Wednesday, November 30, 2011

ሰዶምና ገሞራ ወደኢትዮጵያ?


ማናቸውም ሰው ከሴት ጋር እንደሚተኛ ከወንድ ጋር ቢተኛ ሁለቱ ጸያፍ ነገር አድርገዋል ፈጽመው ይገደሉ ደማቸው በላያቸው ነው» ዘሌ 20፣13
በኢትዮጵያ የአራቱም ሃይማኖቶች መሪዎች በአዲስ አበባ በቅርቡ በሚካሄደው 16ኛው የአይካሳ ጉባዔን አስታክኮ በአገሪቱ ጸያፍ፣ ከሥነ ምግባር ውጭና ባህልን የሚያንቋሽሽ አጀንዳ ለማስፈጸም ተነሣሥቷል ያሉትን የአንድ ቡድን እንቅስቃሴን በመቃወም ትናንት ሊሰጡት የነበረው ጋዜጣዊ መግለጫ ላልተወሰነ ጊዜ ተላለፈ፡፡
የሪፖርተር ፎቶግራፍ ጋዜጠኛ መሪዎቹ መግለጫ ለመስጠት እንደተዘጋጁ ያነሳውም ፎቶግራፎች እንዲጠፉ ተደረገ፡፡

መሪዎቹን በመወከል መግለጫው ለሌላ ጊዜ መተላለፉን ያስታወቁት ከኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ ቄስ ኢተፋ ጎበና ሲሆኑ፣ የጋዜጠኛው ፎቶ ግራፎች እንዲጠፉ ያደረገውም በሥፍራው የነበረ አንድ የደኅንነት አባል ነው፡፡

መግለጫው የሚሰጥበት ትክክለኛው ቀን መቼ ነው ተብሎ ከጋዜጠኞች ለቀረበላቸው ጥያቄ ‹‹ከጉባዔው በፊትም ሆነ በኋላ ሊሆን ይቻላል፡፡ ከዚህ ውጭ ትክክለኛው ቀን ይህ ነው ብዬ ለመናገር ያስቸግረኛል፤›› ሲሉ ቄስ ኢተፋ መልሰዋል፡፡

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን፣ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት፣ የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያን፣ የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ መሪዎች በተወካያቸው አማካይነት መግለጫው ላልተወሰነ ጊዜ መተላለፉን ያስታወቁት፣ የጤና ጥበቃ ሚኒስትሩ ዶክተር ቴዎድሮስ አጽሃኖም በተገኙበት የዝግ ስብሰባ አድርገው በጉዳዩ ላይ ለአንድ ሰዓት ያህል ከተወያዩ በኋላ ነው፡፡

ጉልበተኛው ረባሽ!!




ቦረና ሀገረ ስብከት በክብረ መንግሥት ከተማ በጽርሐ አርያም ቅዱስ ሚካኤል አጥቢያ ቤተክርስቲያን እስከ ህዳር 19 ቀን 2004 ዓ.ም ላለው ጊዜ የተዘረጋው የእግዚአብሔር መንግሥት ወንጌል ጉባዔ መቋረጡን በዚያው ያሉ ምንጮቻችን አረጋግጠዋል፡፡ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች በተደጋጋሚ እንደሚደረገው የ"ማኅበረ ቅዱሳን" ቡችሎች በለኮሱት ሁከት ጉባዔው መቋረጡ ታውቋል፡፡ በተለይም የግጭቱ አስተባባሪ በመሆን ቀዳሚውን ድርሻ የወሰደው ያሬድ ውብሸት የተባለ የማኅበሩ አባል ሲሆን፣ ይኸው ግለሰብ ለማኅበሩ መረጃ በማቀበልና በመሰለል ወንድሞችን ለአደጋ የሚጥል መሆኑ ጭምር ተገልጿል፡፡ በዚሁ ጉባዔ ላይ፣ ለጊዜው ስሙና ማንነቱ ካልተገለጸ ሌላ ግለሰብ ጋር በመሆን ጠቡን እንዳስነሱት የታወቀ ሲሆን፣ ይኸው ግብረ አበር ሰዎችን ከደበደበ በኋላ ጌታዋን እንደተማመነች በግ ከተማዋ ውስጥ በነፃነት ሲንሸራሸር፣ የወንጌል መምህር የሆኑትን ቀሲስ ተስፋዬ መቆያን ለእሥራት እንዳበቋቸው የደረሰን መረጃ ያመለክታል፡፡

የክብረ መንግሥት ጽርሐ አርያም ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን፣ ቀሲስ ተስፋዬ መቆያ ከፊደል ቆጠራ እስከ ዲቁና ከዚያም እስከ ቅስና ያገለገሉባት፣ ጥርስ ነቅለው ያደጉባት እናት ቤተክርስቲያናቸው ስትሆን፣ የከተማዋ ምዕመናን የወንጌሉ የምሥራች ቃል እንዲሰበክላቸውና በመንፈሳዊ ሕይወታቸው እንዲጎለብቱ፣ የዘማሪያንንና የሰባክያንን ወጪዎች በመሸፈን ጭምር በተደጋጋሚ የወንጌል ጉባዔ ያዘጋጁ ቅን የቤተክርስቲያን አገልጋይ መሆናቸው ተገልጿል፡፡

Sunday, November 27, 2011

ታቦት በአዲስ ኪዳን እንዴት?




ታቦት በአዲስ ኪዳን እንዴት?to read in PDF

ለዚህ ጽሑፍ መነሻ የሆነው በኢቢኤስ ቴሌቪዥን በዲያቆን ዓባይነህ ካሴ የተሰጠውና ስለጽላት የአዲስ ኪዳን ዘመን አስፈላጊነት ስብከቱ የተነሳ ነው። አባይነህ ካሴ ያልገለጻቸው፣ ያልመለሳቸውና ያላብራራቸው፣ ነገር ግን በምንም መልኩ ሊታለፉ የማይገባቸው ነጥቦች ስላሉ በዚህ ጽሁፍ ይዳሰሳሉ። ምክንያቱም ለክርስቲያኖች ከየትኛውም መረጃ በላይ የእምነታቸው መሠረት መጽሐፍ ቅዱስ ሲሆን እሱም ሳይሸፋፍን ለብሉይ ኪዳኑ ሥርዓትም ይሁን ለአዲስ ኪዳኑ ዘመን እምነት መመሪያን፣ትእዛዛቱንና መንገዶቹን በግልጽ አስቀምጦት ስለሚገኝ ነው።
ዓባይነህ ካሴ ስሜቶቹን ከመጽሐፍ ቅዱስ ጋር እያዛመደ በዚህ የጽላት ዓለም እምነት ላሉ፣ በዚያው እንዲጸኑ፣ ይህንን ለማይቀበሉት ደግሞ ለሚያነሷቸው ጥያቄዎች መልስ በመስጠት የሁለት ወገን ስራውን ለመስራት ሞክሯል። ይሁን እንጂ መረጃውን በማብራሪያ ለማጠናከር ከመሞከር ባለፈ በተጨበጠ ማስረጃ ማስደገፍ ባለመቻሉ ግልጽ እውነቶችን እያነሳንሥነ አመክንዮ «Give reasons or cite evidence in support of an idea, action, or theory, typically with the aim of persuading others to share one's view» እንሰጥበታለን።
ታቦት ለእስራኤል ዘሥጋ ያስፈለገበት ዋናው ምክንያት
ነብዩ ሙሴ ከእግዚአብሔር ቃል እየተቀበለ ለሕዝቡ መልእክቱን ያደርስ ነበር።
ዘጸ 3፣15 እግዚአብሔርም ደግሞ ሙሴን አለው። ለእስራኤል ልጆች እንዲህ ትላለህ። የአባቶቻችሁ አምላክ፥ የአብርሃም አምላክ የይስሐቅም አምላክ የያዕቆብም አምላክ እግዚአብሔር ወደ እናንተ ላከኝ ይህ ለዘላለሙ ስሜ ነው፥ እስከ ልጅ ልጅ ድረስም መታሰቢያዬ ይህ ነው።

Saturday, November 26, 2011

ይድረስ ለቀሲስ ደጀኔ!!


«እስራኤል ዘሥጋን በመንገዳቸው ሁሉ የጠበቃቸው፥ መና ከሰማይ ያወረደላቸው፥ ተአምራትን ያደረገላቸው፥ ማርና ወተት ወደምታፈስሰው ርስታቸው የመራቸው፥ በደመና መጋረጃ የጋረዳቸው፥ በክንፎቹም የሸፈናቸው መጋቤ ብሉይ የተባለ ቅዱስ ሚካኤል ነው»በማለት በብሎግዎ ላይ ጽፈዋል። ገረመኝና አንዳንድ ጥያቄዎችና መጽሐፍ ቅዱሳዊ ማስረጃዎችን አቀረብኩልዎ!!
ቀሲስ ደጀኔ ሽፈራው- ይህንን ከየትኛው መጽሐፍ ላይ አገኙት? ሚካኤል ነው የሚል ተጽፏል? ወይስ ነገረ ሥራው ሚካኤልን ይመስላል ብለው ያልተገለጸውን አቅኚ ሆነው ነው? እግዚአብሔር ሚካኤል ስለመሆኑ ያልገለጸው ረስቶ ወይም ተሳስቶ እርስዎ ግን በትርጉም ፈትተውት ያገኙት እውቀት ነው?
መቼም እንደማይቀበሉኝ አውቃለሁ፣ እኔን ሳይሆን ለዚያውም መጽሐፍ ቅዱስን።
ዘፍ  21፥17
    31፥11
     48፥16
ዘጸ  3፥2
    14፥19
    33፥1-3
ዘኁ  22፥22 - 22፥23 - 22፥24 - 22፥25 - 22፥26 - 22፥27 - 22፥31   -  22፥32    22፥34   22፥35  
አንድም ቦታ ሚካኤል የሚል ስም ተጠቅሶ አይገኝም። እግዚአብሔር ስሙን ያልጠቀሰው ለምን ይመስልዎታል? እኛስ ስሙን መጥቀስ ለምን ይገባናል? የኛ መጥቀስ እግዚአብሔር ያልጠቀሰውን ጉድለት ለመሙላት ነው ወይስ ስውር  የሆነውን ሚካኤል በትርጉማችን ገልጸን በማውጣት መልአኩን ለማክበር?
ለዚያውም ስሙ ባልተገለጸ መልአክ እጅ እግዚአብሔር ያደረገውን ድንቅና ተአምራት ለሚካኤል ለመስጠት «እስራኤል ዘሥጋን በመንገዳቸው ሁሉ የጠበቃቸው፥ መና ከሰማይ ያወረደላቸው፥ ተአምራትን ያደረገላቸው፥ ማርና ወተት ወደምታፈስሰው ርስታቸው የመራቸው፥ በደመና መጋረጃ የጋረዳቸው፥ በክንፎቹም የሸፈናቸው መጋቤ ብሉይ የተባለ ቅዱስ ሚካኤል ነው» ማለት በፍጹም ትልቅ ስህተትና ክህደት ነው።
 እርስዎ እግዚአብሔር ያለውን ለምን መተው ይወዳሉ?
 ዘፍ 28፣15 «እነሆም እኔ ከአንተ ጋር ነኝ፥ በምትሄድባትም መንገድ ሁሉ እጠብቅሃለሁ፥ ወደዚችም ምድር እመልስሃለሁ የነገርሁህን ሁሉ እስካደርግልህ ድረስ አልተውህምና»
 ዘጸ 6፣6 «ስለዚህም ለእስራኤል ልጆች እንዲህ በላቸው። እኔ እግዚአብሔር ነኝ፥ ከግብፃውያንም ባርነት አወጣችኋለሁ፥ ከተገዥነታቸውም አድናችኋለሁ በተዘረጋ ክንድ በታላቅ ፍርድም እታደጋችኋለሁ»

ዘጸ 6፣7ለእኔም ሕዝብ እንድትሆኑ እቀበላችኋለሁ፥ አምላክም እሆናችኋለሁ እኔም ከግብፃውያን ባርነት ያወጣኋችሁ እግዚአብሔር አምላካችሁ እንደሆንሁ ታውቃላችሁ።

ዘጸ 6፣8 «ለአብርሃምና ለይስሐቅ ለያዕቆብም እሰጣት ዘንድ ወደ ማልሁባት ምድር አገባችኋለሁ እርስዋንም ርስት አድርጌ እሰጣችኋለሁ እኔ እግዚአብሔር ነኝ»
ዘጸ 10፣3 «ሙሴም አሮንም ወደ ፈርዖን ገቡ፥ አሉትም። የዕብራውያን አምላክ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ በፊቴ ለመዋረድ እስከ መቼ እንቢ ትላለህ? ያገለግሉኝ ዘንድ ሕዝቤን ልቀቅ»
ዘጸ 13፣21 «በቀንና በሌሊትም ይሄዱ ዘንድ፥ መንገድ ሊያሳያቸው ቀን በደመና ዓምድ፥ ሊያበራላቸውም ሌሊት በእሳት ዓምድ እግዚአብሔር በፊታቸው ሄደ»
ዘጸ 14፥24
ንጋትም በሆነ ጊዜ እግዚአብሔር በእሳትና በደመና ዓምድ ሆኖ የግብፃውያንን ሠራዊት ተመለከተ፥ የግብፃውያንንም ሠራዊት አወከ። 25 የሰረገሎቹንም መንኰራኵር አሰረ፥ ወደ ጭንቅም አገባቸው ግብፃውያንም። እግዚአብሔር በግብፃውያን ላይ ይዋጋላቸዋልና ከእስራኤል ፊት እንሽሽ አሉ»
ዘጸ 15፥3 «እግዚአብሔር ተዋጊ ነው፥ ስሙም እግዚአብሔር ነው»
ዘጸ 16፥15
የእስራኤልም ልጆች ባዩት ጊዜ ያ ምን እንደ ሆነ አላወቁምና እርስ በእርሳቸው። ይህ ምንድር ነው? ተባባሉ። ሙሴም፦ ትበሉት ዘንድ እግዚአብሔር የሰጣችሁ እንጀራ ነው»
ከብዙ በጥቂቱ እስራኤል ዘሥጋን የመገባቸው፣የጠበቃቸው፣ያሻገራቸው፣ የጋረዳቸው እግዚአብሔር እንጂ እርስዎ እንዳሉት ሚካኤል የሚባል መልአክ አይደለም።  
ዘሌ20፥24 ነገር ግን እናንተን፦ ምድራቸውን ትወርሳላችሁ ትወርሱአትም ዘንድ ወተትና ማር የምታፈስሰውን ምድር እሰጣችኋለሁ አልኋችሁ። እኔ ከአሕዛብ የለየኋችሁ አምላካችሁ እግዚአብሔር ነኝ»
ዘዳ 26፣8 እግዚአብሔርም በጸናች እጅና በተዘረጋ ክንድ፥ በታላቅም ድንጋጤ፥ በተአምራትም፥ በድንቅም ከግብፅ አወጣን
ዘዳ 26፣9 ወደዚህም ስፍራ አገባን፥ ወተትና ማር የምታፈስሰውንም ይህችን ምድር ሰጠን።
ቀሲስ- እርስዎ ግን በድፍረት በእግዚአብሔር ላይ ዐምፀው ላልተገለጠና ላልተጻፈ የመልአክ ስም ሰጥተው፣ ያሻገራቸው፤ መናን የመገባቸው፣ ወተትና ማር የምታፈሰውን ሀገር ያወረሳቸው ሚካኤል ነው ይላሉ። እግዚአብሔር እኔ ነኝ እያለ እርስዎ ግን የለም ሚካኤል ነው ማለትዎ ለምን ይሆን? ላልተገለጠ መልአክ ክብሩን ከእግዚአብሔር ላይ ወስደው ሲሰጡ ለእኔ እንደተደረገ ይቆጠራል የሚል ይመስልዎት ይሆን? ላልተገለጠና ላልተጻፈ የመልአክ ስም ክብሩን ሁሉ መስጠትዎ ሳያንስ ሌሎችም ይህንኑ ስህተትዎን እንዲቀበሉና ፊታቸውን ወዳልተነገረውና እግዚአብሔር ወዳልገለጸው መልአክ እንዲመልሱ ማስተማርዎ ያሳዝናል !! በዘለበ ምላስ የሚናገሩትና የሚጽፉትን ለራስዎ እንዲመች ተርጉመው የመጽሐፍ ቅዱስን ቃል ማጣመምዎ ለምንድነው?
ምናልባት እግዚአብሔር ይቅር ቢልዎ ንስሐ ይግቡበት!! ምክንያቱም እኔ ሰራሁ ያለውን ላልተጻፈ መልአክ ሰጥተው፣ አስቀንተውታልና!!
እርስዎ እግዚአብሔር ያደረገውን ተአምራት ሁሉ ለሌላ አውለው እንዳስቀኑት ሰዎች ሆነዋል።
ዘኁ 14፣22-23 በግብፅ ምድርና በምድረ በዳ ያደረግሁትን ተአምራቴንና ክብሬን ያዩ እነዚህ ሰዎች ሁሉ አሥር ጊዜ ስለ ተፈታተኑኝ፥
 ነገሬንም ስላልሰሙ፥ በእውነት ለአባቶቻቸው የማልሁላቸውን ምድር አያዩም ከእነርሱም የናቀኝ ሰው ሁሉ አያያትም» ይላልና ያስቡበት!!!!!!

Friday, November 25, 2011

እሬት የተቀባ ጡት ማን ይጠባል?



 ሁላችንም ህጻን ልጅ ሆነን አድገን አሁን ካለንበት መድረሳችን እርግጥ ነው። ህጻናትን በተመለከተም ህጻናት ወንድሞችና እህቶችም ይኖሩን ይሆናል። ምናልባትም ህጻናት ልጆች ይኖረንም ይሆናል። ባይኖረን እንኳን ስለህጻናት ያለን እውቀት ትንሽ እንደማይሆን ተስፋ አደርጋለሁ። ስለህጻናት ማንሳት የወደድኩት «ምርጥ ምርጡን ለህጻናት» የሚል አስተምህሮ ለመስጠት አይደለም። አእምሮአችሁን ለአፍታ ስለህጻናት እንዲያስብና ላነሳ ስለፈለኩት ጉዳይ ግንዛቤ እንዲኖራችሁ ነው።
ጥያቄ ላቅርብላችሁ? ህጻናት ጡት የሚተዉት እንዴት ነው? ጡት የሚጠባ ህጻን ጡት ሲያጣ ወይም ጡት ሲከለክሉት እንዴት ያደርገዋል? መቼም እንደማይስቅና እንደማይፍለቀለቅ አናጣውም። ይነጫነጫል፣ያለቅሳል፤ በአቅሚቲ እናቱን ይቧጥጣል፣ጡት አምጪ ብሎ ይማታል ብንል እውነት ነው። ሲያገኝና ሲጠግብ ደግሞ ጤነኛ እስከሆነ ድረስ ይስቃል፣ይጫወታል። እንዲህ እንዲህ እያለ ሁለትና ሶስት ዓመት ሲሞላው ደግሞ ደግሞ ጡቱን ያስጥሉታል።አራትና አምስት ድረስ የሚጠባ ልጅ እንዳለ ሳይዘነጋ መሆኑን ልብ ይሏል? ጡት የምታስጥል የገጠር እናት ያንን የለመደውን ነገር ለማስጣል ከባድ ይሆንባታል። እንዲጠላው ለማድረግ እሬት ይቀቡታል። ይቆነጥጡታል። ሌላም ነገር እያደረጉ ይከለክሉታል። ይሁን እንጂ የህጻኑ ለቅሶ ሲበረታ ልምድ አደገኛ ነውና እንደገና ያጠቡታል። እንደዚያ እንደዚያ እያደረጉ ምግብ እያቀረቡ፣ጡት እየነፈጉ ከህጻንነት የጡት መጥባት ዓለም ያወጡታል።

Monday, November 21, 2011

የሚያድን ዕይታ


የዘመኑ መስታወት.......



by Dagnu Amde on Friday, November 18, 2011 at 7:11pm

አቤቱ÷ እኔን ለማዳን ተመልከት
አቤቱ÷ እኔን ለመርዳት ፍጠን
(መዝ.69÷ 1)::

በሕይወታችን ብዙ ነገሮችን ዐይተናል፡፡ ዐይተናቸው በውስጣችን የቀሩ፣ ዐይተናቸው የረሳናቸው፣ ዐይተናቸው ደግመን ለማየት ያልፈቀድናቸው፣ ዐይተን እንዳላየ ያለፍናቸው፣ ዐይተን የታዘብናቸው ብዙ ነገሮች አሉ፡፡ ጽጌረዳን ዐይተን እሾህን እናያለን፡፡ የተንሰራፉ አበቦች በአሜከላዎች ላይ ተጐዝጉዘው እናያለን፡፡ ዐይናችን ሁለቱንም ታያለች፡፡ ኅሊና ግን አጥርታና መርጣ ታያለች፡፡ በዐይናችን ብዙ መልካምና ክፉ ነገሮችን እናያለን፡፡ ላየነው ሁሉ ምላሽ መስጠት አያስፈልገንም፡፡ ምላሻችንን የሚፈልጉ ዕይታዎች ግን አሉ፡፡ ማየት ከመስማት በላይ ነው፡፡ ሰምቶ ምላሽ ያልሰጠ ሲያይ ግን ምላሽ ይሰጣል፡፡ ማየት የተግባር አዛዥ ናት፡፡

Saturday, November 19, 2011

የመላእክት ተፈጥሮና ተልእኰ



ቅዱሳን መላእክት ተፈጥሮአቸው ረቂቅ ነው። አይጨበጡም፣አይዳሰሱም። ዳዊትም በመዝሙሩ እንዲህ ሲል ገልጿቸዋል። መዝሙር 104መላእክቱን መንፈስ የሚያደርግ፥ አገልጋዮቹንም የእሳት ነበልባል»
ስለዚህ መላእክቱ መንፈስና እሳት ናቸው ማለት ነው። ስጋዊ ደማዊ አይደሉም። እርጅናና ሞት አይስማማቸውም። ምንም እንኳን መላእክት መንፈስና እሳት ቢሆኑ፣ እርጅናና የዚህ ዓለም ሞት ባይስማማቸው በራሳቸው ኃይል ምንም ሊደርጉ አይችሉም። ምክንያቱም እሳትና መንፈስ ያደረጋቸው ፈጣሪያቸው ገዢያቸውና ኃይላቸው እሱ ስለሆነ ነው። መላእክት ፍጡራን ስለሆኑ በቦታ ውሱን ናቸው። በሁሉም ስፍራ በአንድ ጊዜ የመገኘት ችሎታ የላቸውም። መላእክት ፍጡርና ውሱን ስለመሆናቸው መጽሐፍ ቅዱስ በብዙ ቦታ በቃሉ ይነግረናል። ለምሳሌ ያህል ያዕቆብ በፍኖተ ሎዛ ድንጋይ ተንተርሶ በተኛ ጊዜ ከምድር እስከሰማይ በተተከለ መሰላል ላይ መላእክት ሲወጡና ሲወርዱ በህልም አይቷል። «ሕልምም አለመ እነሆም መሰላል በምድር ላይ ተተክሎ፥ ራሱም ወደ ሰማይ ደርሶ፥ እነሆም የእግዚአብሔር መላእክት ይወጡበት ይወርዱበት ነበር» ዘፍ 2812 መላእክቱ ውሱን ፍጥረት ስለሆኑ በዚያ መሰላል ላይ ይወጣሉ፣ ይወርዳሉ። በሁሉም ስፍራ የመገኘት ብቃት የላቸውም። በራሳቸው ምንም ማድረግ የማይችሉ ስለሆነ ነው በዚያ መሰላል ላይ የሚወጡት የሚወርዱት። ያም መሰላል ኢየሱስ ክርስቶስ ነበረ።
«እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ ሰማይ ሲከፈት የእግዚአብሔርም መላእክት በሰው ልጅ ላይ ሲወጡና ሲወርዱ ታያላችሁ አለው» ዮሐ 152 መላእክት የሚወጡበትና የሚወርዱበት ለመላእክት ሰማያዊ የኃይላቸው መሰላል ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። ይህንን ራሱ ባለቤቱ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው የተናገረው!
አንዳንዶች ግን ያዕቆብ በፍኖተ ሎዛ መላእክት ሲወጡበትና ሲወርዱበት ያየውን መሰላል እመቤታችን ማርያም ናት ይላሉ። «አንቲ ውእቱ ስዋስዊሁ ለያዕቆብ» የያዕቆብ መሰላል አንቺ ነሽ። (ቅዳሴ ማርያም)ይህ በፍጹም ተቀባይነት የሌለው ነው። ቅድስት ማርያም በዘመነ ያዕቆብ አልተፈጠረችም። ማርያም ከሐናና ከኢያቄም በሥጋ ተወልዳለች ካልን ከዚያ ቀደም በመንፈስ ነበረች ማለት ክህደት ነው። ማርያም መንፈስ ሳትሆን የሰው ልጅ ናትና፣ ስጋ ሳትለብስ በዘመነ ያዕቆብ በሰማይ ወይም በምድር የነበረችና መላእክት ይወጡባት፤ይወርዱባት ነበር ማለት ክርስቶስ ከእሷ የለበሰውን ስጋ አለመቀበል ነው። ይህ ደግሞ አደገኛ ክህደት ነው። ደግሞም ኢየሱስ ክርስቶስ ራሱ «እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ ሰማይ ሲከፈት የእግዚአብሔርም መላእክት በሰው ልጅ ላይ ሲወጡና ሲወርዱ ታያላችሁ አለው»ያለውን ቃል በማርያም ስም መለወጥ ኃጢአት ነው። ቅድስት ማርያም አምላክን በስጋ ስለወለደች ወደአምላክነት አልተቀየረችም። ዘመን የማይቆጠርላት ረቂቅ መንፈስ አይደለችም። (ሎቱ ስብሐት እንላለን)
ወደ ተነሳንበት ርእስ ስንመጣ መላእክት ለመውጣትም ለመውረድም የክርስቶስ ኃይል የሚያስፈልጋቸው ፍጥረታት መሆናቸውን እንረዳለን።




በሌላ ቦታም መጽሐፍ ቅዱስ ስለመላእክት ውሱንነት በደንብ ይነግረናል። በትንቢተ ዳንኤል መጽሐፍ ላይ እንዲህ የሚል ተጽፎልናል። ዳንኤል በምድረ ፋርስ በሀዘን ላይ በጾምና በጸሎት ተወስኖ በነበረበት ወቅት ከእግዚአብሔር ዘንድ አንድ መልአክ ተልኮለት ወርዷል። ዳን 1011 «እርሱም፦ እጅግ የተወደድህ ሰው ዳንኤል ሆይ፥ እኔ ዛሬ ወደ አንተ ተልኬአለሁና የምነግርህን ቃል አስተውል፥ ቀጥ ብለህም ቁም አለኝ። ይህንም ቃል ባለኝ ጊዜ እየተንቀጠቀጥሁ ቆምሁ» ይላል። ይህ መልአክ ግን ዳንኤል ካለበት ዘንድ ከመድረሱ በፊት የፋርስ መንግሥት አለቃ ይለዋል( ንጉሱን የሚመራው የሰይጣን መንፈስ) ማለት ነው። የተላከውን መልአክ ከዳንኤል ዘንድ እንዳይደርስ 21 ቀን በአየር ላይ ተዋግቶታል። በኋላም የመላእክት አለቃ ሚካኤል መጥቶ ሲያግዘው እሱ ወደ ዳንኤል መምጣት ችሏል። «የፋርስ መንግሥት አለቃ ግን ሀያ አንድ ቀን ተቋቋመኝ እነሆም፥ ከዋነኞቹ አለቆች አንዱ ሚካኤል ሊረዳኝ መጣ እኔም ከፋርስ ነገሥታት ጋር በዚያ ተውሁት» ዳን 1013
የዚህ ዓለም ገዢ(ዮሐ1430) የተባለው ሰይጣን የፋርስ መንግሥት ገዢ መንፈስ ሆኖ ለዳንኤል የተላከለትን መልአክ 21 ቀን እንደተቋቋመው መልአኩ ራሱ ለዳንኤል ሲነግረው እናነባለን። ያኔም የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል ደርሶለታል። ሰይጣን ደግሞ በሌላ ጊዜም ከቅዱስ ሚካኤል ጋር ሲከራከር እንደነበር በይሁዳ መልእክት ላይ እናገኛለን። (ይሁዳ19)ሰይጣን ጳውሎስንም ከሚሄድበት መንገድ አዘግይቶታል።
«ወደ እናንተ ልንመጣ ወደን ነበርና፥ እኔ ጳውሎስም አንድና ሁለት ጊዜ፥ ሰይጣን ግን አዘገየን»1 ተሰ218
እንግዲህ ከላይ የምንረዳው የመላእክት ኃይል ውሱን መሆኑን፤ ከአንዱ መልአክ የአንዱ ሊበልጥ እንደሚችል፤የሚያዘገያቸው ነገር ሊያጋጥማቸው እንደሚችል፣ ሰይጣን የሚከራከራቸው መሆኑን፣ የሚያሸንፉትም የስድብን ቃል በመናገር ሳይሆን«እግዚአብሔር ይገስጽህ» በማለት ስመ እግዚአብሔርን መከታ በማድረግ ኃይል እንደሆነ ነው።

መላእክት የተፈጠሩበትን ቀን የሚያመለክት ቁልጭ ያለነገር ከመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ አልተቀመጠም። ይሁን እንጂ መምህራን አባቶች በእለተ እሁድ(በመጀመሪያው ቀን) ስለመፈጠራቸው ያስተምሩናል። ሰይጣንም በዚሁ ቀን ብርሃን ከመገለጡ ቀደም ብሎ በትእቢቱና ስልጣንን በመሻቱ እንደወረደም ይነግሩናል። ይህንን የሚያጠናክር መረጃ ከትንቢተ ኢሳይያስ 1412-15« አንተ የንጋት ልጅ አጥቢያ ኮከብ ሆይ፥ እንዴት ከሰማይ ወደቅህ! አሕዛብንም ያዋረድህ አንተ ሆይ፥ እንዴት እስከ ምድር ድረስ ተቈረጥህ! አንተም በልብህ ወደ ሰማይ ዐርጋለሁ፥ ዙፋኔንም ከእግዚአብሔር ከዋክብት በላይ ከፍ ከፍ አደርጋለሁ፥ በሰሜንም ዳርቻ በመሰብሰቢያ ተራራ ላይ እቀመጣለሁ። ከዳመናዎች ከፍታ በላይ ዐርጋለሁ፥ በልዑልም እመሰላለሁ አልህ፣ነገር ግን ወደ ሲኦል ወደ ጕድጓዱም ጥልቅ ትወርዳለህ» የሚለውን በማቅረብ ያስተምሩናል። አክሲማሮስ የተሰኘው የስነፍጥረት መጽሐፍንም በዋቢነት ያቀርባሉ። በጥቅሉ ግን ሰይጣን ከክብሩ የወደቀ መልአክ ነው።
ቅዱሳን መላእክት ግን ለእግዚአብሔር ተልእኮ ይፋጠናሉ። እግዚአብሔር ወደ ላካቸው ስፍራም ይሄዳሉ።«ያዕቆብም መንገዱን ሄደ፥ የእግዚአብሔር መላእክትም ተገናኙት።ያዕቆብም ባያቸው ጊዜ። እነዚህ የእግዚአብሔር ሠራዊት ናቸው አለ የዚያንም ስፍራ ስም መሃናይም ብሎ ጠራው» ዘፍ 321-2
ሎጥንም ቅዱሳን መላእክት ተልከው አድነውታል። «ጎህም በቀደደ ጊዜ መላእክት ሎጥን፦ ተነሣ፥ ሚስትህንና ከዚህ ያሉትን ሁለቱን ሴቶች ልጆችህን ውሰድ በከተማይቱ ኃጢአት እንዳትጠፋ እያሉ ያስቸኵሉት ነበር» ዘፍ 1915
መላእክት የምስራች ቃልን ያደርሳሉ። ለሶምሶን መወለድ ምስራች የተናገረው መልአኩ ነበር። «የእግዚአብሔርም መልአክ ለሴቲቱ ተገልጦ እንዲህ አላት፦ እነሆ፥ አንቺ መካን ነሽ፥ ልጅም አልወለድሽም ነገር ግን ትፀንሻለሽ፥ ወንድ ልጅም ትወልጃለሽ» መሳ 133
መላእክት የተላኩበትን ፈጽመው ስማቸውን ሳይነግሩን ሊሄዱ ይችላሉ። «ሴቲቱም ወደ ባልዋ መጥታ። አንድ የእግዚአብሔር ሰው ወደ እኔ መጣ፥ መልኩም እንደ እግዚአብሔር መልአክ እጅግ የሚያስደነግጥ ነበረ ከወዴትም እንደ መጣ አልጠየቅሁትም፥ እርሱም ስሙን አልነገረኝም» መሳ 136
መላእክት የተራበውን ለማብላት የተጠማውን ለማጠጣት ሊላኩ ይችላሉ። «በክትክታውም ዛፍ በታች ተጋደመ እንቅልፍም አንቀላፋ እነሆም፥ መልአክ ዳሰሰውና። ተነሥተህ ብላ አለው፣ሲመለከትም፥ እነሆ፥ በራሱ አጠገብ የተጋገረ እንጎቻና በማሰሮ ውኃ አገኘ። በላም ጠጣም፥ ተመልሶም ተኛ። 1 ነገ 195-6
መላእክት ሰዎችን ለተልእኰ ያፋጥናሉ። የሐዋ 826 «የጌታም መልአክ ፊልጶስን።፣ተነሥተህ በደቡብ በኩል ከኢየሩሳሌም ወደ ጋዛ ወደሚያወርደው ምድረ በዳ ወደ ሆነ መንገድ ሂድ አለው»
እግዚአብሔርን ለሚፈሩና ለሚታዘዙ መልአክ ይላክላቸዋል። « እርሱም ከቤተ ሰዎቹ ሁሉ ጋር እግዚአብሔርን የሚያመልክና የሚፈራ ለሕዝብም እጅግ ምጽዋት የሚያደርግ ወደ እግዚአብሔርም ሁልጊዜ የሚጸልይ ነበረ። ከቀኑም ዘጠኝ ሰዓት ያህል፣ ቆርኔሌዎስ ሆይ የሚለው የእግዚአብሔር መልአክ ወደ እርሱ ሲገባ በራእይ በግልጥ አየው» የሐዋ 102-3
የእግዚአብሔር መልአክ ቅዱሳንን ለማበረታታት ይላካል።
የሐዋ 2723-25 «የእርሱ የምሆንና ደግሞ የማመልከው የእግዚአብሔር መልአክ በዚች ሌሊት በአጠገቤ ቆሞ ነበርና፥ እርሱም፦ ጳውሎስ ሆይ፥ አትፍራ፤ በቄሣር ፊት ልትቆም ይገባሃል፤ እነሆም፥ እግዚአብሔር ከአንተ ጋር የሚሄዱትን ሁሉ ሰጥቶሃል አለኝ። ስለዚህ እናንተ ሰዎች ሆይ፥ አይዞአችሁ፤ እንደ ተናገረኝ እንዲሁ እንዲሆን እግዚአብሔርን አምናለሁና»
መላእክት የጌታ አገልጋዮች ናቸው።
«ያን ጊዜ ዲያብሎስ ተወው፥ እነሆም፥ መላእክት ቀርበው ያገለግሉት ነበር»ማቴ 411
የመጨረሻውን የዓለም መከር የሚያጭዱት መላእክት ናቸው። «እንክርዳዱም የክፉው ልጆች ናቸው፥ የዘራውም ጠላት ዲያብሎስ ነው፤ መከሩም የዓለም መጨረሻ ነው፥ አጫጆችም መላእክት ናቸው» ማቴ1339
መላእክት የእግዚአብሔርን የምስጢር ቀን አያውቁም። «ስለዚያች ቀንና ስለዚያች ሰዓት ግን ከአባት ብቻ በቀር የሰማይ መላእክትም ቢሆኑ ልጅም ቢሆን የሚያውቅ የለም»ማቴ2436
በጌታ ትእዛዝና በመላእክት አለቃ ድምጽ በክርስቶስ ለሞቱት ትንሳዔ ይሆናል።
«ጌታ ራሱ በትእዛዝ በመላእክትም አለቃ ድምፅ በእግዚአብሔርም መለከት ከሰማይ ይወርዳልና፥ በክርስቶስም የሞቱ አስቀድመው ይነሣሉ» 1 ተሰሎ 416
ከላይ ያለተጨማሪ ማብራሪያ እያየነው የመጣነው በነጥብ የተቀመጡት ጥቅሶች ሲጠቃለሉ ቅዱሳን መላእክት ለማዳን፤ ለማስተማር፤ የምስራችን ቃል ለመንገር፤ ለማበርታት፤ ለማወጅ፣ ለማገልገልና ለማመስገን የተመረጡ መሆናቸውን ነው።
እነዚህ ቅዱሳን መላእክትን የተመለከተ ሲሆን የወደቁት መላእክትስ ምን ይሰራሉ? የሚለውን እንመልከት!
የወደቁ መላእክት
አለቃቸው ዲያብሎስ ነው፣


 ስራቸው

ዋና ዋና ስራዎቻቸው 5 መደብ ሊከፈል ይችላል።
1/የእግዚአብሔርን ዓላማ መቃወም። ለዳንኤል የተላከውን መልአክ 21 ቀን እንደተዋጉት ማለት ነው።
2/ የዚህ ዓለም ገዢ ሆኖ መንግሥታትን፣ ነገሥታትን አገልጋዩ ማድረግ (ዮሐ1231)(ራእ 1614)
3/ሰዎች አምነው እንዳይድኑ የወንጌልን ቃል ከሰው ልብ በመስረቅ። (ሉቃ 812)
4/ ኃጢአተኞችን በኃጢአታቸው፤ ቅዱሳንን በመልካም ስራቸው ዘወትር በመክሰስ። (ኢዮ17-8)
ዘካ 31-2 እርሱም ታላቁን ካህን ኢያሱን በእግዚአብሔር መልአክ ፊት ቆሞ አሳየኝ፥ ሰይጣንም ይከስሰው ዘንድ በስተ ቀኙ ቆሞ ነበር። እግዚአብሔርም ሰይጣንን፦ ሰይጣን ሆይ፥ እግዚአብሔር ይገሥጽህ ኢየሩሳሌምን የመረጠ እግዚአብሔር ይገሥጽህ በውኑ ይህ ከእሳት የተነጠቀ ትንታግ አይደለምን? አለው።
ራእ1210 ታላቅም ድምፅ በሰማይ ሰማሁ እንዲህ ሲል፦ አሁን የአምላካችን ማዳንና ኃይል መንግሥትም የክርስቶስም ሥልጣን ሆነ፥ ቀንና ሌሊትም በአምላካችን ፊት የሚከሳቸው የወንድሞቻችን ከሳሽ ተጥሎአልና።
5/ የእግዚአብሔርን ቃል በማጣመም። (የሐዋ 1310)(2 ጴጥ 316)(መዝ 565) ዘፍ 31 እባብም እግዚአብሔር አምላክ ከፈጠረው ከምድር አውሬ ሁሉ ይልቅ ተንኰለኛ ነበረ። ሴቲቱንም፦ በውኑ እግዚአብሔር ከገነት ዛፍ ሁሉ እንዳትበሉ አዝዞአልን? አላት። ብሎ እንደተናገረው ዛሬም እንዲሁ ይሰራል። ለሃይማኖቶች መበራከትና የየራሳቸውን ስም ይዘው ራሳቸው ብቻ ጻድቅ፣ ሌላው ግን የውሸት መሆኑን የሚያስተምሩት ባጣመመው ቃሉ የተነሳ ነው።
ሌላውን ዐመጻና ኃጢአት ሁሉ የሚሰራውና የሚያሰራው በእነዚህ ነጥቦች ላይ ተንተርሶ ነው።
ሰይጣን(ዲያብሎስ) አብረውት የወደቁ የአጋንንት ሰራዊት አሉት። እነሱን በማሰማራት ይዋጋል።
ከእግዚአብሔር ፈቃድ ሲያገኝ ሊፈትን ይችላል። ኢዮብን እንደፈተነው ማለት ነው። ከሰማይ እሳትን ሊወረውር፣ አውሎ ንፋስን አስነስቶ ሊያጠፋ፣ ጦረኞችን አስነስቶ እልቂት ሊያደርስ ይችላል። ከዚያም አልፎ ተርፎ ስጋን መግደልም ይችላል። ኢዮ 117 (ማቴ 1028)ሥጋንም የሚገድሉትን ነፍስን ግን መግደል የማይቻላቸውን አትፍሩ፤ ይልቅስ ነፍስንም ሥጋንም በገሃነም ሊያጠፋ የሚቻለውን ፍሩ» እንዳለው።
ሰይጣን ይህን ማድረግ የመቻል ብቃት ቢኖረውም የወደቀ መልአክና በክርስቶስ መስቀል ከቅድስና መንገዳችን ላይ የተወገደ ነው። ቆላስ 214 የምናሸንፍበትን ኃይል አግኝተናል። ኤፌ 320 «እንግዲህ በእኛ እንደሚሠራው ኃይል መጠን ከምንለምነው ወይም ከምናስበው ሁሉ ይልቅ እጅግ አብልጦ ሊያደርግ ለሚቻለው»
«በእኛ ላይ የነበረውን የሚቃወመንንም በትእዛዛት የተጻፈውን የዕዳ ጽሕፈት ደመሰሰው። እርሱንም በመስቀል ጠርቆ ከመንገድ አስወግዶታል»

ማጠቃለያ፣

ቅዱሳን መላእክት በእግዚአብሔር አገዛዝና ሥልጣን ስር ያሉ፤ የሚታዘዙ፤ የሚላኩ፤ ፈቃዱን የሚፈጽሙና ዘወትር የሚያመሰግኑ ናቸው።
ውዱቃን መላእክት፤ ከእግዚአብሔር አገዛዝ ስር ያሉ ግን ከስልጣኑ ያፈነገጡ፤የማይታዘዙ፤ የማይላኩ ፈቃዱን የማይፈጽሙና የማያመሰግኑ ናቸው። በአገዛዙ ስር ስላሉ ያለፈቃዱና ያለእውቅናው አንዳች ማድረግ አይችሉም። ኤፌ 21 «አሁን ያሉት በአየር ላይ፣ በምድር ላይና በሲኦል ሲሆን በመጨረሻበበደላችሁና በኃጢአታችሁ ሙታን ነበራችሁ፤ በእነርሱም፥ በዚህ ዓለም እንዳለው ኑሮ፥ በማይታዘዙትም ልጆች ላይ አሁን ለሚሠራው መንፈስ አለቃ እንደ ሆነው በአየር ላይ ሥልጣን እንዳለው አለቃ ፈቃድ፥ በፊት ተመላለሳችሁባቸው።ም በገሀነም ይኖራሉ»
ሉቃ833 አጋንንትም ከሰውዬው ወጥተው ወደ እሪያዎች ገቡ፥ መንጋውም ከአፋፉ ወደ ባሕር ተጣደፉና ሰጠሙ»
የሰው ልጅ የእግዚአብሔር ቸርነትና ምሕረት የበዛለት በአርአያውና በአምሳሉ ስለፈጠረው ነው። ያም ጥልቅ በሆነው የእግዚአብሔር ፍቅር አማካይነት በአንድያ ልጁ እንዲድን አስችሎታል። «ፍቅር ሰሐቦ ለወልድ ኃያል እመንበሩ፣ ወአብጽሖ እስከለሞት» የተባለውም ለዚህ ነው።
አምላካዊ ጥበቃውንና ድጋፉን በቅዱሳን መላእክቱ በኩል ያደርግልናል። ቅዱሳን መላእክቱም እግዚአብሔር በላካቸው ስፍራና ቦታ ተገኝተው ትእዛዛቱን ይፈጽማሉ። ቅዱሳኑ መላእክት ግን ትእዛዝ ሳይደርሳቸው የትም አይንቀሳቀሱም። የሰው ልጅ በሰው ሰውኛነት የመረጠውን መልአክ ስለጠራ ወይም ስለለመነ መልአኩ ስሜ ስለተነሳ ልሂድ፤ልውረድ አይልም። እንኳን ተጠርቶ፣ ሳይጠራ ከተፍ የሚለው ሰይጣን ብቻ ነው። ከቅዱሳን መላእክት ከተማ ውጪ ያለው እሱና ሰራዊቱ ናቸው። በእዚህ ምድር ያለውን የሰው ልጆች የሚንከባከበን የሁሉ መገኛ የእግዚአብሔር ጥበቃና መግቦት ነው። ነቢዩ ዳንኤልን በጾም በጸሎቱ ወቅት ይጠብቀውና ያጸናው የነበረው የእግዚአብሔር ኃይል ነበረች። መልአኩንማ 21 ቀን እንዳይደርስ ጠላት ሲዋጋ አቁሞት ነበር።
ስለዚህ ቅዱሳን መላእክትን እናከብራቸዋለን፤ ይራዱናል፤ ያግዙናል ስንል እነርሱን በተለየ ስም በምናደርግላቸው ጥሪና ልመና ሳይሆን ለእግዚአብሔር በምናቀርበው ጸሎት ተቀባይነት የተነሳ እኛ የማናውቀው መልአክ ሊላክልን ሲችል ብቻ መሆኑን እንረዳ!!
በተጨማሪ ገብሩ ወልዱ የተባሉ ጸሐፊ በሰይጣን ባህሪይ ላይ የጻፉትን መጽሐፍ ቢያነቡት ብዙ እንደሚጠቀሙ አምናለሁ።
ለሁሉም ነገር እግዚአብሔር አእምሮውን ለብዎውን ያሳድርብን፣አሜን።