Wednesday, February 29, 2012

ዳንኤል ክብረት፣ ዘበነ ለማና ምህረተአብ ሃዋሳ ላይ ለመስበክ መመሪያ አይፈቅድላቸውም!

 የአቡነ ገብርኤል የገጽታ ግንባታ ተግባር!

የተሰደዱት የሰንበት ት/ቤት ወጣቶች ጉባዔውን ለማደናቀፍ ምንም ዓይነት ዕቅድ እንደሌላቸው አስታወቁ

በሀዋሳ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ገብርኤል ገዳም ከመጪው የካቲት 23 ቀን 2004 ዓ.ም ጀምሮ ለሦስት ቀናት የሚቆይ መንፈሳዊ ጉባዔ ሊዘጋጅ እንደሆነ የሀገረ ስብከቱ ሥራ አስኪያጅና የ"ማኅበረ ቅዱሳን" ስምዓ ጽድቅ ተከፋይ ዐምደኛ መልአከ ብርሃን ይትባረክ ታጠቅ ድምፅ ማጉያ ይዘው በሹሽሹክታ ለሕዝብ መናገራቸውን መግለጻችን ይታወሳል፡፡  በሀዋሳ ዳቶ ኪዳነ ምሕረት ቤተክርስቲያን ለእመቤታችን በዓለ ንግሥ ለተሰበሰበው ሕዝብ ዳንኤል ክብረት፣ ዘመድኩን በቀለና ዘማሪ ቴዎድሮስ ዮሴፍ ሄደው እንደሚያስተምሩ መናገራቸውን ጭምር መግለጻችን አይዘነጋም፡፡ ሆኖም አሁን በደረሰን መረጃ ሄደው የሚያስተምሩት መ/ር ዘበነ ለማ ከአሜሪካ፣ ዳንኤል ክብረት፣ መ/ር ምሕረተአብ አሰፋ፣ ዘማሪ ቴዎድሮስ ዮሴፍና ሌሎችም ስማቸው ያልተገለጹ ሰዎች እንደሆኑ ታውቋል፡፡

ይሁን እንጂ የመ/ር ዘበነ ባይታወቅም ዳንኤል ክብረት ከፍተኛ የ"ማኅበረ ቅዱሳን" አመራር፣ እንዲሁም መ/ር ምሕረተ አብ አሰፋ የ"ማኅበሩ" አባልና ደጋፊ በመሆናቸው ሄደው ለማስተማር ቀደም ሲል የተላለፉ መመሪያዎች እንደማይፈቅዱላቸው ታውቋል፡፡ እነዚህም:-
  1. ክቡራን የመንግሥት ሚኒስትሮች በታዛቢነት በተገኙበት አቡነ ገብርኤል ራሳቸው የቅዱስ ሲኖዶስ አባል ሆነው መስከረም 12 ቀን 2002 ዓ.ም በተካሄደው የሠላም ጉባዔ የወሰኑትና የፈረሙበት "ማኅበረ ቅዱሳን" በማናቸውም የቤተክርስቲያን አስተዳደራዊ መዋቅሮች ውስጥ ጣልቃ እንዳይገባ ጥቅምት 6 ቀን 2002 ዓ.ም በቁጥር 44/70/2002 መመሪያ ወጥቷል፡፡
  2. የሀዋሳን ግጭት ለማብረድ በብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ የምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀጳጳስ የተመራው አጣሪ ቡድን ያቀረበው ሪፖርት ግጭቱ የተከሰተው ተስፋ ኪዳነ ምሕረትና ፀረ ኤች አይ ቪ ኤድስ ማኅበር እና "ማኅበረ ቅዱሳን" ባስነሱት ሁከት መሆኑን ይገልጽና ተስፋ ኪዳነ ምሕረት ማኅበርን ጨምሮ "ማኅበረ ቅዱሳን" እንደማንኛውም ተቋምና ግለሰብ አስቀድሶና ተገልግሎ ከመውጣት በስተቀር በቤተክርስቲያን አስተዳደራዊ ጉዳይ ጣልቃ እንዳይገቡና በዐውደ ምሕረት ላይ እንዳያስተምሩ፣ የካቲት 2 ቀን 2003 ዓ.ም በቁጥር 92/54/2003  ከቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት መመሪያ ተላልፏል፡፡

Monday, February 27, 2012

በክብረ መንግሥት የማኅበረ ቅዱሳን ግጭት

በጉጂ ቦረና ሀገረ ስብከት በክብረ መንግሥት (አዶላ ወዩ) ከተማ ዓርብ የካቲት 16 ቀን 2004 ዓ.ም "ማኅበረ ቅዱሳን" በቀሰቀሰው ግጭት የእመቤታችን የቅድስት ኪዳነ ምሕረት በዓለ ንግሥ ሳይከበር መዋሉን ከሥፍራው የደረሰን መረጃ ያመለክታል፡፡ በክብረ መንግሥት (አዶላ ወዩ) ከተማ በቅድስት ሥላሴ ቤተክርስቲያን ዓመታዊ በዓለ ንግሷ የሚከበረው የእናታችን የኪዳነ ምሕረት መታሰቢያ በዓለ ንግሥ ሳይከበር የዋለው በአካባቢው ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ሲሆን፣ የቅዳሴ ሥርዓቱም ሳይካሄድ ቤተመቅደሱ ተቆልፎበት መዋልና ማደሩን አረጋግጠናል፡፡ የግጭቱ መነሻ የሆነው "ማኅበረ ቅዱሳን" በመላው ዓለም ከጠረፍ እስከ ጠረፍ እንደሚያደርገው ሁሉ በክብረ መንግሥትም እኔ ያልፈቀድኩት ሥርዓት አይካሄድም፤ እኔ ያልፈቀድኩለት አገልጋይ ቤተክርስቲያን ቅጥር ግቢ አይደርስም በሚል ትዕቢት ተነሳስቶ የቀሰቀሰው ሁከት ነው፡፡ የሁከቱ ቀንደኛ መሪ ሲያምር ተክለ ማርያም የተባለ የቀድሞው የሀገረ ስብከቱ ሥራ አስኪያጅ የነበረ ሰው መሆኑ ታውቋል፡፡ ይኸው ግለሰብ በሀገረ ስብከቱ መኪና ኮትሮባንድና ሌላም ሌላም የንግድ ሥራ ሲሠራበትና "ማኅበረ ቅዱሳን"ን ሲያገለግልበት ቆይቶ፣ በዚሁ የሙስና ሥራውና የመልካም አስተዳደር ብልሹነቱ የተማረረው ሕዝብ እንዲነሳለት ለጠቅላይ ቤተክህነት ባቀረበው ጥያቄ መሠረት ካለፉት ስድስት ወራት በፊት ከቦታው ተነስቶ አዲስ አበባ ወደሚገኘው ትንሣኤ ዘጉባዔ ማተሚያ ቤት የተዛወረ ሰው ነው፡፡ ይሁን እንጂ ግለሰቡ፣ የጠቅላይ ቤተክህነቱን ሕጋዊ አሠራር ተቀብሎና አክብሮ በማተሚያ ቤቱ መደበኛ ሥራው ላይ ተገኝቶ መሥራት ሲገባው የሀገረ ስብከቱን ተሽከርካሪ መኪና ይዞ በመሰወር የግል ጥቅሙን ሲያሳድድበት መክረሙን በዚሁ ብሎጋችን መዘገቡ አይዘነጋም፡፡ የቦረና ሀገረ ስብከት ሥራ አስኪያጅ የጽ/ቤቱን መኪና ይዘው ተሰወሩ በሚል ርዕስ ያቀረብነውን ዘገባ እዚህ እዚህይመልከቱ ሰውዬው የሚደረግበትን የፖሊስና የኅብረተሰቡን ክትትል በመፍራት ባልተጠበቀ ሰዓት መኪናዋን ሀገረ ስብከቱ ጽ/ቤት አቁሟት የጠፋ ሲሆን፣ ከጊዜ በኋላ ደግሞ አረሳስቶ ብቅ ማለቱንና ጽ/ቤቱን እንደገና መውረሱን የአካባቢው ምንጮች ያስረዳሉ፡፡ ይህ ግለሰብ፣ የሀገረ ስብከቱን ጽ/ቤትና በእጁ የሚገኘውን ንብረት አላስረክብም ብሎ ሙጭጭ ከማለቱም በላይ የ"ማኅበረ ቅዱሳን"ን ጭፍሮች በዙሪያው በመኮልኮል፣ በምትኩ የሀገረ ስብከቱ ሥራ አስኪያጅ ሆነው የተመደቡትን ሊቀ ትጉሃን ተሾመ ኃ/ማርያምን አላሰገባም በማለት ከስድስት ወራት በላይ ሲያንከራትቷቸው መቆየታቸው ታውቋል፡፡

Friday, February 24, 2012

ለእንዳለ ገብሬ 200ሺህ ተዋጣ!


ቀሪውን 250 ሺህ ብር ሰፋ ባለ መርሐ ግብር ለማሟላት ዕቅድ ተይዟል
በከፍተኛ የልብ ሕመም በመሰቃየት ላይ ላለው ወጣት እንዳለ ገብሬ መታከሚያ በአንድ ቀን መንፈሳዊ አገልግሎት 200 ሺህ ብር ያህል ማሰባሰብ መቻሉን የደረሰን መረጃ ያመለክታል፡፡ (ታሪኩን በይበልጥ ለመረዳት፣ ከዚህ ቀደም ሲል ስለ ወጣቱ ችግር ካወጣናቸው ዘገባዎች ጋር ያስተያዩት) ይህንን ያህል ገቢ ሊሰባሰብ የቻለው በአሁኑ ወቅት "ማኅበረ ቅዱሳን" በሚያሳድዳቸው ውድ የሆኑት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን የስብከተ ወንጌልና የመዝሙር አገልጋዮች ባዘጋጁት መንፈሳዊ ጉባዔ ነው፡፡
የካቲት 12 ቀን 2004 ዓ.ም ከምሽቱ 12 ሰዓት ጀምሮ በሻላ 17 17 መናፈሻ አዳራሽ በተካሄደው በዚህ መንፈሳዊ አገልግሎት ላይ በግል በአድራሻ ጥሪ የተደረገላቸው ሦስት መቶ ያህል ሰዎች ተገኝተው ግማሽ ያህሉን ገንዘብ የለገሡ ሲሆን ቀሪውን ግማሽ መጠን በቃል መግቢያ ሠነድ እንደሚሰጡ ማረጋገጣቸው ታውቋል፡፡ የዕለቱን መርሐ ግብር የመራው መምህር ተረፈ አበራ ሲሆን፣  መምህር ታሪኩ አበራም በበኩሉ የወደቀውን ስላነሳው የደጉን ሣምራዊ ታሪክ ከወንጌል ጋር በማጣቀስ፣ ችግር ላይ የወደቁትን ወገኖች መርዳት ክርስቲያናዊ ግዴታችን መሆኑን ሰፋ ባለ ሁኔታ ትምህርት ሰጥቷል፡፡

ኪዳናት ስንት ናቸው?


                                         እግዚአብሔር ስንት ኪዳን ሰጠ?

      “..........አዎ! እግዚአብሔር ልጆቹ ይጠቀሙ ዘንድ በተለያዩ ጊዜያት ከተለያዩ ቅዱሳኑ ጋር ቃል ኪዳን  ገብቷል፡፡ ከእነዚህም ኪዳነ አዳም፣ ኪዳነ ኖኅ፣ ኪዳነ አብርሃም፣ ኪዳነ ዳዊት እንዲሁም በጌታችንና   በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ለሰው ልጆች በሙሉ የተሰጠ ሐዲስ ኪዳን ተጠቃሾች ናቸው ….....”             
                  
                                 ( የአንድ አድርገን ብሎግ አስተምህሮ)

 
                   «.....ፊተኛው ኪዳን ነቀፋ ባይኖረው፥ ለሁለተኛው ስፍራ ባልተፈለገም ነበር»ዕብ ፰፣፯
    « ስለዚህም የፊተኛው ኪዳን ሲጸና ሕግን የተላለፉትን የሚቤዥ ሞት ስለ ሆነ፥ የተጠሩት የዘላለምን ርስት የተስፋ ቃል እንዲቀበሉ እርሱ የአዲስ ኪዳን መካከለኛ ነው»ዕብ ፱፣፲፭
                                 (መጽሐፍ ቅዱስ)
  
አንድ አድርገን ብሎግ  የአዲስ ኪዳኑን የኢየሱስ ክርስቶስን ኪዳንና  ሌሎችንም ዘርዝሮ የኪዳነ ምሕረትን ጨምሮ ብዙ፣ ብዙ ለመዳን የሚሆኑ ኪዳኖች  እግዚአብሔር ለሰው ልጆች እንደሰጠ ያለምንም መሸማቀቅ በኩራት ዘግቦልን ይገኛል። ስህተቱን የከፋ የሚያደርገው እግዚአብሔር ለሰው ልጆች የሰጠው «ኪዳን» ሁለት ብቻ መሆኑን በመጽሐፍ ቅዱስ የተነገረውን በመካድና በዚህ የክህደት አስተምህሮ ውስጥ ሌሎችንም ይዞ ወደጥፋት ለማምራት ማወጁ ነው።
 አንድ አድርገን ብሎግ ክህደቱን ለማስፋፋት «ኪዳነ አዳም፣ኪዳነ ኖኅ፣ኪዳነ አብርሃም፣ ኪዳነ ዳዊት እንዲሁም በኢየሱስ ክርስቶስ ለሰው ልጆች ሁሉ የተሰጠ ሐዲስ ኪዳን» እግዚአብሔር ለእኛ ጥቅም የሰጠን ኪዳኖች ናቸው ሲል ያለምንም ሀፍረት ጽፏል።
መጽሐፍ ቅዱስ ግን እግዚአብሔር የሰጣቸው ኪዳኖች ሁለት ብቻ መሆናቸውን በግልጽ አስቀምጧል። «ነቀፋ የተገኘበት ፊተኛውና የዘለዓለም ርስት የሚሆን አዲስ ኪዳን » ናቸው በማለት።
 «.....ፊተኛው ኪዳን ነቀፋ ባይኖረው፥ ለሁለተኛው ስፍራ ባልተፈለገም ነበር»ዕብ ፰፣፯
                     
          «  « ስለዚህም የፊተኛው ኪዳን ሲጸና ሕግን የተላለፉትን የሚቤዥ ሞት ስለ ሆነ፥ የተጠሩት የዘላለምን ርስት የተስፋ ቃል እንዲቀበሉ እርሱ የአዲስ ኪዳን መካከለኛ ነው»ዕብ ፱፣፲፭                         
        

                    «ፊተኛው ወይም ብሉይ ኪዳን»

እግዚአብሔር ይህንን ኪዳን የሰጠው ለሰው ልጆች ሁሉ ሳይሆን እርሱ ለመረጣቸው ሕዝቦች ብቻ ነበር። ይኸውም ከጥፋት ውሃ በኋላ የአባታቸውን የኖኅን ገመና የሸፈነውና፣ የበረከት ልጅ ሆኖ የተመረቀ በምድር ቡሩክነት  የተመረጠው የሴም ዘር  ነበር። «እንዲህም አለ፦ የሴም አምላክ እግዚአብሔር ይባረክ፥ ከነዓንም ለእነርሱ ባሪያ ይሁን»፱፣፳፮  የተመረጡትና የበረከት ምርቃት የወረደላቸው ሴማውያን የእግዚአብሔር«ሕዝቦች» ሲባሉ ከነዓናውያን ግን «አሕዛብ» ተብለው መቅረታቸውንና የመጀመሪያውንም ቃልኪዳን እግዚአብሔር የሰጠው ለእነዚህ ሴማውያን እስራኤል ብቻ እንደሆነ ከቅዱሱ መጽሐፋችን ላይ እናነባለን። የሴም የትውልድ ሐረግ እስከአብርሃም ድረስ ያለውን ከዘፍጥረት ፲፩ ጀምሮ እናገኘዋለን። እንግዲህ እነዚህ ሕዝቦች ናቸው ከአሕዛብ የተለዩ ተብለው በእግዚአብሔር የተመረጡት።
«አሁንም ቃሌን በእውነት ብትሰሙ ኪዳኔንም ብትጠብቁ፥ ምድር ሁሉ የእኔ ናትና ከአሕዛብ ሁሉ የተመረጠ ርስት ትሆኑልኛላችሁ»ዘጸ ፲፱፣፭
«ሙሴና ሌዋውያን ካህናት ለእስራኤል ሁሉ እንዲህ ብለው ተናገሩ። እስራኤል ሆይ፥ ዝም ብላችሁ አድምጡ ዛሬ የአምላክህ የእግዚአብሔር ሕዝብ ሆነሃል» ዘዳ ፳፯፣፱
 እነዚህን ሕዝቦች እግዚአብሔር መርጧቸዋል። ከእነዚህ ምርጦቹ ጋር ለእርሱ ቅድስና በሚሆን መልኩ የመሪና የተመሪ ሕግ የሆነውን ውል በሙሴ በኩል በኮሬብ ተራራ ላይ  ሰጥቷል። ይህ ህዝብ በዚህ ህግ እየተመራ ኖሯል። ህጉን ሲጥሱ እየቀጣቸው፣ ሕጉን ሲጠብቁ እየባረካቸው እንደኖሩ ሙሉ የብሉይ ኪዳን መጽሐፍ በሰፊው ይነግረናል። ይህ የመጀመሪያው ኪዳን መሆኑ ነው። ለሕዝብና ለአሕዛብ የሚሆን ሌላ ሕግ እስኪመጣ ድረስ እግዚአብሔር ከመረጣቸው ጋር ቃል የተገባባበት የቀደመው ኪዳን  ስፍራውም ኮሬብ ነው። ኪዳኑንም በ፲ ቱ ሕግጋት ሥር የሚጸና ልዩ ልዩ አፈጻጸሞችን የያዘ መተዳደሪያ ውል ነበር።

Thursday, February 23, 2012

«ክርስቶስን መምሰል»

  ‹‹ለእኔ ክርስትና ክርስቶስን ለመምሰል መጣር ነው››

በጋዜጣ ሻጩ ጐልማሳ ክንድ ላይ ከተደረደሩት የህትመት ውጤቶች መካከል ትኩረቴ ባረፈበት መሔት የፊት ገላይ ከቲያትር ባለሙያዋ ጀማነሽ ሰለሞን ጉልህ ምስል በታች የተፃፈውን “እኔ ክርስትና ክርስቶስን ለመምሰል የጣር ነው” የሚለው ዓ.ነገር እንዲያ ባለ ሁኔታ ደመቅ ብሎ ይሰፍር ዘንድ የቻለበትን ምክንያት ለመፈተሽ የመîሔቱን  የውስጥ ገጾች መግለጥ አስፈለገኝ፡፡ ይህንኑም ባደረኩ ጊዜ በውስጡ ከዚህ አባባል የማይተናነሱ ሃሳቦችን ማግኘቴ ሲገርመኝ ሰንብቶ ይህንን አደርግና እናገር ዘንድ ገፋፋኝ፡፡
ጀማነሽ ሰለሞንን የማውቃት ከሁለት አስርት ዓመታት በፊት እሷ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ቲያትር ጥበባት ዘርፍ ተማሪ በነበረችበትና እኔ ደግሞ ለዚያ ዘርፍ እንደ ቤተ-ሙከራ ሆኖ በሚያገለግለው በዩኒቨርስቲው ባህል ማዕከል አባል ሆኜ ሳለ ነው፡፡ በወቅቱ አብረዋት ከነበሩት እንስት ተማሪዎች በባህሪያቸው ልስልስ ሆነውልኝ ወዳጃዊ ቀረቤታን ከቸሩኝ የሻሽወርቅ በየነና ኤልሳቤጥ መላኩ በተቃራኒ ጀሜ ኮስተር ያለችና ኩሩ ቢጤ ስለነበረች ያንን ሁኔታ አልፌ ገንዘቤ አደርጋት ዘንድ የወቅቱ ስሜቴ ባይፈቅድልኝም ግና ልጅት በትምህርት ቤት ሳለችም ሆነ ወደ ሥራ ዓለም ከገባች በኋላ የተሰጥኦዋን ከፍተኝነት፣ ጉብዝናዋንና ሙያዊ ጥንካሬዋን ከሚያደንቁላት የጥበቡ አፍቃሪዎች አንዱ መሆኔን መካድ አልችልም፡፡

Wednesday, February 22, 2012

ልሳን


ልሳን ምንድን ነው

ሀ . ልሳን ምንድን ነው፤ በመጽሐፍ ቅዱስ የተጠቀሰቸው ቦታዎችሰ
1.ልሳን ቋንቋ ማለት ነው።
ልሳን ማለት ቋንቋ ማለት ነው። በአዲስ ልሳን መናገር ማለትም በአዲስ ቋንቋ መናገር ማለት ነው። በአዲስ ቋንቋ መናገር ሲባልም ተወልደው ባላደጉበት፤ ባልተማሩት ቋንቋ በመንፈስ ቅዱስ ገላጭነት መናገር ማለት ነው። የመጀመሪያውና ትክክለኛው ልሳን የተገለጸው በጰራቅሊጦስ እለት ነው። ታሪኩም በሐዋርያት ስራ ምዕራፍ ሁለት ተገልጿል። ሐዋርያትም ሆነ በዘመኑ የነበሩ ክርስቲያኖች የተናገሩት በሚሰማና ሊተረጎም በሚችል ቋንቋ ነበር። ሐዋ 2፡ 6 ይህም ድምፅ በሆነ ጊዜ ሕዝብ ሁሉ ተሰበሰቡ፥ እያንዳንዱም በገዛ ቋንቋው ሲናገሩ ይሰማ ስለ ነበር የሚሉትን አጡ። ሐዋርያት በልሳን ሲናገሩ የተሰበሰቡት አይሁድ በራሰቸው ቋንቋ ሲናገሩ ሰምተዋቸዋል። ሐዋርያት የሚያወቁት የራሳቸውን ቋንቋ ብቻ ነበር ነገር ግን እነዚህ ሰዎች የተሰበሰቡት ከዓለም ሁሉ ነበር። ሐዋርያትም የተናገሩት የአለምን ቋንቋ ነበር።ጌታችንም በማር 16፤ 17 በአዲስ ቋንቋ ይናገራሉ ሲል በሚሰማ ቋንቋ ማለቱ ነው።
1ኛቆሮ 14፡ 9-11 እንዲሁ እናንተ ደግሞ የተገለጠውን ቃል በአንደበት ባትናገሩ ሰዎች የምትናገሩትን እንዴት አድርገው ያስተውሉታል ? ለነፋስ የምትናገሩ ትሆናላችሁና። በዓለም ምናልባት ቁጥር የሌለው የቋንቋ ዓይነት ይኖራል ቋንቋም የሌለው ሕዝብ የለም፤ እንግዲህ የቋንቋውን ፍች ባላውቅ ለሚናገረው እንግዳ እሆናለሁ፥ የሚናገረውም ለእኔ እንግዳ ይሆናል።
ብሎ ቋንቋ ሁሉ ሰሚ እንዳለውና እናንተም የምትናገሩት ቋንቋ ሰሚ ባለው ህዝብ መሐከል መሆን አለበት ብሎ ያብራራል።
2.ልሳን መንፈስ ቅዱስ ከሚሰጣቸው ልዩ ልዩና ስፍር ቁጥር ከሌላቸው ጸጋዎች አንዱ ነው።

Monday, February 20, 2012

«ብጹእ አቡነ አብሳዲ እኒህ ነበሩ»

 

«ብጹእ አቡነ አብሳዲ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ»

ብጹእ አቡነ አብሳዲ (በቀድሞ ስማቸው አባ ገ/ማርያም) ግንቦት 12 ቀን 1912 /ም በትግራይ ተወለዱ። እድሜያቸው ለትምህርት ሲደርስ በተወለዱበት ደብር  ከፊደል ቆጠራ ጀምሮ ንባብና እስከ ግብረ ዲቁና ያለውን ከዚያም ወደ ቀድሞው የኤርትራ ክ/ሀገር በአባ አብሳዲ ገዳም ገብተው ቅዳሴና ዜማ ቀጽለዋል። በዚያው በተማሩበት በአባ አብሳዲ ገዳም ማእረገ ምንኩስናን ተቀብለው እስከ 1942 /ም ቆይተው ሲያበቁ የግብጽን ገዳማት ለማየት ባደረባቸው ጉጉት ተነሳስተው የሱዳንን በረሃ በእግራቸው አቋርጠው ወደትልቁ የግብጽ ገዳም ገዳመ አስቄጥስ ሄደዋል። እዚያም የገዳሙ አባቶች በፈቀዱላቸው መሰረት ከገዳሙ አንድነት ገብተው እስከ 1944 /ም ቆይተዋል። እንደገና ኢየሩሳሌምን ተሳልሜ እመጣለሁ በማለት ከአንድ መንፈሳዊ ጓደኛቸው ጋር በመሆን የሲናን በረሃ በእግራቸው በማቋረጥ ወደኢየሩሳሌም አምርተው በዚያ ከሚገኙ የኢትዮጵያ ገዳም ተቀላቅለዋል። ገዳሙን ያስተዳድሩ የነበሩት አቡነ ፊልጶስ ተቀብለው ከገዳሙ አንድነት ያስገቧቸው ሲሆን ከዚህ ዓለም በሞት እስከተለዩበት የካቲት 11/ 2004 /ም ድረስ ላለፉት 60 ዓመት በኢየሩሳሌም የኢትዮጵያ ገዳም በተለያዩ ኃላፊነቶች ደከመኝ፣ ሰለቸኝ ሳይሉ ሲያገለግሉ ቆይተዋል። ብጹእ አቡነ አብሳዲ ከውጭ ቋንቋዎች እብራይስጥኛና አረብኛ ቋንቋዎችን በደንብ የሚያውቁ ሲሆን በዚህ የቋንቋ ችሎታቸው የኢትዮጵያ ገዳም ከግብጾች ጋር ባለው የይገባኛል ችግር እንዲያግዙና ማንኛውንም ጉዳይ መፍትሄ እንዲያመጡ ተመርጠው በገዳሙ አስተዳዳሪነት ለ27 ዓመታት አገልግለዋል። ብጹእነታቸው ለሰው አዛኝና ርኅሩህ፣ በኢየሩሳሌም የኢትዮጵያ ገዳም ተቆርቋሪና ጠበቃ ነበሩ።
ብጹእ አቡነ አብሳዲ በቀድሞ ስማቸው መጋቢ ገ/ማርያም ለኢትዮጵያ ገዳማት ያበረከቱት መንፈሳዊ ተጋድሎ ከታየ በኋላ በ1985 /ም በቅዱስ ሲኖዶስ ተመርጠው በብጹእ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ በኤጲስ ቆጶስነት ማእረግ ተሹመው በኢየሩሳሌም የኢትዮጵያ ገዳማት ረዳት ሊቀጳጳስ ተብለው ሲያገለግሉ ቆይተው የካቲት 11/2004 /ም ባደረባቸው ህመም በተወለዱ 92 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል።
የብጹእነታቸውን ነፍስ ከቅዱሳን ጋር ያሳርፍልን! አሜን
ከመንፈሳዊ ልጃቸው ኃ/ማርያም- ግሪክ አቴንስ

Saturday, February 18, 2012

የቤተክርስቲያን መታደስ!

ክፍል ፪ 


ኦርቶዶክስ ተሃድሶዎች

በአንደኛ ደረጃ ያስቀመጥናቸው ኦርቶዶክስ ተሃድሶዎች በኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን ዶግማ የሚያምኑ ሲኖዶሱ ቀኖና ማውጣት እንደሚችል ቀኖናውን መቀበልና ማክበር እንደሚገባ የሚያምኑ ናቸው :: ሆኖም ግን በአንዳንድ ጉዳዮች ቤተ ክርስቲያን ስር ነቀል ለውጥ ማድረግ አለባት በለው ለውጥ የሚናፍቁ ናቸው :: እነዚህ ቡድኖች እንዳይገለሉ የሚፈሩ ነገር ግን ቤተ ክርስቲያን ቀኖናዊ ለውጥ ብታደርግ የተሻለ ትጠናከራለች ብለው የሚያስቡ ናቸው :: ህዝቡን ለመያዝና አብዛኛው የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ምእመን ንቁ ክርስቲያን ሆኖ እንዲቀጥል ቤተ ክርስቲያን በልዩ ልዩ ጉዳዮች ዙሪያ ቀኖናዊ ለውጥ ብታደርግ ጥሩ ነው ብለው የሚናገሩ ናቸው :: በአብዛኛው ጊዜ ፍላጎታቸውን በቀጥታ ባይናገሩም በእውቀት ዳብሯል ብለው ለሚያስቡት ሰው ግን ሃሳባቸውን ይገልጻሉ ::

እነዚህ ቡድኖች እንደ ምሳሌ የሚወስዱት የእህት አብያተ ክርስቲያናትን የአምልኮ ስርአትና ነው በተለይም የግብጽ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያንን የአምልኮ ስርአት ብዙ ጊዜ ይጠቅሳሉ :: የግብጽ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያንና የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን በትምህርተ ሃይማኖት ደረጃ አንድ ሊባል የሚችል እምነት ያምናሉ በጣም ጥቂት ልዩነቶች ከመኖራቸው ውጭ ዶግማችንና እንዲሁም የቅዳሴው ጸሎት ይዘትም አንድ ሊባል የሚችል ነው :: አብዛኛው ቀኖናቸውም እንዲሁ ይመሳሰላል :: ለምሳሌ የክህነት አሰጣጣቸው፡ የጳጳሳት ስልጣናቸው፡ የቤተ ክርስቲያን አስራራቸውና አከባበራቸው፡ የበአላት ቀናቸው፡ የጾም ጊዜቸው፡ የጾም አጿጿማቸው፡ የንስሃ አገባባቸው እና የመሳሰሉት የሚመሳሰሉ ናቸው ::

Friday, February 17, 2012

የቤተክርስቲያን መታደስ!


.............................በአሁኑ ወቅት ማንም ሰው ሊያስተውለው እንደሚችል በቤተ ከርስትያን ውስጥ ሁለት የሚጋጩና እርስ በእርሳቸው መጠፋፋት የሚፈልጉ አካላትን እናገኛለን :: አካላት ስንልም ሃሳቦች ናቸው :: ሃሳቦች ግን ሰዎችን ይዘዋል :: ሁለቱ አካላት በእየራሳቸው ለአንድ ዓላማ ይኽውም ለቤተ ክርስቲያን ለመጥቀም እንደሚሰሩ ይናገራሉ ::

ማህበረ ቅዱሳንና ማህበረ ቅዱሳናዊ አስተሳሰብ

ማህበረ ቅዱሳናዊ አስተሳሰብ የምለው ቤተ ክርስቲያን እንከን የለሽ በመሆንዋ ምንም አይነት ትችት ማቅረብ የለብንም የሚለውን እና አብዛኛው የማህበሩ አባላት እንዲሁም ብዙ የሰንበት ትምህርት ቤት ተማሪዎችም የሚጋሩት ነው :: ይህ ሃሳብ በመሰረተ ሃሳብነት ማነኛውም ኦርቶዶክሳዊ ሊደግፈውና ሊጋራው የሚገባው ነው :: የራስን ቤት ይልቁንም መክራና ዘክራ ያሳደገችንን ቤተ ክርስቲያን እንዲህ ናት እያሉ በእየ ሜዳው ስሟን ማጥፋት ክብሯን ማጉደፍ የማይገባ ስራ መሆኑ እሙን ነው :: በሌላ በኩል ደግሞ ምእመናኑ ወደ ኑፋቄ የሚነጠቁበትን እና በሃይማኖት ያሉትም ደግሞ ወደ ቤተ ክርስቲያን አገልግሎት የማይቀርቡበትን ምክነያት አጥንቶ እነዚህ እንዲህ ይደረግ ይህ ይስተካከል ማለት አግባብ ነው ::

ማህበረ ቅዱሳን በእየ ዜናው መውጣት ከጀመረ አለፈ ከረመ እንዳንዶች አይንህን ላፈረ አይነት ጽሁፍ ሲጽፉበት አንዳንዶች ደግሞ እርሱ ከሌለ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ አትኖርም ብለው ክርር ያለ ክርክር ያደርጋሉ :: ታዲያ ሁለቱም ትክክል ሊሆኑ ስለማይችሉ ትክክለኛው የቱ ይሆን ማለቱ አስፈላጊ ነው :: የዚህ ጽሁፍ ጸሓፊ ማህበሩን በሚገባ የሚያውቅ ድክመቶቹንም የማያስተባብል ስለሆነ የማህበሩን በጎ ጎኖችን ሙሉ በሙሉ ዘርዝሮ መጨረስ ባይችልም ዋና ዋና በጎ ጎኖችንና ድክመቶቹን ይጽፋል :: የጽሁፉም አላማ ሰዎች ጥሩውንና መጥፎውን ለይተው ከመልካሙ ጋር እንዲተባበሩ ከመጥፎው ደግሞ እንዲርቁ ነው ::

Thursday, February 16, 2012

የምንገዛው ለማነው?


                        
1/ ነፍስ ሁሉ በበላይ ላሉት ባለ ስልጣኖች ይገዛ፡፡ ከእግዚአብሔር ካልተገኘ በቀር ስልጣን የለምና፤ ያሉትም ባለስልጣኖች በእግዚአብሔር የተሾሙ ናቸው፡፡
2. ስለዚህ ባለ ስልጣንን የሚቃወም እግዚአብሔርን ሥርዓት ይቃወማል፤የሚቃወሙትም በራሳቸው ላይ ፍርድን ይቀበላሉ፡
3. ገዢዎች ለክፉ አድራጊዎች እንጂ መልካም ለሚያደርጉ የሚያስፈሩ አይደሉምና፡፡ባለስልጣንን እንዳትፈራ ትወዳለህን? መልካሙንአድርግ ከእርሱም ምስጋና ይሆንልሃል፤
4. ለመልካም ነገር ለአንተ የእግዚአብሔር አገልጋይ ነውና፡፡ በከንቱ ግን ሰይፍ አይታጠቅምና ክፉ ብታደርግ ፍራ፤ ቁጣውን ለማሳየት ክፉ አድራጊን የሚበቀል የእገዚአብሔር አገገልጋይ ነውና፡፡


Wednesday, February 15, 2012

በኤርትራዊው አሸባሪ የተመራው የማኅበረ ቅዱሳን ቡድን!

ለዘማርያን የመዝሙር ግጥምና ዜማ በመቀመር የሚታወቀው ዲ/ን ጋሻዬ መላኩ ጥር 4 ቀን 2004 ዓ.ም ጋብቻውን  በሥርዓተ ተክሊል በአዲስ አበባ ደብረ ጽጌ ቅዱስ ኡራኤል ቤተክርስቲያን ፈጸመ፡፡ (ምናልባት ዲ/ን ጋሻዬን ለማታውቁት በዘማሪት ዘርፌ ከበደ እውነተኛ ታሪክ ዙሪያ በሚያጠነጥነው የ"ፓራሜራ" ፊልም ላይ ከዘማሪ ዲ/ን ሀብታሙ ሽብሩ ጋር ሆኖ ግጥምና ዜማ ሲያስጠናት የሚታየው ነው)፡፡

በዲ/ን ጋሻዬ መላኩ ሥርዓተ ተክሊል ላይ ከሌሊቱ 10፡00 ሰዓት ጀምሮ በርካታ የቤተክርስቲያናችን ሰባክያንና ዘማሪያን እንዲሁም ልዩ ልዩ አገልጋዮች የተገኙ ሲሆን እስከ ጥዋቱ 2፡30 የነበረው መርሐ ግብር የተረጋጋ እና የሰከነ እንደነበር ተገልጿል፡፡ ይሁን እንጂ፣ ሥጋ ባየበት እንደሚዞር ጆፌ አሞራ ከአገልጋዮች ሥር የማይጠፋው "ማኅበረ ቅዱሳን" ዝግጅቱን ለማደናቀፍ መሞከሩ አልቀረም፡፡

"ማኅበረ ቅዱሳን" ያዘጋጀው ይህ የረባሽ ቡድን ሦስት መታወቂያዎችን ይዞ ሲንቀሳቀስ በካራማራ ወረዳ ፖሊስ የተያዘና ጉዳዩ በፍርድ ቤት በመታየት ላይ ያለ ተስፋዬ በሚባል ኤርትራዊ አሸባሪ ግለሰብ እና ሐጂ እና እንድዬ በሚባሉ ሁለት ረዳቶቹ እንደተመራ ታውቋል፡፡ ቁጥጥር በማይደረግበት በቤተክርስቲያን አንጡራ ሀብት ከ"ማኅበረ ቅዱሳን" በወር እስከ 3500 (ሦስት ሺህ አምስት መቶ) የሚከፈላቸው እነዚህ ግለሰቦች ጥቅምት 11/2004 ዓ.ም በዲ/ን ዘማሪ ትዝታው ሳሙኤል ላይ ድብደባ የፈጸሙና በዘመድኩን በቀለ የክስ ሂደት ላይም በየችሎቱ እየተገኙ በአገልጋዮች ላይ የዛቻ እና የማስፈራራት ወንጀል የሚፈጽሙ መሆናቸው በተጨማሪ ታውቋል፡፡

እነዚህ ሦስት ግለሰቦች የተመደቡላቸውን ወደ ሰባ የሚሆኑ ወሮበሎች መርተው ወደ ተቀደሰው የቤተክርስቲያን ቅጥር ግቢ ገብተው ሁከት ለማሰነሳት የሞከሩ ሲሆን፣ በቅድሚያ መረጃ የደረሰው የፖሊስ ሠራዊት ደርሶ ሁከቱን በቁጥጥር ሥር ሊያውለው ችሏል፡፡ ይህ የወሮበላ ቡድን አገልጋዮችን በስም እየጠራ እነ እከሌ፣ እነ እከሌ ይውጡልኝ እያለ ላንቃው እስኪላቀቅ ቢጮኽም፣ በቤተክርስቲያን የሚካሄደው የዲ/ን ጋሻዬ መላኩ የጋብቻ ሥነ ሥርዓት መርሐ ግብር በስብከተ ወንጌል አዳራሹ በተሳካ ሁኔታ መካሄዱን በሥፍራው የነበሩ ታዳሚዎች ገልጸውልናል፡፡

በስብከተ ወንጌል አዳራሹ በነበረው አገልግሎት መጋቤ ሀዲስ በጋሻው ደሳለኝ ተገኝቶ ለዕለቱ የሚገባ መንፈሳዊ መልዕክት ያስተላለፈ ሲሆን፣ መምህር አሰግህድ ሣህሉ፣ መምህር ተረፈ አበራ እና ሌሎችም አገልጋዮች መታደማቸው ተገልጿል፡፡ በዕለቱ መርሐ ግብር መሠረት ከመምህር ተረፈ ቀጥሎ ትምህርቱን ያቀረበው መጋቤ ሀዲስ በጋሻው ሲሆን፣ በዚሁ ትምህርቱ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ወደ ልጇ በማማለድ የእነ ዶኪማስን ጉድለት በማሟላት የአማላጅነቷ ሚስጥር የተገለጠበት እና በጌታ ዘንድም ጋብቻ ክቡር መሆኑ የተመሠከረበት ነው በማለት በመሳጭ ስብከቱ ምዕመናንና ምዕመናትን አገልግሏል፡፡

"ማኅበረ ቅዱሳን"፣  "በሃይማኖት ጉዳይ መፍረድ የአንተ ሥልጣን አይደለም፤ አርፈህ ተቀመጥ" ቢባልም የሚሰማበት ጆሮ ስለሌለው ቤተክርስቲያንንና ሕዝብን የማወክ ተግባሩን ቀጥሎበታል፡፡

"ማኅበረ ቅዱሳን" በቤተክርስቲያንና በፍርድ ቤት ፊት እውነትን መጋፈጥ ሲያቅተው፣  በውድቅት ሌሊት እንደሚልከሰከስ ሰይጣን በየአጥቢያ ቤተክርስቲያናቱ፣ በየጎዳናውና በየቤቱ እየዞረ የሚረብሽ ተናካሽ ውሻ ወደመሆን ደረጃ ወርዷል ሲሉ ታዛቢዎቻችን ገልጸዋል፡፡ በወንጌል ብርሃን ሲፈተሽ እንደ ቅቤ የሚቀልጠው "ማኅበረ ቅዱሳን" በእግዚአብሔር ቤተመቅደስ እንደዚህ ዓይነቱን ርኩሰት እየደጋገመ መፈጸሙ የዘመኑ መጨረሻ ዓይነተኛ ምልክት መታየት መጀመሩን አንባቢ ያስተውል ብለዋል፡፡

የዝግጅት ክፍላችንም እግዚአብሔር ለወንድማችን ለዲ/ን ጋሻዬ መላኩ፣ ጋብቻው የሠመረ የአብርሃምና የሣራ እንዲያደርግለትና ቀሪው የአገልግሎት ዘመኑን እንዲባርክለት፣ እንዲሁም በሚሠራው ሥራና በሚሰጠው አገልግሎት ፀጋውን እንዲያበዛለት  ይመኛል፡፡

የእግዚአብሔር ጥበቃና ቸርነት ከሁላችን ጋር ይሁን!!!
አሜን!!!

Tuesday, February 14, 2012

የይስሙላ ድርድር እንዳይሆን እንሰጋለን!


የይስሙላ ድርድር እንዳይሆን!
ሰሞኑን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የ20 ዓመት የሁለት ሲኖዶስ ክፍፍል ለማቆም ድርድር እንደተጀመረ ከሚዲያው ሰምተናል። ምንም ይሁን ምንም እርቅና ስምምነት ከልብ ከሆነ መልካም ነው። እነዚህ ሁለት ወገኖች የራሳቸው ጥቅምና መብት የማስከበር ዓላማ እንዳላቸው ሁሉ ለስምምነቱ እልባት አለመድረስም ያንን በማስጠበቅ ላይ የተመሰረተ ስለሆነ የከዚህ በፊቶቹ ድርድሮች ውጤታማ ሳይሆኑ ቀርተዋል። ያሁኑን የተለየ የሚያደርገው ምን እንደሆነ በግልጽ የተነገረ ነገር ባይኖርም እኛ ግን ያለፈው ነገር እንዳይደገም ከመስጋት አንጻር የግላችንን ሃሳብ ከታች በአጭሩ ለማቅረብ ሞክረናል።

ድርድር የእርቅ መነሻ ምእራፍ ነው። ተደራዳሪዎች ግራና ቀኝ ሆነው ይሄንን ማግኘት ወይም ማስጠበቅ አለብኝ ብለው ይዘው የሚቀርቧቸው የድርድር ጭብጦች ይኖራቸዋል። ጭብጡ የሚወሰነው ተደራዳሪው ወገን በሚያመጣው ነጥብ ላይ ነው። የትኛውም ተደራዳሪ ወገን አስቀድሞ እነዚህን አምስት ነጥቦች አስወግዶ ወደ ድርድሩ ጠረጴዛ ካልመጣ ድርድሩ ውጤታማ አይሆንም።
የተደራዳሪዎች ውስጣዊ ሁኔታዎች፥
1/ ለድርድር የሚያቀርባቸው ነጥቦች ከተደራዳሪው ወገን የሚጠብቀው በነባራዊ ሁኔታ ያልተመሰረተ ጥያቄ ከሆነ፣
2/ ከምፈልጋቸው ነጥቦች ምንም አላጎድልም ወይም ሁሉም ይጠበቁልኝ ብሎ ከተዘጋጀ፣
3/ ከሁለቱ ተደራዳሪዎች ውጪ የሚያግባባ የሶስተኛ ወገን አደራዳሪን ሃሳብ ለመቀበል ካልፈቀደ፣
4/ ተደራዳሪው ወገን ለሚያቀርበው ሃሳብ «ምን እያለ ነውብሎ ከማጣጣል «እያለ ያለው ለምንድነውብሎ ለመረዳት ካልፈለገ፣
5/ ነገሮችን በሰከነ መንፈስ ለመገንዘብ ከመሞከር ይልቅ ከተደራዳሪው ወገን ምንም ላይገኝ ብሎ እልህ በመጋባት የሚያከር ከሆነ፣ የሁለት ወገን ተደራዳሪዎች ድርድር ውጤታማ ላይሆን ይችላል።
የተደራዳሪዎች ውጫዊ ሁኔታዎች፣
የትኛውም ተደራዳሪ ወገን ከጎኑ በድጋፍ የቆሙ ወይም በእጅ አዙር የሚደግፉ ወይም ሃሳቡን የሚመሩ ወገኖች ድርድሩን ሊያከሩበት ወይም ተደራዳሪው በማይፈልጋቸው የኃይል ውጫዊ አሰላለፎች ድርድሩን ውጤታማ እንዳይሆን ሊያደርጉት ይችላሉ።
1/ ተደራዳሪውን ከኋላ የሚነዱት ኃይሎች፣ በተደራዳሪያቸው ሳቢያ የሚደርስባቸውን ጉዳት ለመከላከል ድርድሩን ከፍጆታ ባለፈ የማይፈልጉት ሆኖ ሲገኝ፣
2/ ተደራዳሪውን የሚደግፉ አባላት፣ በተደራዳሪያቸው ምክንያት የአባልነት ወይም የደጋፊነት መብታቸው የማይጠበቅ ከሆነ ወይም ካልተከበረ፣ ድርድሩ በውጪያዊ ተጽእኖ ሊስተጓጎል ይችላል።
በተደራዳሪዎቹ ውስጣዊ የድርድር አቋምና ዓላማ እንዲሁም ድርድሩ በቀጥታ ባይመለከታቸውም ከድርድሩ የሚጠቀሙ ወይም የሚጎዱ አካላት በድርድሩ ላይ ተጽእኖ በማሳረፍ ውጤታማነት እንዲጎድለው ሊያደርጉ ይችላሉ።
ከነዚህ ነጥቦች ተነስተን በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የውጪና የሀገር ውስጥ ሲኖዶስ መካከል ያለውን የእርቅ ድርድር መገምገም ይቻላል።
በሀገር ውስጥና በውጪው ሲኖዶስ አንጻር፣
1/ የኢትዮጵያ መንግሥት፣ በግዛቱ ያለውን ሲኖዶስ በራሱ ሕግ ጥላ ሥር እስካለ ድረስ እንደሕጋዊ ሲኖዶስ ስለሚቆጥር በድርድሩ ላይ በውጪ ካለው ሲኖዶስ የሚቀርቡ የድርድር መልኮች ሁሉ የእሱን(የመንግሥትን) ሉዓላዊነት የማይነኩ እንዲሆኑ ይፈልጋል።
2/ በሀገር ውስጥ ያለው ሲኖዶስ ድርድሩ በስደተኝነት ወይም በሁለተኛ ሀገር የሚኖር ባለመሆኑ ከውጪ ያለውን ሲኖዶስ እንደአቻ ሳይሆን እንደመብት ጠያቂና ተቀባይ ወገን አድርጎ የመመልከት ሁኔታ ሊኖር ይችላል።
3/ በውጪ ያለው ሲኖዶስ በድርድሩ መነሻ እርቁ ፍጻሜ ቢኖረው የሚያጣው ነገር ሊኖር እንደሚችል ከገመተ ወይም ድርድሩ የነበረውን ሁኔታ ቀይሮ ፍጹም ሊያደርገው አይችልም ብሎ ካመነ ድርድሩን ውጤታማ ላያደርገው ይችላል።
ስለሆነም በሁለቱ ሲኖዶስ ወገኖች በኩል ያሉትን ነባራዊ ሁኔታዎች ገምግመውና አስቀድመው ለሲኖዶሱ ድርድር መልካምነት በየራሳቸው መንገድ ጠርገው በዚያ ላይ እየተረማመዱ ወደድርድሩ ጠረጴዛ ካልመጡ በስተቀር ስምምነቱ ፍጻሜ ይደርሳል ማለት አስቸጋሪ ነው።
እስካሁን የተደረጉ ግንኙነቶች ሁሉ ውጤታማ ያልሆኑበት ምክንያት ይህንን መሠረት ያደረጉ ናቸው።
እኛም እነዚህን ነጥቦች ያነሳነው ቤተክርስቲያንን እንደክርስቶስ አካልነቷ ሳይሆን እንደፖለቲካ መሳሪያነቷ እየተጠቀሙ በሚገኙት የውጪና የሀገር ውስጥ ሲኖዶስ አመለካከት ላይ ተንተርሰን እንጂ እንደመንፈሳዊ ተቋም ሰዎች አይተናቸው አይደለም። ሥልጣንንና ኃይልን (Authority & Power) ስለመካፈል እንደፖለቲካው የድርድር መሳሪያነት (Negotiation tools) ከላይ ያየናቸው ነጥቦች ጠቃሚ ናቸው። ከሃዲና ከሃዲ ተባብለው ተወጋግዘው ሲያበቁ አሁን ስለክህደቱ ጉዳይ ጉባዔ ለመጥራት ሳይሆን ስለሥልጣኑ ጉዳይ ሼር ለመነጋገር እንደሆነ ስንመለከት ቀድሞውኑ የተጣሉት ስለክርስቶስ ቤተክርስቲያን እንዳልነበረ ያረግጥልናል። ስለሆነም ፖለቲከኞቹ የሃይማኖት ሰዎች ድርድራችሁን አለዝባችሁ ስምምነት ላይ በድርድር መርህ ለመድረስ ሞክሩ!
ለዚህም የድርድሩ መርህ ይርዳችሁ እንላለን!

Monday, February 13, 2012

የአቡነ ገብርኤል ተልዕኰ!


በሲዳማ፣ ጌዴኦ፣ አማሮና ቡርጂ ዞኖችና ልዩ ወረዳዎች ሀገረ ስብከት በተለይም በሀዋሳ ለአንድ ዓመት ከስምንት ወራት ያህል የቆየው ውዝግብ እስካሁን መቋጫ አለማግኘቱን መረጃዎች ያመለክታሉ፡፡ ለውዝግቡ መባባስ የአቡነ ገብርኤል አንዱን አቅርቦ አንዱን የማራቅ አድሏዊ አመራር ትልቁን ድርሻ ሲወስድ፣ ቅዱስ ሲኖዶስ፣ የመንበረ ፓትርያርክ ልዩ ጽ/ቤትና ጠቅላይ ቤተክህነት ጽ/ቤት ተገቢውን እርምጃ ባለመውሰዳቸው የምዕመናኑ ሰቆቃ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መምጣቱን ከተለያዩ ምንጮች ለመረዳት ችለናል፡፡

አቡነ ገብርኤል በሁለንተናዊ የስብዕና ቀውስ ውስጥ ያሉ ሰው ናቸው ያሉ ታዛቢዎቻችን እንዳስረዱን፣ ሊቀጳጳሱ የሚናገሯቸውና የሚፈጽሟቸው ድርጊቶች የትላንቱ ከዛሬው፣ የዛሬው ከነገ የማይጣጣሙ ርስ በርሳቸው የሚምታቱ ናቸው ብለዋል፡፡ በተከበረውና በተቀደሰው ዐውደ ምሕረት ላይ አንድ ጊዜ በድያለሁ ይቅርታ ሲሉ፣ ሌላ ጊዜ ደግሞ በግል መጽሔት ጭምር በአምሳለ ሥላሴ የተፈጠሩትን ምዕመናንንና ምዕመናትን ቀበሮዎች እያሉ የሚሳደቡ መሆናቸው ተገልጿል፡፡  ሰውየው በዚህ ብቻ ሳያበቁ በቅዱስ ሲኖዶስ ፊት ከቤተክርስቲያን የተለየ እና የተከፈለ ሕዝብ የለም ጥቂት ተሃድሶአውያን ናቸው እያሉ የ"ማኅበረ ቅዱሳን"ን የውሸት አሉባልታ ያስተጋባሉ፡፡ ሌላ ጊዜ ደግሞ አዎን የተሰደደ ሕዝብ አለ፡፡ ዕድሉ ይሰጠኝና ሁለቱንም አስማማለሁ እያሉ ሲማጸኑ ይታያሉ፡፡

አቡነ ገብርኤል በግል ቀርቦ ለሚያነጋግራቸው አሁን ያለው የቤተክርስቲያን ቀውስ በዋነኛነት በ"ማኅበረ ቅዱሳን" የተንኮልና የጥፋት ዕቅድ እንደሚመራ፣ እንዲሁም አገልጋዮች ያለ ጥፋታቸው እንደሚሰደቡና በግላቸውም አገልጋዮቹን እንደሚያደንቋቸው ሲመሰክሩ፣ በአደባባይ ሲሆን ግን ከማኅበሩ ብሰው ሽንጣቸውን ገትረው ይራገማሉ፡፡ አቡነ ገብርኤል የማስመሰል ድርጊታቸው ከውስጥ ባህርያቸው የሚመነጭ ነው ያሉ እነዚህ ወገኖች፣ እንደማሳያ የሚሆነን በዕድሜ ያረጁ ሆነው ሳለ ወጣት ለመምሰል ጥቁር ሂና (የፀጉር ቀለም) መቀባታቸው ራሳቸውን በወጣትነት ውስጥ ደብቀው ከሁኔታዎች ጋር ለመመሳሰል መሞከራቸው ነው ብለዋል፡፡ ቤተክርስቲያንንም የሚያጠቁት የዋህና ምንም የማያውቅ ቅን ክርስቲያን በመምሰል ነው ብለዋል፡፡

ምክራችሁን እሻለሁ!

 ጥያቄ፦

እባካችሁ ወገኖች ምክራችሁን እሻለሁ!

በጌታ የተወደዳችሁ ወገኖቼ ሰላም ለናንተ ይሁን!

ባለትዳርና የልጆች እናት ነኝ፡፡ ባለቤቴ እጅግ የሚወደድና ምስጉን ባህርይ ያለው ሰው ነው፡፡ ስራው የግሉ ንግድ ላይ ሲሆን ብዙውን ጊዜ ለስራው ሲሮጥ ከወዲህ ወዲያ ሲል ለስኬቱም ሲለፋ ነው የሚውለው፡፡ ለኔም ሆነ ለልጆቹ ያለው ፍቅር ሰው የሚቀናበትና እጅግ የሚገረምበት ነው፡፡ ትልቁ ህልሙ ልጆቹን ውጤታማ አድርጎ ለማየት ሲሆን ብዙውን ጊዜም እኔ ባለፍኩበት ልጆቼ እንዲያልፉ አልፈልግም ብሎ ይናገራል፡፡

እኔ ደግሞ በስነ ጥበብ ስራ ላይ ስገኝ ከስራዬ ባህርይ የተነሳ ከብዙ አለማውያን ወንዶች ጋር እገናኛለሁ፡፡ በስራዬ ደግሞ ስኬታማና ስም ያለኝ ሴት ነኝ፡፡ በሃገር ውስጥም ሆነ ከሃገር ውጪ የተለያዩ ግለሰቦችም ሆኑ ድርጅቶች እያዘዙኝ እሰራለሁ፡፡ ከዚህ በተጨማሪ በአንድ የውጪ ድርጅት ውስጥም ተቀጠሬ እየሰራሁ ነው፡፡

ከኢትዮጵያ ውጪ ካሉት አሰሪዎቼ ውስጥ አንደኛው ግለሰብ ብዙውን ጊዜ ወደሃገር ቤት ይመላለሳል፡፡ የስራ ትእዛዞችን ሰጥቶኝና የተሰሩትንም ይዞ ለመሔድ እዚህ በመጣ ጊዜ በተደጋጋሚ እንገናኛለን፡፡ ይሄ ሰው ዳጎስ ያለ ክፍያ የሚከፍለኝ ሲሆን ከውላችን ውጪም ተጨማሪ ገንዘብ በስራዬ መደሰቱን በመግለጽ አልፎ አልፎ ይሰጠኛል፡፡ ባለበት ሃገር ሆኖም ለሰላምታ ይደውልልኛል አልያም ኢሜይል አልፎ አልፎ እንጻጻፋለን፡፡

ከቅርብ ጊዜ ውዲህ ደግሞ በፌስቡክ ላይ ተገናኝተን ቻት እየተደራረግን ቀረቤታችን ለየት ያለ ወሬን ወደማውራት እና ወደመነፋፈቅ ተሸጋገረ፡፡ በወሬያችን እንደሚወደኝ እና ለኔ ለየት ያለ ስሜት እንዳለው ሲገልጽልኝ ባለትዳርና የልጆች እናት መሆኔን እያወቀ እንዲህ አይነቱን ነገር ማሰብ እንደሌለበት ደጋግሜ እናገረዋለሁ አኩርፎኝ እንለያያለን፡፡ (ሳልገልፀው የማላልፈው ጉዳይ ቢኖር እርሱ ትዳሩን ከጥቂት አመታት በፊት የፈታ ሲሆን የልጆች አባትም ነው)፡፡

የሄንን ሰው በስራየ ማጣት የለብኝም ባይሆን ረጋ ብዬ አስረዳዋለሁ እልና በሌላ ጊዜ ኦን ላይን ሳገኘው ረጅም ሰዓት ወስጄ ሃሳብ እንለዋወጣለን፡፡ በሃላም የተረዳኝ መስሎ ለጥቂት ጊዜ ተወኝ፡፡ የምናወራውም እነዴት ነህ እንዴት ነሽ ብቻ ሆነ፡፡ መጻጻፉንም እንደድሮው ሳይሆን ቀነስ አደረገ፡፡

እኔም በራሴ ወስኜ ፌስ ቡክ የሚባለውን ነገር ከስንት አንዴ ከመጠቀም በቀር በአብዛኛው ተውኩት፡፡ የምከፍተውም ከሃገር ውጪ ያሉ አብሮ አደጎቼን ለማግኘትና ከክርስቲያን ወገኖቼ ጋር መንፈሳዊ ነገሮችን ለመዋወጥ ብቻ ነው፡፡ እርሱንም ሊያገኘኝ የማይችልበትን ሰዓት እየተጠቀምኩ ነበር፡፡


በቅርቡ በግል ኢሜይሌ የተላኩልኝን መልእክቶች በማየትና ምላሽ በመስጠት ላይ እያለሁ በዚያም ቻት ማድረጊያው ላይ መልእክት መጣልኝ፡፡ ከዚህ በፊት በዚህ ተጠቅሜ ስለማላውቅ በመገረም ሳነበው የእርሱ እንደሆነ ገባኝ፡፡ በመጥፋቴ እንደተጨነቀና እንዳጋጣሚ እንዳገኘኝ ገልጾልኝ ተቀይሜው እንደሆነ ጠየቀኝ፡፡ በፍጹም ቅያሜ በኔ ልብ ውስጥ እንደሌለ ገልጬለት ስለ ስራችን አውርተን ተለያየን፡፡

በሳምንቱ ይመስለኛል ስልክ ደውሎ ለየት ላለ ስራ እንደሚፈልገኝ ገልጸልኝ ስለሁኔታውም አስረድቶኝ ለኔ ቀላልና ልሰራው የምችለው መሆኑን ገለጽኩለት፡፡ እግረ መንገዱንም ስለነበረው ያለፈው ሁኔታ አንስቶብኝ ፈጽሞ እንዲረሳውና ግንኙነታችን እንደቀድሞ እንዲሆን ገልጨለት በዚሁ ተለያየን፡፡ በማግስቱ ኢሜይል አድርጎልኝ አገኘሁ፡፡ ለኔ የተለየ ልብ እንዳለው፤ ፈጽሞ ሊያጣኝ እንደማይፈልግ ፤የሚያጣኝ መስሎት ተጨንቆ እንደነበርና አሁን ግን እረፍት እንዳገኘ የሚገልጽ ነበር፡፡ ምላሽ ግን አላኩለትም፡፡

Sunday, February 12, 2012

መመለስ አቃተኝ!

 ጠያቂ፦ አብርሃም እባላለሁ፤ በኢየሱስ ክርስቶስ ወንጌል አምናለሁ፡ ቃሉንም ዘወትር አነባለሁ፡ ነገር ግን በአሳፋሪ የዝሙትና የስንፍና ሃጢአት ባሪያ ሆኝለሁ....ብዙ ጊዜ ለመመለስ ብሞክርም በተደጋጋሚ ወደቅኩ። እባካችሁ ይህንን ጥያቄ ያነበባችሁ ሁሉ ባላችሁበት ቦታ ጸልዩልኝ። ምክራችሁንም ለግሱኝ።
 መልስ፦
የዝሙት ኃጢአት ባሕርያት

ከሁሉ አስቀድሜ እየተለማመድክ ስላለኸው ኃጢአት ምንነትና ባህርይ የበለጠ መረዳት እንድትችል አንዳንድ ነገሮችን ለማለት እወዳለሁ።

እንደዚህ አይነት ኃጢአቶች ብዙ ጊዜ በትንሹ የሚጀመሩና ከጥቂት ጊዜ በኋላ የራሳቸው የሆነ ሕይወት አበጅተው በራሳቸው ጉልበትና ኃይል የሚንቀሳቀሱ ኃጢአቶች ናቸው። ብዙ ጊዜ የሚጀመሩት በፈተና ነው። የሚፈትኑና የፍትወት ፍላጎትን የሚያነሳሱ ሁኔታዎች ይገጥሙና የመጀመሪያውን ፈተና መቋቋም ባለመቻል ይጀመራል። ብዙ ጊዜ ይህንን አይነት ኃጢአት የሚለማመድ ሰው (ቀድሞውኑም ጤናማ የክርስትና ሕይወት የነበረው ሰው ከሆነ) ኃጢአቱን ለማሸነፍና ፈተናውን ለመቋቋም የተወሰኑ ትግሎችን ያደርጋል። የሚፈትን ነገር ይኖራል፤ እናም ያንን ለመቋቋም ይሞከራል፡ ነገር ግን ይወደቃል። እንደ ማንኛውም ኃጢአት ከመደረጉ በፊት የነበረው "ደስታ"ና ግፊት ኃጢአቱ ከተደረገ በኋላ ከመቅስበት ጠፍቶ ወደ ጸጸትና ሃፍረት ስለሚለወጥ፤ ፈተናውን ሳይቋቋሙ ቀርተው በዚህም ኃጢአት ሲወድቁ ሰዎች በመጀመሪያ አካባቢ ይጸጸታሉ፤ ሁለተኛም ደግመው ላለማደረግ ይወስናሉ። ነገር ግን ከጥቂት ጊዜያት በኋላ ተመሳሳይ ፈተና ይመጣል፤ ትንሽ ያንገራግራሉ ደግመውም ያንኑ ኃጢአት ሲለማመዱ ራሳቸውን ያገኙታል ወዘተ።

እንዲህ እንዲህ ይልና መጀመሪያ ፈተና ከዚያም ማንገራገር በመጨረሻም መውደቅ የሚለው አዙሪት እየተደጋገመ ይሄዳል። ይህ ድግምግሞሽ ግን ወደሚቀጥለው የኃጢአት ደረጃ ይሻገራል። ይህም ከጊዜ በኋላ ኃጢአቱ እየተወደደና እየተደጋገመ ስለሚሄድ በራሱ ሕይወት ያለው ልምድ ይሆናል። ልምድ ደግሞ የሕይወት አካል ከሆነ ኃጢአቱ የሚደረገው ፈተና ስላለ ብቻ ሳይሆን ደስ ስለሚልና ስለ ለመድነው ነው። ከፈተና አልፎ የራሱ የሆነ ሕይወት አበጀ ማለት ነው። ከፈተና አልፎ በየጊዜው የምንለማመደው የሕይወታችን አካል ሆነ ማለት ነው። በዚህ ደረጃ ከደረሰ ደግሞ ኃጢአቱን ለመለማመድ ግዴታ የሚፈትኑ ነገሮች መኖር የለባቸውም። እኛው ራሳችን፤ በራሳችን ተነሳሽነት እንደ ልማዳችን ኃጢአቱን መለማመድ እንጀምራለን። መጀመሪያ ላይ ፈተናው የሚመጣው ከውጪ ነበር፤ በኋላ ልምድ ሲሆን ግን ያለ ወጪያዊ ፈተና ኃጢአቱ መጥፎ ልማድ ስለሆነብን ተነሳሽነቱ ከእኛው ውስጥ ነው የሚመነጨው። ይህ አደገኛ አካሄድ ላይ እንዳለን የሚያሳይ ምልክት ነው። ኃጢአቱ በሕይወታችን ቤቱን እየሠራና የእኛ አንዱ አካል እየሆነ የሚያመልክት ትልቅ ማስጠንቀቂያ ነው

ያልገባኝ ነገር አለ!

ጥያቄ፦ እኔ ያልገባኝ ነገር አለ፤ እሱም ጌታ ፍቅር ነው እና ኃጢአት የሚሠራ ሥጋ ነው እና እሱ ራሱ ካልቅደሰኝ እንዴት ራሴ ልቀደስ እችላለሁኝ? ራሴ የምቀደስ ከሆነ ሕግ ይሆንብኛል እና እወድቃለሁ። አታድርግ ከሆነ ሰው በኋላ አይበርታም፡ ሰለዚህም ግራ መጋባት ላይ ነኝ።
 መልስ፦
ጸጋና ኃጢአት

በቅድሚያ አዲስ ኪዳን ስለ ሁለት ኃጢአቶች ይናገራል። አንደኛው ሳናውቅና ሳናስብ አንዳንዴ ስለምናደርገው ኃጢአቶች። እንደዚህ ያሉትን ኃጢአቶች ካደረግን፤ ንስሐ ገብተን ኃጢአታችንን እግዚአብሔር ይቅር እንደሚለን ተጽፎአል።

Quote:
1ኛ የዮሐንስ መልእክት 1
8 ኃጢአት የለብንም ብንል ራሳችንን እናስታለን፥ እውነትም በእኛ ውስጥ የለም።
9 በኃጢአታችን ብንናዘዝ ኃጢአታችንን ይቅር ሊለን ከዓመፃም ሁሉ ሊያነጻን የታመነና ጻድቅ ነው።

Saturday, February 11, 2012

የጤናማ ቤተክርስቲያን አስተምህሮ!

ጠያቂ፦ ስለኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ዶክትሪን ብታስረዱኝ?

መልስ፦
በኢትዮጵያ ውስጥ ብዙ አብያተ ክርስቲያናት አሉ። የእያንዳንዳቸውን ዶክትሪን ልዩነት ለመጻፍ አስቸጋሪ ነው። ቢሆንም ግን አንዲት ቤተ ክርስቲያን ጤነኛ መሆንዋን የሚያመለክተን ዶክትሪንዋ (አስተምህሮትዋ) ነው። ጤነኛ ዾክትሪን ያላትን ቤተ ክርስቲያንን ለመለየት የሚከተሉትን መስፈርቶች መጠቀም ያስፈልገናል፦

1. ስለመጽሐፍ ቅዱስ ያላት አመለካከት ምን ነው - Bibliology
- መጽሐፍ ቅዱስ የ እግዚአብሔር ቃል ነው ብላ የማታምን፤ እንዲሁም ለቀደመው ዘመን እንጂ ለዚህ ዘመን አልተጻፈም ብላ የምታምን ከሆነ ወይንም ከመጽሐፍ ቅዱስ ሌላ አግንና የምትጠቀምበት ሌላ አይነት መጽሐፍት ያላት ከሆነ ይህች አይነቱ ቤ/ክ ጤናዋ ትክክል አይደለም። ከመጽሐፍ ቅዱስ ይልቅ ሌላ ነገር የምታስተምር ከሆነ መስመር የሳተች ናት።
2. ሰለ ስነመለኮት (ስለ እግዚአብሔር) ያለት አስተምህሮት ምንድነው? - Theology
- አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ በሦስትነት አንድነትን የማታስተምር ከሆነች ጤነኛ አይደለችም።
3. ስለ ክርስቶስ ያላት እምነት ምንድነው?- Christology
-ኢየሱስ ክርስቶስ ፍጹም ሰው ፍጹም አምላክ መሆኑን የምታምን ቤ/ክ ጤነኛ ቤ/ክ ናት
4. ስለመዳን ያላት እምነት ምንድነው? እንዴትስ ይዳናል ብላ ታምናለች? - Soteriology
- በክርስቶስ ከማመን ውጪ ሌላ ወይንም ተጨማሪ የመዳኛ መንገድ የምታመለክት ቤ/ክ ጤነኛ አይደለችም።
5. ስለመንፈስ ቅዱስ ምን ብላ ታምናለች? - Pneumatology
- መንፈስ ቅዱስ ከስላሴ አካላት አንዱ እንደሆነ ፣ ለቤተ ክርስቲያንን በሃይል የሚያጠምቅ፣ወደ እውነት የሚመራና አስተማሪ መሆኑን ወዘተ. የምታምን ቤ/ክ ጤነኛ ናት።
6. ስለመላዕክት ምን ብላ ታምናለች? - Angelology
- መላዕክት የእግዚአብሔር ፍጥረትና አገልጋይ መልዕክተኞች እንደሆኑ እንጂ አማላጅ እንዳልሆኑ የምታምን ቤ/ክ ጤነኛ ናት። መላእክት ከምድር እስከሰማይ በተዘረጋው መሰላል ላይ ይወጣሉ፣ ይወርዳሉ እንጂ ራሳቸው መውጪያና መውረጃ መሰላል አይደሉም። ናቸው የምትል ከሆነ በክርስቶስ ቦታ መላእክትን ተክታለችና ጤናማ አይደለችም።
7. ስለርኩሳን መላዕክትስ ምን ብላ ታምናለች - Demonlogy
- ርኩሳን መናፍስቶች የ እግዚአብሔርን አላማ አሰናካዮች፣ የሰውም የ እግዚአብሔርም ጠላቶች እንደሆኑ፤ በመንፈስ ቅዱ ኅይል በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ከሰዎች መውጣት እንዳለባቸው የምታምን ቤ/ክ ጤነኛ ናት። ከክፉ መናፍስት መካከል ክርስቲያን መሆን የሚችሉ እንዳለ የምታስተምር ከሆነ ጤናማ ቤ/ክ አይደለችም።
8. ስለቤተ ክርስቲያንስ ምን ብላ ታምናለች - Ecclesiology
- ቤተ ክርስቲያን የክርስቶስ አካል፤የክርስቶስ ሙሽራ የምታምን ቤተ ክርስቲያን ጤነኛ ናት።
9 ሰለመጨረሻው ዘመን ምን ብላ ታምናለች? - Eschatology
- ቤ/ክ እንደምትነጠቅ፣የመከራው ዘመን  በምድር ላይ  እንደሚመጣ የምታምን፣ ከክርስቶስ ጋር እንደገና በክብር እንደምትገለጥና  ከንጉሡ ጋር በክብር ነግሳ እንደምትኖር የምታምንም ቤ/ክ ጤነኛ ቤ/ክ ናት።

እንግዲህ የዶክትሪን ልዩነቶች ከላይ በተጠቀሱት ዙሪያ በሁሉም አብያተ ክርስቲያናት ሊኖር ይችላል። በወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያን ውስጥ በአብዛኛው ተቀራራቢ መረዳት አለ ብዬ አምናለሁ። በዚህ ምሳሌ ነገሬን ልደምድም.... ጊታር የሚጫወቱ ሰዎች ይህ ምሳሌ በቀላሉ ይገባቸዋል። ጊታር ስድስት ክሮች አሉት የሁሉም ድምጽ ይለያያል። ሁሉም አይጠብቁም ሁሉም ደግሞ አይላሉም። ከሚገባው በላይ የጠበቀ ድምስ ዲስኮርድ ይፈጥራል፤ ከሚገባው በላይም የላላ እንዲሁ። በዶክትሪንም ዙሪያ ከላይ የዘረዘርኩት የሚጠብቁ ናቸው.... ይህንን ማላላት አይቻልም። ስለዚህ የሚጠብቀውን አጥብቀን የሚላላውን እናላላ። በሚያጨቃጭቁ ዶክትሪን ዙሪያ ከመናቆር አንድነታችንን ጠብቀን ወንጌልን እናሩጥ!
ከኢየሱስ.ኮም ድረገጽ የተገኘና በጥቂት ማስተካከያ የቀረበ

Friday, February 10, 2012

«ኢያሱ ወልደ ነዌ በአባቶች እግር»



«ኢያሱ ወልደ ነዌ በአባቶች እግር»

ምድራችን አንዱን በአንዱ እየተካች እዚህ ዘመን ላይ ደርሳለች። ቀድሞ የነበረው ዛሬ የለም። ዛሬ ያለው ደግሞ ነገ ላይኖር ይችላል። በለውጥ ሂደት ውስጥ እንዳለን እንገነዘባለን። ዓለም እንኳን እየተለወጠች ነው። ድሮ የሌለ እምነት ዛሬ ተፈልስፏል። የነበረውም ቢሆን ገሚሱ ረስቶታል ወይም ከልሶታል አለያም ጥሩ አድርጎ አክርሮታል። ዝናባማው ዘመን በፀሐይ ተተክቷል። የሙቀት ጨምሯል ጩኸት፣ የዕለት ከዕለት ዜና ከሆነ ውሎ አድሯል። ሉላዊነት(Globalization) የሚሉት ስልጥንና በመንፈሳዊ ሀብት የሚታይ አብሮነትና አንድነት ባይኖረውም የሳይንስ ቁስ ዓለምን አቀራርቧል። ዓለምን ለመቃኘት ማጄላንን ወይም ኢብን ባቱታን መምሰል አይጠበቅብንም። ቁርስ አዲስ አበባ፣ ምሳ አቴንስ ለመመገብ ተችሏል። ድምፀትን ለመቀበል ወይም ለመስጠት ዛሬ ሁሉ ነገር የዓይንና የጆሮ ያህል ቀርቧል። ሲሰየጥኑ ይሁን ሲሰለጥኑ «ገንዘብ ካለ በሰማይ መንገድ አለ» የሚለው ትረካ ዓለምን እየነዳት ይገኛል። ይህ እንግዲህ ዓለም ደርሼበታለሁ የምትለው ግኝቷ ሲሆን የተቆላለፈው ችግሯ ደግሞ የትየለሌ ሆኗል።
ኤድስ የሚሉቱ አይድኔ በሽታ ብዙዎችን ወደ መቃብር ሸኝቷል። ኢቦላና የአእዋፍ ጉንፋን(BIRD FLU) ስንቱን ፈጅቶ የታገሰ ቢመስልም ጨርሶ እንዳልጠፋ ይወቃል። ካንሰር፣ ወባ፣ ስኳር፤ ግፊትና ብዛት፣ ማነስና ድክመት ልዩ ልዩ ህመሞች በርክተዋል፣ ወይም ህመምተኞችን አበራክተዋል። ከቺሊ እስከጃፓን፣ ከግሪንላንድ እስከ አንታርክቲካ የመሬት መንቀጥቀጡና የበረዶ መደርመሱ፣ የመሬት መናዱና ጎርፉ ብዙዎችን አጥፍቷል።
ሀይቲ 230,000 ሰው ሲሞትባት፤ሱናሚ ከኢንዶኔዢያ እስከ ሶማሊያ ጠረፍ ከ280,000 በላይ ሰዎችን መጥረጉን ሰምተናል። ጃፓንም ሀገር አማን ባለችበት ሀብቷን ሳይጨምር10 ሺዎችን ዜጋ አጥታለች።
ጦርነቱ፣ ፍጅቱ፣ የስልጣን ሽኩቻው፣ የሃይማኖት ፉክክሩ፣ የአሸናፊና ተሸናፊ ግብግቡ አይሏል። ያም ሆኖ ዓለም አለሁ፣ ማለቷን አልተወችም። ያለፈውን እየረሳች፣ መጪውን ትኖር ዘንድ ትጥራለች። «ገንፎ እየሞተ፣ ይተነፍሳል» እንዲሉ መሆኑ ነው። አዎ ዓለማችን እየሞተች መተንፈሷን አላቋረጠችም። ባለውና በሚታየው ነገር ለመጽናናት ትሻለች። ቁም ነገሩ ባለውና በሚታየው ነገር ፍጹም መጽናናትን ማግኘት አለመቻሏን አለማወቋ ነው። የተነገረውን አልሰማችም ወይም አልሰምቶም ሆኖባታል።
ማቴ 243-8
እርሱም በደብረ ዘይት ተቀምጦ ሳለ፥ ደቀ መዛሙርቱ ለብቻቸው ወደ እርሱ ቀርበው። ንገረን፥ ይህ መቼ ይሆናል? የመምጣትህና የዓለም መጨረሻ ምልክቱስ ምንድር ነው? አሉት።
ኢየሱስም መልሶ እንዲህ አላቸው፦ ማንም እንዳያስታችሁ ተጠንቀቁ።
ብዙዎች። እኔ ክርስቶስ ነኝ እያሉ በስሜ ይመጣሉና፤ ብዙዎችንም ያስታሉ።
ጦርንም የጦርንም ወሬ ትሰሙ ዘንድ አላችሁ፤ ይህ ሊሆን ግድ ነውና ተጠበቁ፥ አትደንግጡ፤ ዳሩ ግን መጨረሻው ገና ነው።
ሕዝብ በሕዝብ ላይ መንግሥትም በመንግሥት ላይ ይነሣልና፥ ራብም ቸነፈርም የምድርም መናወጥ በልዩ ልዩ ስፍራ ይሆናል፤
እነዚህም ሁሉ የምጥ ጣር መጀመሪያ ናቸው።
እናም ዓለም የምትወልደውን በምትወልድበት በመጨረሻው ወር ውስጥ ነው ያለችው። እንደነፍሰ ጡር ሴት በምትወልድበት በ9ኛው ወር ውስጥ እንዳለች ልትረዳና «ወልደ አብ፣ ኢየሱስ» 9ነኛው ሰዓት ያስተማራትን ጸሎት ልታሰማ ይገባታል። «
ማቴ2746
ዘጠኝ ሰዓትም ኢየሱስ፦ ኤሎሄ ኤሎሄ ላማ ሰበቅታኒ? ብሎ በታላቅ ድምፅ ጮኸ። ይህም። አምላኬ አምላኬ፥ ስለ ምን ተውኸኝ? ማለት ነው።

በዚህ ጽሁፍ ስለዓለም የዳሰስኩት ጽሁፌን በዚያ ላይ ለማንተራስ እንጂ ስለዓለም ለማስተማር ስላለሆነ ዋናው ነጥቤ ዓለም ያለችበትን ደረጃ በማሳየት የዓለም አንድ ክፍል የሆንን እያንዳንዳችን ከዚህ የዓለም ጣር ለመዳን ምን ማድረግ እንዳለብን «የኢያሱ ወልደ ነዌ»ን አብነታዊ መንገድ ለማሳየት ነው። ኢያሱ እንደልጅ ልጅ ሆኖ ኅሊናውን ሳያባክን፣ መንፈሳዊ ልቡናውን በጊዜው ከነበረው መሳሳቻ ጠብቆ የአባቶቹን እግር እንደተረከበ በማሳየት እኛም በዚያ መሠረትነት ላይ ቆመን ዛሬ ዓለምን ከሚንጣት ወጀብ በመዳን የኃጢአት ከተማ ኢያሪኰን አፍርሰን ርስታችንን ለመውረስ እንድንችል ለማስገንዘብ ነው። ፍየል በኃጢአተኛ የምትመሰልበት ዋናው ምክንያት፣ ግልገሎቿን አድፍጦ ወደበላባት የቀበሮ ጫካ ቅጠል ለመቀንጠስ ዳግመኛ የምትመለስ በመሆኗ ነው። እንዲሁ ሁሉ ከጎናችን ብዙዎች ንስሐ ሳይገቡ መሞታቸውን እያየን፣ በቅጽበታዊ አደጋ ዓለም ብዙዎችን እንደሸኘች እየተመለከትን፣ እኛ ዘንድ እንደማይደርስ አስበንና ለእነርሱ እያዘንን በመቆየት ሰንበትበት ሲል ሁሉን ነገር ረስተን እንደነበረው የምቀጥል መሆናችን ነው።

ይቀጥላል.............

Tuesday, February 7, 2012

ሞርሞኒዝም ምንድነው?


ካለፈው የቀጠለ
ክፍል 3
በባለፈው ጽሁፋችን ሞርሞኒዝም የብዙ አማልክት እምነት ቦታ ሆኖ የእምነቱ ተከታዮችም ወደዚህ ወደአማልክትነት ለመቀየር ብዙ መታገልና መጣር እንደሚገባው ተመልክተናል። የዚያኑ ቀጣይ ክፍል ደግሞ እነሆ አቅርበናል።
«እስራኤል ሆይ ስማ አምላካችን እግዚአብሔር አንድ እግዚአብሔር ነው»ዘዳ6፣4
እግዚአብሔር አንድ አምላክ ሆኖ ሳለ ብዙ አማልክት አድርጎ ማቅረብን ጆሴፍ ስሚዝ ከየት አመጣው? ብለን ብንጠይቅ መልሳችን አጭር ነው። ከሔዋን ጀምሮ ሲያሳስት የኖረው ሰይጣን በመኖሪያ ቤቱ ውስጥ የብርሃንን መልአክ መስሎ ከሰጠው መገለጥ የተገኘ ትምህርት ነው። መሐመድ በ7ኛው ክ/ዘመን «ሂሩ»ዋሻ እየሄደ ከአላህ መልአክ ከጅብሪል አገኘሁት ባለው በሚያንዘፈዝፍና በሚያንቀጠቅጥ መገለጥ አላህ አይወርድም፣አይወለድም፣ ዒሳ(ኢየሱስ) ነብይ እንጂ የእግዚአብሔር ልጅ አይደለም፣አልተሰቀለም፣ አልሞተም የሚል የክህደት ትምህርትን ከሰይጣን ተቀብሎ ለዓለም አስተላለፈ። እነሆ እልፍ አእላፋት ይህንኑ አምነው ይገኛሉ።
እግዚአብሔር አንድ አካል፣አንድ ገጽ ነው በማለት በመሐመድ በኩል ሲያሳስት የኖረው ሰይጣን በጆሴፍ ስሚዝ በኩል ደግሞ የለም «አምላክ ቁጥር ስፍር የለውም» ሲል መገኘቱ ሰይጣን የሰውን ልጅ ለማሳሳት መቼም ቢሆን አርፎ እንደማያውቅ ነው። እሱ ስራው ሰው የሚጠፋበት መንገድ ማዘጋጀት፣ ከእውነት ጋር የስህተት ትምህርቶችን አቀላቅሎ መስጠትና ለጥፋት ማዘጋጀትን መደበኛ ስራው አድርጎ ይንቀሳቀሳል። የሚገርመው ግን እስላሞች ይሁኑ ሞርሞኖች ያለእነርሱ ሌላው እንደማይጸድቅ፣ ሲኦል እንደሚወርድና ፈጣሪ የወደድኩት ሃይማኖት የእናንተን ነው እንዳላቸው አድርገው ራሳቸውን አሳምነው መገኘታቸው ነው።

Saturday, February 4, 2012

ማኅበሩ አያንቀላፋም!

« ማኅበሩ አያንቀላፋም»

እንቅልፍ ለሰዎች የተሰጠ የሥጋ እረፍት ነው። «ቀን ለሰራዊት፣ሌሊት ለአራዊት»እንዲሉ! ዛሬ ግን ዓለማችን ቀንና ሌሊቱን አቀላቅላው ሰውም አራዊቱም ጉዞአቸው ባንድ ሆኗል። በሌሊት! ከነዚህ ቀኑንም ሌሊቱንም ከማያንቀላፋው ሀገርኛ ድርጅት አንዱ ራሱን በራሱ የቅዱሳን ማኅበር ነኝ የሚለው «ማኅበረ ቅዱሳን» በቁልምጫ ስሙ «ማቅ» የተባለው ድርጅት ነው። በቤተክርስቲያን ውስጥ ስፍራውና ድርሻው ለጊዜው ባይገባንም ረጅምና ስውር እጁ የሌለበት ቦታ የለም በሚባል ደረጃ ያለእረፍት ይንቀሳቀሳል። ለዚህም ነው የጽሁፋችንን ርእስ «ማኅበሩ አያንቀላፋም» ያልነው። አዎ! ማኅበረ ቅዱሳን አያንቀላፋም። የማያንቀላፋው ራሱን የቤተክርስቲያን ተጠሪ በማድረግና ሲኖዶሱ ባልሰጠው ውክልና በቤተክርስቲያኒቱ መዋቅር ውስጥ ስውር እጁን እንደአባጨጓሬ እያርመሰመሰ በመገኘቱ ነው። ማኅበሩ በሲኖዶስ መሃል ቁጭ ብሎ በስውር እጁ ጳጳስ ሆኖ ይወስናል፣ ያስወስናል፣ይከራከራል፣ይሞግታል። ለሲኖዶሱ አጀንዳ ይቀርጻል፣ የማይስማማውን ይጥላል፣ የፓትርያርኩ የራስ ህመም እስኪነሳ ያሳብዳል። ምክንያቱም ማኅበሩ ጳጳስ ስለሆነ አያንቀላፋም። በአምሳለ ጳጳስ «ማኅበረ ቅዱሳን ባይኖር ቤተክርስቲያን ምን ተስፋ አላት» ያሰኛል። በአድባራትና ገዳማትም መካከል ሳያንቀላፋ በአለቃነት ወይም በሀገረ ስብከት ደረጃ በሥራ አስኪያጅነት ወይም በመምሪያ ኃላፊነት ውስጥም ኅቡእ መንፈስ ሆኖ ይንቀሳቀሳል። የሰባኪዎችን፣የሰንበት ት/ቤቶችን ወይም የምእመናንን ማንነት ይቆጣጠራል፣ ይመረምራል፣ ይሰልላል። ማኅበረ ቅዱሳን አያንቀላፋምና እዚህም ቦታ አለ። ንግዱ ውስጥ! ይነግዳል፣ያስነግዳል። ግብርና ታክስ የማይከፍል የንግድ ተቋም ሆኖ በሆቴሎች፣ በሱቆች፣ በንዋያተ ቅድሳት መሸጫዎች፣በኢንኮርፖሬትድ ድርጅቶች፣ በህትመት፣ በሚዲያ ውጤቶች ውስጥ ሁሉ አለ።

ሞርሞኒዝም!

 

በዳኒ ይትባረክ የተጻፈ( በደጀብርሃን ለብሎጉ እንዲያመች የቀረበ)
.... ክፍል ሁለት

                            ሞሮኒ ማነው?

ስለዚህ ሰው በመጽሐፍም ይሁን በታሪክ ምንም ዓይነት መረጃ አናገኝም። መዝገበ ቃላትም ቢሆን ሞሮኒ(MORONI)የኮሞሮስ ዋና ከተማ መሆኗን እንጂ ሌላ የሚሰጠን ፍንጭ የለም። ታዲያ ይህ ሞሮኒ የተባለው የጆሴፍ ስሚዝ ሰው ማነው?
በመጽሐፈ ሞርሞን (THE BOOOK OF MORMON) መግቢያ ላይ «,,አ በ421 /ም ገደማ መጨረሻ አካባቢ የኔፊ(*) ባለታሪክና ነብይ የነበረ «ሞሮኒ» በጥንታዊ ነብያት አማካይነት በእግዚአብሔር ድምጽ በኋለኛው ቀን እንደሚመጣ እንደተተነበየው ቅዱሱን መዝገብ አተመው፣ እናም በጌታ እንዲጠበቅ ደበቀው» ካለ በኋላ በጌታ ተደብቆ የተቀመጠው ሞሮኒ ከሞት ተነስቶ በ1823 /ም በቤቱ እየጸለየ ሳለ የተገለጠለትና እጅግ በሚደንቅ ግርማ እንደታየው የጆሴፍ ስሚዝ መጽሐፍ ያትታል።
እንግዲህ ሞሮኒ ማለት እንደተከታዮቹ አባባል በ421 /ም ሞቶ በ1823 /ም ትንሳዔ በማግኘት ለጆሴፍ ስሚዝ የተገለጠ መልአክ ነው ማለት ነው።
ከዚህ አባባል የምንረዳው ነገር ሰይጣን በኢየሱስ ክርስቶስ ሕይወት የታየውን መለኮታዊ መልክ በሚመስል ነገር በሞሮኒ ስም ለጆሴፍ ስሚዝ በመገለጥ እንደሆነ እንረዳለን።
ሰይጣን ጆሴፍ ስሚዝን እንዳታለለው ዛሬም ቢሆን ህልም አለምኩ፣ ራዕይ አየሁ፣ መልዕክት መጣልኝ፣ እመቤታችን ታየችኝ፣ እሳት ከሰማይ ወረደ፣ በዘንዶ የሚጠበቅ ቤተክርስቲያን፣ በእባብ የታጠረ ጸበል በሚል ሰበብ በክርስትናው ውስጥ ዛሬም ብዙ ጆሴፎች አሉ።)
ሰይጣን መቼም አይተኛም። ጆሴፍ ስሚዝን እንዳጭበረበረው እኛንም ሊያጭበረብረን ይፈልጋል። ምክንያቱም ለሞርሞኖች ተስፋቸው አዲስቱ ኢየሩሳሌም ሳትሆን አሜሪካ ነች። ከድርሳናቸው አንዱ ክፍል ኔፊ እንዲህ ይላል።
«የያዕቆብ ቅሪት የሆኑትም ጌታ አምላካቸውን ወደማወቁ ይመጣሉ፣ እናም አሜሪካንን ይወርሳሉ» 3ኔፊ201
ጆሴፍን አሜሪካ የርስት ምድር እንደሆነችና አሜሪካንን የሚናፍቁ ሕዝቦች የሚፈጠሩበት ዘመን እንደሚመጡ ያኔም ሞሮኒ የተነበየላት ስለሆነ እንደሚባረኩ መዋሸቱን ስንመለከት ይህ ሰይጣን በኢትዮጵያም ውስጥ መልኩንና ማሳሳቱን ለውጦ «ደጅህን የረገጠ ኢየሩሳሌምን እንደተሳለመ እቆጥርለታለሁ ብሎ ቃል ገብቶለታል፣ ፍርፋሪህን የበላ የ40 ቀን ህጻን አደርግልሃለሁ ብሏል፣ በስሜ የተጠራ ዘው ብሎ ገነት ይገባል፣ የቅዳሴዬን ጸበል የቀመሰ 30 ትውልድ ሰተት አድርጌ ገነት አገባልሃለሁ ወዘተ ሞርሞናዊ ማሳሳቻዎች ከሰይጣን የወጣ ስለመሆኑ የታወቀ ነው። ሰይጣን ምን ጊዜም ክርስቶስ ያደረገልንን የሕይወት ስጦታ በመቀየር ወደሌላ የማዳኛ ምክንያቶች ለመለወጥ ሳይደክም እንደሚሰራ እንረዳለንና ነው።
ሐዋርያው እንዲህ ብሏል።« ስለዚህም ምክንያት፥ በእውነት ያላመኑ ነገር ግን በዓመፅ ደስ ይላቸው የነበሩ ሁሉ ፍርድን እንዲቀበሉ፥ ሐሰትን ያምኑ ዘንድ እግዚአብሔር የስሕተትን አሠራር ይልክባቸዋል»2ተሰ 211-12


               ሞርሞኖች ስለእግዚአብሔር ያላቸው አስተምህሮ

ሞርሞኖች በአጽናፈ ዓለም ላይ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ፕላኔቶች እንዳሉ፣ በነዚህም ፕላኔቶች ላይ በአንድ ወቅት ሰዎች ይኖሩበት እንደነበረና አሁን ግን አማልክት በሆኑ ኃይሎች እንደሚተዳደሩ ያምናሉ። ከዚህም በተጨማሪ እግዚአብሔርን በተመለከተ 4 ዓይነት አስተምህሮዎች አላቸው።
1/ እግዚአብሔር ሥጋና ደም አለው ይላሉ።
2/እግዚአብሔር አምላክም ሰውም ሆኖ በሰማይ አለ ይላሉ።
3/አማልክት አባት፣ እናት፣ አያት ወዘተ ሆነው በዘር ሐረግ በየፕላኔቶቹ አሉ ብለው ያምናሉ።
4/ እያንዳንዱ ሞርሞናዊም ወደአማልክትነት ለመቀየር መጣር አለበት ይላሉ።
(Mormon doctrine, page 557 &, Doctrine & covenantes section 130. verse 22)

.....ይቀጥላል
(*) የተመለከተው «ኔፊ» የሞርሞኖች ድርሳን ነው።

Friday, February 3, 2012

ሞርሞኒዝም !

            ሞርሞኒዝም ምንድነው? 

በዳኒ ይትባረክ

ሞርሞኒዝም የሞርሞንን የእምነት ፍልስፍና መከተል ማለት ሲሆን የዚህ የእምነት ፍልስፍና መስራቹ ደግሞ ጆሴፍ ስሚዝ ይባላል።

                 ጆሴፍ ስሚዝ ማነው? 

ጆሴፍ ስሚዝ ኒዮርክ ውስጥ ሻሮን ቬርሞንት በሚባል አካባቢ ይኖር የነበረ ሰው ሲሆን የተወለደውም እ,ኤ,አ በ1805 ነው። በሚኖርበትም አካባቢም ማዕድን ለማግኘት ሲል አስማታዊ ልምምድን ያደርግ እንደነበር የብሪንግሃም ዩኒቨርሲቲ የታሪክ ፕሮፌሰር ሚካኤል ኪውን «Early Mormonizm in the Magic World» በሚለው መጽሐፋቸው ላይ ጠቁመዋል። ብሪንግሃም ዩኒቨርሲቲም የሞርሞኖች ዩኒቨርሲቲ ነው። ስለዚህ እኛ ከዚህ ፍንጭ በመነሳት ጆሴፍ ስሚዝ መተተኛ ወይም ድግምተኛ ነበር ብንል ስህተት አይሆንም።

            ሞርሞኒዝም መቼ ተጀመረ? 

ሞርሞኒዝም የተጀመረው በነጮቹ አቆጣጠር በ1830 ሲሆን የተጀመረውም ጆሴፍ ስሚዝ ተገለጠልኝ ባለው መገለጥ አማካይነት ነው። ጽሁፋቸውን ስናነብ ጆሴፍ ስሚዝ ከ14 ዓመቱ ጀምሮ «የትኛዋ ቤተክርስቲያን ትሆን ትክክል?» የሚል ጥያቄ እንደነበረውና አንድ ቀን «አብና ወልድ» ተገልጠው እውነተኛይቱ ቤተክርስቲያን ምድር ላይ እንደሌለችና በእርሱ( በጆሴፍ በኩል) እንደሚያስተካክሏት ከነገሩት በኋላ ወደየትኛዋም ቤተክርስቲያን እንዳይሄድ እንደከለከሉት «the testimony of the prophet Joseph Smith, page, 1» ላይ ተቀምጦ ይገኛል።

                      የጆሴፍ ስሚዝ ራዕይ

ጆሴፍ ስሚዝ በ1823 መስከረም 21 ቀን ምሽት ላይ አምላክ ነው ወደሚለው እየጸለየ ሳለ የተገለጠለትን ራዕይ እንዲህ በማለት ተናግሯል። «እግዚአብሔርን በመጥራት ላይ ሳለሁ ብርሃን በነበርኩበት ክፍል ሲመጣ አየሁ፣ ብርሃኑም ከቀትር ጸሀይ ይበልጥ ነበር፣ ወዲያውም አንድ ሰው በአልጋዬ አጠገብ እግሩ መሬት ሳይነካ በአየር ላይ ተገለጠልኝ,,» ሲል ከተናገረ በኋላ የተገለጠለት ሰው መልክና ማንነት ከመነገር በላይ እንደነበር ተርኳል። አንዳንድ መጽሐፍ ቅዱሳዊ መገለጦችን መነሻ አድርገን ለጆሴፍ የተገለጠለት ኢየሱስ ክርስቶስ ይሆን እንዴ? ብለን ብንገምት ግምታችን ግምት ሆኖ የሚቀረው ጆሴፍ ስሚዝ የተገለጠለትን ሰው ማንነት ሲነግረን ነው። እሱም «ሞሮኒ» የተባለ ነው።

               ሞሮኒ ማነው?

ይቀጥላል.................

Thursday, February 2, 2012

በጋሻውን ለማጥቃት፤ሕሙምን መበቀል?

ከደጀብርሃን፤
ለልብ ሕመምተኛው የድረሱለት ጥሪ ማቅረብ ተሀድሶን መደገፍ ነው! አንድ አድርገን ብሎግ(እዚህ ላይ ይጫኑ)
በጠቅላይ ቤተክህነት አዳራሽ የቤተክርስቲያን በዓላት ሲከበሩ ከካቶሊክ ፣ ከግሪክ እና ከሌሎች ተቋማት በእንግድነት እንደሚጠሩ ይታወቃል። ምነው ያኔ በሃይማኖት የማይመስሉን ተገኝተዋል የሚል ተቃውሞ ያልቀረበ?
ጉዳዩና ቂም በቀሉ ያለው ለህመምተኛው የእርዳታ ጥሪ ለማድረግ የተንቀሳቀሱት እነትዝታው ሳሙኤል፣ እነምርትነሽ ጥላሁን በመሆናቸው ብቻ ነው። ምርትነሽ በመዝሙሯ ያስተማረችውንና ያነጸችውን የክርስትና ምግባር ዋጋ ማሳጣት ለምን?
እነምርትነሽ ካልጠፉ የልብ ህሙምም የእርዳታ በሩ ድርግም ይበልበት ክርስትና ነው? ወይስ ጸረ ክርስትና?
ያገኘነውን መረጃ እናካፍላችሁ! መልካም ንባብ!
ለእንዳለ ገብሬ የተዘጋጀው የዕርዳታ ገቢ ማሰባሰቢያ ጉባዔ በቀሲስ ሳሙኤል እሸቱ የግል ውሳኔ ታገደ ዕገዳው ቀሲስ ሳሙኤል በሰው ሕይወት ላይ ያስተላለፉት ውሳኔ በመሆኑ፣ በወንጀል ሊያስጠይቃቸው ይችላል ቤተክርስቲያን የበላይ ኃላፊ ሲያዝ፣ የበታች ኃላፊ የሚሽርበት ሥርዓት አልበኝነት የነገሠባት ተቋም ሆናለች በከፍተኛ የልብ ሕመም ለሚሰቃየው እንዳለ ገብሬ ማሳከሚያ የሚውል ገቢ ለማሰባሰብ ጥር 20 ቀን 2004 ዓ.ም የተዘጋጀው ጉባዔ በቀሲስ ሳሙኤል የግል ውሳኔ መታገዱ ከጠቅላይ ቤተክህነት ጽ/ቤት ያገኘነው መረጃ አመለከተ፡፡ ታማሚው አቶ እንዳለ ገብሬ ቤተክርስቲያን ድጋፍ እንድታደርግለት ባቀረበው ማመልከቻ ላይ ብፁዕ አቡነ ፊሊጶስ በስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዊ ተልዕኮ መምሪያ በኩል አስፈላጊው የገቢ ማሰባሰቢያ ጉባዔ እንዲዘጋጅለት መርተውለታል፡፡ የመምሪያው ኃላፊ መምህር አዕመረም በግል ከታማሚውና ከልዩ ልዩ ክፍሎች ጋር በመነጋገር ጉባዔውን የሚያዘጋጁት መምህራን የስብከት አገልግሎት ማስረጃዎችን ከመንፈሳዊ ኮሌጆችና ከአጥቢያ ቤተክርስቲያናት አቅርበው እንዲያካሂዱለት ከመወሰናቸውም በላይ አንድ የፕሮግራም መሪ እና የስብከት መምህር ከጠቅላይ ቤተክህነቱ በማከል ጉባዔው በተጠቀሰው ዕለትና ቦታ እንዲካሄድ ወስነው ወደ ባህርዳር አካባቢ መጓዛቸው ታውቋል፡፡ ይሁን እንጂ ጉባዔው ካልታገደ ተኝተን አናድርም ያሉት የ"ማኅበረ ቅዱሳን" ሠራዊት አባላት መምህር አዕመረ አለመኖራቸውን አይተው የመምሪያውን ምክትል ኃላፊ ቀሲስ ሳሙኤል እሸቱን በመወትወትና በማስፈራራት ጭምር አለቃው የወሰኑትን በመሻር የዕገዳ ማስታወቂያ እንዲያወጡ ያዟቸዋል፡፡ ቀሲስ ሳሙኤል እሸቱም ያለአንዳች ማቅማማት የአለቆችን ትዕዛዝ በመሻር ጉባዔው መታገዱን ዓርብ አመሻሽ ላይ ማስታወቂያ የለጠፉ ሲሆን፣ የአዳራሽ ቁልፍ የያዘውን አቶ በሪሁንን ቁልፉን ይዞ ከአካባቢው እንዲሰወር በመንገር ጉባዔ አለብኝ በማለት ወደ ድሬዳዋ ተጉዘዋል፡፡ ቅዳሜና እሁድ ጉዳዩ የሚመለከታቸው ኃላፊዎች ሆን ብለው ይሁን በአጋጣሚ በሥፍራው ባለመኖራቸው ጉባዔው እንዲካሄድ ማስደረግ ባለመቻሉ አስተባባሪዎች ፕሮግራሙን ለመሠረዝ መገደዳቸው ታውቋል፡፡ የዕርዳታ ጥሪውን በመስማት ወደ ጠቅላይ ቤተክህነት አዳራሽ የተመመው ሕዝብ በርካታ ሲሆን፣ ለምን ይታገዳል በሚል ብሶት ውስጥ ስለነበር ከአቅም በላይ በሆነ ምክንያት ለሌላ ቀን መተላለፉ በማስታወቂያ እንዲነገረው ተደርጓል፡፡ ታማሚው አቶ እንዳለ ታክሞ ለመዳን የቀረው ከአንድ ወር ያነሰ ጊዜ ሲሆን እስከ መጨረሻው ሰዓት ከቀሲስ ሳሙኤል እሸቱ ዘንድ በመሄድ "ስለ እግዚአብሔር ብለው አይጨክኑብኝ" ብሎ ቢማፀንም፣ ቀሲሱ ከ"ማኅበረ ቅዱሳን" ለሚሰጣቸው ድርጎ ልባቸው ተሸንፎ ክርስቲያናዊ ግዴታቸውን ሊወጡ አልቻሉም፡፡ ቤተክርስቲያን የዕርዳታ እጆቿን ስትዘረጋ ዕርዳታው በአግባቡ እንዳይደርስና የታማሚው ሕይወት አደጋ ላይ እንዲወድቅ ማድረግ በኃላፊነት የሚያስጠይቅ ከመሆኑም በላይ አደጋ ላይ ያለን ሰው በቸልተኝነት (ምን አገባኝ በሚል ስሜት) ተገቢውን አለማድረግ ራሱን የቻለ ወንጀል መሆኑ በወንጀለኛ መቅጫ ሕጉ ተደንግጓል፡፡ ጉዳዩ በዚህ ብቻም የሚታለፍ ሳይሆን ቤተክርስቲያናችን ዘርና ቋንቋ፣ ሃይማኖትና ጾታ ሳትለይ ለማንኛውም ሰብዓዊ ፍጡር ዕርዳታ የምትሰጥ ከመሆኑ አንፃር የቤተክርስቲያናችንን መልካም ገጽታ የሚያጎድፍ እኩይ ተግባር ነው፡፡ የጉባዔው አስተባባሪዎችም አስፈላጊውን መረጃዎች አሟልተው በቤተክርስቲያን ልጆች አገልግሎቱ የሚሰጥ በመሆኑ፣ ጉባዔው የሚታገድበት አንዳች ምክንያት አልነበረም፤ የለምም፡፡ በቤተክርስቲያናችን፣ በተለይም "ማኅበረ ቅዱሳን" እንደልብ ጣልቃ እየገባ ማተረማመስ ከጀመረ ወዲህ ሥርዓት ታውኳል፡፡ ማንም ማንንም ከማይሰማበት ደረጃ ላይ ተደርሷል፡፡ ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ፣ ቅዱስ ሲኖዶስና የጠቅላይ ቤተክህነት ሥራ አስኪያጁ የሚያስተላልፉት መመሪያና ትዕዛዝ በተራ የበታች ሠራተኞች ይሻራል፤ ይቀለበሳል፡፡ የአቶ እንዳለን ጉዳይ እንደማሳያ ብንቆጥረው የመንበረ ፓትርያርክ ልዩ ጽ/ቤት፣ የጠቅላይ ቤተክህነት ሥራ አስኪያጅ ጽ/ቤትና የስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዊ ተልዕኮ መምሪያ የሰጡት ትዕዛዝ በአንድ ቀሲስ ሳሙኤል እሸቱ ተሽሯል፡፡ በሪሁን የተባለው የአዳራሽ ቁልፍ ያዥ ቁልፉን ይዞ ተሰውሯል፡፡ ይህ በቤተክርስቲያን የተካሄደ ውንብድና እንጂ አገልግሎት ሊባል አይችልም፡፡ ዓለም በግልፀኝነትና በተጠያቂነት ዘመን ስትራመድ ቤተክርስቲያን ግን ርስ በርስ መጠላለፍ በበዛበት እና የጨለማው ዓለም ተንኮል ተተብትባ ስትታይ ይህንን ትውልድ በእጅጉ ያሰቅቀዋል፡፡ ውሳኔዎች የሚመሩት በእምነትና በሥርዓት መሆኑ ቀርቶ፣ ገንዘብ የዳኝነቱን ቦታ ሲረከብ ማየት ያለንበትን አሳዛኝ ሕይወት ያመላክታል፡፡ የእግዚአብሔር ምሕረትና ጥበቃው ከእኛ አይለይ!!! አሜን!!! Posted by Dejeselaam at 1:48 AM
source' dejeselaam blog