Tuesday, December 25, 2012

ማቅ የቤተክህነቱ እዳ ብቻ ሳይሆን የመንግሥትም እዳ ነው!!!

ከዚህ በፊት አንድ አንጋፋ ፖለቲከኛ፣ ማኅበረ ቅዱሳን የሚባለው ድርጅትየቤተ ክህነቱ እዳ ነውበማለታቸው በማቅ መንደር አቧራው ጨሰ ማሰኘቱ  አይዘነጋም። ቹ ጠቅላይ ሚኒስትርም “ማቅ፣ሰለፊያ መሰል ማኅበር ነው” በማለታቸውም ብዙ ጊዜ የማኅበሩ ስውር ልሳኖች ወይም አፍቃሬ ማቅ እንደሆኑ ከሚታሙት የሀገር ቤት  መጽሔቶችና ጋዜጦች አንስቶ እስከ የመረጃ መረብ ድረ ገጾች ድረስ ማቅ እንዴት ተነክቶ? የሚል ጩኸት በአንድነት አስተጋብተው ነበር።  የማኅበሩ የጡት አባት የሆነው የሜሪላንዱ ሰውዬ ደግሞ እንባ ቀረሽ ጽሑፍ በማቅረብ የማኅበሩን ቅዱስ መሆን በመለፈፍ ለማሳመን ብዙ መጣሩን እናስታውሳለን። ማኅበሩ ያሰማራቸውና  በፍቅሩ የወደቁለት የጋሪ ፈረስ የመጦመሪያ ድረ ገጾችም ስለማኅበሩ ቅድስና በተጠራው  የምስክርነት ለቅሶ ላይ የቻሉትን ያህል የሀዘን እንባ ጽሁፍ በማቅረብ ትብብራቸውን አሳይተዋል። ማኅበሩ ከሰፈረበት የአሸባሪነት የመንግሥት /Black list/ ጥቁር መዝገብ ላይ ባያሰርዘውም ጊዜ ለመግዛትና መንግሥት ሊያፈርሰን ነው ከሚለው ፍርሃት ለጊዜውም ቢሆን መጽናኛ ሆኗቸው ማለፉ አይዘነጋም። የማቅ አልቃሾችን የአዞ እንባ ጽሑፍ ተከትሎ የማኅበሩን ዐመል በደንብ የመረመሩ  ጸሐፊያንምማኅበረ ቅዱሳን የቤተ ክህነቱ እዳበሚል ርእስ መጽሐፍ አሳትመው  ማኅበሩ ቅዱስ እንዳልሆነና በቅዱሳን ሽፋን ተሰባስቦ  የራሱን አጀንዳ  የሚያራምድ የእውነት ሁሉ እንቅፋት መሆኑን የሚያስረዳ  ጽሁፍ ለንባብ ማብቃት
 የተናጋሪ ፖለቲከኞችንም ይሁን የጸሐፊያኑን ማንነት ትተን በማቅ ዙሪያ የሚነገሩትን የተነገሩትን ልብ ብለን ብንመለከት ከማኅበሩ ጠባይ አንጻር የምንደርስባቸው እውነታዎች መኖራቸው  በምንም መልኩ የሚስተባበሉ አይደሉም።  ለመሆኑ ማኅበረ ቅዱሳን ማነው?   የቅዱሳን ማኅበር የሚባለው የማኅበሩ አባላት ራሳቸው ናቸው ወይስ ስማቸው ያልተገለጸ ቅዱሳን? ከማኅበሩ ጠባያት አንጻር ብዙ ማለት የሚቻል ቢሆንም ስለ ቅድስናው ትተን ከዓላማው አንጻር ጥቂት አመክንዮታዊ ነጥቦችን እናንሳ።

የገጽታ ግንባታውን በቤተ ክርስቲያኒቱ መዋቅር ውስጥ መዘርጋት፣

1/ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከመንበረ  ፓትርያርክ አንስቶ እስከ አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን ድረስ ወጥ የሆነ መዋቅር እንዳላት ይታወቃል። ማኅበረ  ቅዱሳን ደግሞ በዚህ መዋቅር ውስጥ የታቀፈ ነገር ግን ራሱን የቻለ አንድ ተቋም ነው። ከመንበረ ፓትርያርክ ጀምሮ እስከ አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን ድረስ ራሱን አክሎ፣ ቤተ ክርስቲያኒቱን መስሎ ተደራጅቷል። የቤተ ክርስቲያኒቱን አባላት ለራሱ አባልነት ይመለምላል። ዐውደ ምሕረቷን ይጠቀማል። ከማእከል ወደ አጥቢያ የሚወርዱ መመሪያዎችን ያስተላልፋል፣ በማኅበሩ ንድፈ ሃሳብ /Theory/ የተጠመቁ ምልምል መምህራንን በስብከተ ወንጌል ስም ይልካል። በየአድባራቱ፣ ዩኒቨርሲቲውና ኮሌጆቹ ውስጥ የማኅበሩ ስም በወጣቱ ልብ ውስጥ እንዲሰርጽ አጥብቆ ይሰራል። ይህም ማኅበሩ የቤተ ክርስቲያኒቱ ተጠሪና ጠበቃ እንደሆነ ለማሳየት የሚከወን የመንፈሳዊነት የስም ግንባታ ሥራ መሆኑ ነው።

በቤተ ክርስቲያኒቱ ባለ ሥልጣናት መጠቀም፣

2/ ራሱን አክሎና ቤተ ክርስቲያኒቱን መስሎ ለመንቀሳቀስ ይችል ዘንድ የጳጳሳቱን ማንነት ለራሱ ጥቅም በመጠምዘዝ፣ በመደለል፣እንዲሁም ቅዱስ በመምሰልና እውነተኛ እንደሆነ በውስጣቸው የማንነት ምስሉን በማስቀመጥ  ተቀባይነት እንዲኖረው የውዴታ መልካም ፈቃዳቸውን ይቀበላል። የማይቀበሉት ካሉ ደግሞ ራሱም ይሁን በአገልጋዮቹ በኩል ይዘምትባቸዋል።  በየደረሱበት ሁሉ ይቃወማቸዋል።/እንደ አቡነ ፋኑኤል ያሉትን፣ ከደቡበ ኢትዮጵያ ጀምሮ  እስከ አሜሪካ  እንዴት እግር በእግር እየተከታተለ ሲዋጋቸው መቆየቱን ልብ በሉ!!/     
በሚቀበሉት ጳጳሳትና የሀገረ ስብከቱ ሥራ አስኪያጆች  የተነሳ ማኅበሩ ቤተ ክርስቲያኒቱ ባለችበት ሁሉ ህልው ሆኖ ይንቀሳቀሳል።

የገንዘብ አቅሙን ማሳደግ፣

3/ “ገንዘብ ካለህ በሰማይ መንገድ አለ” በሚለው ብሂለ አበውና / GYM fitness makes you healthy man but  money GYM makes you powerful/  በሚለው ብሂለ  ፈረንጅ እየታገዘ የገንዘብ አቅሙን ለማዳበርና ፈርጣማ ክንድ እንዲኖረው ያለመታከት በመስራት ላይ ተጠምዶ የሚገኝ ሲሆን ይህንንም በመጻሕፍት፣ በመጽሔቶችና በሲዲ ሽያጭ  እንዲሁም ሆቴሎችን በመክፈት፣ የንግድ ተቋማትን በመትከል፣ ህንጻ በመገንባት ላይ መሰማራቱ የ20 ዓመታት እውነታ  ነው። በዚህም የሚሊዮኖች ብር ባለሃብት ለመሆን አስችሎታል። ይህ ከበጎ አድራጊዎችና ከአባላት መዋጮ የሚያግበሰብሰውን ሳይጨምር ነው። ባለሃብት መሆን ክፋት ባይኖርውም የሰንበት ተማሪዎች ማኅበር ነኝ የሚል ማኅበር በዚህ ሁሉ የንግድ ዘርፍ ውስጥ መሰማራቱ ለስውር ዓላማው መሳካት የገንዘብን አስፈላጊነት ከማመን የተነሳ ካልሆነ በስተቀር እወክለዋለሁ ከሚለው ስም አንጻር የቀደሙት ቅዱሳን  በኢንቨስትመንት ላይ ተሰማርተው ነበር የሚል ጽሁፍ እስካሁን ቤተ ክርስቲያኒቱ አላቆየችንም።

Friday, December 21, 2012

ቤተ ክርስቲያኒቱ የወንበዴዎች ዋሻ፣ ንስሐ የማይገቡ ሌቦች መሸሺያ ሆናለች!!


የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን ሰይጣን እንደ ስንዴ  ሊያበጥራት እግዚአብሔርን የለመነ ይመስላል። ልክ የክርስቶስን ደቀ መዛሙርት በጭንቅ ይፈትናቸው ዘንድ እንደለመነው ማለት ነው።

ጌታም፦ ስምዖን ስምዖን ሆይ፥ እነሆ፥ ሰይጣን እንደ ስንዴ ሊያበጥራችሁ ለመነሉቃ 22  እንዳለው።

ከዚህ ፈተና ቤተ ክርስቲያኒቱ ትወጣ ዘንድ ወደ እግዚአብሔር አጥብቆ የሚጸልይ ኤልያሳዊ ማንነት  ያለው አንድም ሰው ጠፍቷል። ገዳማቱን የዐመጻ ሰዎች ሞልተውበታል። ዋልድባን በመሳሰሉ ትላልቅ ገዳማት ሳይቀር ቀጣፊዎች እርስ በእርስ በመነቃቀፍና  የሀሰት ስም በመለጣጠፍ፣ ስለሃይማኖት ልዩነት በማውራትና በማስወራት የሰይጣንን አገልግሎት በተገቢው እየፈጸሙ መገኘታቸው  በጸሎታቸው እንኳን ለዓለሙ ሊተርፉ የራሳቸውን ይዞታ ከስኳር ልማት ለማስጠበቅ የማኅበረ ቅዱሳን የአሜሪካ የተቃውሞ ሰልፍ አስፈልጓቸዋል። አብዛኛዎቹ ገዳማትም የመርበብተ ሰሎሞን፣ የመድፍነ ጸር፣ የዐቃቤ ርእስና የገድላ ገድል መፈልፈያዎች ከመሆን አልፈው የሀገሪቱን ችግር ማቃለል የሚችል የጸሎት መልስ የሚገኝባቸው ናቸው ብሎ መጠበቁ ከቀረ ዓመታት አልፈዋል። ደብረ ሊባኖስን ያየ ዓለም እንዴት ሰነበትሽ? ማለቱ እንደማይቀር  ጥርጥር የለንም።  ያላየም ሄዶ በማየት እውነታውን ሊያረጋግጥ ይችላል።

አዲስ አበባ ላይ ማጅራት መቺዎችና ኪስ አውላቂዎች ንስሐ ሳይገቡ አስተዳዳሪዎች፣ጸሐፊዎችና ገንዘብ ያዥዎች ሆነው አብያተ ክርስቲያናቱ የደም እንባ እያለቀሱ ይገኛሉ። ሰሞኑን በልደታ ቤተ ክርስቲያን በመቶ ሺዎች የሚቆጠር ብር ሲዘርፉ የተደረሰባቸው የቢሮ ሠራተኞች ተጠቃሾች ናቸው። ቤሳ ቤስቲን የሌላቸው ሹመኞች ሚሊየነሮች ሆነዋል። ኑሮ በከበደበት ሀገር የቤተ ክህነቱ ሰዎች ቱጃሮች ለመሆን መቻላቸው ያስገርማል። ለሌቦቹ ካህናት ቤት መገንባትና መኪና መግዛት ቀላል ነገር ነው። እንደ እነ ቄስ ኃይሌ ዓይነቶቹ ዓይን አውጣዎች ደግሞ የሕዝብ ማመላለሻ መኪና ወደ መግዛት ተሸጋግረዋል። በብሔረ ጽጌ /ማርያም ቤተ ክርስቲያን የራያ ሰዎች መፈልፈያ ያደረገ ዘረኛ መሆኑም አንዱ የአሳዛኝ  ግብሩ ማሳያ ነው። እነ ኃይለ መለኮት በጎፋ ገብርኤል የኪስ ማደለቢያ ኢንቨስትመንት ከፍተው ያጋብሳሉ። የሰዋስወ ብርሃኑ ቤተ ክርስቲያን  አስተዳዳሪ ደግሞ ከእነ መሐመድ ጋር በድለላ ሥራ ተሰማርቶ ለቤተ ክርስቲያን አገልግሎት ጊዜ የለሽ ሆኗል።

   እነ ተክለማርያም፣ ነአኩቶ ለአብ፣እነ እዝራ  ኧረ  ስንቱ ተቆጥሮ!!!  አብዱልቃድርና አሕመድም በስመ /ማርያም  ተሸሽጎ የማይጠፋ የሚመስለው ጭካኔ የተሞላበቱ ዘረፋና ዘረኝቱ ሲታይ ነው። ግራኝ አህመድስ ከዚህ ወዲያ ምን  አደረገ?  የአብያተ ክርስቲያኒቱ ዘረፋና ዘረኝነቱ ከመቼውም ጊዜ በላይ  መግነኑ ያንን ያሳያል።  ቤተ ክርስቲያኒቱ መሪና ተመሪ የሌላት የባለጊዜዎች መፈንጫ ሆናለች። በግብራቸው  እነ አቡነ ኢብራሂም፣ እነ አቡነ ኢሊያስ፣እነ አቡነ ጅብሪል፣እነ አቡነ ጊርጊስ  የሚመሯት፣ እነ የሃዘን ልብሱ (ማቅ) የሚያሾሯት ቤተ ክርስቲያን የወንበዴዎች ዋሻ፣ ንስሐ የማይገቡ ሌቦች መሸሸጊያ መሆኗ እውነት ነው። ጳጳሳቱ ሚሊየነሮችና G+ ባለህንጻዎች፣ ማኅበራቱ የሚሸጡባትና የሚሸቅጡባት የእርግብ ለዋጮች ሜዳ ካደረጓት ውሎ አድሯል።  በዚህም መሃከል ግን ብዙዎች ምስኪናን ቀሳውስትና  ዲያቆናት የበይ ተመልካች ሆነው በኑሮ እሳት ይጠበሳሉ።

Thursday, December 20, 2012

ጳጳሳቱንም ሆነ መንግሥትን በፓትርያርክ ምርጫ ላይ ስህተት እንዳይፈጽሙ እናሳሰባለን!

አባ ጎርጎርዮስ ፓትርያርክ ለመሆን የጓጓ ይመስላል።
Ø መንግሥትም እሱን የፈለገ ቢመስልም ምርጫው ከምራጭ ላይ የወደቀ ነው!!
Ø አባ ጎርጎርዮስ ምርጫው በእጣ ሳይሆን በካርድ ይሁን ሲል ውሏል። ለምን ይሆን?
Ø የውጭ ዜግነት ያላቸው ጳጳሳት ከጫወታው ውጪ ስለተደረጉ ሸክሙ ቀሎላቸው ይሆን?
ከአሜሪካው ሲኖዶስ ጋር ሲደረግ የቆየውና እርቅ ይሁን የሥልጣን ሼር /አክሲዮን/ መሆኑ ያልታወቀው ጉዳይ ያበቃለት ይመስላል። ይህም የምርጫ ህግና አስመራጭ በመምረጥ የሀገር ቤቱ ሲኖዶስ  ስለምርጫው አይቀሬነት እቅጩን ተናግሯል። ሥልጣን፣ ሥልጣን ከሚል ጩኽት ባሻገር መንፈሳዊ እርቅ ፈጽሞ የማይታይበትን ጉዞ በወጪና በኪሳራ ከማጀብ ይልቅ አዲስ ምርጫ አድርጎ  ሁለቱም ወገን ቁርጣቸውን አውቀው በያዙት ተግባር ላይ ትኩረት እንዲሰጡ ማድረጉ የተሻለ ነው የሚል እምነት አለን። ዋናው ነገር የክርስቶስን ቤተ ክርስቲያን፣ ክርስቶስ እንደሚወደው አድርጎ ከመምራቱ ላይ እንደነበር ያኔም ይሁን ዛሬ ሁላችንም ችግሩን ስለምናውቀው ስለ ሥልጣን ሼር በመጨቃጨቅ ጊዜ ማጥፋት የለብንም። ሁሉም ባለበት የሐዋርያነትን ሥራ ይሥራ!!!
ይልቅስ አፋችንን ከፍተን ውጪ ውጪውን ስናማትር ብልጦች ተሽቀዳድመው ለቀም ሳያደርጉ የሀገር ቤቱን ሹመት ነቅተን መከታተሉ ጠቃሚ ነው።
የምርጫ ህጉ ከጸደቀ በኋላ ምርጫው በእጣ እንዳይሆንና እንደ ቀበሌ ሊቀመንበር ምርጫ በካርድ እንዲሆን ብዙ እንደተከራከረ የሚነገርለት አባ ጎርጎርዮስ፣ የውጭ ዜግነት ያላቸውን በህግ ሽፋን ለምርጫ እንዳይቀርቡ ካስወገደ በኋላ ራሱን ለፓትርያርክነት ማዘጋጀቱን ይነገራል። ላለፉት 20 ዓመታት በምሥራቅ ሸዋ / ስብከት ተቀምጦ ምንም ዓይነት የልማት እንቅስቃሴ ሳያሳይ ይህችን ቀን ሲጠባበቅ የቆየው ጳጳስ፣ ዛሬ ፓትርያርክ ለመሆን ሲሯሯጥ እጅግ ያስገርማል። ከዝዋይ ገዳም የአትክልት ሽያጭ በሚሊዮኖች የሚቆጠር ብር እንደሰበሰበ የውስጥ አዋቂ መረጃዎቻችን  ከመጠቆማቸውም  ከዚያም ባሻገር በጆሮ ለመስማት በሚቀፍ ግብር ላይ የሚጠረጠር ሰው ዓይኑን በጨው ታጥቦ ቢቀርብ ቤተክርስቲያን እንዲህ ዓይነቱን ፓትርያርክ አድርጋ ልትሸከም መዘጋጀት አይገባትም። የውስጥ ጉዳችንን ለማን እንነግራለን ብለው እንጂ ይህንን መጥፎ ግብሩን ጳጳሳትም ሳይቀሩ ያውቁታል። መንግሥትም ቢሆን በህዝቡ ዘንድ የጠራ ስምና ግብር የሌለውን እንደዚህ ዓይነቱን ሰው ወደ ሥልጣን እንዲመጣ በማድረግ በራሱ ላይ እሳት ሲያነድ መኖር የለበትም እንላለን።  መንግሥት ለዚህ ሰው ውስጥ ውስጡን ድጋፍ ለማድረግ የወደደው በምን መለኪያ ይሆን?
የውጭ ዜግነት ያላቸው ጳጳሳት በምርጫ የመወዳደር ፋይል በምርጫ ህጉ ተዘግቶ ወደ መዝገብ ቤት ተመልሷል። በዚያ ላይ ምርጫው በእጣ ሆኖ እግዚአብሔር የወደደው ይሁን እንዳንል እነ አባ ጎርጎርዮስ በካርድ ሽፋን ሥልጣን እጃችው ሊያስገቡ እጣ የሚባል ነገር መነሳት የለበትም በማለት መጽሐፍ ቅዱሳዊውን የምርጫ ሥርዓትን ሲቃወሙ ይገኛሉ።