰብ ውስጥ በሰንሰለት የተያያዘ ነው። ቤተሰባዊውን የአባልነት ማኅበር «ኡስራ» ይሉታል። አንድ «ኡስራ» አምስት አባላት ሲኖሩት ከአምስት በላይ ከሆነ በሁለተኛ የኡስራ ስያሜ ደረጃ ይዋቀራል። በቤተሰቡ ያሉትን ኡስራዎች የሚመራ ደግሞ የቤተሰቡ አባል የሆነ በእስልምና ሃይማኖቱ የበሰለና የብራዘር ሁድ አስተምህሮት በደንብ የገባውን ሰው የቤተሰቡ ጉባዔ ይመርጠውና «ናቂብ» ተብሎ ይሰየማል። ይህ «ናቂብ» የተባለው ሰው የቤተሰቡ አባላት በእስልምናው ደንብ ዘወትር ስለመንቀሳቀሱ ይቆጣጠረዋል፤ ያስተምረዋል፤ ይነግረዋል። ያልተመለሰውን በማኅበረሰቡ ደረጃ ለተቀመጠውና ከፍ ላለው ሃይማኖታዊ መሪ ያቀርበዋል። ይህ ሁሉ ሲሆን ስለእስልምናው የሚደረግ እርምጃ በመሆኑ በደስታ ከሚቀበል በስተቀር ማንም በተቃውሞ አያንገራግርም፤ ሊያንገራግርም አይችልም። ምክንያቱም ጸረ እስልምና እንደሆኑ ራሳቸውን አስገዝተዋልና። በዚህ ዓይነት አደረጃጀት የሙስሊም ወንድማማቾች ማኅበር ከላይ ወደታችና ከታች ወደላይ የተሳሰረ መዋቅር አለው።

2/   የገንዘብ ምንጮቹን ማሳደግ

ገንዘብ የዚህ ዓለም እንቅስቃሴ የደም ሥር ነው። አባላት ለመመልመል፤ እንቅስቃሴውን ለማስፋፋት፤ የሽብር ተግባሩን ለመፈጸም፤ ለመደለል፤ ለመሰለል፤ ሃይማኖታዊ ዶክትሪኑን ለማስተማር  እጅግ ጠቃሚ ነገር መሆኑን ጠንቅቆ የተረዳው ብራዘር ሁድ የገንዘብ አቅሙን ለሀገር ውስጥና ድንበር ዘለል ተግባሩ ያውለው ዘንድ ተግቶ ይሰራል።

የእስላም ወንድማማቾች ማኅበር ሁለት ዓይነት የገንዘብ ምንጮች አሉት። አንዱ በውጪ ሀገራት ካሉ አባላቱ በመዋጮ የሚሰበሰብ እንዲሁም ብዙ ሃብት ካላቸው የድርጅቱ ደጋፊ ሚሊየነሮች  የሚደረግለት የገንዘብ ፈሰስና በእስላማዊ መንግሥታት ስር ከተሸሸጉ ባለስልጣናት የሚዋጣለት ገንዘብ ነው።  ሁለተኛው ደግሞ በተራድዖ ስም ከውጭ የሚያሰባስበውን ገንዘብ ወደልማት ካዝና በመቀየር በአካባቢ ልማት፤ በትምህርት ቤቶችና መድራሳ ማቋቋም፤ ሥራ አጥ ህብረተሰብን በማደራጀት፤ የራስ አገዝ እንቅስቃሴን በመመሥረት የሚሳተፍ ሲሆን ለዚህም ሀገር በቀል የእርዳታ ስልት በመቀየስ መዋጮውን ቅርጹን ለውጦ ያግበሰብሳል። ይህም፤

ሀ/ ከአባልነት መዋጮና
ለ/ ከንግድ ድርጅቶቹና ከሚዲያ ተቋማቱ የሚገኝ ገቢ ነው። በዚህ አካሄዱ ማኅበረ ቅዱሳን ትክክለኛ ገፅታው የሙስሊም ብራዘርሁድ ግልባጭ ነው። በሚሊየን ብሮችን ይሰበስባል፣ ያንቀሳቅሳል።

ይህንን ገንዘብ በተለያየ የገንዘብ ማስቀመጫ ስልቶችና በብዙ የሂሳብ አካውንቶች ቋት ውስጥ በተለያየ ስም በማስቀመጥ ለሚፈልገው ዓላማ በፈለገበት ሰዓት ማንም ሳያውቅበት ያውለው ነበር።

3/ በመንግስታዊ ተቋማት ውስጥ ሰርጎ መግባት

ብራዘር ሁድ አባላቱን ሲመለምል ነጻና ገለልተኛ የሆኑትን ብቻ አይደለም። ከሚኒስትሮች እስከፍርድ ቤቶች፤ ከመከላከያ እስከ ፖሊስ መምሪያዎች፤ ከድርጅት ሥራ አስኪያጆች እስከ አስተዳደር ኃላፊዎች ድረስ በአባልነት መልምሎ፤ አሰልጥኖና ሃይማኖታዊ ትጥቅ አስታጥቆ የሚንቀሳቀስ ድርጅት ነበር። እነዚህ የመንግሥታዊ አካላት ክፍሎች ድርጅታቸው ለሚነሳበት ተቃውሞና ኅልውናውን ፈታኝ ለሆኑ ችግሮች የግብዓት ምንጭ ሆነው ያገለግላሉ። አስፈላጊ በሆነ የመረጃ፤ የፋይናንስና የአፈና ሥራው በትጋት ይሰራሉ።
ይህ ድርጅት እንደሃይማኖታዊ ተቋም አራማጅነት ተነስቶ ወደፖለቲካዊ ሥልጣን መቆናጠጥ እርምጃው ለማደግ መሠረት አድርጎ የሚነሳው የእስልምና ሃይማኖትን ነው። ይህም ብራዘር ሁድን መቃወም እስልምናን እንደመቃወም እንዲቆጠር በሕብረተሰቡ ዘንድ የኅልውናውን ስዕል በማስቀመጥ እንዳይነካ ወይም እንዳይጠፋ ረድቶታል። የእስልምናውን አስተምህሮ መነሻ በማድረጉ የማይነቃነቅ ፖለቲካዊ ግብ ለማስረጽ ያገዘው ሲሆን የዚህም መገለጫው በአልሲሲ መንግሥት ላይ በአንድ ጊዜ እስከ 33 ሚሊዮን ተቃዋሚ ሰልፈኞችን በመላ ሀገሪቱ ማንቀሳቀስ የሚችል ድርጅት አድርጎታል።
 ይሁን እንጂ የጀነራል አልሲሲ መንግሥት እርምጃ ስልታዊ በመሆኑ በአንድ ቀን ብቻ ከሁለት ሺህ በላይ ከፍተኛና ዝቅተኛ አመራሩንና የሃይማኖታዊ ተፍሲር መምህራኖቹን ለቃቅሞ ወደማጎሪያ ካምፕ በመክተቱ ድርጅቱ በ85 ዓመት እድሜው አይቶት የማያውቀውን ውድቀት ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ እንዲያስተናግድ አድርጎታል። በአልሲሲ መንግሥት የተተገበረው «ወፎቹ እንዲበተኑ ቅርንጫፉን መቁረጥ» የሚለው አባባል ብቻ ሳይሆን ግንዱን መንቀል በመሆኑ የብራዘር ሁድ ዋና መሪ መሐመድ ሙርሲን ጨምሮ ከፍተኛውን የሹራ ካውንስል ሳይቀር ከስር ገርስሶታል። በሺዎች የሚቆጠሩ አባላቱም የሞትና የእስራት ፍርድ ተከናንበዋል። አልሲሲ በቲቪ ቀርበው "ብራዘር ሁድን ከስረ መሠረቱ ነቅለን ካላጠፋን ሰላም የለንም" በማለት ድራሹን አጥተውታል። ዛሬም ድረስ የተቃውሞ ሰልፎች ያሉ ቢሆንም በሃይማኖት ካባ ስር በተሸፈነው ድርጅት በኩል የአእምሮ አጠባ ተደርጎ የተታለለው ሕብረተሰብ እንጂ ብራዘር ሁድ እንደተቋም በግብጽ ታሪክ ግብዓተ መሬቱ ተፈጽሟል። ያ ማለት ግን ብራዘር ሁድን የሚደግፍ፤ የሚጠባበቅና እንዲያንሰራራ የሚፈልግ የለም ማለት አይደለም። ኢትዮጵያዊው ሙስሉም ብራዘርሁድ ማምጣት የሚፈልገው ለውጥ በራሱ ቅኝት የሚዘወር ቤተ ክህነትና በአባላቱ ተሳትፎና ስውር እጆቹ የሚቆም አዲስ ስርአተ መንግስት ነው። ያ ካልሆነ በኦርቶዶክስ መንፈሳዊ መዋቅር ውስጥ ሳይዋጥ የራሱን ልእልና እያስጠበቀ ተከልሎ ለመቆም ባልፈለገም ነበር።

4/ማኅበረ ቅዱሳን እንደክርስቲያን ብራዘር ሁድ ስንል ምን ማለታችን ነው?

1/ ተቋማዊ አደረጃጀቱ ከመንግሥትም፤ ከቤተ ክህነትም ቁጥጥር ነጻ መሆኑ
2/ የራሱን አባላት የሚመለምልና የሚያደራጅ መሆኑ
3/ የራሱ የሆነ የገቢ ምንጭ ያለውና የንግድ ተቋማትን የሚያንቀሳቅስ መሆኑ
4/ ከአባላቱ ልዩ ልዩ መዋጮዎችና የስጦታ ገቢዎችን በመሰብሰብ በልማት ውስጥ እየተንቀሳቀሰ እንዳለ የማሳየት ብልሃት ያለው መሆኑ
5/ በመንግሥት ተቋማትና መሥሪያ ቤቶች፤ ፍርድ ቤቶች፤ ፖሊስ መምሪያዎች፤ በኮሌጆችና ዩኒቨርሲቲዎች ስውር መዋቅር ያለው መሆኑ
6/ በቤተ ክርስቲያኒቱ ላዕላይ መዋቅርና እስከ አጥቢያ ድረስ በተዘረጋው አስተዳደር የራሱ አደረጃጀት የዘረጋ መሆኑ
7/ በቅዱስ ሲኖዶስ አባላት ውስጥ የራሱን ጳጳሳት በመመልመል ማስሾም የቻለ መሆኑ፣




በመመልመል ማስሾም የቻለ መሆኑ
9/ ከሀገር ውጭ ዓለም አቀፍ ቢሮዎችን ከፍቶ የሚንቀሳቀስና አባላት ያሉት መሆኑ
10/ ከዓለም አቀፍ የገቢ ፈጠራው ውስጥ በልማት ሰበብ የሚያጋብስ መሆኑ
11/ የመረጃ፡ የስለላና የትንተና መዋቅር ያለው መሆኑ
12/ የቤተ ክርስቲያኒቱን አደረጃጀቶች ለራሱ ዓላማ የመጠቀም አቅም ያለው መሆኑ
( ሰንበት ት/ቤቶችን፤ የጥምቀት ተመላሽና የጽዋ ማኅበራትን)
14/ የግለሰቦችን ስም በማጥፋት ወይም ራሳቸውን በማጥፋት፡በማባረር፡በመደብደብ ወይም ግለታሪካቸውን ለራሱ ዓላማ ጠምዝዞ በማዋል እርምጃ መውሰድና ማስወሰድ የቻለ መሆኑ
15/ ስሙን ለማግነን፤ ክብሩን ለማስጠበቅ የሚያስችል በራሱ የሚመራ እንዲሁም በፖለቲካ የተቃውሞው ጎራ የተሰለፉ ደጋፊዎችና በስውር መረብ የሚንቀሳቀስ የሚዲያ ተቋም ያለው መሆኑ፤
ማኅበረ ቅዱሳንን ክርስቲያናዊ ብራዘር ሁድ እንድንለው ያስችለናል።

እስካሁንም ማንም ምላሽ ሊሰጥበት ያልቻለው ዋናው ነጥብ ማኅበረ ቅዱሳን ከመንግሥት እይታ ውጪ መሆን ባይችልም ከመንግሥት ቁጥጥር ውጪ የሆነ ክርስቲያናዊ ማኅበር መሆኑ ሲሆን እንደክርስቲያናዊ ተቋምነቱ  ደግሞ ቤተ ክርስቲያኒቱ በማኅበሩ ላይ ቁጥጥርና ክትትል የማድረግ ችሎታ አንዳችም አቅም የሌላት በመሆኑ ያሳዝናል:: በመንግሥትም፤ በቤተ ክህነቱም ማንም ጠያቂ የሌለው ሆኖ መቆየቱን ለማመን ያለመፈልግ ዝንባሌ መኖሩም ያስገርማል::  ማኅበሩ እንደምክንያት ሁልጊዜ የሚያቀርበው ሲኖዶስ በሰጠኝ ደንብ እመራለሁ ቢልም እውነታው ግን ብራዘር ሁድ በሆኑ ጳጳሳት አባላቱ በኩል የሚመቸውን ደንብ አስጸድቆ ያለጠያቂ በነጻነት ከሀገር ውስጥና ከሀገር ውጪ የገቢ አቅሙን እያሳደገ፤ የቤተ ክርስቲያኒቱን አባላት ለራሱ አባላት እየመለመለ፤በቤተ ክርስቲያኒቱ ቁመናና መልክ የራሱን አደረጃጀት፤ መዋቅርና እንቅስቃሴ እያከናወነ ያለ ማኅበር መሆኑ የማይካድ እውነታ ነው። ለምሳሌ የማኅበሩ ብራዘር ሁድ አባላት ጳጳሳቱ አባ ማቴዎስ፡አባ ቀውስጦስ፡ አባ ቄርሎስ፡ አባ ያሬድ፡አባ አብርሃም፡አባ ሳሙኤል፡ በአባ ማቴዎስ አደራዳሪነት የትግሬን መንግስት በጋራ መዋጋት በሚል ፈሊጥ ከማኅበሩ እግር ላይ ወድቀው የታረቁት አባ ፋኑኤል ተጠቃሾች ናቸው:: አባ ገብርኤል ግን ከአቶ ኢያሱነታቸው ጀምሮ የተጠጋቸው የውግዘት በሽታ  መቼም አይለቃቸውም::

5/ ለመሆኑ አሁን ያለው ማኅበረ ቅዱሳን አደረጃጀት፤  

የሰንበት ት/ቤት ስብስብ ነው? እርዳታ ድርጅት ነው? የልማት ተቋም ነው? የበጎ አድራጎት ማኅበር ነው? ራሱን ከሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ውጪ አስደርጓል። በዋና ሥራ አስኪያጅ ሥር የሚተዳደር ነገር ግን የቤተ ክህነቱ መምሪያ ያልሆነ መምሪያ ነው?
በቤተ ክርስቲያኒቱ ውስጥ ሥፍራው ከየት ነው? በምንስ እንመድበው? ማኅበሩ በምን ሂሳብ እንደተቋቋመና በምን አደረጃጀት ኅልውና እንዳገኘ አይታወቅም::

እስከሚገባን ድረስ እንቅስቃሴውንና ያለውን አደረጃጀት ተመልክተን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ማኅበረ ቅዱሳናዊ ብራዘር ሁድ ብንለው ተግባሩ ያረጋግጣል።
በሌላ መልኩ መንግሥት በኢትዮጵያ የእስልምና ሃይማኖት ተከታዮች ዘንድ እንዲህ ዓይነት ማኅበር ከእስልምና ምክር ቤቱ ውጪ እንዲቋቋም ይፈቅዳል ወይ ብለን እንጠይቃለን? መልስ የሚያሻው ጥያቄ ነው።

Wednesday, October 5, 2016

"የጎርፍ ዘመን ላይ ደርሰናል"


ቀን 08/27/2016

ይድረስ
       
ለክቡር ጠቅላይ ሚኒስቴር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ፣
ለኢትዮጵያ የመንግሥት ከፍተኛ ባለሥልጣናት በሙሉ ።

   በቅድምያ እናንተ በዚህ በአገራችን በኢትዮጵያ የሥልጣን ወንበር ላይ ለበጎም ይሁን ለክፉ ያስቀመጣችሁ ቸሩ አምላክ እግዚአብሔር እርሱ ባወቀው መንገድ እንደሆነ ስለማምን ለዚህም ኃላፊነትና ሥልጣን የተሰጣችሁ ናችሁና በእየ መዓርጋችሁ የከበረ የአክብሮት ሰላምታዬን አቀርባለሁ።

  ከዚህ በመቀጠል ሌላው
 ፩ኛ ሳሙ ፲፭፥፳ "....ሳሙኤልም እግዚአብሔር የእስራኤልን መንግሥት ዛሬ ከአንተ ቀደዳት፥ ከአንተም ለሚሻል ጎረቤትህ አሳልፎ ሰጣት...."ይላል።

 ይህንን ካልኩ በኋላ በእውነቱ የኢትዮጵያ ሕዝብ የዛሬ ሃያ አምስት ዓመት የደርግን መንግሥት አስተዳደራዊ ሥርዓትን አስወግዳችሁ እናንተ በትረ መንግሥቱን በጨበጣችሁ ጊዜ ምናልባት ከደርግ የተሻለ ለአንድነት ለእኩልነትና ለነፃነት የሚያስብልን፣የብሔር ብሔረሰቦችና፣ሁሉን ያቀፈ፣በሕገ መንግሥቱ የሚተዳደር መንግሥት ይፈጠራል ብሎ ሲጠብቅ እናንተ ግን የሕገ መንግሥቱን ሥርዓት ባልጠበቀ መልኩ የኢትዮጵያን ሕዝብና የኤርትራን ሕዝብ ፍላጎት ባላካተተ፣ ባልጠበቀና፣ባላገናዘበ መልኩ የኹለቱን ሰላማዊ ሕዝብ አንድነት አጥፍታችሁ፣በአንድነቱ ፈንታ ኹለትነትን ፈጥራችሁ፣ ለያይታችሁ፣በኹለቱ ሕዝብ መካከል ጥቁር ነጥብ ጥላችሁ፣ ለኢትዮጵያ ሕዝብ አንድነት፣ነፃነትና እኩልነት ያልቆማችሁ ለመሆናችሁ የምልክት ማህተብ በአንገታችሁ ያጠለቃችሁባትን ቀን ሳስብ መቼ ይሆን ይህ ዘመን የሚያልፈው ብዬ አስብ ነበር። የሚመጣውም ዘመን ምን እንደ ሚመስልና እንደሚሆን ስገምት በጣም ያስፈራኛና ያስጨንቀኝ ነበር።ታዲያ ዘመናትም ተቆጥሮ ዕለታትም አልፎ ኢየዋለ ኢያደረ ልዩነቱ፣መከፋፈሉ፣መለያየቱ፣መናናቁ፣መተራረዱ፣መገዳደሉና፣መጠላላቱ...ወዘተ በዝቶ ተባዝቶ እነሆ ዛሬ ያለንበት የደም ጎርፍ ዘመን ላይ ደርሰናል።

  ቅዱስ መጽሐፍ በማቴ ፩፪፥፳፭ ላይ "....ኢየሱስ ግን አሳባቸውን አውቆ እንዲህ አላቸው።እርስ በእርሷ የምትለያይ መንግሥት ሁሉ ትጠፋለች፤እርስ በእርሱ የሚለያይም ከተማም ወይም ቤት አይቆምም....."ይላልና ይህንን በአንድነት ሊያኖረን የማይችለውን ነገር አስወግደን ለሕዝብ የፈለገውን የመጠየቅ፣የመኖር፣ፍትህ የማግኘት እድል ካልሰጠን የኛም ሕልውና አጠራጣሪ ነው የሚሆነው።ሕዝብን ሁሉ በመግደልና፣በማሰር የምንመራው ከሆነ የሚቀረው ማነው?ሁሉም ከሞተ? ሁሉ ከታሰረ? በመንግሥት ስር የሚተዳደረው ማነው?ሕዝብ አልገዛም፣ አልተዳደርም፣እምቢ ካለ? ካመፀ? ።
ስለዚህ መንግሥት ለሕዝቡ ተማርኮ እጁን ሰጥቶና በቃኝ ብሎ መውረድና ሥልጣኑንም ለሕዝቡ መልቀቅ ላለፈው ላጠፋው ጥፋትና፣ በደል ይቅርታ ጠይቆ መቀመጥ አለበት።
   ምክንያቱም እስከ ዛሬ ድረስ ለተፈጠረው ጥፋት ሁሉ በየሚድያችሁ የመንግሥት የመልካም አስተዳደር ብሉሽነት ነው ኢያላችሁ ትናገራላችሁ።ሕዝቡም ያላችሁ ይህንኑ ነው።ትርፍ ነገርም አልጨመረም።መልካም አስተዳደር ከሌለ ያለው በተቃራኒው ክፉ አስተዳደር ነው ማለት ነው።ክፉ አስተዳደር ደግሞ ለሃያ አምስት ዓመታት ከመምረር አልፎ ይጎመዝዛል።አሁን ዛሬ የናንተን የመንግሥት አስተዳደር ማብቃት የሚፈልግና የሚጠይቅ ሁሉ ዕድሜ ተርፎትና በሚመጣው አዲስ የመንግሥት አስተዳደር ውስጥ ገብቶ ተደስቶና ተንደላቆ ለመኖር ፈልጎ ሳይሆን ለቀሪውና ለተተኪው አዲስ ትውልድ መልካም አስተዳደር ይምጣለት ሲል ብቻ ነው እንጂ፤እርሱማ አስራ ሰባት ዓመታት በደርግ መንግሥት፣ሃያ አምስት ዓመታት በእናንተ/ኢህአዴግ/ በአጠቃላይ ከአርባ ዓመታት በላይ በጥይት ሲቆላና ሲታመስ፣አንጀቱ አሮና ከስሎ፣ተስፋው ተሟጦ፣የሞተው ሞቶ፣የቀረው ያለ ፍትህ በየእስር ቤቱ ታፍኖና፣ታስሮ፣ሌላውም በዘር፣በጎሳ፣ቋንቋና፣ክልል ተከፏፍሎና፣ተበትኖ፣በስደት የአውሬና የውቅያኖስ እራት ኢየሆነ ይገኛል።

      ስለዚህ እናንተ የኢትዮጵያ መንግስት ባለሥልጣን ሆይ፥እስቲ እናንተም አሁን ይብቃችሁና ይህንን ምስኪን ሕዝብ በተራው በቃህ በሉትና ዕረፍት ስጡት፤እናንተም ደግሞ ዕረፉ።ደክሞአችኋል፣ዝላችኋል።አሥራ ሰባት ዓመታት በጫካ ሃያ አምስት ዓመታት በሕዝብ ጫንቃ ላይ ሳትወርዱ ተንጠላጥላችሁ በጣም ብዙ ዓመታትና ዘመናት ነው ይከብዳል።ከዚህ በላይ ብዙ ብትደክሙ መልካም አስተዳደርን ለሕዝቡ ልታመጡ በፍፁም አትችሉም።ምክንያቱም ሃያ አምስት ዓመታትን በሙሉ ተደክሞበት ያልታየ መልካም አስተዳደር በአንድ ሌሊት ስብሰባና ግምገማ በተአምራት ልታመጡ አትችሉም፣አይሆንም።ጊዜያችሁና ዕድላችሁ ሻግቶ ተበላሽቶአል።ስለሆነም እናንተ በሰላማዊ መንገድ እውነተኛ ሰላምን ፈልጋችሁ መልካም አስተዳደራዊ መንግሥት ሊፈጠርበት የሚችለውን የሕዝብ የሆነ የሽግግር መንግሥት ይመሠረት ዘንድና ሥልጣናችሁንም ለአንድ የፖለቲካ ፓርቲ ወይም ድርጅት ሳይሆን ለኢትዮጵያ ሕዝብ አስረክባችሁ በሰላም ውረዱና የዘመኑን ታሪክ ሥሩ።ያን ጊዜ የታሪክ ባለቤቶች ትሆናላችሁ።
አለበለዚ ግን ነቢየ እግዚአብሔር ሳሙኤል ለእስራኤል ንጉሥ ለሳዖል እንደ ነገረው ሳዖል በእስራኤል ሕዝብ ላይ መልካም አስተዳደርን አላመጣምና "... እግዚአብሔር መንግሥትህን ዛሬ ከአንተ ላይ ቀደዳት፣ለጎረቤትህም ሰው ሰጣት.." እንዳለው የዚህ ምስኪንና ደግ ሕዝብ እንባ
ወደ አምላኩ ወደ እግዚአብሔር ወደ ፀባዖት ጌታ ደርሶ መንግሥታችሁን ከእናንተ ላይ በቀደደ ጊዜ ያን ሰዓት ወየውላችሁ፣ወዮታ አለባችሁ።ምክንያቱም ያን ወቅት እናንተ በሰፈራችሁበት መስፈሪያ፣በመዘናችሁበት ሚዛንና፣በፈረዳችሁበት ፍርድ መሰፈር፣መመዘንና መፈረድ አለና ነው።
ያን ጊዜ ጩኸት ይሆናል የማይጠቅም ጩኸት ነው፤ያን ጊዜ ልቅሶ ይሆናል የማይጠቅም ልቅሶ ነው።ይህ ሁሉ የብድራታችሁ ክፍያ ውጤት ነው።

    ጊዜያት ሁሉ የአምላክ ናቸው።ሰዎች የጊዜያት ባለቤቶች አይደሉም።ነገር ግን በተሰጣቸውና፣ በተወሰነላቸው ጊዜ ውስጥ ኖረው መልካምም ይሁን ክፉ ሠርተው ያልፋሉ።ያ የሠሩትም መልካምም ይሁን ክፉ ሥራቸው ለዘለዓለም ሲነገርና ሲዘከር ይኖራል።እናም ምናልባት እናንተም ሥልጣናችሁን ተመክታችሁ ያላችሁበትን ወቅትና ሰዓት ሁሉ የእኛ ብቻ ብላችሁ የምታስቡ ከሆነ ተሳስታችኋል።ትላንት ያልነበራችሁብትን፣ዛሬ ደግሞ ያላችሁበትንና ነገ ደግሞ በተራው የማትኖሩበትን ጊዜ እንዳለ ማስተዋል ያስፈልጋችኋል ነው የምለው።ነገር ግን
እናንተ የደነደነ ልባችሁን ሰብራችሁ በይቅርታ ከዚህ ንፁህ፣ቅዱስና፣ደግ ሕዝብ ጋር ባትደራደሩ ነገ የጊዜያት ባለቤት ቸሩ አምላክ በጊዜው ለዚህ የዋህ ሕዝብ እጁን አጥፎና፣አመሳቅሎ፣ኢየታሰረ፣ኢየተደበደ፣ኢየደማና፣ኢየሞተ፣ለነፃነቱ፣ለእኩልነቱ፣ለአንድነቱና፣ለፍትህ ለሚጮኸው እናንተ ጩኸቱን ባትሰሙትና፣ባትፈርዱለት የሰማይ አባታቸው ቸሩ አምላክ ግን እንኳን ወደ እርሱ ጮኸው ለምነውት ቀርቶ ያልለመኑትንና ያልጠየቁትን
ሳይለምኑትና ሳይጠይቁት ይሰማቸዋል፣
ይሰጣቸዋል፣ይፈርድላቸዋል።

ክቡር የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስቴር ኃይለ ማርያም፥
ክቡራን የኢትዮጵያ መንግሥት ከፍተኛ ባለ ሥልጣናትና ኃላፊዎች በሙሉ፥
እስከ ዛሬ ድረስ ለሃያ አምስት ዓመታት እኛ ብቻ ነን የምንናገረው፣እኛ ብቻ ነን የምናውቅላችሁ ብላችሁ ስትናገሩልንና፣ስታውቁልን እውቀታችሁንም፣ንግግራችሁንም ሰምተናል፣ተቀብለናል።ዛሬ ደግሞ የእኛ ተራ ነው።እናንተም ስሙን።ስለ እናንተ እናውቅላችኋለን አድምጡን።
እግዚአብሔርን በማመን የሚሠሩት ሥራ ይባረካል፣ ይቀደሳል።
እግዚአብሔር በማመን የሚጓዙት መንገድ ቀና ነው።
እግዚአብሔርን በማመን ለሚቀርቡት ይቀርባልና እመኑበት።
እግዚአብሔርን በማመን የሚመሩት ሕዝብ
ታዛዥ ይሆናል።
ስለዚህ እስቲ እናንተ ደግሞ ዛሬ ላለፈው ጊዜና ዘመን በሕዝብ ላይ ለሠራችሁት በደልና ግፍ ምህረቱ ይደረግላችሁ ዘንድ ከልባችሁ ቸሩ እግዚአብሔርን በነገሮች ሁሉ ጠይቁት።ንስሐ ጠማማውን ያቀናል፣ኃጥኡን ጻድቅ፣ክፉውን መልካም፣
 መልካም አስተዳደርን፣ቅን ፍርድንና ሰላማዊ ሕይወትን ለሕዝቡና ለአገሩ ያጎናፅፍላችኋል። ለዚህ ሁሉ ጥፋት ጉስቁልና የመሪዎች ከእግዚአብሔር ሕግና መግቦቱ መራቅና ከእርሱ ጋር ያይደለ ድካም ለብቻቸው በክፉ መንፈስ ኃይል ስለሚድክሙ ጭምር ነው።
ነቢየ እግዚአብሔር ዳዊት በመዝሙሩ
መዝ፦፻፳፮፥፩-፫
"እግዚአብሔር ቤትን ካልሠራ
ሠራተኞች በከንቱ ይደክማሉ፤
እግዚአብሔር ከተማን ካልጠበቀ
ጠባቂ በከንቱ ይተጋል፤
በማለዳ መግሥገሣችሁም ከንቱ ነው...."
ይላልና እናንተ መሪዎች ቸሩ አምላካችን በነገሮች ሁሉ ተጨምሮ ለአገሪቱና ለሕዝቡ ሥልጣናችሁን በማስረከብ መልካም አስተዳደርን የምታመጡበትን የንስሐ ዘመንን ይሰጣችሁ ዘንድ አምላኬን እለምነዋለሁ።ለዚህም ቅን ልቡናን፣ አስተዋይ አእምሮን፣እግዚአብሔርን የምትፈሩበትን፣ሰውንም የምታከብሩበት ሕሊናን ይስጣችሁ።አሜን።

ቅዱስ እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦችዋን ይባርክ!!!
ወስብሐት ለእግዚአብሔር.
ተፃፈ
በቀሲስ አሸናፊ ዱጋ ዋቄ።

Thursday, September 8, 2016

"ሳይቃጠል በቅጠል"




by ኢትዮ - አፖሎጂስት

አክራሪ እስልምና አፋጣኝ መፍትሄ ይሻል

ይህ ጊዜ ዓለማችን በከፍተኛ ሁኔታ እየተናጠችና እየታመሰች ያለችበት ጊዜ ነው፡፡ ሰላሟን እያናጉ የሚገኙ ዘርፈ ብዙ ችግሮች ቢኖሩም አብይ መንስኤው ግን ለሰው ልጆች ሰላምና ደህንነት እንደቆመ የሚሰብከው የእስልምና ሃይማኖት መሆኑ የሚያከራክር አይደለም፡፡ በሦርያ፣ በኢራቅ፣ በየመን፣ በሊብያ፣ በናይጄሪያ፣ በሶማሊያ፣ በፓኪስታን፣ በአፍጋኒስታንና በሌሎችም ብዙ የዓለም ሃገራት የሚታዩት ሁኔታዎች ይህንኑ የሚያረጋግጡ ናቸው፡፡ በሌላ ወገን ደግሞ እስልምና “የሰላም” ሃይማኖት መሆኑ በተደጋጋሚ ይነገረናል፡፡ እንዲህ ዓይነት ስብከቶች ከሙስሊሞች ዘንድ ብቻ ሳይሆን ሙስሊም ካልሆኑት እና እንዲያውም የሽብር ተግባራቱ ሰለባዎች ከሆኑት ግለሰቦችና ሃገራት ዘንድ መሰማታቸው ጉዳዩን አደናጋሪ ያደርገዋል፡፡ እስልምና የሰላም ሃይማኖት ከሆነ እምነቱን አክርረው የያዙ ሙስሊሞች ስለምን እጅግ ሰላማውያን ከመሆን ይልቅ እጅግ ነውጠኞች ሆኑ? እንዲህ ዓይነት ተግባራትስ ስለምን የእምነቱ መታወቂያዎች ሆኑ? በማለት ተገቢ የሆነውን ጥያቄ የሚሰነዝሩ ወገኖች “እስላሞፎብያ” የሚል “የአዕምሮ ህመም” ስም ይለጠፍላቸዋል፡፡ እስልምና የሰላም ሃይማኖት እንዳልሆነ በድፍረት የሚናገሩ ሰዎች ሕይወታቸውን ለአደጋ ያጋልጣሉ፡፡ ታዋቂ ግለሰቦች እስልምና የሰላም ሃይማኖት አለመሆኑን ሲናገሩ ከተደመጡ ፅንፈኛ ሙስሊሞች አደባባይ በመውጣት ንብረት ያወድማሉ፣ የንፁኀንን ደም ያፈስሳሉ፣ በእምነት ተቋማት ላይ ቦምብ ይጥላሉ፣ የሰላም ሃይማኖት መሆኑን ለማሳመን ሰላምን ያደፈርሳሉ፡፡ የሙስሊሞች ተግባርና ስለ እምነቱ የሚሰበከው ስብከት አራምባና ቆቦ ሆኖብን ግራ ተጋብተን ሳናበቃ እስልምና የሰላም ሃይማኖት አለመሆኑንና “ካፊሮችን” ማሸበር እስላማዊ መሆኑን የሚናገሩ ሙስሊም ሊቃውንት ይገጥሙናል፡፡ በአንድ ወቅት የቀድሞው የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ጆርጅ ደብሊዩ ቡሽ “እስላም ሰላም ነው” በማለት መናገራቸውን ተከትሎ አቡ ቀታዳ የተሰኘ በጂሃድ የሚያምን ሙስሊም አስተማሪ የሚከተለውን ብሎ ነበር፡- “ፕሬዚዳንት ቡሽ በእስልምና ስም የሚደረገውን የጂሃድ ሽብር የሚደግፍ ምንም ዓይነት ነገር በቁርአን ውስጥ አለመኖሩን መናገሩ በእጅጉ አስገርሞኛል፡፡ ለመሆኑ እርሱ የሆነ ዓይነት የእስልምና ሊቅ ነውን? እንደው በእድሜ ዘመኑ ቁርአንን አንብቦ ያውቃልን?”[1]
ሙስሊሞች በሚበዙባቸው ሃገራት ውስጥ የሚገኙት ብዙ ሙስሊም ሊቃውንት እስልምና የሰላም ሃይማኖት አለመሆኑን ይናገራሉ፡፡ በምዕራብ ሃገራት እና ሃገራችንን በመሳሰሉ የሙስሊሞች ቁጥር ከአጠቃላዩ የሕዝብ ቁጥር በሚያንስባቸው ሃገራት ውስጥ የሚገኙት ደግሞ እስልምና የሰላም ሃይማኖት መሆኑን ይሰብካሉ፡፡ የፖለቲካ መሪዎቻችንና የሃይማኖት አባቶቻችንም ከእነርሱ ጋር ይስማማሉ፡፡ እውነቱ የቱ ነው? ማንን እንስማ? የቱን እንቀበል? ከዚህ ግራ መጋባት ለመውጣት እስላማዊ የሃይማኖት መጻሕፍትን ማጥናት አማራጭ የሌለው መፍትሄ ነው፡፡
ከፊት ለፊታችን ከባድ አደጋ የተጋረጠ ቢሆንም ብዙዎቻችን የአደጋውን ግዝፈት ማየት አለመቻላችን ወይም ለማየት አለመፈለጋችን የሚያሳዝን ነው፡፡ በአክራሪ ሙስሊሞች በዚህች ሃገር ውስጥ ለደረሱት ጉዳቶች የኛ ቸልተኝነትና ዝምታ አስተዋፅዖ ማበርከቱን መካድ አንችልም፡፡ ባለፉት ጥቂት ዓመታት ውስጥ ነገሮች ከልክ አልፈው ሃገሪቱ ከገደሉ አፋፍ ደርሳ ከመውደቋ በፊት እግዚአብሔር መንግሥትን ባያነቃ ኖሮ መፃዒ እጣ ፋንታችን ምን ሊሆን እንደሚችል ሳይታለም የተፈታ ነው፡፡ አሁንም ቢሆን የማስታገሻ እርምጃ እንደተወሰደ እንጂ ትክክለኛ መፍትሄ እንደተሰጠ በልበ ሙሉነት መናገር አይቻልም፡፡ ምክንያቱም የህመሙ ምልክት እንጂ መንስኤው አልታከመምና፤ መንስኤው እስካልታከመ ድረስ ደግሞ ጊዜ ጠብቆ መልሶ ማገርሸቱ የማይቀር ሃቅ ነው፡፡ የአክራሪነት ሥረ መሰረት በቁርአን፣ በሐዲሳትና በሌሎችም እስላማዊ ምንጮች ውስጥ ሰፍረው የሚገኙት ትምህርቶች መሆናቸውን መካድ አያዋጣንም፡፡ ሽብርተኝነት የዛፉ ፍሬ በመሆኑ ሥራ መሰራት ያለበት ከፍሬው ይልቅ በግንዱ ላይ ነው፡፡ ይህንን የተረዱት የግብፁ ፕሬዚዳንት አብዱል ፈታህ ኧል-ሲሲ የዓለም ግምባር ቀደም እስላማዊ ዩኒቨርሲቲ እንደሆነ በሚነገርለት በአል-አዝሃር ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ሊቃውንት ፊት ያደረጉት ዓለምን ያስደመመ ንግግር ጥሩ ምሳሌ ይሆነናል፡፡ ፕሬዚዳንቱ ያለ ምንም መሸፋፈን ችግሩ የሚገኘው እድሜ ጠገብ በሆኑት እስላማዊ ቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ መሆኑን በማስገንዘብ በዓለም ላይ ለሚገኘው የሽብርተኝነት ችግር መፍትሄ እንዲመጣ ከተፈለገ እነዚህ ቅዱሳት መጻሕፍት መስተካከል እንዳለባቸው ጥብቅ ማሳሰብያ ሲሰጡ ተደምጠዋል፡፡ ሙስሊሞች በዓለም ላይ የሚገኙትን ሕዝቦች ሁሉ በማጥፋት እራሳቸው ብቻ ለመኖር መፈለጋቸው የሚያስከትለውን አደጋ በመጠቆም የማስጠንቀቂያ መልእክት አስተላልፈዋል፡፡ የሚከተለው ከንግግራቸው ተቀንጭቦ የተወሰደ ነው፡-
“… እዚህ ጋ እየተናገርኩ ያለሁት የእምነት አባቶችን ነው፡፡ እየተጋፈጥን ስላለነው ነገር በአንክሮ ማሰብ ያስፈልገናል – በእርግጥ ይህንን ጉዳይ ከዚህ ቀደም አንድ ሁለት ጊዜ አንስቻለሁ፡፡ በጣም ክቡርና ቅዱስ አድርገን የያዝነው አስተሳሰብ አጠቃላይ ኡማውን [እስላማዊውን ማሕበረሰብ] ለዓለም ማሕበረሰብ የጭንቀት፣ የአደጋ፣ የግድያ እና የጥፋት ምንጭ እንዲሆን ማድረጉ የማይታመን ነው፡፡ ይህ ሊሆን አይችልም!
ያ አስተሳሰብ – “ሃይማኖት” እያልኩ አይደለም ነገር ግን “አስተሳሰቡ” – ከእርሱ ማፈንገጥ የማይቻልበት ደረጃ ላይ እስክንደርስ ድረስ ለክፍለ ዘመናት አክብረን የያዝነው የመጻሕፍትና የአስተሳሰብ ስብስብ መላውን ዓለም እየተፃረረ ይገኛል፡፡ ዓለምን በሞላ እየተፃረረ ነው!
እነዚህን ቃላት እዚህ በአል-አዝሃር ዩኒቨርሲቲ፣ በዚህ የሊቃውንትና የኡላማ ጉባኤ ፊት እየተናገርኩ ነው – አሁን እየተናገርኩ ያለሁትን ነገር በተመለከተ ሁሉን ቻይ የሆነው አላህ በፍርዱ ቀን ስለ እውነተኛነታችሁ ምስክር ይሁንባችሁ፡፡
እየነገርኳችሁ ያለሁትን ይህንን ሁሉ ነገር በዚህ አስተሳሰብ ውስጥ ተጠምዳችሁ የምትኖሩ ከሆነ ልትረዱት አትችሉም፡፡ በትክክል መገምገም እንድትችሉና የበለጠ አብርሆት ካለው ፅንፍ ማየት ትችሉ ዘንድ ከራሳችሁ ሁኔታ መውጣት ያስፈልጋችኋል፡፡
ደግሜ ደጋግሜ እላለሁ ሃይማኖታዊ አብዮት ያስፈልገናል፡፡ እናንተ ኢማሞች በአላህ ፊት ተጠያቂዎች ናችሁ፡፡ መላው ዓለም፣ እደግመዋለሁ መላው ዓለም የእናንተን ቀጣይ እርምጃ እየተጠባበቀ ይገኛል… ምክንያቱም ይህ ኡማ እየፈረሰ ነው፣ እየወደመ ነው፣ እየጠፋ ነው – እየጠፋ ያለው ደግሞ በገዛ እጃችን ነው፡፡[2]
በዚህ ንግግር ውስጥ ፕሬዚዳንት ኧል-ሲሲ በእስላማዊ ቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ የተሰገሰገው የነውጠኝነት አስተሳሰብ የዓለም ስጋት ምንጭ መሆኑን በግልፅ አስረድተዋል፡፡ በዚህ ገፅ ላይ በተከታታይ ስናወጣ እንደቆየነው የሽብርተኝነት ሥረ መሰረት እስላማዊ መጻሕፍት እንጂ ሌላ አይደለም፡፡ (አይ ኤስ የተሰኘው የሽብር ቡድን እየፈፀማቸው የሚገኙት የሽብር ተግባራት በእስላማዊ ምንጮች የተደገፉ መሆናቸውን ማስረጃዎችን በመጥቀስ ያሳየንበትን ጽሑፍ ለአብነት ያህል ማየት ይቻላል፡፡) ካለማወቅም ይሁን ከፖለቲካዊ ትክክለኝነት (Political Correctness) በመነጨ አስተሳሰብ እስላማዊ መጻሕፍት ሰላምን እደሚያስተምሩ በመስበክ ለእስልምና ጥብቅና ሲቆሙ የነበሩ ወገኖች ይህንን ማድረጋቸው ምንም አልፈየደም፡፡ አንድን ከሥነ ምግባር የወጣ ሰው ሥነ ምግባሩ ጥሩ እንደሆነ ደጋግሞ በመንገር ፀባዩን እንዲያርም ማድረግ እንደማይቻል ሁሉ ሽብርን የሚሰብክ ሃይማኖት ሰላምን እንደሚሰብክ በመናገር ሰላማዊ ማድረግ አይቻልም፡፡ ይልቁኑ ስህተቱን ነቅሶ በማውጣት እንዲያስተካከል መንገር እንጂ መፍረግረግና መለማመጥ አጥፊው የልብ ልብ እንዲሰማው ማድረግ ነው፡፡ እውነትን ሸሽጎ ውሸትን በመናገር ችግሩን ማፈርጠም መፍትሄ አይሆንም፡፡ የፖለቲካዊ ትክክለኝነት ንግግሮች ዘላቂ መፍትሄ ሊያመጡ ይቅርና ጊዜያዊ መፍትሄ እንኳ ሊሆኑ አልቻሉም፡፡ የሃይማኖት አባቶችና የፖለቲካ መሪዎች የእስልምናን ሰላማዊነት አጥብቀው ቢሰብኩንም ነገር ግን ችግሮች እየተባባሱ ሄዱ እንጂ ሲቀንሱ አልታዩም፡፡ እውነትን በመናገር ሊፈጠር የሚችለውን ጊዜያዊ ችግር በመፍራት ዝንተ ዓለም በሽብር እየተናጡ ከመኖር እውነቱን አፍረጥርጦ በመናገር ዘላቂ መፍትሄ መፈለግ ይበጃል፡፡ “ጅቡ እግሬን እየበላው ነውና እንዳይሰማን ዝም በል” እንዳለው ሞኝ ሰው መሆን ይበቃናል፡፡
ማሕበረሰባችንን ከዚህ አስከፊ የጥፋት ማዕበል ለመታደግ የመጀመርያው እርምጃ መሆን የሚገባው የችግሩን ምንጭ ለመረዳት ጥረት ማድረግ ነው፡፡ በአንድ ወቅት የምንጊዜም ምርጥ ሳይንቲስት የሆነው አንስታይን ዓለምን ከጥፋት ለመታደግ አንድ ሰዓት ብቻ ቢሰጠው የተሰጠውን ጊዜ እንዴት እንደሚጠቀም ተጠይቆ ሲመልስ 55 ደቂቃዎችን ችግሩን ለመረዳትና 5 ደቂቃዎችን ብቻ መፍትሄ ለማፈላለግ እንደሚጠቀም ተናግሮ እንደነበር ይነገራል፡፡ የብዙ ችግሮቻችን መፍትሄ ያለማግኘት ምክንያቱ ችግሮቹን ራሳቸውን በትክክል አለማወቃችን መሆኑ እሙን ነው፡፡ ሽብርተኝነት በህዝባችን ላይ አደጋን የደቀነ የዘመናችን ችግር መሆኑን እናውቃለን፡፡ ነገር ግን የሽብርተኝነት ምንጭ ምን እንደሆነ ስለማናውቅ የችግሩ አሳሳቢነት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ ይገኛል፡፡ ዛሬ ኢትዮጵያ ሃገራችን በዙርያዋ ከሚገኙት ጎረቤቶችዋ ጋር ሊነፃፀር በማይችልበት ሁኔታ ከሽብር አደጋዎች ተጠብቃ ትገኛለች፡፡ ነገር ግን የሽብርተኝነት ምንጭ የሆነውን የእስልምናን ትምህርት በትክክል ተረድተን መፍትሄ ካላፈላለግን በስተቀር ይህ አንፃራዊ ሰላም በዚህ ሁኔታ ለመቀጠሉ ምንም ዋስትና አይኖረንም፡፡ ስለዚህ ዜጎችም ሆንን መሪዎች እስልምና ሽብርተኝነትን በተመለከተ ምን እንደሚያስተምር፣ ምን እንደሚያቅድ፣ የአፈፃፀም ስልቶቹ እንዴት እንደሆኑ፣ ወዘተ. ማጥናት ያስፈልገናል፡፡ እውቀቱ ካላቸው፣ በተለይም ደግሞ በእስልምና ትምህርቶች ከሰለጠኑና እስልምናን ለቀው ከወጡ ሰዎች መማር እጅግ ጠቃሚ ነው፡፡
አክራሪ እስልምና ለዓለምም ሆነ ለሃገራችን አዲስ አይደለም፡፡ ቤተ ክርስቲያን በየዘመናቱ የአክራሪ እስልምናን ተግዳሮቶች ስትጋፈጥ ኖራለች፡፡ አንዳንዶች አክራሪ እስልምና ፖለቲካዊ ችግር በመሆኑ መፍትሄው ፖለቲካዊ ነው ስለዚህ ችግሩ ለመንግሥት ብቻ መተው አለበት ይላሉ፡፡ ነገር ግን፡-
መንግሥት ሥልጣንና ጉልበት ቢኖረውም የትምህርቱን ውጤት እንጂ ትምህርቱን መጋፈጥ አይቻለውም፡፡ የመንግሥት አካላት ብዙ ጊዜ በሃይማኖት ካባ ተሸፍኖ ለክፍለ ዘመናት የኖረውን አይ የእስልምናን ፖለቲካ ለመረዳት ሲቸገሩ ይስተዋላሉ፡፡ ስለዚህ ትክክለኛ መፍትሄ ለመስጠት ይቸገራሉ፡፡
የመንግሥት አካላት የነገሩን ውስጠ ሚስጥር ቢረዱትም እንኳን መንግሥት ሁሉን አቀፍ በመሆኑ ገለልተኛነትን ይመርጣሉ፡፡ ስለዚህ የችግሩ መንስኤ የሆነውን የእስልምናን መሰረት መንካት አይፈልጉም፡፡
አክራሪ እስልምና አይዲዎሎጂ በመሆኑ በጉልበት አይቀለበስም፡፡ ስለዚህ መንግሥት አክራሪ እስልምና የጦር መሳርያ ይዞ አደባባይ ሲወጣ በጦር መሳርያ ማስታገስ ቢችልም ነገር ግን ትምህርቱን የሚጋፈጥበት ሥነ መለኮታዊ መሳርያ የለውም፡፡
ባለፉት ጥቂት ዓመታት እንደታዘብነው አንዳንድ የፖለቲካ ፓርቲዎች ይባስ ብለው ከአክራሪ እስልምና ጋር በመተባበር አጀንዳውን ሲያራግቡና ጥብቅና ሲቆሙለት ታይተዋል፡፡ ይህ የሚያመለክተው አንዳንድ ፖለቲከኞች የዛሬ ጥቅማቸውን እንጂ የነገውን አደጋ ማየት አለመፈለጋቸውን ነው፡፡ እንዲህ ዓይነት ሰዎች ሥልጣን ቢይዙ ችግሩን ከማባባስ ውጪ መፍትሄ መስጠት አይችሉም፡፡
የመገናኛ ብዙኃንን ስንመለከት እንኳንስ መፍትሄ ሊሰጡ ይቅርና ጥያቄውን እንኳ በትክክል የተረዱት አይመስልም፡፡ በትክክል ቢረዱትም እንኳን ፖለቲካዊ ትክክለኝነት ስለሚጫናቸው የችግሩን ስረ መሰረት በመንካት መፍትሄ ማፈላለግ አይችሉም፡፡
ምሑራን ጥያቄውን የተወሰነ ያህል ይረዱታል ነገር ግን የችግሩን ስረ መሰረት በመጥቀስ የመፍትሄ ሐሳቦችን እንዳይሰነዝሩ በፍርሃትና በፖለቲካዊ ትክክለኝነት ተሸብበዋል፡፡
አንዳንድ ለዘብተኛ አመለካከት ያላቸው ምዕራባውያን የሚከተሉትን “መፍትሄዎች” ያስቀምጣሉ፡-
ለአክራሪ ሙስሊሞች ምንም ትኩረት አለመስጠትና ችላ ማለት፡፡ ነገር ግን ችላ የሚባሉት እምን ድረስ ነው? ብሎ መጠየቅ ያስፈልጋል፡፡ ሰይፍ አንገታችን ላይ ተቀምጦ ትኩረት አንሰጠውም ማለት የሞኝ መፍትሄ ነው፡፡
ባሉበት እንዲሆኑ ማገድ (ወደ ክልላችን እንዳይገቡ ማድረግ፡፡) o አሁን ካለው የሕዝቦች እንቅስቃሴና የመረጃ ቴክኖሎጂ ደረጃ አኳያ አያስኬድም፡፡ የውጪዎቹ እንዳይገቡ ማገድ ይቻል ይሆናል፣ ውስጥ የሚገኙትንስ? መግደል? ማሰር? ከሃገር ማባረር? አያዋጣም፡፡
እስልምናን ከፖለቲካዊ ይዘቱ በማፋታት ምዕራባዊ መልክ ያለውን እስልምና መፍጠር [ለምሳሌ ኪልያም (Quilliam) ፕሮጀት]፡፡[3]

Monday, August 22, 2016

ወሀቢዝም በኢትዮጵያ ውስጥ!


by ኢትዮ - አፖሎጂስት

ከ1983 ዓ.ም. የመንግሥት ለውጥ ወዲህ በኢትዮጵያ ውስጥ የሃይማኖት ነፃነት ከቀደሙት ዘመናት ጋር ሊነፃፀር በማይችልበት ሁኔታ መከበሩ የማይካድ ሃቅ ነው፡፡ ነገር ግን ይህንን ነፃነት የለአግባብ የተጠቀሙና የጥፋት መርዛቸውን በትውልዱ መካከል ለማሰራጨት የተጉ፣ ከዚህም የተነሳ ብዙ ጥፋቶችን ያስከተሉ ቡድኖች መኖራቸው አልቀረም፡፡ በዚህ ረገድ በተለይ የወሃቢዝም (ሰለፊ) ፍልስፍናን የሚከተሉ ወገኖች ይጠቀሳሉ፡፡ ዛሬ በሃገሪቱ ውስጥ በብዛት ተሰራጭቶ በሕዝቦች መካከል ያለውን የመቻቻልና አብሮ የመኖር ባሕል እያደፈረሰ የሚገኘው ወሃቢዝም ይህንን ነፃነት ተጠቅሞ የተስፋፋ ይሁን እንጂ እግሩን  በሃገሪቱ ውስጥ ካሳረፈ ብዙ አስርተ አመታት አልፈዋል፡፡

ፋሺስት ኢጣልያ  በኢትዮጵያ ላይ የነበረውን እኩይ አጀንዳ ለማስፈፀም ሙስሊሞችን መንከባከብ የሚል መርሃ ግብር ስለነበረው ሙስሊሞች የሐጅ ጉዞ እንዲያደርጉ ያበረታታ ነበር፡፡ በገንዘብም በመደጎም ይልክ ነበር፡፡ በ1933 ለሐጅ ወደ መካ የተጓዙት ኢትዮጵያውያን ቁጥር 11 ብቻ ሲሆን ከ1934-1935 የሄዱት 29፣ ከ1935-1936 ደግሞ 7 ሰዎች ብቻ ነበሩ፡፡ ነገር ግን በ1937 ይህ ቁጥር ወደ 1,700 አድጓል፡፡ ሁሉም ደግሞ በኢጣሊያ መንግሥት ድጎማ የሄዱ ነበሩ፡፡[1] ሳዑዲ አረብያ ለሐጅ የሚሄዱትን ኢትዮጵያውያን በወሃቢዝም ፍልስፍና አጥምቃ ወደ ሃገር ውስጥ በማስገባት ፍልስፍናውን የማስፋፋት ሥራዋን የጀመረችው ኢጣሊያ ኢትዮጵያን ከመውረሯ በፊት ነበር፡፡ በተለይም ደግሞ ሼኽ ዩሱፍ አብደል ረህማን እና ሐጂ ኢብራሂም ሀሰን የተሰኙ ሁለት ሰዎች ለዚህ በዋናነት ይጠቀሳሉ፡፡ ሁለቱም ወደ ሳዑዲ የተጓዙት በ1930ዎቹ መጀመርያ አካባቢ ነበር፡፡ ሼኽ ዩሱፍ በ1939 ወደ ኢትዮጵያ በመመለስ በሐረር ከተማ የወሃቢዝም ትምህርታቸውን ማስተማር የጀመሩ ሲሆን የሐረርን ከተማ የቀድሞ ነፃነት ለመመለስ የከተማይቱን ሙስሊም ሊቃውንት አደራጅተው ፊርማ በማሰባሰብ በወቅቱ የብሪቲሽ የአካባቢው አማካሪ ለነበሩት ለኮሎኔል ዳላስ ጥያቄ አቅርበው ነበር፡፡ ነገር ግን ኮሎኔሉ ጥያቄያቸውን ውድቅ አድርገዋል፡፡ ከዚህ በኋላ ነበር ሼኽ ዩሱፍ ለረጅም ጊዜ ትግል መሰረት ለመጣል የወሰኑት፡፡ ከዚያም ብሔራዊ እስላማዊ ማሕበር (አል-ጀማኢያ አል-ወኒያ አል-ኢስላሚያ) ወይም አል-ዋታኒ የተሰኘ ማሕበር በማቋቋም መንቀሳቀስ ጀመሩ፡፡ የማሕበሩ አባላት በሙሉ ሐረርን “ከኢትዮጵያ ቅኝ ነፃ በማውጣት” አሕመድ ግራኝባስቀመጠው ምሳሌነት መሰረት እስላማዊ መንግሥት እንደገና ለማቋቋም ቃል ኪዳን ገቡ፡፡ የሐረርን ሕዝብ በሚገባ ሳያስተምሩ መንግሥትን መጋፈጥ እንደማይቻል ስለተገነዘቡም ዋታኒ እስላማዊ ማሕበር ቀደም ሲል የተሰራውን ትምህርት ቤት በመጠቀም እስላማዊውን ትምህርት በማስተማር ላይ እንዲያተኩር ተወሰነ፡፡ ትምህርት ቤቱም ዘመናዊ መልክ ኖሮት አረብኛና በሐጂ ኢብራሂም ሀሰን አማካይነት ደግሞ የወሃቢዝም ትምህርት እንዲሰጥ ተባለ፡፡ ሐጂ ኢብራሂምም በከፍተኛ ትጋት በየምሽቱ በቤታቸውም ጭምር ይህንን ፍልስፍና ማስተማር ተያያዙ፡፡ የግራኝ ታሪክና ወታደራዊ አካሄድ እንደ አንድ ዋና ትምህርት ይሰጥ ነበር፡፡ ዋታኒ እስላማዊ ማሕበር በሚያዘጋጃቸው ክብረ በዓላት ላይ በአሕመድ ግራኝ ዙርያ የሚያጠነጥኑ ግጥሞችና የውዳሴ መዝሙሮችም ተዘጋጅተው በተማሪዎች ይዘመሩ ነበር፡፡ ሼኽ አብደል ረህማን ደግሞ በአዲስ አበባ ውስጥ በነበራቸው የመጻሕፍት መደብር አማካይነት በአረብኛ የተዘጋጁ የወሃቢያ መጻሕፍትን እያስመጡ ያከፋፍሉ ነበር፡፡ ነገር ግን ኋላ ላይ የትምህርት ሚኒስቴር ሆነው የተሾሙት ከበደ ሚካኤል ትምህርት ቤቱን በጎበኙበት ወቅት ለግራኝ የሚዜሙትን መዝሙሮች ትርጉም ከሰሙ በኋላ እንዳይዘመሩ ያገዱ ሲሆን አማርኛም የመማርያ ቋንቋ እንዲሆን አዘዋል፡፡[2]

ነገር ግን ከመንግሥት ይልቅ የዋሃቢዝም ዋና ጠላት የነበሩት ሼኽ አብደላህ ኢብን ሙሐመድ ኢብን ዩሱፍ (አብደላህ አል-ሐረሪ) የተሰኙ ሙስሊም ሊቅ ነበሩ፡፡ እኚህ ሰው የሃገራችን አብዛኛው ሙስሊም የሚከተለው በአንፃራዊነት ሰላማዊ ሊባል የሚችለው የሱፊ እስልምና ተከታይ ሲሆኑ ከፀረ ሰላም ትምህርቱ በተጨማሪ አሁን በዝርዝር የማናያቸውን የወሃቢዝም አስተምህሮዎች ይቃወሙ ነበር፡፡ ሼክ አብደላህ ከሐረር ወደ አዲስ አበባ በመምጣት ውሏቸውን በመርካቶ አካባቢ በማድረግ ሙስሊሙን ህብረተሰብ በማስተማር ዝነኛ ሆነው ነበር፡፡ ኋላም ወደ ሊባኖስ በማቅናት በመካከለኛው ምስራቅ ትምህርታቸውን በማስፋፋት በዓለም ላይ ዋነኛ ፀረ ወሃቢዝም ለሆነው ዓለም አቀፍ እስላማዊ ማሕበር ሊቀ መንበር ሆነዋል፡፡[3] የኚህን

ኢትዮጵያዊ ትምህርት አረቦች “አሕባሽ” በማለት ይጠሩታል፡፡ ምክንያቱ ደግሞ ሐጂ አብደላህ ከሐበሻ ምድር የመጡ መሆናቸው ነው፡፡ ትምህርቱ ግን በኢትዮጵያ ውስጥ ለዘመናት የኖረውና አብዛኛው የኢትዮጵያ ሕዝበ ሙስሊም የሚከተለው የሱፊ እስልምና እንጂ ሌላ አይደለም፡፡ ትምህርቱን የተቀበሉና ከኢትዮጵያዊው የተማሩ ሊቃውንት ስልጠናዎችን ለመስጠት ከሊባኖስ በመጡበት ወቅት ወሃቢዮች “መንግሥት አሕባሽ የሚባል አዲስ ሃይማኖት አመጣብን” በማለት ሁከት መፍጠር ጀመሩ፡፡ እነርሱ ባለ ሃገር ሆነው የሃገሪቱን የሱፊ ሊቃውንት ማሳደድና መግደል ተያያዙ፡፡ መንግሥትም የኢትዮጵያ ሕዝብ ቅሬታ እስኪገባው ድረስ ታገሳቸው፡፡ አሁንም አቅማቸው ቢሟስስም በየስርቻው መሽሎክሎካቸውንና “ድምፃችን ይሰማ” እያሉ በሰላላ ድምፆቻቸው መጮኻቸውን አልተውም፡፡

ሼኽ አብደላህ በአንድ ወቅት በሐረር ውስጥ በነበረው የወሃቢዮች ትምህርት ቤት ላይ ባስነሱት ተቃውሞ ምክንያት ለእስር ተዳርገው ነበር፡፡ አዲስ አበባ በነበሩበት ጊዜ ሐጂ ኢብራሂም ለአንድ የአረብኛ ጋዜጣ በፃፉት መጣጥፍ ክርስቲያናዊት ኢትዮጵያንና ንጉሡን ማጣጣላቸውን ለመንግሥት መረጃ እንደሰጡም ይነገራል፡፡ በዚህም ምክንያት ሐጂ ኢብራሂምና የትምህርት ቤቱ የወሃቢያ መምህራን ታስረው ለፍርድ የቀረቡ ሲሆን ሐጂ ኢብራሂም ከሐረር ከተማ ወደ ሌላ የኢትዮጵያ ክፍል ሄደው እንዲኖሩ ተፈርዶባቸዋል፡፡ እኚህ ሰው አሁን በሕይወት የሉም፡፡ ከዚያም ሼኽ አብደላህ የሐረር ከተማ ሙፍቲ ሆነው በመሾማቸው ምክንያት ወሃቢዮች ድምፃቸውን አጥፍተው ለመኖር የተገደዱበት ሁኔታ ነበር፡፡ የሐረር ወሃብዮች ኋላ ላይ በ1948 የሶማሌ ወጣቶች ክበብ ተብሎ በመንግሥት ፈቃድ በተቋቋመው ቡድን ውስጥ እጃቸውን አስገብተው የነበረ ሲሆን የአሕመድ ግራኝ መንፈስ እንደገና በመምጣት ከተማይቱ ላይ አንዣቦ ነበር፡፡ ነገር ግን ጥር 1948 ጉዳዩ ይፋ በመሆን 200 የሚሆኑ የክበቡ አባላት በቁጥጥር ስር ዋሉ፡፡ ወጣቶቹ ይቅርታ በመጠየቅ የተፈቱ ሲሆን ሰማንያ አንድ የሚሆኑ የወሃቢያን እንቅስቃሴ የሚመሩ የዋታኒ ማሕበር አባላት ከተማይቱን በመልቀቅ እንዲበተኑ ተደርጓል፡፡ በዚሁ ዓመት ኢትዮጵያ የኦጋዴን ግዛቷን በማግኘቷ ምክንያት በሐረርጌ ላይ ያላት ሙሉ ቁጥጥር እውን ስለሆነ በ1936 በሐረር ከተማ የተጀመረውም በወሃቢዝም የተመራው የእስላማዊ ፖለቲካ መነቃቃት ሊከሽፍ ችሏል፡፡[4]ኢትዮጵያዊ ትምህርት አረቦች “አሕባሽ” በማለት ይጠሩታል፡፡ ምክንያቱ ደግሞ ሐጂ አብደላህ ከሐበሻ ምድር የመጡ መሆናቸው ነው፡፡ ትምህርቱ ግን በኢትዮጵያ ውስጥ ለዘመናት የኖረውና አብዛኛው የኢትዮጵያ ሕዝበ ሙስሊም የሚከተለው የሱፊ እስልምና እንጂ ሌላ አይደለም፡፡ ትምህርቱን የተቀበሉና ከኢትዮጵያዊው የተማሩ ሊቃውንት ስልጠናዎችን ለመስጠት ከሊባኖስ በመጡበት ወቅት ወሃቢዮች “መንግሥት አሕባሽ የሚባል አዲስ ሃይማኖት አመጣብን” በማለት ሁከት መፍጠር ጀመሩ፡፡ እነርሱ ባለ ሃገር ሆነው የሃገሪቱን የሱፊ ሊቃውንት ማሳደድና መግደል ተያያዙ፡፡ መንግሥትም የኢትዮጵያ ሕዝብ ቅሬታ እስኪገባው ድረስ ታገሳቸው፡፡ አሁንም አቅማቸው ቢሟስስም በየስርቻው መሽሎክሎካቸውንና “ድምፃችን ይሰማ” እያሉ በሰላላ ድምፆቻቸው መጮኻቸውን አልተውም፡፡

የደርግ መንግሥት ባጠቃላይ ሃይማኖትን በተመለከተ ከሚከተለው ፖሊሲ የተነሳ ያን ያህል የጎላ የወሃቢዝም እንቅስቃሴ አልነበረም፡፡ ነገር ግን ውስጥ ለውስጥ የተሰሩ ሥራዎች እንደነበሩ እሙን ነው፡፡ በ1958 ከየመን በመጣ ስደተኛ የተመሰረተው የአል-አወልያ ትምህርት ቤት በዘመነ ደርግ ጥብቅ በሆነ የመንግሥት ቁጥጥር ስር ነበር፡፡[5] ደርግ ወደ መውደቂያው አካባቢ “የሰርገኛ መጣ…” ዓይነት የፖሊሲ ለውጦችን በማድረጉ ምክንያት ለሳዑዲ እንቅስቃሴዎችም በር ከፍቶ ነበር፡፡ በዚህም መሰረት የዓለም የሙስሊሞች ሊግ ከእርዳታ ማስተባበርያና ማቋቋሚያ ኮሚሽን (እማማኮ) ጋር በመተባበር ትምህርት ቤቶችን፣ እጓለ ሙታንን እና ክሊኒኮችን ለማቋቋም ስምምነት አደረገ፡፡ መንግሥትና ሊጉ ያላቸው ግንኙነት መጥበቁን ከሚያመለክቱ ተግባራት መካከል አንዱ ሊጉ የሃይማኖትና የአረብኛ ቋንቋ ሥልጠናዎችን እንዲሰጥ መፈቀዱ ነበር፡፡ በ1991 ወደ ኢትዮጵያ ለጉብኝት የመጣው የሊጉ ልዑካን ቡድን በወሎ፣ በሐረር፣ በአዲስ አበባና በደብረ ዘይት ትምህርት ቤቶችን በመገንባት ሥራ ላይ መሆኑን መግለፁ ኢትዮጵያን የማስለም እንቅስቃሴው በአዲስ መልክ መጀመሩን አመላካች ነበር፡፡[6]

ከ1991 ወዲህ የተደረገውን የመንግሥት ለውጥ ተከትሎ በሃገራችን ውስጥ የተገኘውን የእምነት ነፃነት ሽፋን በማድረግ ብዙ ጥፋቶች ተፈፅመዋል፡፡ በተለይ የወሃቢዝም ፍልስፍና ተከታዮች ነፃነቱ የሰጣቸውን ክፍተት በመጠቀም አክራሪ የሆኑ ትምህርቶችን በማስተማር  ግርምቢጠኛ ባህርያቸውም ከልክ አልፎ በሚያሰራጯቸው ጽሑፎችና የድምፅ እንዲሁም የምስል መልዕክቶች ሌሎች ሃይማኖቶችን በነገር በመጎሽመጥ ሃገሪቱን ሲያምሱ ቆይተዋል፡፡ የተሰጣቸውንም የመንግሥት ሥልጣን ለእምነታቸው ማስፋፍያ በመጠቀም ብዙ በደሎችን ፈፅመዋል፡፡ በአንድ ወቅት ከውጪ ሃገራት በገፍ በመግባት ሃገሪቱን ያጥለቀለቁት የጂሃድ ፊልሞችና አክራሪነትን የሚሰብኩ የህትመት ሥራዎች ያስከተሉትን ውጤት ሁላችንም በግልፅ ያየነው ነው፡፡ በተለይ ከሳዑዲ አረብያ በሚመጣው ፔትሮ ዶላር የተገነቡት መስጊዶችና እስላማዊ ማዕከላት  ሃገሪቱን እንደሙጃ ውጠዋታል፡፡ በበጎ አድራጎት ሥም ወደ ሃገር ውስጥ የገቡ በርካታ እስላማዊ ድርጅቶችም ውስጥ ለውስጥ ጂሃዳውያንን እያሰለጠኑና የገንዘብ ድጋፍ እያደረጉ ሃገሪቱን ቁልቁል ወደ ጥፋት አዘቅት ነድተዋታል፡፡ እቅዳቸው ተሳክቶ ቢሆን ኖሮ ሊከተል የሚችለውን አደጋ ማሰብ በእጅጉ ይከብዳል፡፡ አደጋውን ከማስቀረት አንፃር መንግስት ይበል የሚያሰኙ እርምጃዎችን ወስዷል፡፡ በተለይም የወሃቢዝም ዋነኛ የርቢ ማዕከል የሆነው አል-አወልያ እስላማዊ ትምህርት ቤት ከወሃቢዮች እጅ ወጥቶ ለተገቢው አካል መሰጠቱ ትክክለኛ እርምጃ ነበር፡፡ ይህ ከአንደኛ ደረጃ ተነስቶ በኢትዮጵያ ውስጥ ብቻ ሳይሆን በምስራቅ አፍሪቃም ጭምር ግምባር ቀደም እስላማዊ ትምህርት ቤት ለመሆን የበቃው የፅንፈኞች ማዕከል በሃገሪቱ ላይ ያሳደረው ተፅዕኖ ቀላል አልነበረም፡፡ የተወሰደው እርምጃ ከረፈደ በኋላ ቢሆንም ነገር ግን ከመሸ በኋላ አለመሆኑ ተስፋ ሰጪ ነው፡፡ አሁንም ቢሆን በመርዛማ ትምህርቱ ተበክለው የወጡ ወጣቶች ክትትል ሊደረግላቸውና በፅንፈኝነት ቅልበሳ መርሃ ግብር (De-radicalisation Program) ሊታቀፉ ይገባል፡፡

በኢትዮጵያ ክርስቲያኖች ላይ የደረሱ እስላማዊ ጥቃቶች የቅርብ ዘመን ትዝታዎች

ቀን ቦታ የሞተ የቆሰለ የክስተቱ ዝርዝር
6/2/97 አርሲ – ቆሬ 10 3 2237 ክርስቲያኖች ተፈናቀሉ፡፡ 1 ቤተ ክርስቲያንና 194 የክርስቲያን ቤቶች ሙሉ በሙሉ ተቃጠሉ፡፡ 24 የክርስቲያን ቤቶች በከፊል ተቃጠሉ፡፡ 304 ከብቶች ተዘረፉ፡፡
16/1/99 ጀምሮ ጂማ – በሻሻ 18 38 488 በግድ ሰልመዋል፡፡ ከ2000 በላይ ተፈናቅለዋል፡፡ ከ850 በላይ የክርስቲያን ቤቶች ተቃጥለዋል፡፡ 3 አብያተ ክርስቲያናት ተቃጥለዋል፡፡ 4 ተዘርፈዋል፡፡
ከላይ የተቀመጡት መረጃዎች የተወሰዱት “በኢትዮጵያ የሃይማኖት መቻቻል አለን” በሚል ርዕስ በአባ ሳሙኤል ከተዘጋጀው መጽሐፍ ገፅ 28-31 እና “አክራሪ እስልምና በኢትዮጵያ” በሚል ርዕስ በኤፍሬም እሸቴ ከተዘጋጀው መጽሐፍ ገፅ 172-175 ነው፡፡ ዓመታቱ እንደ ኢትዮጵያ አቆጣጠር ናቸው፡፡

ቀን ቦታ የሞተ የቆሰለ የክስተቱ ዝርዝር
3/8/11 ጅማ – አሰንዳቦ 2 – በቁጣ የተሞሉ ሙስሊሞች አብያተ ክርስቲያናትን የማቃጠል ዘመቻ አድርገዋል፡፡
3/1/11 ባሌ – ሆማ ቀበሌ – 17 ወንጌልን ለማስተማር በወጡ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ ክርስቲያን ተማሪዎች ላይ ድብደባ ተፈፅሟል፡፡
9/13/10 አፋር – ዱፍቲ – 1 ከእስልምና የወጣን አንድ ክርስቲያን ወጣት ሙስሊሞች በስለት ወግተዋል፡፡
8/21/10 አዲስ አበባ – 1 ታዋቂ ክርስቲያን መሪ በበትር ተደብድቧል፡፡
7/16/2010 አዲስ አበባ – 1 ከእስልምና የመጣ ክርስቲያን በቁጣ በተሞሉ ሙስሊሞች ተደብድቧል፡፡
9/11/09 ሸዋ – ሰንበቴ – 3 የሙስሊሞች ቡድን ወደ ቤተ ክርስቲያን ግር ብሎ በመግባት በፀሎት ላይ የነበሩትን ክርስቲያኖች ክፉኛ አቁስለዋል፡፡
7/3/09 ደሴ 2 – በቤተ ክርስቲያን ቅጥር ግቢ ውስጥ በሥራ ላይ የነበሩ 2 ክርስቲያኖች ተኩስ ተከፍቶባቸው ተገድለዋል፡፡
9/20/08 አዲስ አበባ – 1 አንድ ዕድሜው 35 ዓመት የሚሆን ክርስቲያን መሪ ለሞት እስኪቀርብ ድረስ በሙስሊሞች ተደብድቧል፡፡
7/19/08 ጂጂጋ – 2 ሁለት ከእስልምና የመጡ ክርስቲያኖች በድንጋይ ተደብድበዋል፡፡
4/30/07 ጂጂጋ 2 3 ሙስሊሞች በድንኳን ውስጥ በተሰበሰቡ ክርስቲያኖች ላይ ቦምብ በመጣል 2 ክርስቲያኖችን ሲገድሉ 3 አቁስለዋል፡፡
1/5/07 ኮፈሌ 1 – ሙስሊሞች አንድ ክርስቲያን በብረት ቀጥቅጠው ገድለዋል፡፡
10/1/06 ጂማ 10 12 ሁለት አብያተ ክርስቲያናት ተቃጥለዋል፡፡
4/16/06 ጂጂጋ 3 23 በሁለት ምግብ ቤቶችና በአንድ ቤተ ክርስቲያን ላይ በሙስሊሞች በተፈፀመ የቦምብ ጥቃት የደረሰ አደጋ
3/22/06 አርሲ ነጌሌ 1 – ሙስሊሞች በአንድ የፕሮቴስታን ቤተ ክርስቲያን በር ፊትለፊት ከእስልምና የመጣን አንድ ክርስቲያን በጥይት ገድለዋል፡፡ ሟች የ 7 ልጆች አባት ነበሩ፡፡
7/19/05 ጂጂጋ 1 – የታጠቁ ሙስሊሞች አውቶብስ በማስቆም በውስጥ የነበሩትን ክርስቲያኖች ሸሃዳ አስብለዋል፤ ወደ መካም በመዞር እንዲሰግዱ አስገድደዋል፡፡ ይህንን ለማድረግ ፍቃደኛ ያልሆነ አንድ ወጣት ተገድሏል፡፡
መረጃዎቹ የተወሰዱት በክርስቲያኖች ላይ የሚደርሱትን እስላማዊ ጥቃቶች በመዘገብ ከሚታወቅ ክርስቲያናዊ ድህረ ገፅ ላይ ነው፡፡ ዓመታቱ እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር ናቸው፡፡

http://www.thereligionofpeace.com/pages/christianattacks.htm

ከላይ የተጠቀሱት ጥቃቶች ከብዙዎቹ ጥቂቶቹ ሲሆኑ ፍትህን በማዛባት፣ አድማ በማድረግ፣ የክርስቲያን ልጆችን አፍኖ በመውሰድ፣ አስገድዶ በመድፈር፣ አስፈራርቶ አካባቢን በማስለቀቅ፣ የክርስቲያን ይዞታዎችን በልዩ ልዩ ዘዴዎች በመንጠቅ፣ ወዘተ. የተፈፀሙ የግፍ ሥራዎችን ዘርዝሮ መጨረስ አይቻልም፡፡

[1] Haggai Erlich, Saudi Arabia & Ethiopia, 2007, p. 73

[2] Ibd, 80-83

[3] Ibd, 84

[4] Ibd, 85-92

[5] Ibd, 189-190

[6] ኤፍሬም እሸቴ፣ አክራሪ እስልምና በኢትዮጵያ፣ 2000፣ ገፅ 142-143