Monday, April 30, 2012

መማለድና አማላጅነት (Interceds & intercession)

 አማለደ፣ በግእዙ ግስ  «ተንበለ» ማለት ሲሆን ትርጉሙም መለመን፣መጸለይ፣ማማለድ አማላጅ መሆን፣ማላጅ፣አስታራቂ፣ እርቅ ፍቅር ይቅርታ መለመን ማለት ነው። for PDF (Click Here )
አማላጅ ሲል አንዱ ለሌላው ይቅርታን፣እርቅን ሰላምን ለማስገኘት በአድራጊውና በተቀባዩ መካከል የሚያገናኝ መስመር ማለት ነው። ይህም ተቀባዩ ከአድራጊው ጋር የሚኖረውን ግንኙነት የተስተካከለ እንዲሆን በመካከለኛነት አገኛኝ ድልድል በመሆን ማገልገል የማማለድ አገልግሎት ይሰኛል።
የአማላጅነትን ወይም የማማለድን ርእሰ ጉዳይ ለማብራራት ከማምራታችን በፊት እስኪ ስለሰውኛነታችን ጥቂት እንበል።
የሰው ልጅ በዚህ ምድር ሲኖር ከተለየው ሰማያዊ  ጸጋ የተነሳ ደካማ ፍጥረት ሆኗል። ሥራው ሁሉ የሚከናወነው በድካምና በመከራ ብቻ ነው። አሜከላ እሾህ የሚወጉትና ጸሐይ የሚያጋየው ደካማ ፣ ይፈሩት የነበሩትን እንስሳት የሚፈራ ፈሪና ድንጉጥ ሆኗል። ሸኰናው የሚነከስ የደዌና የሞት ሰው በመሆኑ አኗኗሩን አስቸጋሪ አድርጎታል። ስለዚህ ከዚህ ዓይነት አሰልቺ አኗኗር ለመገላገል ወይም የኑሮውን የክፋት ኃይል ለመቀነስ ልዩ ልዩ መንገዶችን ለመጠቀም ተገዷል። የሰው ልጅ ዛሬ ካለበት ስልጣኔ ደረጃ ለመድረስ የቻለው ለመኖር አዳጋች የሆነበትን የውደቀት ምድር የተሻለችና ድካሙን የምትቀንስለት ለማድረግ ከመፈለግ  የተነሳ መሆኑ ይታወቃል። ያማ ባይሆን ኖሮ በእሾክና በእግር መካከል ጫማን፣ በአቧራና በጸሐይ መካከል መነጽርን፤ በጊዜ ክፍልፋይ መካከል ሰዓትን፤ በእርዛትና በመጠለያ  ግኝት መካከል ቤትን፣ በህመምና በደዌ መካከል መድኃኒትን በመፍጠር የሚያስማማ ነገርን ለመስራት ባልቻለነበር።
የኑሮው መጠን እየሰፋና ቁጥሩ እየጨመረ በሄደ ጊዜ ደግሞ አንዱ አንዱን የማገዝ፣ የመረዳዳት፣ የመደጋገፍ አስፈላጊነቱ እያየለ በመምጣቱ ሰው ያለሰው ለመኖር አለመቻሉ ገሃድ እየሆነ መጥቶ ዛሬ ላለንበት የማኅበራዊ መስጋብሮቻችን ትስስር ከፍተኛ ደረጃ ላይ መድረስ አብቅቶናል። የሉላዊው ዓለም  (Globalization) ነባራዊ ኩነትም ይህንን በግልጽ ያሳየናል።
እያንዳንዱ ሰው እርሱ የማይችለውን ለመስራት ወይም ለመፈጸም በሌላው ላይ ጥገኛ የመሆን ወይም የሌላውን አጋዥነት የመፈለግ ሁኔታ በእለት ከእለት ኑሮው ውስጥ በመስተዋሉ ጉልበትን በገንዘብ በመግዛት ወይም የሌላውን እውቀት ለጥቅም በማዋል ወይም  በእውቀትና ጥበብ ሌላውን በመጨበጥ ወይም የማያገኘውን ለማግኘት በመሞከር ከአቅሙ በላይ ለሆነው ተግዳሮት ሁሉ ድጋፍ የሚፈልግበት ዓለም ውስጥ በመገኘቱ የተነሳ ሰጪና ተቀባይ፣ ለማኝና ተለማኝ፣ ኃያልና ደካማ፣ ሀብታምና ደሃ፣ ገዢና ተገዢ፣ መሪና ተመሪ የመሆን ክስተቶች ሊስተዋሉ የግድ ሆኗል። እናም የሰው ልጅ ችግሮቹን፣ እንቅፋቶቹንና መሻቱን ለመቋቋም መደገፊያ አስፈልጎታል።
     ከሰፊውና ውስብስቡ  ነባራዊ ሁኔታዎቻችን ውስጥ ለማሳያነት ብንጠቅስ፤ አንድ ሰው በአንድ መሥሪያ ቤት የሚኖረውን ጉዳይ በአቋራጭ ለማስፈጸም ቢፈልግ ከጉዳዩ ባለቤት ጋር ቅርበት ወይም የጠበቀ ግንኙነት ያለውን ሰው እንዲያስፈጽምለት በአገናኝነት ይልካል። ብዙ ውጣ ውረድ ሳያስፈልገው ጉዳዩን በላከው መካከለኛ ሰው ድጋፍ በኩል ያስፈጽማል ማለት ነው። ያንን ድጋፍ ለማግኘት ባይችል ዓላማው ላይፈጸም ይችል ይሆናል ወይም በሌላ ወገን ሊበላሽ ይችላል። ሰዎች እርስ በእርሳቸውን ያላቸውን ግንኙነት ከሁኔታዎች ስፋት አንጻር የተራራቀ ሲሆን  ስፋቱን የሚያጠ’ቡ’ ድልድዮችን ሊዘረጉ ይገደዳሉ።
ዛሬ በእለት ኑሮአችን ውስጥ ከምናያቸው ነገሮች መካከል ለጋብቻ ሽማግሌ፤ ለቤት ኪራይ ደላላ፣ ለሥራ እውቀት፣ ለጸብ አስታራቂ፣ ለጦረኞች ጠብመንጃ  አስማሚና አገናኝ ኃይል ሆነው ሲያገለግሉ እናያለን። ቤት ተከራይንና ኪራይ ቤትን በመካከል የሚያገኛኝ መንገዱ ደላላ መሆኑ ሰው ለችግሮቹ መፍትሄ ማግኛና ጥቅም ማስገኛ እንዲሆን የፈጠረው መላ ስለመሆኑ አይጠፋንም።
  እንግዲህ በዚህ ምድር ላይ የሰው ልጅ  ተገቢ የሆነ አገልግሎት ለማግኘት ይሁን  ያልሆነ ጥቅም ለማግኘትም ጭምር ቢሆን በዘመዱ፤ በገንዘቡ፣ በወዳጁ፤ ከጉዳዩ ጋር ቅርበት ባላቸው ሰዎችም በኩል አሸማጋይ፣ አስታራቂ፣ አማላጅ በማዘጋጀትና በመላክ እርሱ በቀጥታ ማድረግ ወይም ማስደረግ የማይችለውን ነገር በሌላ በሦስተኛ ወገን  ጉዳዩን ከፍጻሜ ሲያደርስ ኖሯል፤ ወደፊትም ይኖራል።

Sunday, April 29, 2012

አማኝ እንጂ አክራሪ አትሁን።

አማኝ ያመነውን የሚኖር በፍቅርም የሚማርክ ጀግና ነው። አክራሪ ግን ጥቂት እውቀቱን ከዱላ ጋር ለማስከበር የሚሞክር ነው። የከረረ ነገር መበጠሱ አይቀርም። የከረረ ነገር ሲከርም ሲበጠስም ስጋት ነው። አክራሪነት የአለሙ ልከኛ ሰው እኔ ነኝ። ከኔ በቀር በአለም ላይ ማንም መኖር የለበትም። ከምስራቅ ስገላበጥ ምእራብ እደርሳለሁ። ከሰሜን ስራመድ ባንድ ስንዝር ደቡብን እረግጣለሁ። ስለዚህ ከኔ ውጪ ማንም መኖር የለበትም ብሎ እንደማሰብ ነው። የአክራሪነት ምንጩ አለማወቅ ነው። አክራሪ ሰው በከሳሽነት መንፈስ የተያዘ እንጂ የሚያሳየው ማራኪ ስራ የሌለው ነው። ጥቂት እውቀቱ ከሰፋች የካደ ስለሚመስለው ላለማወቅ ተጠንቅቆ የሚጓዝ ነው። እርሱ ካለበት ገድጓድ ውጪ አለም ያለ የማይመስለው የለመድኩት ሰይጣን ይሻላል ብሎ ከመቃብር ጋር በኪዳን የሚኖር ተስፋ የሌለው ሳይሞት መኖር ያቆመ ሳይቀበር እውቀቱን የጨረሰ ሰው ነው። የአክራሪነት ወንድሙ አለማወቅ ነው። እኔ ያወቁት ብቻ ትክክል እኔ ከሰማሁት ውጪ ያለው ያተነገረ ነው አለም በኔ ጓዳ በኩል ነው የምታልፈው እኔ ያልገባኝ ነገር እንዴት ልክ ይሆናል? ብሎ የሚያስብ ነው። መሀይም ማለት ያልተማረ ሳይሆን መማር የማይፈልግ ነው። የሰይጣን ትልቁ ግዛቱ ድንቁርና ነው። ሰዎች የህሊናን አይናቸውን ካላሳወረ በቀር አያመልኩትምእና ህሊናቸውን ያጨልማል ማወቅ እንደጨረሰ ሰው የምትኖር ከሆነ መኖርህ ምክንያት አልባ መሆኑን አስብ። ባለህበት ጉድጓድ መጠን ሁሉንም ነገር ካየሀው ሁሉም ነገር ይጠብብሀል። ትንሽ እውቀትም የስጋን ሀይልን ይሻልና እውቀትህን አሟላው

    በጉልበቱ እያስፈራራ ከደጀ ሰላም የሚበላ አንድ ወጠምሻ ሰው ነበረ። የሌሊቱን ቁመት ሳይቆም ደግሞም ቅዳሴ ሳይቀድስ ያለ’ፋበትን እንጀራ በመብላቱ ቀሳውስቱ ሁል ጊዜ ቢያጉረመርሙበትም ማንም ደፍሮ የከለከለው አልነበረም። እርሱም ያልተማረ እንደሚሉት ስለሚሰማ እማራለው ብሎ ወደ አንድ መምህር ሄዶአባቴ ዳዊት አስደግሙኝብሎ ይጠይቃቸዋል። እርሳቸውምአንተ ተማር እንጂ እኔ ምን ከብዶኝ?” ብለው በደስታ እሺ ብለው ማስተማር ጀመሩ።አርሱም መዝሙረ ዳዊት ምእራፍ አንድ በደንብ እንደቻለ በቃኝ አላቸው። እሳቸውም ገና እኮ ነው ቢሉትአይ አባቴ ይህቺህ ትምህርቴ ከዱላዬ ጋር ትበቃኛለችአላቸው ይባላል ዛሬም ከዱላዬ ጋር ትንሽ እውቀቴ ትበቃኛለች ብለው የሚኖሩ ብዙዎች ናቸው። አንተ ግን እንደ እነርሱ አትሁን።
                            http://awdemihret.blogspot.com

ማኅበረ ቅዱሳን እና ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ካልእ አይተዋወቁም!

  To read in PDF ( Click Here )
                            A source from: www.abaselama.org
አክራሪውና ወግ አጥባቂው የሰለፊያ የግብር ወንድም ማኅበረ ቅዱሳን የተመሰረተበትን 20 ዓመት ሰባት ያህል ወራትን አሳልፎ ሚያዝያ 27 በእግር ጉዞ ሊያከብር መሆኑን ሲገልጽ የቆየ ቢሆንም፣ የተመዝጋቢ ቁጥር በማነሱና በሌላም ምክንያት መራዘሙ እየተወራ ነው። ይሁንና ማስታወቂያው ላይ በትልቁ የብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ፎቶ ተሰቅሏል። የእርሱ የጉዞ መርሀ ግብርና አቡነ ጎርጎርዮስ፣ የእርሱ 20 ዓመትና አቡነ ጎርጎርዮስ ምን እንዳገናኛቸው ለጊዜው ባይታወቅም ብቻ ፎቷቸው በትልቁ የማስታወቂያው ማዳመቂያ ሆኗል።
1980 ብፁዕነታቸው እስካረፉበት እስከ 82 . ድረስ ወደ ዝዋይ የካህናት ማሰልጠኛ ገብተው የተማሩ አንዳንድ የዩኒቨርሲቲና የኮሌጅ ተማሪዎች መካከል አንዳንዶቹ በኋላ ላይ የማኅበረ ቅዱሳን መስራቾች እንደነበሩ ይነገራል። ይህን አጋጣሚ መነሻ በማድረግ ነው ማኅበሩና የማኅበሩ ሰዎች ብፁዕነታቸውን የማኅበሩ መስራች አባት አድርገው ይቆጥራሉ።
ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስን በቅርብ የሚያውቋቸው እንደሚናገሩላቸው ግን ቤተ ክርስቲያን በለውጥ ጎዳና ላይ እንድትራመድ የሚፈልጉ ሰው ነበሩ። ይሁን እንጂ ከሕዝቡ ወግ አጥባቂነትና ንቃተ ህሊና አንጻር ለውጡ አዝጋሚ መሆን እንዳለበት ነበር የሚያምኑት ይባላል። ከላይ እንደገለጽኩት ይህ የብፁዕነታቸው ዓላማ ባይገባቸውም አንዳንድ የማኅበረ ቅዱሳን ቀደምት ሰዎች ዝዋይ ከርመው ተመልሰዋል። ምክንያቱም እነዚህ የማኅበሩ ሰዎችና ማኅበሩም እንደማኅበር ከብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ውጪ መሆናቸውን እየታዘብን ነው። ዛሬ የማህበሩ ሰዎች በስፋት የሚቃወሙት ብፁዕነታቸው በጽሁፍ ያስተላለፏቸውን ትምህርቶች ነው። የማኅበሩ መሠረት ወንጌል ሳይሆን ተረት ነውና።

Saturday, April 28, 2012

16 ክርስቲያኖች ታሰሩ!

ታቸው ዶኒ አስቸጋሪና ለቤተክርስቲያን የማይመች ሰው መሆኑን እናውቃለን። አጥማቂ ነኝ እያለ ቅብዓ ቅዱስና እምነት ነው፤ እያለ አፈር እንደሚሸጥም ይታወቃል። በሽሮ ሜዳ ሥላሴ፣ በቃሊቲ ማርያምና በአቃቂ መድኃኔ ዓለም በሺናሻ ቅጠል ብዙዎችን ሲያጮህ የነበረ ሰው ነው። ሌላም ሌላም ነገር.....! ሰውዬው ለቤተክርስቲያን ሸክምና እንቅፋት ከመሆን ባለፈ መፍትሄ መሆን የሚችል ሰው አይደለም። ደጀ ብርሃን ብሎግም ከሰውዬው ጠባይ የተነሳ በባቦ ጋያ መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን አካባቢ ምስቅልቅል ከመፍጠር አይመለስም ብሎ ስለሚገምት በዓላማና በአቋም ባንመሳሰልም የቤተክርስቲያን ችግር የእኛም ችግር ስለሆነ ከአንድ አድርገን ብሎግ ላይ የወጣውን መረጃ እንዳለ አቅርበነዋል።
(አንድ አድርገን ሚያዚያ 19 ፤ 2004ዓ.ም)፡- የባቦጋያ መድሀኒአለም ቤተክርስትያን የቦታ ጉዳይ ለያዥ ለገናዥ እያስቸገረ ይገኛል ፤  ጌታቸው ዶኒ እንዳሰበው ነገሮች እየሄዱ አለመሆናቸውን ሲረዳ የቤተክርስትያኒቱን ቄሰ ገበዝ ትላንት አመሻሽ ላይ የመቅደሱን ቁልፍ ካለመጡ ብሎ ጠይቋቸው ነበር ፤ እርሳቸውም ‹‹አንተ ማነህና ነው የቤተክርስትያኒቱን ቁልፍ የምሰጥ ›› በማለት እምቢ ሲሉት ጉልበት ተጠቅሞ ቁልፉን እጁ ለማስገባት ሙከራ አድርጎ  ነበር ፤ ቄሰ ገበዙ የመቅደሱን ቁልፍ አልሰጥም በማለት ለአካባቢው ክርስትያኖች ስልክ ደውለው በአጭር ጊዜ ውስጥ ክርስትያኖቹ የተሰበሰቡ ሲሆኑ ከደቂቃዎች በኋላ ጌታቸው ‹‹አመጽ ለማስነሳት ሰዎች ተሰብስበዋል›› ብሎ በደወለላቸው ፖሊሶች አማካኝነት በጊዜው የነበሩትን 16 ክርስትኖችን  እስር ቤት ሊያስገቧቸው ችለዋል ፡፡ ከእነዚህ ውስጥም ሶቶች ጎልማሶችና ፤ ወጣቶች ይገኙበታል ፤  የእነዚህ ንጹሀን ክርስትያኖች  ተቃውሞ ‹‹ጌታቸው ዶኒ  የቤተክርስትያኒቱን ቁልፍ ለምን ይቀበላል ? ቁልፉን ተቀብሎ ከዚህ በፊት ሲናገር እንደነበረው የባቦጋያን መድሀኒአለም ቤተክርስትያን ለመዝጋት የሚያደርገውን ተግባር እንቃወማለን ፤ ›› በማለታቸው ነው ለእስር የበቁት፡፡

ደጀ ሰላም ብሎግ ኢትዮጵያ የክርስቲያን ደሴት ናት ሲል ህገ መንግሥቱ ደግሞ ኢትዮጵያ የሁሉም ሃይማኖቶች ሀገር ናት ይላል! የደሴቲቱ ገዢስ ማኅበረ ቅዱሳን ይሆን?

 ኢትዮጵያ የክርስቲያን ደሴት ናት ካልን እስላሞቹና ሌሎቹ ወደየት ይድረሱ?
ደጀ ሰላም ብሎግ- ህገ መንግሥት፣ የጠ/ሚኒስትር መግለጫ፣ ገለመሌ አይሰራም የሚል ይመስላል፤ ይህንን የሚያረጋግጠው ኢትዮጵያ የክርስቲያን ደሴት መሆኗን ከሁለት ዓመት በፊት ዘግቦ ነበር። ሌሎች ሃይማኖቶች ኢትዮጵያ ውስጥ እንዳሉና ሊኖሩ እንደሚገባ አምኖ ባለመቀበል ሀገሪቱ የአንዲት ሃይማኖት ደሴት ናት ማለት ምን ማለት ነው? ሁሉም ኦርቶዶክሳዊ ኢትዮጵያ የክርስቲያኖች ብቻ ናት እንደማይል ይታወቃል። እነዚህኞቹ ግን የክርስቲያን ብቻ ደሴት ነን እንዲል በመንፈሳዊ ታዛ ተጠልለው ይቀሰቅሱታል። ሰለፊ/ወሀቢ የሚባለው ደግሞ በሌላኛው ጽንፍ በኢትዮጵያ የሙስሊም መንግሥት መቆም ይገባዋል ይላል። ማሸበር የሚባለውስ ከዚህ ወዲያ ምን ሊሆን ይችላል? ይህንን የቲ-ሸርት ጫወታ የማኅበረ ቅዱሳን ሌላኛው አፍ እንደሆነ በሚነገርለት ከደጀ ሰላም ብሎግ ላይ ያገኘነው ስለሆነ ያንብቡትና ሚዛናዊ ግምትዎን ይውሰዱ።

(ደጀ ሰላም፤ ጃኑዋሪ 17/2010):- በዓለ ከተራ ሰኞ በመላ ኢትዮጵያ ታቦታተ ሕጉ ከየመንበራቸው ወጥተው ይከበራል። በሀገራችን ዋና ከተማ በአዲስ አበባ በዐቢይነት በጃን-ሜዳ ሲከበር፣ በመላው ሀገሪቱ ደግሞ ታቦታተ-ሕጉ ወደ ጥምቀተ-ባሕር ወደሚፈጸምባቸው ውሃዎች ይወርዳሉ። ከተራን ማክበር አዲስ አይደለም። ነገር ግን አምና በተከበረው “የከተራ” በዓል ላይ የታየው የሕዝቡ አከባበር፣ ሥነ ሥርዓቱና በጎ አርአያው ተጠቃሽ በመሆኑ ልናስታውሰው ወደድን። ወጣቶች አንድ ዓይነት ካናቴራ (ቲ-ሸርቶች) አሰርተው በመልበስ ራሳቸው የሕዝባቸውና የበዓላቸው አስተናባሪ ሆነው የታዩበት ሁኔታ ሁሉንም ያስደመመ ነበር። ከመንግሥት እስከ ቤተ ክህነት ባለሥልጣናት፣ ከኦርቶዶክሳውያን እስከ ሌሎች እምነት ተከታዮች ድረስ መነጋገሪያ መሆኑ ይታወሳል። በወቅቱም የሚከተሉትን መዘገባችን ይታወሳል።






የአባቶቻችንን ርስት ምን ያህል እንፈልገዋለን?
(በብርሃናዊት)

በዘንድሮው የጥምቀት በዓል ላይ: የተለያዩ ኢትዮጵያውያን "ኢትዮጵያ የክርስቲያን ደሴት ናት" እና "የአባቶቼን ርስት አልሰጥህም" የሚሉ ጽሑፎች የታተሙበትን ቲሸርቶች ለብሰው በዚህ ድረ-ገጽ ላይ ሳይ: ሁለት ዓይነት ስሜት ተሰማኝ::

1. የመጀመርያው ሕዝበ-ክርስቲያኑ ለእምነቱና የእምነት ሥርዓቱን በነጻነት ለማካሄዱ ምን ያህል ተቆርቋሪ እንደሆነና: ሙሉ ለሙሉ የእምነቱን ጉዳይ ችላ እንዳላለው: ምናልባትም እንደማይለውም ጭምር የተረዳሁበት ስለሆነ: አዎንታዊ ገጽታው ታይቶኛል::

2. ሁለተኛው ስሜቴ ግን: ሕዝበ-ክርቲያኑ ስሜቱ እንደሻከረና: በትንሹም በትልቁም ሊገነፍል የሚችል ስሜታዊነትን እንዲያዳብር በጽንፈኞች መደረጉን ሳይ የፈጠረኝ ስሜት ነው:: በእውነቱ መልካሙን መንፈሳዊነት የሚያደፈርስና የሚሠርቅ: የጨቅጫቃ መናፍቃንና የተንኳሽ ጽንፈኞች ፍላጻ የኢትዮጵያን ሕዝበ ክርስቲያን ወግቶ እስከዛሬ ሳይገድለው በመቅረቱ ጥበበ-እግዚአብሔርን እንዳደንቅ ተገድጃለሁ:: ሰአሊ ለነ ቅድስት የምንላት ድንግል ማርያም አሁንም በእኛ ተስፋ አልቆረጠችም::

Friday, April 27, 2012

አዲስ አበባ በሚገኙ አንዳንድ የ"ማኅበረ ቅዱሳን" ሱቆች ላይ የማሸግ እርምጃ ተወሰደ!

ሊያደርግ ያቀደውን የእግር ጉዞ ለሌላ ጊዜ አስተላለፈ
አዲስ አበባ ውስጥ በሚገኙ የ"ማኅበረ ቅዱሳን" ሱቆች ላይ የማሸግ እርምጃ መወሰዱን የደረሱን መረጃዎች አመለከቱ፡፡ በተለይም በኡራኤልና በሜክሲኮ አካባቢ የሚገኙ የ"ማኅበረ ቅዱሳን" ሱቆች ላይ "ባልተፈቀደ የንግድ ሥራ ላይ ስለተሠማራ ሱቁ ታሽጓል" በሚል ማስታወቂያ የታሸጉት እነዚህ ሱቆች፣ "ማኅበረ ቅዱሳን" ከማንኛውም አካል የንግድ ሥራ ፈቃድ ሳይወስድ የሚሠራባቸው መደብሮች መሆናቸው ታውቋል፡፡
"ማኅበረ ቅዱሳን" በፖለቲካዊና ሃይማኖታዊ እንዲሁም በቤተክርስቲያን ስም እና በራሱ ስም እያዛነቀ ሚናው ባልለየ እንቅስቃሴ ውስጥ እዚህም እዚያም የሚነከር በመሆኑ በሰሞኑ ከሕግ ጋር ለመፋጠጥ ተገዷል ተብሏል፡፡ ከንግድ ሥራ ጋር በተያያዘም ለመንግሥትም ሆነ ለቤተክርስቲያን ተገቢውን ገቢ ሳያስገባ ዝም ብሎ የሚዘርፍ ድርጅት እንደመሆኑ መጠን ሕጋዊ መሥመር እንዲይዝ ሲደረግ ጨርሶ ፈቃደኛ ሊሆን አለመቻሉ ተገልጿል፡፡

ፍትወተ - ሥጋ


- ትንሹ እሳት (የዓለም፣ የሥጋ፣ የሰይጣን እሳት)
በመሠረቱ  ማንኛውም እሳት ኃይል ነው (አለው)፡፡ በትክክል ከሠሩበት ጠቃሚ ነው፡፡ ያለ አግባብ ከሠሩበት ደግሞ አጥፊና ደምሳሽ ነው፡፡ በዘህ ክፍል ውስጥ ከሚገኙት የእሳት ዓይነቶች ውስጥ አንዳንዶቹ ምንም ጥቅም የማይገኝባቸው፣ እንዲያውም አጥፊ ብቻ የሆኑ እሳቶች ሲሆኑ፣ አንዳንዶቹ ደግሞ በአግባቡና በእግዚአብሔር ፍቃድ መሠረት ከተሠራባቸው ለበረከት የሚሆኑ፣ በሥጋ ምሪት ከተሠራባቸው ደግሞ የኩነኔ መሰላሎች የሆኑ እሳቶች ናቸው፡፡
1. ፍትወተ - ሥጋ (Sex) - እግዚአብሔር ለሰዎች ከሰጣቸው ጠቃሚ ኃይሎች አንዱ የሆነው ፍትወተ ሥጋን በአብዛኛው ለክፋት መገልገያነት ሲውል ማየታችን መጥፎ እንደሆነ አድርገን እንድንመለከተው አድርጎናል፡፡ በእግዚአብሔር ቃል ላይ ተመርኩዘን ስለዚህ ጉዳይ ያጠናን እንደሆነ ግን መልካም ስጦታ እንደሆነ ነው የምናገኘው፡፡ ይህን ስጦታ በአግባቡ ለተጠቀመበት ሰው የበረከት ምክንያት ይሆንለታል፡፡ ከጌታ ፍቃድ ውጪ ለሠራበት ደግሞ የጥፋት መሣሪያ ይሆንበታል፡፡ "እግዚአብሔርም ሰውን በመልኩ ፈጠረ፤ በእግዚአብሔር መልክ ፈጠረው፣ ወንድና ሴት አድርጎ ፈጠራቸው፡፡ እግዚአብሔርም ባረካቸው፣ እንዲህም አላቸው፡- ብዙ ተባዙ ምድርንም ሙሉአት...." (ዘፍ. 127-28) ከሚለው የመጽሐፍ ቅዱስ የመጀመሪያው ገጽ ጥቅስ አንስቶ በመላው መጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች ውስጥ ጋብቻና የጋብቻ ውጤቶች የሆኑት ልጆች የእግዚአብሔርን ቡራኬ ሲቀበሉ እናያለን፡፡ በጋብቻ ውስጥ ውትወተ ሥጋ አለ፣ ቀጥሎም ልጆች ይገኛሉ፡፡ ስለዚህ በቃል ኪዳን መሐላ ማኅተም በታሰረ ጋብቻ ውስጥ የባልና ሚስት ግንኙነት የተቀደሰ ተግባር እንጂ፣ ርክሰት አይደለም፡፡ በዚህ መልኩ ብቻ ከተሠራበት የፍትወተ-ሥጋ እሳት ጠቃሚና ቅዱስም ይሆናል፡፡ ከዚህ ውጪ ግን የገሃነመ እሳትን የመጀመሪያ ነበልባሎች እዚህ ምድር ላይ የሚጭር እርኩስ እሳት ይሆናል፡፡ ፍትወተ-ሥጋ እሳት ስለመሆኑ ቅዱስ ጳውሎስ በተለያዩ መልእክቶቹ አመልክቷል፡፡ ለምሳሌ 1 ቆሮ. 78-9 ላይ እንዲህ ይላል - "ላላገቡና እንዲሁም ባሎቻቸው ለሞቱባቸው ሴቶች የምለው እንዲህ ነው፤ ሳያገቡ እንደ እኔ ቢኖሩ መልካም ነው፡፡ ነገር ግን ራሳቸውን መቈጣጠር ቢያቅታቸው ያግቡ፤ ምክንያቱም በሥጋ ምኞት ከመቃጠል ይልቅ ማግባት የተሻለ ነው፡፡" የሥጋ ምኞት (ፍትወት) ለምን ያቃጥላል; መልሱ ግልጽ ነው እሳት ስለሆነ፡፡ እዚህ ላይ .ጳውሎስ ስለዚህ እሳት መልካምነት ይናገራል፡፡ በሌላ ቦታ ግን ያለአግባቡ በጥቅም ላይ ስለዋለ ርኩስ እሳት ይናገራል፡፡