Thursday, May 31, 2012

ማኅበረ ቅዱሳን እንዲህም ነበር! በቀሲስ መልአኩ

ቀሲስ መልአኩ ባወቀ  «ስውሩ አደጋ» ከሚለው መጽሐፍ  ስለ «ማኅበረ ቅዱሳን እና ሃይማኖተ አበው » ከጻፉት የተወሰደ።
 ተሐድሶ ምንድነው ?
በአሁኑ ወቅት የኢትዮጵያን ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ አብያተ ክርስቲያናትን በሰፊው እያነጋገረ ያለው ነገር ቢኖር "ተሐድሶ " የሚለው ቃል ነው ቃሉ እንዲህ  እንደ አሁኑ ፕሮቴስታንታዊ ለሆነ አስተሳሰብ ከመዋሉና አከራካሪ ከመሆኑ በፊት በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ከሚጠቅሱት ታላላቅ የነገረ መለኮት ቃላት አንዱ ነውንስሐንና ውስጣዊ የሆነ የሕይወት ለውጥን፤ ወደ እግዚአብሔር መመለስን የሚያመለክት ነውበሌላ በኩል ደግሞ ሲኖዶሳዊ የሆነ ለውጥን (መሻሻልን ) ሊያመልክት ይችላል። ለምሳሌ በቅዱስ ፓትርያርኩና በብጹዓን ሊቃነ ጳጳሳት ታስቦበትና ተመክሮበት ለቤተ ክርስቲያን ዕድገት ይረዳሉ የሚባሉ መሻሻሎችን፤ ለውጦችንና አዳዲስ ተቋሞችን ሁሉ ይመለከታል።  ከዚህም ታላቁና ቤተክርቲያንን በአስቸጋሪ መከራ ውስጥ መከታ ሆኖ እንድታልፍ ያደረጋት የሰበካ ጉባኤ መቋቋምና የቃለ ዓዋዲ ድንጋጌ ነው :: ይህ ድንጋጌ ብዙዎች እንደሚያስቡት የሰዎች የአስተሳሰብ ፈሊጥ ሳይሆን የሲኖዶስ ቀኖናዊ ውሳኔ ነው።  አሁን ግን "ተሐድሶ " የሚለውን ቃል ፕሮቴስታንቱ ዓለም ብቻ ሳይሆን የፖሊቲካው ዓለምም እየተጠቀመበት አስቸጋሪ ቃል ሆናል።
«ተሐድሶ በኦርቶዶክሱ ዓለም»
ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን እምነትን የምትጠብቅ እንጂ እምነትን በዘፈቀደ ወይም ባሰኛት መንገድ የምትቀያየር ስላይደለች ዛሬ ኣንዳንዶች ከዚህ ቤተክርስቲያን የወጡ ሰዎች እንደሚናገሩት «ተሐድሶ» የሚለውን ቃል እምነትን በተመለከተ አታውለውምሃይማኖት ምን ዓይነት መልክ እንዳላት ሐዋርያው ይሁዳ በመልእክቱ ጽፎልናል "አንድ ጊዜ ፈጽሞ ለቅዱሳን የተሰጠች በማለት " ስለሆነም አትበረዝም፤ አትከለስም ወይም ብልየት እርጅና አያገኛትም። በሌላ በኩል ግን የክርስቲያን ሕይወት ዕለትለት ይታደሳልውስጣዊ የሆነውን የሕይወት ተሐድሶ የሚያገኘውን በንስሀ በጾም፤ በጸሎት ነው :: ይህን በተመለከተም በብዙ ቦታዎች ቅዱሳት መጻሕፍት ይናገራ።
በሌላ በኩል ደግሞ አስተዳደራዊ የአሠራር ለውጦችና አልፎ አልፎ ቀኖናዊ ለውጦች ይኖራሉ :: እነዚህም ቢሆኑ የሚከናወኑት በብጹዓን ሊቃነ ጳጳሳት ስለሆነ ለውጡ ሲኖዶሳዊ ነው እንጂ የአመጽ ወይም የጥቂት ግለሰቦች አይደለም።
ይህም በኦርቶዶክሱ ዓለም የተለመደ እንደሆነ በቤተ ክርስቲያንችን የከፍተኛ መንፈሳዊ ትምህርት ቤቶች ለብዙ ዓመታት በማስተማር ሥራ ላይ የተሰማሩትና አያሌ ደቀ መዛሙርትን ያፈሩት ሉሌ መላኩ "የቤተ ክድርስቲያን ታሪክ " በሚለው መጽሐፋቸው በግብጽ ቤተ ክርስቲያን የነበረውን ሲኖዶሳዊ ተሐድሶ ሲገልጡ ,,,«በኮፕቶች (በግብጾች ) ዘንድ የተሐድሶ አባት በመባል የሚታወቀው ቄርሎስ አራተኛ (1854-1861) የእስክንድርያ ቤተክርስቲያን ፓትርያርክ ነው :: ዋነኛ ዓላማ አድርጎ የተነሣው ትምህርትን ማስፋፋት (የማሰራጨት ) ሰለነበር በግብጽ ካህናት ዘንድ ሰፍኖ የነበረውን የትምህርት ጉድለት፤ ዝቅተኛነትን ለማሻሻል ካህናት ተግተው እንዲማሩ አደረገከፍተኛ መንፈሳዊ ትምህርት ቤትም ከፍቶ ዓለማዊና መንፈሳዊ ዕውቀት የነበራቸውን በማሰማራት መጻሕፍትን በገፍ በማቅረብ ካህናትና ምእምናን የቅብጥ (ኮፕት ) የዐረብኛ፤ የእንግሊዝኛ፤ የፈረንሳይኛ፤ የኢጣልያንኛ፤ የቱርክ .. ወዘተ ቋንቋዎችና የተለያዩ መንፈሳዊ ትምህርቶችን እንዲማሩ አደረገ »ይሉናል።
የገሞራው ጋዜጣ ጽሑፍ እና የሃይማኖተ አበው መዘጋት "
እንግዲህ በዚህ ወቅት ነው ማን እንደጻፈው የማይታወቅ ጽሑፍ "ገሞራው " በሚባልና አሁን ከሕትመት ውጭ በሆነ የግል ጋዜጣ ላይ የወጣው።  ጽሑፉ ሰፊ የሆነና የተሐድሶ ማኅበር እንዴት እንደሚንቀሳቀስና ዓላማውም ምን እንደሆነ የሚገልጥ ነበር።  ከሁሉ የሚገርመው ግን ጽሑፉ ሰለተሐድሶ ሆኖ ሳለ ከጽሑፉ ጋር አብሮ የወጣው ግን በጎፋ ገብርኤል ለረጅም ጊዜ ያገለገሉና  የኢትዮጵያዊው ስማእት የብጹእ ወቅዱስ አቡነ ቴዎፍሎስ ልጅ የሆኑ መነኩሴና እርሳቸው የሚያስተምሩዋቸው የሃይማኖተ አበው ተማሪዎችን የያዘ ፎቶ ነበር እኚህ አባት ጋዜጣው በወጣ ማግሥት ያለ ምንም ጥያቄ ከሚያገለግሉበት ደብር እንዲወገዱ ተደረገእምነት፤ ክህደታቸውን የጠየቀ፤ አጥፍተውም  ከሆነ በንስሐ እንዲመለሱ የመከረ ማንም አልነበረምማኅበረ ቅዱሳንም አባ እገሌ መናፍቅ ናቸው እያለ ይጽፍ ጀመረይህ ሁኔታ ቢያሳዝናቸውና  አቤት የሚሉበት ቦታ ቢያጡ ጉዳዩን ወደ ፍርድ ቤት ወስደው፤ ከብዙ እንግልት በኋላ ወደ ቤተክርስቲያናቸው እንዲመለሱ ተፈርዶላቸዋልዛሬ በቤተክርስቲያኒቱ ውስጥ በታላቅ የሥልጣን ደረጃ ላይ ናቸውየጋዜጣው ጽሑፍ መደምደሚያ ሃይማኖተ አበው የኢትዮጵያ ተማሪዎች ማኅበር የተሐድሶ ድርጅት አካል እንደሆነ የሚናገር ነበ።

Wednesday, May 30, 2012

ከዓመታትም በኋላ ምንም መሻሻል ስለሌለው ወንጀለኛው ማኅበር እንዲህም ተዘግቦ ነበር!


ፊያሜታጋዜጣ  ልዩ ዕትም ነሐሴ 29 ቀን 1990
ከሲኖዶስ ወደገዳም የተላኩ መምህራን በመቋሚያና በድንጋይ ተደበደቡ!

በሐምሌ ወር 1990 በተደረገው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ጠቅላላ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ወደ ደብረ ሊባኖስ ገዳም ሄደው የነሐሴን ወር እንዲያሳልፉ የተወሰነባቸው፣ ዲያቆን ግርማ በቀለ፣ የሰዋሰው ብርሃን /ጳውሎስ ከፍተኛ መንፈሳዊ /ቤት የሐዲስ ኪዳን መምህርና ዲያቆን ፅጌ ስጦታው የጐፋ /ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ሰባኬ ወንጌል፣ በሄዱበት ገዳም የድንጋይ ናዳ እንደወረደባቸው ተገለፀ።

ድርጊቱ ለኦርቶዶክስ ተዋህዶ ተከታይ በሙሉ የሚያሳፍር፣ ለማመንም የሚያስቸግር ነው። ሆኖም የተፈፀመው አሳፋሪ ተግባር ግን እውነት ነው። ከቤተ ክህነቱ የደረሱን ተማኝ ምንጮች እንዳረጋገጡት፣ ቀደም ሲል ማህበረ ቅዱሳን በተባለው ክፍል በቀረበባቸው ሃይማኖታዊ ክስ መነሻነት ስለ ሁለቱ መምህራንና ተባባሪ የተባሉትን ተጨማሪ መምህራን አክሎ የቤተ ክህነቱ የሊቃውንት ጉባኤ የቀረበውን ክስ በማጣራት ጉዳዩን ወደ ቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ አቅርቦ ከታየ በኋላ ክሱን ፍሬ ቢስ በማድረግ ሁለቱ መምህራን በደብረ ሊባኖስ በሚገኙት የሐዲስ የትርጓሜ መምህር በመሄድ ለአንድ ወር እንዲቆዩ ቢወሰንም በሲኖዶሱ ትዕዛዝ ወደ ደብረ ሊባኖስ ያመሩትን መምህራን ቀድሞ የጠበቃቸው ነገር ቢኖር ግን የዱላ እና የድንጋይ መዓት መሆኑን እነዚህ ምንጮች ገልፀዋል።

በማህበረ ቅዱሳን፣ መናፍቅና እምነትን የሚሸረሽሩ ከተባሉት የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ተከታዮች መካከል፣ ከዲያቆን ግርማ በቀለ እና ዲያቆን ፅጌ ስጦታ ሌላ አባ ገሪማ ተስፋዬ፣ አባ ቀፀላ፣ ዲያቆን ልዑለ ቃል እና ዲያቆን ኤልያስ የተባሉ የሚገኙበት ሲሆን፣ የሊቃውንት ጉባኤውም ሆነ የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ ተከሳሾቹን በፍቅር ተቀብሎ፣ ጥቃቅን ነገሮች ቢኖሩ እንኳ በኃላፊነቱ መክሮና ዘክሮ ቤተ ክርስቲያናቸውን እንዲያገለግሉ መመሪያ ሰጥቶ ሲያሰናብት፣ በኃላፊነት ቁንጮ ከተቀመጠው ቅዱስ ሲኖዶስና የሊቃውንት ጉባኤ ይልቅ ለሃይማኖት ተቆርቋሪ በመምሰል እየተከታተሉ ጦርነት መክፈቱ ግን መሰረቱም በቀልና ጥላቻ እንጂ የሃይማኖት ቅንዓት አለመሆኑን ከድርጊታቸው ማወቅ ተችሏል ሲሉ ምንጮቹ ከሳሾቹን ይኰንኗቸዋል።

ማህበረ ቅዱሳን እና የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ተሃድሶ ያስፈልጋታል የሚሉ ተሃድሶዎች!


ጽሁፍ በተስፋ አዲስ (ኢትዮ ሰን ድረ ገጽ በ 2003 ዓ/ም እንደተዘገበው)
ክፍል አንድ

ተሐድሶዎች እነማን ናቸው?

ብዙ ጊዜ ቤተ ክርስቲያን ስሄድ የስብከት ካሴት ሳዳምጥ፤ የተለያዩ ሥነ ጽሑፎችን ሳነብ ፡ተሃድሶዎች ተሐድሶዎች፡ የሚል ጩኸት እሰማለሁ። በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ሥር የተቋቋመው ማህበረ ቅዱሳን የሚባለው ድርጅት አባላቱም ሆኑ አመራሮቹ ስለተሃድሶዎች በስብከታቸው እና በጽሑፋቸው ሁሉ በቀጥታም ሆነ በተዛዋዋሪ ሳያነሱ አያልፉም።

እኔም ተሐድሶዎችን ለማወቅ ብዙ ጥረት አድርጌአለሁ። ምን ዓይነት አቋም እንዳልቸውና የት እንደሚገኙ፤ አላማቸው ምን እንደሆነ ለኢትዮጵያ ሕዝብ ማሳወቅ ፈለግሁ። እነርሱ ግን ተሃድሶ የሚለውን  ስም አይቀበሉትም።  እኔ ተሃድሶዎች ስል አንባቢ በሚገባው ቋንቋ ለመጠቀም እንዳሰብሁ ይረዳልኝ። ማህበረ ቅዱሳን የሚባለው ማህበርም ከተሐድሶዎች ጋር ያለውን ቅራኔ ለማቅረብ እሞክራለሁ። አንባቢ የራሱን ተቃውሞም ሆነ ድጋፍ እንዲሠጥ አንዳችም ሳልቀንስ እና ሳልጨምር ትክክለኛውን መረጃ ለማቅረብ እሞክራለሁ። መነሻየ ግን ከማህበረ ቅዱሳን እና ከተሐድሶዎች ሥነ ጽሑፎች ነው። የሁለቱንም ቡድን እንቅሥቃሴ በተከታታይ አቀርባለሁ መልካም ንባብ።

ተሀድሶ ማለት ይላሉ ቤተ ክርስቲያን መታደስ አለባት የሚሉ ወገኖች ማደስ፣ መጠገን፣ ማጽዳት፣ ማለት ነው ይላሉ።ለምሳሌ ቤት ከተሠራ በኋላ ሳይታደስ ብዙ ከቆየ ከጥቂት ጊዜ በኋላ ሊፈርስ ይችላል ስለዚህ ከመፍረሱ በፊት የሚደርግለት እንክብካቤ ቤቱን ያጸናዋል። እንደሸረሪት ድር፤ የጢስ ጠቀርሻ ያሉ ነገሮችም ከቤቱ ላይ ሊጠረጉ ይገባል። ማደስ ማለት ማፍረስ አይደለም በቤቱ ውስጥ ያለውን ቆሻሻ፤ ማስወገድ እና በፈረሰው በኩል መጠገን ነው በሌላ አነጋገር መሠረቱን ሳይነኩ እና ሳያናውጡ ጥንታዊነቱን እንደያዘ ቤቱን ማሳመር ማለት ነው።የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያንም ብዙ ዘመን ከመኖሯ የተነሣ ብዙ ስሕተቶች ይገኙባታልና መጽዳት አላባት፤ ባህሉን ከሃይማኖቱ፤ ውሸቱን ከእውነቱ፤ ክፉውን ከደጉ መለየት አለባት የሚል ራእይ ያላቸውና ለዚህ ሌት ተቀን ያለ እረፍት የሚሠሩ ናቸው።

የሚገኙት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ነው ጳጳሳት፤ ቀሳውስት፤ ዲያቆናት፤ መምህራን፤ የድጓ፤ የቅኔ የቅዳሴ መምህራን የሰንበት ተማሪዎች፤ እንዲሁም ምእመናን ሁሉ ያሉበት የአስተሳሰብ ኃይል ነው። የታወቀ ማህበር ግን የላቸውም። አንዳንዶች ማህበር መሥርተዋል ። ኑራቸው እና ሥራቸው በዚያው በቤተ ክርስቲያኒቱ ውስጥ ሲሆን በተለያየ ቦታ /ቤት እና በርካታ ማሰልጠኛዎች አሏቸው። በርካታ መነኮሳት እና ሰባኪዎች በነዚህ ቦታዎች ይሰለጥናሉ። ይህን ሁሉ እንቅሥቃሴ የሚያደርጉት ግን ቤተ ክህነቱ ሳይውቅ ነው። ቀሳውስቱ ስልጠናውን ከወሰዱ በኋላ በየቤተክርስቲያናቸው ሌሎች ቀሳውስት በመመልመል ያሰልጥናሉ። ከጳጳሳትም ውስጥ ለዚሁ ሥራ የሚውል በግላቸው ከፍተኛ እርዳታ ያደርጋሉ። ተሐድሶዎች ቤተ ክርስቲያኒቱ ውስጥ ቁልፍ ቦታና ስልጣን አላቸው። በተለይ በአሁኑ ሰዓት በየአብያተ ክርስቲያናቱ  ሚሊዮኖች በብዛት ይገኛሉ። በገጠር አጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት እና በገዳማት ሁሉ አሉ። ደሞዛቸውን የሚያገኙት ከዚያው ከቤተ ክርስቲያኒቱ ነው። ግን ከሌሎች የእምነት ድርጅቶችም እርዳታ ያገኛሉ ተብለው ይታማሉ። ተሐድሶዎች  እንደቀደምት ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ አማኞች እንጂ እራሳቸውን ተሃድሶ ብለው አይጠሩም።  ስማቸው በሥራቸው ምክንያት ከሚጠሏቸው ወገኖች የተሰጣቸው ነው። በቤተ ክርስቲያን ባሕላዊ ትምህርት ጥልቅ የሆነ ዕውቀት ያላቸው ስለሆኑ የቤተ ክርስቲያኒቱን ሁለንተና ደካማ ጎንም ሆነ ጠንካራ ጎን ለይተው የሚያውቁ ሊቃውንት ናቸው። የተሃድሶዎች እንቅሥቃሴ ከባድ እንቅሥቃሴ ነው ምክንያቱም እስከሞት ድረስ የቆረጡ ሲሆኑ ታላቅ ራዕይ ያላቸው ናቸው። በማኅበር መደራጀት ሳይሆን  በግል እያንዳንዱ አውቆ መስራት አለበት ስለሚሉ እዚህ ጋ ወይም እዚያ ጋር ናቸው ያሉት አይባልም። በአጭሩ የሌሉበት ቦታ የለም።
የማኅበረ ቅዱሳን ደጋፊ ነን የሚሉ ጳጳሳት ሳይቀሩ የዚህ ተሐድሶ የሚባለውን እንቅስቃሴ በስውር ይደግፋሉ። አሁን ባለው ሁኔታ ተሐድሶ የሚባሉት ክፍሎችን ከቤተክርስቲያኒቱ ማስወገድ በፍጹም አይቻልም። ከላይ እስከታች በተያያዘ ሰንሰለት የሚሰሩ ናቸው።

Monday, May 28, 2012

እውን “ማኅበረ ቅዱሳን” (ሰለፊያ) እየተዘጋ አይደለምን???

 የጽሁፉ ምንጭ፦ ዓውደ ምሕረት ብሎግ
To read in PDF ( Click Here )
አንዳንድ የዚህ ክፉ ነብሰ በላ የሆነ ድርጅት አመራሮችና አባለት “አባሠረቀንና አቡነ ጳውሎስን ብንገድል መንግስተ ሰማያት መግባታችን አይቀርም እንጸድቃለንም። በዚህ አንጠየቅም” እያሉ ሲያወሩ ስንሰማ ግራ እየገባን ይህ ከምን የመጣ አመለካከት ነው? መጽሐፍ ቅዱስ የማይደግፈውን አስተሳሰብ እንዲህ በድፍረት የሚናገሩት ለምንድን ነው እያልን ለአመታት የቆየን ቢሆንም በስተመጨረሻ ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንዲህ የሚሉት ለምን እንደሆነ በግልጽ ነግረውናል። እኛም ነገሩ ገብቶን ሰው በመግደል ገነት እንደሚወርሱ የሚያምኑ ሰለፊዎች መሆናቸውን አረጋግጠን ከየትኛው መጽሐፍ ይህን ትምህርት እንዳገኙት አውቀናል። ከማቅ ሰዎች ጋር በሀሳብና በአመለካከት ብቻ የተለያየን መሰሎን የነበረ ቢሆንም በምንመራበት መጽሐፍም ቢሆን ልዩነት እንዳለን አውቀናል።
ከዚህ እውነት በመነሳት “ጊዜ ገቢር ለእግዚአብሔር” እንዲሉ በግንቦት ርክበ ካህናት የቅዱስ ሲኖዶስ ስብሰባ የታዩ ክስተቶችን የተመለከተ ትንታኔ መስጠት አስፈላጊ ሆኖ ተገኝቶአል፡፡
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እራሱን በቅዱሳን ስም “ማኅበረ ቅዱሳን” በሚል የሰየመው የፖለቲካ ድርጅት ለአለፉት ሁለት አሥርት አመታት በቅድስት ቤተክርስቲያናችንም ሆነ በሀገራችን ኢትዮጵያ ላይ እያደረሰው ያለውን አሉታዊ ተጽእኖ ሁሉም የኢ/ኦ/ተ/ቤተ ክርስቲያን አገልጋዮችና ሀገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን የሚያውቁት ሐቅ ነው፡፡
ከዚህ በፊት በተደጋጋሚ እንዳስነበብናችሁ ዘርፈ ብዙ ችግሮችን የታቀፈውና በዲያቢሎስ መንፈስ የሚመራው ማቅን ለመሆኑ ማን መሠረተው? እነማንስ ስም ሰጡት የሚለውን እውነታ ስንመለከት ‹‹ማቅ›› የተሀድሶ ኮሚቴ ይባሉ በነበሩ የደርግ ደጋፊ አባላት የተመሠረተ ሲሆን ይኽ የጥፋት መልዕክተኛ ዘር ግንዱ እነኮሎኔል አጥናፉ አባተ ካቋቋሙት ”ጊዜያዊ የተሐድሶ ጉባኤ” ይነሳል። ጊዜያዊ የተሐድሶ ጉባኤ የማኅበረ ቅዱሳን አባቱ መሆኑ ነው። ይኽ አባቱ የቤተ ክርስቲያንን ሥርዓት ለማፍረስ እና በውስጥዋም ሥርዐት አልበኝነት በማንገስ ቤተ ክርስቲያን ደካማ እንድትሆን ለደርግ ያገለገለ ነው። የእኛ ጊዜዋ ማቅ አገልግሎት ሁለት መልክ አለው - የሞተውን ሥርዐት ለመመለስ እና የየግል ጥቅማቸውን ማሳደግ እንዲሁም በሃይማኖት ሽፋን ስውር አላማን ማስፈጸም ነው፡፡

”ከሞኝ ደጅ ሞፈር ይቆረጣል” እንደሚባለው ይኽ ጊዜጣዊ የተሀድሶ ጉባኤ የመንደረተኝነቱን ቂም ለማርካት ሲል ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ቴዎፍሎስን ፓትርያርክዋን በገመድ አሳንቆ ያስገደለ የሠይጣን መልእክተኛ ነው። እንኩዋን የቤተ ክርስቲያኒቱን አደረጃጀት ሊያድስ ቀርቶ የዕሪያ መፈንጫ አድርጓት አረፈው። የያኔው የጊዜያዊ ተሀድሶ ጉባኤ አባላት ግማሹም በሹመት ግማሹም በሞት ሲበታተኑ ያደረገው ቀለማቸውን ለውጠው ”ማኅበረ ቅዱሳን” በሚል ሥያሜ የደርግ ወታደሮችን ሰብስቦ(አዲሱ ማቅ የተመሰረተው በደርግ ወታደሮች አማካኝነት እንደሆነ ማኅበርዋ አትክድም)ወራሹን ማደራጀት ነበር። ቤተ ክርስቲያኒቱን ተጠልሎ የወደቀ ሥርዐት ለማስመለስ ስለነበረ አባቱ የቤተ ክርስቲያኒቱን ጉልላት እየናደ ሲደልቅ ቆይቶ ልጁ ማኅበረ ቅዱሳን ደግሞ እንደሌሊት ሌባ መሠረትዋን እንዲሰረስር ክህነት ሰጥቶ ባረከና አደራጀው።

Sunday, May 27, 2012

ወርቁ እንዴት ደበሰ!(ሰቆ.ኤር. 4÷1)

           የጽሁፉ ምንጭ፤ቤተ ጳውሎስ/.www.betepawlos.com/
  /  ከደጀ ብርሃን፦ ቅዱሱን መጽሐፍ መሠረት አድርጎ ከወዲያም ይሁን ከወዲህ ያሉትንና ራሳቸውን የጽድቅ ሰራተኞች አድርገው የሚቆጥሩ ነገር ግን በዚያ ሥፍራ ተቀምጠው ያልተገኙትን ሁሉ የተመለከተበትን ይህንን ድንቅ ጽሑፍ እንድታነቡት አቅርበናል። /                  
ገና ሻዩን አዝዤ ወደ አፌ ላስጠጋው ስል ከወዲያ ማዶ ለመቆም የምትጣጣረውን መኪና እያየሁ ዓይኔ ተተክሎ ቀረ፡፡ መኪናዋን አላወቅኋትም፡፡ ዓይኔ ግን በእርሷ ላይ ቀረ፡፡ የሾፌሩ በር ተከፍቶ የወጣው ሰው ግን የማውቀው ወንድም ነበረ፡፡ ወዲያው ግን ማወቄ ወደ አለማወቅ ተለወጠ፡፡ እንኳን የእርሱን ህልውና የራሴን ህልውና ያጣሁት መሰለኝ፡፡ እውኑ ሕልም መሰለኝ፡፡ የጨበጥኩት የጉም ስፍር ሆነብኝ፡፡ ሻዩን ሳልቀምሰው አፌ እሬት ሆነብኝ፡፡ አጠገቤ ያሉትን ሰዎች ሁሉ ሕልውናቸውን መቀበል ከበደኝ፡፡ ዓለም ለቅጽበት ውሸት፣ የአሳብ ቤት ሆነችብኝ፡፡ ዓይኔ እዚያች መኪና ላይ የተተከለው የቀጠርኩት ሰው መጣ ብሎ አይደለም፡፡ ራሴን ቀጥሬ ራሴን እየጋበዝኩ ነበር፡፡ ያም ሰው እንደሚያገኘኝ ፍጹም አላሰበም፤ ነገር ግን ቀጠሮው ሞላ፡፡ እንደዚህ ባንገናኝ እመርጥ ነበር፡፡ በዓለም ግን የሆነው እንጂ የመረጡት አይታይም፡፡ ወዳጅ የሆነ ሰው ሊያየውም ላያየውም የሚገባ ሁኔታ ነበር፡፡ ማየቱ ለማጽናናት፣ አለማየቱ ላለመሰበር ነው። የመጣው ትንሽ ኬክ ቢጤ ገዝቶ ሊበላ ነው፡፡
ወደ እኔ መጓዝ ጀመረ፣ ይበልጥ ልቤ ፈራ፡፡ ያላየኝን ሰው ቀድሜ ዓይቼ የአሳብ ፍልሚያ ውስጥ ገባሁ፡፡ ያየ ታጋይ ነው፣ ያላየ ምን አለበት! ይህ ወንድሜ ቁመናው ያማረ፣ አንገቱ የንጉሥ ሕለተ ወርቅ የመሰለ፣ መልኩ የብር እንኮይ፣ አለባበሱ የጥቅምት አበባ፣ ቆፍጣናነቱ የድሮ ወታደር፣ አነጋገሩ በሥልጣን የተሞላ፣ ለሚረግጠው የሚጠነቀቅ፣ ለሚለብሰው የሚጨነቅ፣ በአጠገብ ሲያፍ ሽቶው የሚያውድ ነበር፡፡ መኪናውን የያዘ እንደሆነ እንደ መኪና ሳይሆን ያለ አቅሟ እንደ ጀት ሁኚ እያለ ያስጨንቃታል። እንደ ንጉሥ ሞተረኛ ለራሱ ድምጽ እያሰማ በመኪናው ጥሩምባ አድባሩን እያወከ ይነጉዳል። ብዙም አልናገረውም ነበር፡፡ ምክንያቱም ወደ መሬት ገና አልወረደም ነበርና ስለማንደማመጥ ነው፡፡ ከመፈለጉ የተነሣ ኩሩ፣ ከመወደዱ የተነሣ ውድ ነበር፡፡ ወደ እግዚአብሔር እንዲቀርብ ብዙ ዘመን ነገርኩት፡፡ እኔን ላለማስቀየም ብቻ በትዕግሥት ይሰማኛል፡፡ ነገር ግን እሺታው የውሃ ሽታ ሆኖ ይቀራል፡፡ የአሁኗ ዓለም እንደ እርሱ ያታላለችው ሰው አልነበረም፡፡ እኔም ሰው ነኝና ደክሞኝ ተውኩት። ዛሬ ያየሁት ከብዙ ወራቶች በኋላ ነው፡፡ ያቺ የቡልጋ አልቃሽ ያለችው በጆሮዬ አቃጨለ፡-
      ‹‹ምን ቆንጆ ቢሆኑ ቢረዝሙ እንዳክርማ
               መጠቅለል አይቀርም በነጠላ ሸማ››

ሰባ ስምንት ነፍስ የገደለው ሰው [በላኤ ሰብእ]በጥርኝ ውሃና በማርያም ጥላ ዳነ

ምንጭ፤ አባ ሰላማ ብሎግ፤ Friday, February 24, 2012
እኔ መንገድ እውነት ሕይወትም ነኝ በኔ በቀር ወደ አብ የሚመጣ የለም [መጽሐፍ ቅዱስ ዮሐ 146]
ታምረ ማርያም የተባለው ጉደኛ መጽሐፍ ድንግል ማርያምን ያከበረ የሚመስል ነገር ግን ስድብ እና ክህደት የሞላበት መጽሐፍ መሆኑን ደጋግመን ለማሳየት ሞክረናል። መጽሐፍ ቅዱስ ከተጻፈ 1400 ዓመት በኋላ በኢትዮጵያ ንጉሥ በዘርዓ ያዕቆብ የተደረሰ ሲሆን በወቅቱ የነበሩ የቤተ ክርስቲያናችን ሊቃውንት እና ምእመናን ይህ ልዩ ወንጌል ከሐዋርያት ትምህርት የወጣ ስለሆነ አንቀበለውም በማለታቸው፣ እስከ አንገታቸው በጉድጓድ ተቀብረው በጭንቅላታቸው ላይ የፈረስና የከብት መንጋ እንደተነዳባቸው ምላሳቸውንና አፍንጫቸውን እንደተቆረጡ እራሱ ታምረ ማርያም ይመሰክራል። [ታምር 24 እና 25 ገጽ 112- 121]

ታምረ ማርያምን ቁጭ ብለን በማስተዋል ብንመረምረው መጽሐፍ ቅዱስን ለመቃወም የክርስትናን ትምህርት ለመበረዝ በጠላት ሆን ተብሎ የተቀመመ ይመስላል። አጼ ዘርዓ ያዕቆብ እስራኤላዊ ነኝ ስለሚል ምን አልባት አይሁዶች መሲሐዊ እምነታችንን ለማጠፋት የፈጸሙት ሴራ ይሆን? ብለን እንድንጠይቅ ያደርገናል። ዘራ ያዕቆብ አይሁዳዊ ነኝ እያለ ይመካ ነበር፤ ከዚያም አልፎ የይሁዳ ነገድ ነኝ ይል ነበር። አባ እስጢፋኖስ ግን ኢትዮጵያዊ ነህ አትዋሽ ከአይሁዳዊነት ይልቅ ክርስቲያን መሆን ይበልጣልና በዚህ አትመካ በማለት እንደተከራከረው ገድለ እስጢፋኖስ ይናገራል [በሕግ አምላክ በፕሮፌሰር ጌታቸው]


መጽሐፉን ዛሬ መመርመር ለምን አስፈለገ? የሚል ጠያቂ ሊኖር ይችላል፣ መልሳችን አብዛኛው የዋሕ ምእመን እምነቱን የመሠረተው በታምረ ማርያም ላይ ነው የሚል ሥጋት ስላለን ነው። ወደ ቤተ ክርስቲያን ሲሄድ ታምሯን ሰምቼ ልምጣ እንጂ ወንጌል ሰምቼ ልምጣ ብሎ አያስብም፣ እሑድ እሑድ ታምር የሚያነብ እንጂ ወንጌል ለማስተማር የሚያስብ ቄስም የለንም። 400 000 ካህናት እንዳላት የሚነገርላት ቤተ ክርስቲያናችን ታምረ ማርያም አንብቦ ከማሳለም ያላፈ አገልግሎት የሚሰጥ አይደለም። በተለይም ታምሯን ሰምቶ የሄደ ሥጋውና ደሙን እንደተቀበለ ይቆጠርለታል የሚለው ባዕድ ወንጌል ብዙ ሕዝብ ወደ ስጋውና ደሙ እንዳይደርስ ስላደረገው ይህም የስሕተት ትምህርቶች ውጤት ሆኖ ስላገኘነው፣ ሲኖዶሱ ከተኛበት እስኪነቃ ድረስ ጩኸታችንን አናቆምም። ወደ ተነሳንበት እርስ እንመለስ፥

መጽሐፉቅምርበሚባል አገር አንድ ሰው ነበር በማለት ታሪኩን ይጀምራል

ወኢየበልዕ እክለ ወኢ ሥጋ ላሕም ወኢ ካልአ እንሥሣ አላ ይበልዕ ሥጋ ሰብእ

ትርጉም እህል፥ የላም፥ ሥጋ የሌሎችንም እንሥሳ ሥጋ አይበላም ነበር የሰው ሥጋ ይበላ ነበር እንጂ 68