Saturday, December 19, 2015

ኢየሱስ፤ ኢየሱስ እየተባለ ቢጠራ ያሳፍራል እንዴ?

መዳንም በሌላ በማንም የለም፤ እንድንበት ዘንድ የሚገባን ለሰዎች የተሰጠ ስም ከሰማይ በታች ሌላ የለምና!
የሐዋ 4፤12

Sunday, December 6, 2015

“የሊቀ ጳጳሱ ልጅ ነኝ” በሚል የቀረበን ጥያቄ ውድቅ አደረገው።

(መማሌት ኪዳነወልድ)
የፍርድ ቤት ክርክሩ ከ3 ዓመት በላይ ፈጅቷል      የሽሬ እንዳሥላሴ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የነበሩት አቡነ ሚካኤል፤ በነሐሴ ወር 2003 ዓ.ም ከሞቱ በኋላ ነው፤ “የሊቀ ጳጳሱ ልጅ ነኝ” የሚል የወራሽነት አቤቱታ ለፍ/ቤት የቀረበው፡፡ “የሟች ልጅ ነኝ” የሚል አቤቱታ ያቀረቡት አቶ ዮሐንስ ተክለሚካኤል፤ ጳጳሱ እንዳሳደጓቸው በመግለጽና ተወላጅነቴን ያስረዱልኛል ያሏቸውን ሰነዶች በማያያዝ፣ የሰዎችን ምስክርነት ለፍ/ቤት አሰምተዋል፤ ፍ/ቤቱም ኅዳር 23 ቀን 2004 ዓ.ም የልጅነት ማረጋገጫ ውሳኔውን አሳወቀ፡፡ ጉዳዩ ግን በዚሁ አልተቋጨም፡፡ የሊቀ ጳጳሱ እኅት፤ የፍ/ቤቱን ውሳኔ በመቃወም ይግባኝ ጠይቀዋል፡፡ በአቶ ዮሐንስ የቀረበው የልደትና የጥምቀት ወረቀቶች በአግባቡ የተረጋገጡ አይደሉም፤ ልጅነቱ በሳይንሳዊ መንገድ በዲኤንኤ መረጋገጥ አለበት በማለት መቃወሚያ አቅርበዋል - የጳጳሱ እኅት ወ/ሮ በላይነሽ ዓባይ፡፡ “ሊቀ ጳጳሱ አሳድገውኛል ከማለት ውጪ፣ ሊቀ ጳጳሱ በልጅነት እንደተቀበሉት የሚያሳይ ማስረጃ አልቀረበም፤” ያሉት ወ/ሮ በላይነሽ፤ በተጨማሪም በቀረበው የጥምቀትና የልደት ካርድ ላይ የአባት ስም የተቀየረው ሊቀ ጳጳሱ ከሞቱ በኋላ ነው፤” ብለዋል፡፡ አቶ ዮሐንስ በሰጡት መልስ፣ “ወ/ሮ በላይነሽ የጳጳሱ እኅት መሆናቸውን አላውቅም፡፡ በሕይወት እያሉ እኅት አለኝ አላሉኝም፤” ብለዋል፡፡ “የአባቱን ስም ቀይሯል” ለሚለው ተቃውሞ አቶ ዮሐንስ ምላሽ ሲሰጡም፤ በሟች አባቴና በእናቴ ስምምነት፤ እናቴ ቤተሰቦችጋ ነው ያደግሁት፡፡ በዚህ ምክንያት፣ በእናቴ አባት ስም ስጠራ ቆይቻለሁ፤” ብለዋል፡፡ “ከልደትና ከጥምቀት ወረቀት ውጭ፤ የሰው ምስክሮች አስደምጫለሁ፡፡ ከምስክሮቹ አንዷም እናቴ ናት፤” በማለትም ተከራክረዋል፡፡ የይግባኝ ክርክሩን የዳኘው ከፍተኛ ፍ/ቤት፤ በአቶ ዮሐንስ ቀረበው የልደት የምስክር ወረቀት ሕጋዊነት እንደሌለው ገልፆ፤ በክሊኒክ የተመዘገበ የወሊድ መረጃዎችንም ጠቅሷል፡፡ በክሊኒኩ የተመዘገበው የወላጅ እናት አድራሻ የተሳሳተ እንደሆነ ፍ/ቤቱ ጠቅሶ፤ የወላጅ እናት ዕድሜ ተብሎ የተመዘገበው መረጃም፤ ከዮሐንስ እናት ዕድሜ ጋር በሰፊው ይራራቃል፤ ብሏል፡፡ ከፍተኛው ፍርድ ቤት እስከ መስከረም 4 ቀን 2008 ዓ.ም ጉዳዩን ሲመረምር ከቆየ በኋላ በሰጠው ውሳኔ፣ አቶ ዮሐንስ “የሊቀ ጳጳሱ ልጅ አይደሉም፤” በማለት የሥር ፍ/ቤትን ውሳኔ ሽሯል፡፡ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሕግ፣ ለማዕርገ ጵጵስና የሚመረጡት በሥርዓተ ምንኩስና በድንግልና መንኩሰው በክህነት ቤተክርስቲያኒቱን የሚያገለግሉ ሲሆኑ ቤተ ክርስቲያኒቱም ይህንኑ በማረጋገጥ በጣልቃ ገብ መከራከሯን የፍርድ ሐተታው ያመለክታል፡፡     

Friday, November 27, 2015

ፖሊስ መምህር ግርማ ወንድሙን በተጨማሪነት በግድያ ወንጀል መጠርጠሩን ገለፀ።

ፖሊስ
አዲስ አበባ ፣ ህዳር 17፣ 2008 (ኤፍ.ቢ.ሲ) መምህር ግርማ ወንድሙ በተጠረጠሩበት የማታለል ወንጀል የተፈቀደው ዋስትና ላይ የመርማሪ ፖሊስ ይግባኝ ውድቅ ተደረገ።

የአዲስ አበባ ፖሊስ የምርመራ ቡድን ከተጠርጣሪው ቤት ያገኘሁት ስምንት ሲም ካርድ ላይ እንዲጣራ ለኢትዮ ቴሌኮም ልኬ ውጤት እየጠበኩ ነው፤ ሌላ ተጠርጣሪም ስላለ ያን ለመያዝ የ14 ቀን የጊዜ ቀጠሮ ይሰጠኝ ቢልም የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት የተጠየቀው የምርመራ ስራ ተጠርጣሪውን ዋስትና የሚያስከለክል አይደለም በማለት ዋስትና መፍቀዱ ይታወሳል።

ይሁን እንጂ መርማሪ ቡድኑ ይግባኝ ጠይቆ ዋስትናውን በማሳገድ በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ችሎት ቀርቦ ተከራክሯል።

ችሎቱ የሁለቱን ወገን ክርክር መርምሮ ፖሊስ የተሰጠው ጊዜ በቂ ነው፤ ቀሪ ምርመራውን ለማድረግም ተጠርጣሪውን ዋስትና የሚያስከለክል አይደለም ሲል የተፈቀደውን ዋስትና አጽንቶታል።

በዚህም መምህር ግርማ በተጠረጠሩበት የማታለል ወንጀል በ50 ሺህ ብር፣ በሀሰተኛ ሰነድ በመገልገል ደግሞ በ40 ሺህ ብር በጠቅላላው የ90 ሺህ ብር ዋስትና ተፈቅዶላቸዋል።

በተያያዘ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን የምርመራ ቡድን መምህር ግርማ መንድሙን ከዚህ በፊት ከተጠረጠሩበት ወንጀል በተጨማሪ በግድያ ወንጀል ጠርጥሬያቸዋለሁ ሲል አመልክቷል።

የምርመራ ቡድኑ ጉዳዩን ለፌደራሉ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ችሎት ያመለከተ ሲሆን፥ ፍርድ ቤቱ ፖሊስ የጠረጠረበትን የግድያ ወንጀል ዝርዝር እና የምርመራ ሂደቱን ለችሎቱ እንዲያቀርብ ለህዳር 20 ቀን 2008 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ይዟል።

ከፖሊስ ባገኘነው መረጃ መሰረት መምህር ግርማ ወንድሙ እስከ ህዳር 20 2008 ዓ.ም ድረስ በእስር የሚቆዩ ይሆናል።







በሀይለኢየሱስ ስዩም  

- See more at: http://www.fanabc.c

Thursday, November 5, 2015

መምህር ግርማ ተጨማሪ የተጠረጠሩበት ወንጀል ይፋ ሆነ



አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 25፣ 2008 (ኤፍ.ቢ.ሲ) መምህር ግርማ ወንድሙ አዲስ የተጠረጠሩበት ወንጀል ይፋ ሆነ።

ይህ የተጠረጠሩበት ወንጀል ሀሰተኛ ሰነድ መገልገል የሚል ነው ብሏል የአዲስ አበባ ፖሊስ።

ጥቅምት 23 2008 የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስትያን ጠቅላይ ቤተ ክህነት ባልሰጠኋቸው የስብከት እና የማጥመቅ ፈቃድ እንደሰጠኋቸው በማስመሰል በሀገር ውስጥ እና በውጭ ሀገር በቤተክርስቲያኒቱ ስም ሲያስተምሩ እና ሲያጠምቁ ቆይተዋል በማለት ለአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን በፃፈው ደብዳቤ አሳውቋል።

ይህንን በተመለከተም የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ያለ ቤተክርስቲያኒቱ እውቅና በህገ ወጥ መንገድ በሀሰተኛ ሰነድ ተጠቅመው ሲያገለግሉ ነበር በማለት ለመምህር ግርማ ወንድሙ የተፃፉ ሰባት ቅፅ ደብዳቤዎችን ጠቅላይ ቤተክህነት ለፖሊስ በመሸኛ ደብዳቤ ልኳል።

በዚህ መሰረት የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን የምርመራ ቡድን ይህንን ምርመራ ለማከናወን 14 ቀን የጊዜ ቀጠሮ ጠይቋል።

ተጠርጣሪው መምህር ግርማ ወንድሙ በበኩላቸው ደቡብ ወሎን ጨምሮ በሀገር ውስጥ እና በውጭ ቤተክህነት ደብዳቤ እየፃፈልኝ ነው ሳገለግል የሰነበትኩት ብለዋል።

ጠበቆቻቸውም እንዲሁ ሌላው ቢቀር እሳቸው በቋሚነት በሚያገለግሉባቸው የረር ስላሴ እና ጀሞ ሚካኤል እንኳን ህገ ወጥ ናቸው የሚል በቤተክህነት  የተላከ አንዳችም ደብዳቤ ያለመኖሩን እንዲሁም መንፈሳዊ አገልግሎት መስጠት ወንጀል ስላልሆነ ፍርድ ቤቱ የተጠየቀውን የጊዜ ቀጠሮ አቤቱታ ውድቅ አድርጎ ደንበኛችን የዋስትና መብታቸው ይከበርላቸው ሲል ጠይቋል።

የምርመራ ቡድኑ በበኩሉ የተጠረጠሩበት ወንጀል ሀሰተኛ ሰነድ መገልገል በመሆኑ ችሎቱ የጠበቆቹን ጥያቄ እንዳይቀበል ሲል አመልክቷል።

የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ችሎት 1ኛ የጊዜ ቀጠሮ ችሎት ፖሊስ ከጠየቀው 14 ቀን የ7 ቀኑን ፈቅዷል።

ውጤቱን ለመጠባበቅ ለህዳር 3 ቀን 2008 ተለዋጭ ቀጠሮ ይዟል።

በሌላ በኩል መምህር ግርማ ወንድሙ ባለፈው ሳምንት ከተጠረጠሩበት የማታለል ወንጀል ጋር በተያያዘ ፖሊስ ተጨማሪ የምርመራ ስራ አለኝ በማለት ከጠየቀው 14 ቀን የጊዜ ቀጠሮ ፍርድ ቤቱ አምስት ቀን ብቻ ነው የፈቀደው።

ፖሊስ ድጋሚ ቀነ ቀጠሮ ለመጠየቅ ካቀረበው ምክንያት መካከል ያልተያዙ ተጠርጣሪዎች አሉ፤ ከቤት ሽያጭ ጋር በተያያዘ ተጠርጣሪው ከሚኖሩበት ወረዳ የሰነድ ማስረጃ አልቀረበልኝም፤ ቤታቸው ላይ በተደረገው ብርበራ ስምንት ሲም ካርዶች የተገኙ በመሆኑ ሲም ካርዶቹ በማን ስም የወጡ ናቸው? እና በስልኩ ውስጥ የሚገኙ መረጃዎችን ኢትዮ ቴሌኮም አጥርቶ እንዲልክልን ደብዳቤ ፅፈን ውጤቱን እየተጠባበቅን ነው የሚሉት ይገኙበታል።

በዚህም ላይ የተጠርጣሪው ጠበቆች ሰው ታስሮ ሌላ ሰው ለመያዝ በሚል ተጨማሪ ቀን ሊጠየቅ አይገባም፤ ህጉም አይፈቅድም፤ እና ፖሊስ ምርመራውን ቀደም ሲል ያጠናቀቀ በመሆኑ ባለፈው በተሰጠው 7 ቀን የተጠርጣሪውን ቃል ተቀብሎ ክስ መመስረት ሲገባው ደንበኛችን ያለአግባብ እየታሰሩ ነው ብለዋል።

ችሎቱ ከኢትዮ ቴሌኮም የሚመጣውን መረጃ ለመጠባበቅ ከተጠየቀው 14 ቀን 5 ቀን ብቻ ፈቅዷል።

የዚህንም ውጤት ለመጠባበቅ ለጥቅምት 30 2008 ተለዋጭ ቀጠሮ ይዟል።


በጥላሁን ካሳ


Wednesday, November 4, 2015

የመጽሐፍ ሕግ ይከበር!!!


ልሳን በሚነገርበት ጊዜ መጽሐፍ ቅዱሱ “በማኅበር መካከል ዝም ይበልና ለራሱና ለእግዚአብሔር ይናገር” እያለ (1ኛ ቆሮ 14፡28)፤ ፓስተር ዳዊት ደግሞ ያውም በመንፈስ ተመስጦ ሳይሆን ሰዓቱን እያየ በተናገረው ልሳን ላይ “እጅ ለእጅ ተያያዙ” እና “አንዴ ለሁለት ደቂቃ ሁሉም ሰው በልሳኑ ይጸልይ” በማለት ትእዛዝ አስተላለፈ፡፡ ሁሉም በማልሰማው ልሳን ይጮሁ ጀመር፤ ፓስተር ዳዊት እና መጽሐፍ ቅዱሱ የሚሉት ለየቅል ሆኖብኛል፡፡ ለመሆኑ በማኅበር መካከል ዝም ይበል እያለ የሚያዝዘው ትእዛዝ በእኛ ጉባኤ መቼ ነው የሚከበረው? ? ?
በመጽሐፍ ቅዱስ የሚነገር ልሳን እየተነገረን ከሆነ፤ እስቲ የፓስተር ዳዊትን ልሳን በ1ኛ ቆሮ 14፡27 “በልሳን የሚናገር ቢኖር ሁለት ወይም ቢበዛ ሦስት ሆነው በተራቸው ይናገሩ አንዱም ይተርጉም” ይላልና ትተረጉሙልኝ ዘንድ በትሕትና እጠይቃችኋለሁ ልሳኑ እነሆ፡-


1. አሞላቫንቶስሳክራቶሊያ
2. ሂላሞሪያማሳንቶኮትራቫሎዣንታ
3. ዚንትሮቪዲያሎማንቴስቴኬፕላዶራስ
4. ማዶሎሎስ ሲያማማንዶስሶኮዶጆኖሎሞስ
5. ኢንሞሎዲያናማሳንቶ
6. ኦላሪያማሴንታዲያካላቫሶንታ
7. ማርዶሎሞሲያናታኪቫ
8. ሃሊቮሪያማሳንቶ … ናሚያኖራሳንታ ….
9. ማትራቫዶላማንሳ
10. ሜሮቫንዶሶትራቮላ
11. አሪዞሞሜንቶኮትሬጅሪዮማንዴ
12. ዚልቮንቶቶድጄኔስቫፓሮዳ
13. አጉልቮኖንቴስቴቮዶሞሞንዶ
14. ሳልቬርኖማንቶሴትራዲያቮላ
15. ሀሞራማሺንዶሎሮሪያማንዳ
16. ዚላቮታካሮማንዲያላማሳ
17. አማሎናንቴኤልቬሌንቶስቶትሮቮሎኮዛ
18. አሙላዢቫዚያንዴ
19. ሪቫልዶሎትሮኮሎዞማንዳ
20. ኬልፕሮቫዶስ

መጽሐፍ ቅዱስ “አንዱም ይተርጉም” በሚለው መሠረት፤ ትርጉሙን በቁጥር በቁጥር ለሚተረጉምልኝ፤ አስቀድሜ ስለ ትብብሩ አመሰግናለሁ፡፡

Thursday, October 29, 2015

መምህር ግርማ ያቀረቡት የዋስትና ጥያቄም ወድቅ ተደርጓል።

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 18፣ 2008 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ትናንት በቁጥጥር ስር የዋሉት መምህር ግርማ ወንድሙ ዛሬ ፍርድ ቤት ቀርበዋል።

መምህር ግርማ ያቀረቡት የዋስትና ጥያቄም ወድቅ ተደርጓል።

የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን የፖሊስ መርማሪ ቡድን ዛሬ ግለሰቡን በፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ 1ኛ የወንጀል ችሎት አቅርቧቸዋል።

ፖሊስ ግለሰቡ በተጠረጠሩበት የማታለል ወንጀል ቀሪ የምርመራ ስራ ስላሉብኝ ተጨማሪ 14 ቀን ይፈቀድልኝ ብሏል።

ተጠርጣሪው በራሳቸውና በጠበቃቸው በኩል ፖሊስ የጠየቀውን ተጨማሪ ጊዜ  በመቃወም የዋስትና መብታቸው እንዲከበር ጠይቀዋል።

የፖሊስ የምርመራ ቡድን በበኩሉ እሳቸው ቢለቀቁ ሌሎች ተፈላጊዎችን እና የተለያዩ ሰነዶችን ስለሚያሸሹብን ጥያቄያቸው ውድቅ ይሁን ብሏል።

ፍርድ ቤቱ የሁለቱንም ወገን ክርክር መርምሮ ፖሊስ አብዛኛውን የምርመራ ስራ ያካሄደ በመሆኑ ለቀሪ የምርመራ ስራዎቹ ይረዳል በማለት ከጠየቀው የ14 ቀን ጊዜ ውስጥ 7 ቀን ብቻ ፈቅዷል።

ውጤቱን ለመጠባበቅም ለጥቅምት 25 2008 ተለዋጭ ቀጠሮ ይዟል።

የወንጀሉ ዝርዝር

ፖሊስ መምህር ግርማ  በቁጥጥር ስር እንዲውሉ ምክንያት የሆነው ወንጀል የተፈፀመው መስከረም 2006 ዓ.ም ነው ብሏል።

በየካ ክፍለ ከተማ በተለምዶ ወሰን ግሮሰሪ እየተባለ በሚጠራው አካባቢ የሚኖሩት አቶ በላይነህ ከበደ በመምህር ግርማ የማታለል ወንጀል የተፈጸመባቸው ግለሰብ ናቸው።

እንደ ፖሊስ የምርመራ መዝገብ እኚህ ግለሰብ ከትዳር አጋራቸው ጋር 400 ካሬ ሜትር ላይ ባረፈ መኖሪያ ቤታቸው ይኖሩ ነበር።

እንደ ምርመራ መዝገቡ መምህር ግርማ የግል ተበዳይን እምነት በመጠቀም የምትኖርበትን መኖሪያ ቤት እስከ ጥር 30 2006 ሽጠህ ካልወጣህ አስከሬንህ ይወጣል ይሏቸዋል።

የፖሊስ የምርመራ መዝገብ እንደሚለው ልጅ ያልወለዱት ባልና ሚስት ከመሞት መሰንበት በማለት ይህንን ቤት በጣም በዝቅተኛ ዋጋ በ800 ሺህ ብር ይሸጡታል።

ቤቱ በዚህ ዋጋ እንዲሸጥ መምህር ግርማ በራሳቸው ሰዎች አማካኝነት ብዙ ያልተገባ ስራ ሰርተዋል ነው የሚለው የምርመራ መዝገቡ።

ከዚያም መምህር ግርማ በዚህ ብቻ ሳይመለሱ የግል ተበዳዩን ቦሌ አካባቢ በራዕይ ያየሁት ቦታ አለ እዚያ ነው ገዝተህ የምትኖረው ይሏቸውና ሌላ የማታለያ ዘዴ ቀየሱ ይላል ምርመራው።

ቤቱ የተሸጠበትን 800 ሺህ ብር አምጣና እንዲበረክትልህ ልፀልይበት ብለው በመውሰድ በዚያው ውለው አደሩ፤ የግል ተበዳዩም በእርሳቸው ላይ ያላቸው እምነት ባለመጥፋቱ በትዕግስት ስልክ ቢደውሉላቸውም ስልካቸው ዝግ ሆነባቸው፤ ይባስ ብሎ ከሀገር ወጡ ተባለ የሚለውም ተጠቅሷል።

የግል ተበዳይ ሁኔታው ማታለል መሆኑን ስለተረዱ 2007 መጋቢት ወር ገደማ ለፖሊስ ያመለከቱ ሲሆን፥ እርሳቸው ከሄዱበት እስኪመለሱ ፖሊስ የግል ተበዳዩን እና የምስክሮችን ቃል ተቀብሎ ቆይቶ ተጠርጣሪው መምህር ግርማ ወንድሙን ትናንት በቁጥጥር ስር አውሏቸው ነው ዛሬ ፍርድ ቤት ያቀረባቸው።

ተጠርጣሪው እኔ የተባለውን ሰው ቀይ ይሁን ጥቁር አይቼው አላውቅም፤ ሆን ተብሎ ከጀርባ የተጠነሰሰብኝ ሴራ አለ በማለት ለችሎቱ አስረድተዋል።

ጠበቃቸውም የተጠረጠሩበት ወንጀል ዋስትና የሚከለክል አይደለም፤ ፖሊስም የሚጠበቁ ምርመራዎቹን አጠናቋል፤ ደንበኛዬ የዋስትና መብታቸው ይከበርልኝ በማለት ጠይውቋል።

ይሁን እንጂ ፍርድ ቤቱ የዋስትና ጥያቄያቸውን ውድቅ አድርጓል።





በጥላሁን ካሳ


Wednesday, October 28, 2015

ሰበር ዜና፣ ፖሊስ አጥማቂ ነኝ ባዩ ግርማ ወንድሙን በቁጥጥር ስር አዋለ።


አዲስ አበባ ፣ ጥቅምት 17 ፣ 2008 (ኤፍ ቢ ሲ) የአዲስ አበባ ፖሊስ መምህር ግርማ ወንድሙን በቁጥጥር ስር አዋለ።

የፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ምንጮች መምህር ግርማ ዛሬ በፖሊስ በቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየተደረገባቸው መሆኑን ተናግረዋል።

መምህር ግርማ በተለያዩ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን አብያተ ክርስቲያናት በማስተማርና በማጥመቅ ሲያገለግሉ የነበሩ ናቸው።

ይሁን እንጂ መምህሩ በማጥመቅ እና በማስተማር በሃገር ውስጥም ይሁን በውጭ ሃገራት ቤተክርስቲያኒቱን ወክለው እንዳያገለግሉ እውቅና መነፈጋቸውን ፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ያነገጋረው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን ጠቅላይ ቤተክህነት አረጋግጧል።

የፋና ምንጮች መምህር ግርማ ከአገልግሎታቸው ጋር በተያያዘ በወንጀል ሳይጠረጠሩ እንዳልቀረ ነው የተናገሩት።

ጣቢያችን ሌሎች ተያያዥ መረጃዎችን እየተከታተለ ያቀርባል።


በጥላሁን ካሳ እና 

Tuesday, October 27, 2015

ስለአንዳንድ በኢ.ኦ.ተ.ቤ.ክ ላይ…ከአንዳንድ የኦሮሞ ጸሐፍት የተሰነዘሩ…ያስቀየሙኝ ክታቦች!!

ከአማን ነጸረ (ክፍል 3)
(6.6) እስኪ እነዚህ ምዕራባውያን ሚሽነሪዎች ስለ ኦሮሞ ሕዝብ ባሕል የነበራቸው አመለካከት ከኢኦተቤክ ሊሻል ይቅርና ምን ያህል የዘቀጠ እንደነበረ በራሳቸው መነጽር እንፈትሽ፡፡ Eric Gilchist የተባለ አሜሪካዊ በነመኩሪያ ቡልቻ ‹‹የአቢሲኒያ ትርክት›› ተጽእኖ ስር ሆኖ እንኳ በሠራው የ2ኛ ዲግሪ (ማስትሬት) ማሙያ ጥናት <<....as a result of their fundamental beliefs, SIM [Sudan Interior Missonary] missionaries viewed all non-Chiristean religious practices as evil and they demanded that their converts compeletly change their life style, with no compromise to accommodate local customs....>> በማለት ሚሲዮናውያኑ ለነባሩ የኦሮሞ ባሕል የነበራቸውን የተዛባ አመለካከት ካሳየን በኋላ Dough Priest የተባለውን በወለጋ ከ10 ዓመታት በላይ የሚሲዮናውያን መሪ የነበርን ትምክተኛ ሰው ጽሑፍ በመጥቀስ <<...the lives of the Galla people in general were one round after another of drunkness,adultery,thievery,lying,fighting,cheating,and worshiping false gods....today,many of the lives in our area have changed greatly....>> እያሉ (ሚሽኖቹ) ራሳቸውን ወለጋን የታደገ መሲኅ አድርገው ይመጻደቁ እንደነበር ጽፏል--ይቅርና ባሕሉን እንደ ባሕል ሊቀበሉ ( Eric Gilchist፡p.74)፡፡አናሲሞስ ነሲብም ቢሆን ሁሉንም የኦሮሞ አኗኗርና ባሕል ‹‹ቅዱስ›› ብሎ የተቀበለ አይመስልም፡፡በአንድ ደብዳቤው ላይ በስብከታቸው ስላመጡት ለውጥ ሲገልጽ ‹‹...በጋብቻ ላይ የሚፈጸም ጋብቻን እና በአካባቢው የሚታዩ ጎጂ ልማዶችን አጥብቀን ተፋልመናል፤እናም በዚህ በኩል ተሳክቶልናል፡፡ከዚህ ሌላ በኅብረተሰቡ መካከል ይዘወተር የነበረው የጥንቆላ፣የድግምት፣ለክፉ መናፍስት መሥዋዕት የማቅረብ ልማድ፣ሐሰተኛ ምስክርነት፣ውሸትና ሌላም ጎጂ ልምዶች ከዓመት ወደ ዓመት እየቀነሱ መጥተዋል›› ብሎ ነበር (ደማቆቹ፡ገ.35)፡፡እዚህ ላይ አንድ ሀቅ ላስታውስ፡፡በሰሜን ኢትዮጵያም ቢሆን አናሲሞስ ያነሳቸው ከክርስትና ጋር የሚቃረኑ ባሕላዊ ጎጂ ልማዶችና አምልኮዎች ነበሩ፡፡ዛሬም ርዝራዣቸው አለ፡፡ችግሩ በኦሮሚያ ብቻ የነበረ/ያለ አይደለም፡፡ስለሆነም ማንም በማንም ላይ ሊመጻደቅ አይችልም፡፡
(6.7) እስልምና የኦሮሞን ባሕል በምልዓት ይቀበላል የሚል ካለም እስኪ እንፈትሽ!! ‹‹Islamic Front for Liberation of Oromia›› የሚል ሃይማኖት ጠቀስ የኦሪሚያ ነጻ አውጪ ሽምቅ ተዋጊ በሼክ አብዱል ከሪም (ሼክ ጃራ አባ ገዳ) መፈጠሩን፣በባሌ አካባቤ ‹‹የሶማሌ አቦ...›› የሚባል አፍቃሬ-ሶማሊያ የኦሮሞ ሙስሊሞች የፖለቲካ ቡድን በታሪክ መታየቱን፣ይኸው ቡድን በ1969 ዓ.ም ከዚያድ ባሬዋ ሶማሊያ በእስልምና ስም ተቃቅፎ ኢትዮጵያን ያውም ሐረርጌን መውጋቱን፣ከሽግግር መንግስቱ ምስረታ ጀምሮ በተደጋጋሚ በምድረ-ኦሮሚያ እየተንቀሳቀሱ በወሐቢያና በሃዋርጃ ስም ብሔር ሳይለዩ ኦርቶዶክሳውያንና ለዘብተኛ ሙስሊሞችን እንዲሁም ፕሮቴስታንቶችን በተለይ ደግሞ የመካነ-ኢየሱስ ሉተራውያንን ያጠቁ የሙስሊም አክራሪዎችን ድርጊት እንደቀላል የእኩልነት ጥያቄ ብቻ እንድናየው እነ አባስ ሀጂ ስለመከሩን እንዳላየ እንለፈው፡፡ነገር ግን ከአክስት ልጅ ጀምሮ መጋባትን የሚፈቅደው የእስልምና ስብከት እንኳንስ ከአክስት ልጅ ጋር ከጎሳ አባል ጋርም ጋብቻን ከሚከለክለው የኦሮሞ ብሉይ ልማዳዊ ሕግ ያለው ተቃርኖ፣ኦሮሙማን በምድረ-ኦሮሚያ ለመገንባት ከሚታገለው የኦሮሞ ብሔርተኝነት ጋር ‹ድንበር-ለምኔ› የሚለው ዘመናዊው እስልምና ያለው አለመጣጣም፣እንዲሁም ወደ ድሬ ሼክ ሁሴን መሄድን ወደ አባ ሙዳ እንደሚደረግ ምትክ መንፈሳዊ ጉዞ (ጂላ) የማይመለከተው የዘመኑ እስልምና (ወሀቢዝም) በነአባስ ሐጂ (Abas Haji:p.110-113) ቀደም ሲል ለስላሳ ትችት ሲደርስበት የነበረ ቢሆንም አሁን አሁን ግን እስልምና በኦሮሚያ ኤሊቶች ዙሪያ ኃይል እየተሰማው ስለመጣ ነው መሰለኝ ትንፍሽ የሚል የለም፡፡በነገራችን ላይ የልሂቁን ኦሮሞ ድምጽ የሚቃኙት በዋናነት ሙስሊም የመደብ ጀርባ ያላቸው ኦሮሞ ልሂቃን ሲሆኑ በተከታይነት የምዕራብ ኦሮሚያ ፕሮቴስታንቶች ያጅቧቸዋል፡፡ለሃይማኖት ልዩነት ልበ-ሰፊ ከነበረው ሜጫ እና ቱለማ መፍረስ በኋላ ባሉ ኦሮሞ-ተኮር አደረጃጀቶች ኦርቶዶክሳውያን ኦሮሞዎች በኅቡዕና በገሀድ ክፉኛ እንዲሸማቀቁና ከኦሮሞነት እንደወረዱ እንዲሰማቸው ሰፊ አግላይ ፕሮፖጋንዳ ተሰርቷል፤እየተሰራ ነው፡፡
(6.8) ካቶሊክስ ለምን ይቅርባት?!ትፈተሸ::የካቶሊክ ሚሽነሪዎች ገና ወደ ክርስትና ያልገባችውን ምድረ-ኦረሚያ (ፊንፊኔ) እንዴት ይመለከቷት እንደነበር አባ አንጦንዮስ ሲጽፍ ‹‹...የፊንፊኔና የአካባቢው ሕዝብ በጨለማ ውስጥ በሞት ጥላ ስር ይኖር ስለነበር የወንጌል ስርጭት በእርግጥ አስፈላጊ እንደነበር አባ ቶረን ሻኽኝ አስረድተው በአካባቢው የወንጌል ትምህርት ለማድረስ ቢያንስ አራት ወይም አምስት ተጨማሪ ሚሲዮናውያን እንደሚያስፈልጉዋቸው ኣሳስበው ነበር››ይሉናል (አባ አንጦንዮስ፡ገ.126) የአባ ቶረን ሻኽኝን የጥቅምት 14 ቀን 1868 ዓ.ም ደብዳቤ ጠቅሰው፡፡የባሪያ ንግድ፣ሴት ልጆችን ያለፈቃዳቸው መዳር፣በጋብቻ ላይ ጋብቻ የመሳሰሉ በኦሮሞና ሲዳማ ግዛቶች የሰፈኑ ልማዶች ለካቶሊካውያን ሚሽነሪዎች ፈተና ሆነው እንደነበርም አባ አንጦንዮስ በዚሁ መጽሐፍ ከገጽ 120 ጀምሮ ለስለስ ባለ የሚሲዮናውያን ቋንቋ በጊዜው የነበረውን ጎጂ ባሕል ተችተው ተርከውታል፡፡
(6.9) ከላይ የቀረቡት በኦሮሞ ባሕልና እምነት ላይ ያሉ አመለካከቶች ከራስ አስተሳሰብ/ሃይማኖት ውጭ ያለውን ባሕላዊ/ሃይማኖታዊ አመለካከት በራሱ በባሕሉ ዐይን ሳይሆን ‹‹በግል›› መለኪያ መለካት የሚያመጣውን የተዛነፈ ችግር ያንጸባርቃሉ፤ችግሩ ይብዛም ይነስም በሁሉም ወገን አለ--በሁሉም--የኢኦተቤክ ምዕመናንና የዋቄፈና አማንያንን ጨምሮ፡፡የዚህ አመለካከት አንጸባራቂ ከሆኑ ግለሰቦች አንዱ የሆነው Krapf የጻፈውን የኛው መሐመድ ሐሰን እንዳለ ገልብጦ በኦሮሞ ጥናት መጽሔት ቁጥር-7 ላይ በገጽ-118 ያሰፈረውን እንይ! <<...the Amhara Clergy were not sensitive to Oromo food habits in which milk, butter and meat were central>> ሲል አስቀምጦታል፡፡በKrapf ፕሮቴስታንታዊ እይታና በመሐመድ የከረረ ብሔርተኛ ምልከታ መሰረት የኢኦተቤክ የዐማራ ብቻ ናት፤የኢኦተቤክ ዶግማና ቆኖና አፈጻጸሙም ከብሔር-ብሔር እየተለያየ መተግበር አለበት!በነመሐመድ እምነት ለምሳሌ፡- የደብረብርሃን ዐማራ ኦሮቶዶክሳውያን በፍልሰታ ከሥጋና ቅቤ ሲታቀቡ የእነሱ ጎረቤት የሆኑት የልቼ እና የሸኖ ኦሮሞዎች ግን በፍልሰታ ስጋና ቅቤ የተከለከሉት በሃይማኖቱ ዶግማና ቀኖና ሳይሆን በዐማራ ቸልተኝነት ነው!!የደጀን (ጎጃም) አባይ ዳር ያሉ የቅ/ሩፋኤል ቤ/ክ አካባቢ ዐማራ ጸዋሚዎች በጾም ከስጋ ታቅበው፤በሌላ በኩል በሰ/ሸዋ ገርበ-ጉራቻ የፍልቅልቅ እና አካባቢዋ የቅ/ሩፋኤል የአባይ ዳር (የደራ?) ኦሮሞ ኦርቶዶክሳውያን ጾማቸውን ከስጋና ወተት ጋር ማከናወን ነበረባቸው!!ይሄ ያልሆነው የኢኦተቤክ ኋላቀር ስለሆነች ነው--በመሐመድና በKrapf አረዳድ!!እሺ!የኢኦተቤክ የጾም ስርዓትስ በነመሐመድ ጥልቅ የነገረ-ኦርቶዶክስ ጥናት የዐማራ ቀሳውስት ፈጠራ ነው ተብሏል!ሰው እንዴት ከግብጽ እስከ ሕንድ፣ከሶርያ እስከ አርመንያ፣ከአቴንስ እስከ ሞስኮ፣ከአስመራ እስከ አልባኒያ ያሉ ኦርቶዶክሳውያን ሁሉ በጾማቸው ወራት ጥሉላት ምግቦችን (የእንስሳት ተዋጽኦዎችን) እንደማይመገቡ ጎግልን ጎልጉሎ መረዳት ያዳግተዋል??መሐመድ ሐሰንን የሚያክል የታሪክ ባለሙያ ለጾም ያን ያህል የተደነገገ ዝርዝር ቀኖና ከሌለው የክርስትና ዘውግ (ፕሮቴስታንት) ሃይማኖታዊ ግንዱ የሚመዘዘውን (ፓስተር?) Krapf ምንጩ አድርጎ እንዴት ስለ ኢኦተቤክ የጾም ቀኖና ብይን ይሰጣል? ከሰጠስ ለምን የረመዳን አጽዋማት በኦሮሚያ ያላቸውን አቀባበል ጨምሮ መርምሮ በንጽጽር አይተነትንልንም?‹‹ሌሊት እየተመገቡ ቀን-ቀን መጾምን የሚደነግገው ረመዳን ከኦሮሞ ባሕል ጋር ያለው ተዛምዶ እንዴት ይታያል?በሙስሊምና በኦሮሞ ኦርቶዶክሳውያን መካከል ያለው የሃይማኖት ሕገጋት አቀባበል ከኦሮሞ ባሕል ጋር ያለው አንጻራዊ ውሕደትስ?›› ብለን ብንጠይቅስ?
7-- ክስ-ሰባት፡- የኢኦተቤክ እንደመሬት ከበርቴ (ባለ‹‹ሲሶ›› ግዛት)!!
በሁሉም የሀገራችን ጸሐፍያን የኢኦተቤክ ባለሲሶ ይዞታ የነበረች መሆኗ በስፋት ተጽፏል--በራሷ መጻሕፍት ሳይቀር፡፡እነ መኩሪያ ቡልቻም ይህንኑ ደጋግመው ጽፈውታል፡፡አባስ ሐጂም የቡልቻን ጽሑፍ ጠቅሶ <<...the clergy were given land that was confiscated from the Oromo peasants and become landlords, they owned Oromo peasants as Gabbars (serfs) and thrived upto their labour...>> በማለት ብሶቱን ያቀርባል (Mekuria cited in Abas Haji:p.104)፡፡ጥሩ፡፡እዚህ ላይ አንድ እውነት አለ::በኦሮሞም ሆነ በተቀሩት ብሔር-ብሔረሰቦች (ዐማሮችንና ትግራውያንን ጨምሮ) ‹የሰሞን መሬት› የሚባል የቤ/ክ ይዞታ አይነት ነበር፡፡ነገር ግን የዚህ መሬት ይዞታ ለስሙ የኢኦተቤክ ይባል እንጂ ባለቤቶቹ ተመልሰው መኳንንቱና መሳፍንቱ ነበሩ፤ያዙበታል፤ምርቱን ይቆጣጠራሉ፤እንዲሁም ሲሞቱ ለልጆቻቸው ያወርሱታል--መሳፍንቱ፡፡የካሕናቱ እጣ-ፈንታ በመሳፍንቱ ስር ቅጥረኛ ሆኖ በድርጎ (የእለት ምግብ) ብቻ ማገልገል ነው፡፡በሌላ አነጋገር ካሕናቱ የበላይነታቸው በመንፈሳዊ ጉዳዮች እንጂ በቤ/ክ ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች የማዘዝ መብት አልነበራቸውም፡፡ስለሆነም መሳፍንቱ በካሕናት ስም በተቆጣጠሩት ይዞታ መልሰው ካሕናቱን በእለት ምግብ ብቻ እየደለሉ በማስገልገል የተረፈውን ምርት ለግላቸው ይጠቀሙበታል፡፡ይሕ የባላባትና የደሃ ካሕናት ሥርዓታዊ የብዝበዛ ግንኙነት በተለምዶ ‹‹የቶፋ ሥርዓት›› ይባላል፡፡እንዲሕ ስር ሰድዶ የኖረው ሥርዓት ብዙም አይተረክም፡፡በቤተክሕነት ወገኖች የቀደሙ ነገሥታትንና ባላባቶችን አንዳንድ የማይካዱ ውለታዎች እንደማሳነስ ስለሚቆጠር ይመስለኛል የማይተረከው፡፡በዓለማዊ ጸሐፍት ደግሞ አንድም አሰራሩን በቅርብ ካለማወቅና ከቸልተኝነት፣ሁለትም ባለፉት 40 እና 50 ዓመታት ተራማጆቻችን (ተራ-ማጆች!) የኢኦተቤክ’ንን በተገኘው አጋጣሚ ሁሉ በጅምላ ፈርጆ ማሳቀል ቀላል ስራ ስለሆነላቸው ይመስለኛል፡፡እንጂማ የኛ ወላጆች (ወላጅ አባቴ ካሕን ነበር!) በልመና እንጀራ ተማሩ፤ከእጅ ወደ አፍ እንኳ ሊባል በማይችል የሰቆቃ ኑሮ እድሜያቸውን ገፉ፤የረባ ጥሪት ለልጆቻቸው ሳያኖሩ ድኅነትን አውርሰውን ያለእድሜያቸው ተንከራተው አለፉ፡፡ሞቱ፡፡‹‹ሕያዋን ለነገሥታት፤ሙታን ለካሕናት ይገብራሉ›› በሚለው ብሂል በሙታን ተዝካርና የሙት አልባሳት ሲደጎሙ ኖረው ሞቱ፡፡በዋናነት 5ቱ ቀዳስያንና በዙፋኑ ዙሪያ ያሉ ‹‹ካሕናተ-ደብተራ›› ብቻ ነበሩ የንጉሡና የምዕመኑ እርጥባን ተቋዳሾች፡፡የተቀረው ለማኝ ነው፡፡በካሕናቷ ‹ምንዳቤ ወረኀብ› የኢኦተቤክ ‹የልመና ሃይማኖት› ተብላ ትጠራ ነበር፤አሁንም ይሕ ስያሜ በከፊል አለ፡፡ይሄ ይታወቃል፡፡ታሪክ ሲጻፍ ግን ‹‹ባለሲሶ ግዛት›› ይባልልናል!!ግና እንዲያ እንዳልሆነ ይታወቅ ነበር፡፡ስለመታወቁ ማስረጃ እንቁጠር...

Saturday, October 10, 2015

ስለአንዳንድ በኢ.ኦ.ተ.ቤ.ክ ላይ…ከአንዳንድ የኦሮሞ ጸሐፍት የተሰነዘሩ…ያስቀየሙኝ ክታቦች!!


 ከበአማን ነጸረ (ክፍል ሁለት)


5-- ክስ-አምስት፡- በኦርቶዶክስ እልህ ወለጋ ጰነጠጠ፤ወሎ-አርሲ-ጅማ-ሐረር ሰለሙ!!
መኩሪያ ቡልቻ ‹‹...In Wollo in the North, in Arsi in Bale and Hararghe in the South and Sout-East, and in Jimma in the South-West Islam was adopted to avoid the often forced mass conversion by the clergy of the Abyssinian Orthodox Church.In Wallaga, in the West many Oromos including most of the traditional elites became protestants>>ይለናል (Being and Becoming Oromo:p.55)፡፡እስኪ ይቺን የመኩሪያ ጽሑፍ ገላልጠን እንያት--አንድ በአንድ!!
(5.1) ወሎ እነ መኩሪያ ቡልቻ ‹‹አቢሲኒያ›› ብለው ከሚጠሩት ግዛት ራሱን ገንጥሎ የኖረ ሳይሆን በግዛቱ ውስጥ ተዋናይ ነበር፡፡‹‹ወሎ በእልህ እስልምናን ተቀበለ›› የሚል ታሪክ ምናልባት ከካቶሊካዊው አቶ አጽሜ አግኝተው እነ መኩሪያ ቡልቻ ‹የአዋቂ አጥፊ› እንሁን ካላሉ በቀር ታሪኩ በራሳቸው በሙስሊም አማንያንና በውጭ ሀገር ጸሐፊዎች ተተርኳል--ወደ ወሎ እስልምና የገባበት ጊዜ፡፡ለማሳያ ያሕል ታቦር ዋሚ ሙስሊም ጸሐፍትንና ፖርቱጋላዊው አልፋሬዝ በ1520ዎቹ ስለሙስሊምና ክርስቲያን ወለየዎች ተፋቅሮ የከተበውን ማስታወሻ ዋቢ አድርጎ የግራኝ አህመድ ጦር በአካባቢው ከመድረሱ በፊት ወሎዬ የእስልምና ሃይማኖት ተከታዮች እንደነበሩና ሕዝቡ [የወሎ] በሃይማኖት ሳይለያይ በሰላም አብሮ ይኖር እንደነበር አትቷል (ታቦር ዋሚ፡ገ.306)፡፡ከዚህ አንጻር ‹ወሎ በኦርቶዶክስ እልህ ሰለመ› ብሎ መጻፍ የኦርቶዶክስን ብቻ ሳይሆን የእስልምናንም ሆነ የወሎን ሕዝብ ታሪክ ያገናዘበ አይመስለም፡፡
(5.2) የአርሲን እስልምና በሚመለከት በአካባቢው ታሪክ ላይ ወረቀቶች የሠራው አባስ ሐጂ ሲገልጽ <<....among the Arsi and the Oromos of Harar where there was an old Islamic presence, Christianity failed to get foot hold>>በማለት (Abas Haji: p.107) አካባቢው የሰለመው ቀደም ብሎ ማለትም ከክርስቲያኑ ኃይል ማንሰራራት በፊት መሆኑን ያመለክታል፡፡አቶ አጽሜ ‹‹ኦሮሞ ዐማራን ስለጠላ ሰለመ›› እያሉ በካቶሊካዊ ሚሽነሪ ወገንተኛነት የጻፉትን አባስ ሐጂ ሲተችም <<This [Atsme’s] explanation is however, not adequate because Islam entered the region long before Imperial conquest...>> እያለ በአርሲ ነዋሪ ነባሪ የእስልምና እርሾ መኖሩን ይነግረናል፡፡የአባስ ትችት ለሀቅ ሳይሆን ለእስልምና ከመቆርቆር ነው ብዬ ለመጠርጠር እገደዳለሁ፤ቢሆንም ለእውነታው ከመኩሪያ እና ከአቶ አጽሜ ጽሑፍ የእሱ ይቀርባልና ተጠቀምኩት!
(5.3) የሐረር እና ጅማ ኦሮሞዎችን ቀደም ብሎ መስለምና የሸዋን ኦሮሞ ኦርቶዶክሳዊነት በሚመለከት ዶናልድ ሌቪን ሲገልጹ ‹‹ሐረር የፖለቲካ ማዕከል መሆኗ ቀርቶ የእስልምና ባህል ማስፋፊያና መስበኪያ ስለሆነች ፣ኦሮሞዎች ለሐረር ቅርብ በመሆናቸው እንዲሁም ደግሞ ምናልባት የሱማሌዎችንና የአፋሮችን ምሳሌ በመከተል ተነሳስተው አብዛኞቹ ኦሮሞዎች የእስልምና ተከታይ ሆነዋል፡፡......በላይኛው ጊቤ የሠፈሩት የኦሮሞ ጎሣዎች....በ18ኛውና በ19ኛው ክፍለ-ዘመን የራሳቸውን ነገሥታት አቋቁሙ፡፡የአቋቋሙት የዘውድ ሥርዓት የእስልምና ሃይማኖትን ተቀብሏል፡፡በአጭሩ በ19ኛው ክፍለ-ዘመን ከምኒልክ ድሎች በፊት፡፡...በሣሕለሥላሴ ዘመን (1813-1847 ዓ.ም)...አብዛኛው የሸዋ ኦሮሞ ክርስቲያን ሆነና በዐማራና ኦሮሞ መካከል የሚፈጸመው ጋብቻ የዘወትር ክስተት ሆነ፡፡››(ሌቪን፡ገ.73-75)፡፡የኢናርያውን ንጉሥ የአባ ባጊቦን አስቀድሞ መስለም የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን መጽሐፍ ጸሐፊው አባ አንጦንዮስም ገልጧል (አባ አንጦንዮስ፡ገ.83)፡፡
(5.4) ዶ/ር ላጵሶ ጌ.ድሌቦ በ‹‹የኢትዮጵያ ረጅም ሕዝብና ታሪክ፣አንደኛ መጽሐፍ›› ሁኔታውን ሲገልጹ ‹‹...በ1840 እና 1870 መካከል ከሸዋና ከሰሜን ኢትዮጵያ እስላማዊ የወርጅ-ጀበርቲ ነጋዴዎች በአምስቱ የጊቤ ማለትም የጉንጋ ኦሮሞ መንግሥታት ከንግድ ጋር እስልምና አስፋፉ፡፡›› በማለት የጊቤ መንግሥታትን ወደ እስልምና መግባት ከሙስሊም ሲራራ ነጋዴዎች ስብከት ጋር አያይዘውታል፡፡ትረካቸውን ሲቀጥሉም ‹‹....በተጨማሪም በደቡብ ምስራቅ ጥንት የባሊ የአዳልና የሀዲያ እስላም አገሮች የሰፈሩ የኦሮሞ ማኅበረሰቦች ከገዳ ሥርዓት ወጥተው በአጭር ጊዜ ውስጥ እስላሞች ሆኑ፡፡›› በማለት የእስልምናን መስፋፋት እንደ መኩሪያ እና አቶ አጽሜ አበባል ‹‹ከዐማራ ቄሶች እልህ ጋር›› ሳይሆን ከንግድ መነቃቃት ጋር አያይዘው ተአማኒ በሆነ መንገድ አቅርበውታል (ዶ/ር ላጵሶ ጌ.ድሌቦ፡ገ.252)፡፡የዶ/ር ላጵሶን አተራረክ ተአማኒ የሚያደርገው በአጠቃላይ በ19ኛው ክፍለዘመን እስልምና በንግድና በግብጻውያን መሪዎች የተጠናከረ ኢስላማዊ ስብከት በኦሮሚያ ብቻ ሳይሆን በሰሜን ኢትዮጵያ አካባቢዎች በተለይም በኤርትራ ቆላማ አካባቢ የነበሩ የትግረ፣የቢለን፣የማሪያ (የሀባብ፣የመነሳ፣የሳሆ) ጥንተ-ክርስቲያን ማኅበረሰቦች ወደ እስልምና መግባታቸው ነው (ዝኒ ከማሁ፡ገ፣258)፡፡የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ታሪክ ፀሐፊው ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ካልዕ (M.A) ከዚህ የዶ/ር ላጵሶ ትረካ ጋር በሚመሳል መልኩ የኤርትራ ቆላማ አካባቢ ቀደምት ኦርቶዶክሳውያን ‹‹መሐመድ አሚን እልሚርጋኒ›› በተባለ ከግብጹ ገዥ ‹‹አህመድ ኢብን ኢድሪስ›› የተላከ ሙስሊም ሰባኪ ተሰብከው ስለመስለማቸው ጆን ስፔንሰርን ዋቢ አድርገው ጽፈዋል (አቡነ ጎርጎርዮስ፡ገ.69-71)፡፡ስለሆነም ይሕን በኦሮሚያ ብቻ ሳይሆን በሁሉም የሀገሪቱ አካባቢዎች በውጫዊ ኃይል ተልእኮና በውስጣዊ የሲራራ ነጋዴ ሙስሊም ሰባክያን የተገኘ የእስልምና መነቃቃት በኢኢተቤክ እልህ ብቻ ያውም በኦሮሚያ ብቻ እንደታየ እንግድ እንቅስቃሴ አድርጎ መተረክ አድማስን ማጥበብ ይመስለኛል፡፡
(5.5) የወለጋን በፕሮቴስታንት ተጽእኖ ስር መውደቅ በሚመለከት ድርጊቱ የተከናወነው በኦርቶዶክስ ጥላቻ ነው ብሎ መደምደም አስቸጋሪ ነው፡፡የቀ.ኃ.ሥ መንግሥት ከጣሊያን መውጣት በኋላ በነበረበት የኢኮኖሚ ድቀት የተነሳ ሚሲዮናውያን ወደ ሀገሪቱ ገብተው ማኅበራዊ አገልግሎት እንዲያበረክቱ ፈቀዱ፡፡በዚህ አጋጣሚ የኦርቶዶክስና የእስልምና ተጽእኖ ወዳልበረታበት ወለጋ ሄዶ በመስበክ የአውሮፓ ሚሽነሪዎች (ኋላ ግንባር ፈጥረው መካነ ኢየሱስን የመሰረቱት) እና የአሜሪካ ሚሽነሪዎች (ኋላ ቃለሕይወትን ያቋቋሙት) እድሉን ተጠቀሙበት፡፡ሚሽኖቹ ተደብቀው ሳይሆን በሕግ ማስታወቂያ ቁጥር 3/1937(?) (decree No.3/1944) በአካባቢው በይፋ እንዲሰብኩ ንጉሡ ፈቅደው ነው የተሰማሩት፡፡ወለጋ ፕሮቴስታንት እንዳይሆን ኃይለሥላሴ አልተከላከሉም፤ይልቅስ ፈቅደዋል ቢባል ይሻላል፡፡ይሕን ደግሞ <<...CMF [Chiristean Missionary Fellowship] ....choose Ethiopia because of Haile Selassie’s friendly policy towards Missionary groups.>> በማለት (Eric Gilchist:p.63) ያብራራልናል፡፡በአጠቃላይ የወለጋ በፕሮቴስታንት ተጽእኖ ስር መውደቅ መኩሪያ ቡልቻ እንደሚለው በኦርቶዶክስ የግዳጅ ክርስትና ሽሽት ሳይሆን ለወትሮውም በአካባቢው ስር የሰደደ የእስልምና እና የክርስትና ዘውጎች ተጽእኖ ስላልነበረ፣ስለ ኦርቶዶክስ ስላልተሰበከ፣በአንጻሩ የሃይማኖት ስብከታቸውን ከማኅበራዊ አገልግሎት (ትምህርትና ጤና) ጋር አቀናጅተው የሚሰሩ ፕሮቴስታንት ሚሽነሪዎች በመንግሥት እውቅና እና ፈቃድ በአካባቢው እንዲንቀሳቀሱ ከ1930ዎቹ ጀምሮ በሕግ ስለተፈቀደ ነዋሪው በብዛት ፕሮቴስታንት ሆነ ቢባል የተሻለ ይሆናል፡፡እንደሚታወቀው ከጣሊያን መውጣት በኋላ ለሚሽኖች በወጣው ሕግ ወለጋ እና ደቡብ ኢትዮጵያ የመሳሰሉት አካባቢዎች open area ተብለው ለሚሽኖች ሲፈቀዱላቸው ማዕከላዊና ሰሜን ኢትዮጵያ ግን closed area ተብሎ ሚሽኖች ወደዚያ ሄደው ለመስበክ ፈቃድ አልነበራቸውም፡፡የሚያሳዝነው mis-ነሪዎቹ ስላላዩትና ስላልሰበኩበት የሰሜን ሕዝብ (በእነሱ አጠራር ‹‹አቢሲኒያ››) እና ስለሚከተለው እምነት በነሲብ (በጨበጣ) እየጻፉ በእንግሊዝኛ የተጻፈን ሁሉ እንደወረደ ለመቀበል የሚያሰፈስፈውን ሐገራዊ ምሑር ስተው ያሳስቱታል፡፡‹እግዜር ይይላቸው› ከማለት በቀር ምን ይባላል!!
6-- ክስ-ስድስት፡- ኦርቶዶክስ የኦሮሞ ባሕል ጸር!!
‹‹ኦሮሙማ›› የሚለውን ቃል ከእምነት (belief)፣ከዘውግ (ethinicity) እና ከማንነት (identity) ጋራ አስተሳስሮ የሚሰብከው ባህል-ተኮሩ ገመቹ መገርሳ <<An Oromo person does not become a member of a beiliving community through a formal rite of incorporation such as baptism.An Oromo is born with Orommuma>> ካለ በኋላ የተለመደውን ‹‹አቢሲኒያ››ን እና ኦርቶዶክስን ሆን ብሎ አመሳስሎ የመጥራት ዘዴ ተጠቅሞ ሲተርክ <<…Borrowing their faith from the Judo-Chiristian tradition, Abyssinians came to revere a white God and reduced the Oromo belifs in Waqqa Guraacha to a form of Devil Worship>>ይለናል (Bieng and Becoming Oromo:p.97)፡፡ንባቡ አጭር ቢሆንም ስንሰነጣጥቀው ትርጉሙ ይበዛል፡፡እናብዛው!!
(6.1) ይቺ ትረካ በራሷ ‹‹አቢሲኒያ›› በሚል በሚገለጸው አካባቢ በውስጡ ከኦርቶዶክ የተለዩ ባሕላዊ እምነቶችና እስልምና መኖራቸውን ትዘነጋለች፡፡አዎ!ይቺ ተደጋግማ የምትነገር ‹‹የአቢሲኒያ ቤ/ክ›› የምትል ቃል ተግሳጽ ያሻታል፡፡የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ራሷን ‹‹የአቢሲኒያ ቤ/ክ›› ብላ ጠርታ አታውቅም፡፡አማንያኗም እንዲያ አይሏትም፡፡እንኳንስ እሷ የሺህ ዘመናት ታሪክ የምትቆጥረው የቅርቦቹ መካነ ኢየሱስ እና ወንጌላውያንም ራሳቸውን ሲጠሩ ‹‹የኢትዮጵያ›› የሚል ቅጽል አስቀድመው ነው፡፡ስለዚህ የኢኦተቤክ ራሷን በማትጠራበት ‹‹አቢሲኒያዊት›› የሚል ስያሜ መጥራት ‹‹ነገር ፍለጋ›› እንጂ ሌላ ስም የለውም፡፡ቤተክርስቲያኒቱን ራሷን በምትጠራበት ሳይሆን ፈረንጅ አኮላትፎ እና አጣሞ በሚጠራት ስያሜ ነው የምንጠራት ማለት የቅንነት አይመስልም፡፡ያስተዛዝባል፡፡
(6.2) በዚህ በነገመቹ መገርሳ እና የሚሽነሪ ማጠቀሻዎቻቸው ለዐማራ-ትግራይ ብቻ በመጠሪያነት በተሰጠው ስመ - ‹‹አቢሲኒያ›› ከሄድን እንደ አገው፣ቅማንት፣ነገደ-ወይጦ፣ኢሮብ፣የወሎና የትግራይ (ራያ-አዘቦ-አሸንጌ) ክርስቲያን ጥንተ-ኦሮሞዎች በትረካው ምክንያት ታሪካቸው ይጨፈለቃል፡፡ከኦሮሚያ ሕዝብ 30.5% የሚሆነው ነዋሪ የሚከተለውን ሃይማኖት እንደዋዛ በባሕላዊ ማንነት ሽፋን ምሑራዊ ቅሰጣ ተጠቅሞ ጥምቀተ-ክርስትናውን ሕሳዌ (የውሸት) ማስመሰልም ደስ አይልም፡፡ምሑራዊ አምባገነንት ይመስላል፡፡ከማንነትም አንጻር ዐማራ እና ትግራይ ራሳቸውን በዜግነታቸው (በብሔር አላልኩም) የሚገልጹት ‹‹ኢትዮጵያዊ›› ብለው እንጅ ‹‹አቢሲኒያ›› ብለው አይደለም፡፡‹‹ኦሮሞ ራሱን በሚጠራበት ስም ነው ሌሎችም ሊጠሩት የሚገባ›› ተብሎ ሁላችንም ከልባችን አምነን ተቀብለን ከተስማማን በኋላ ዐማራና ትግራይ ዐረቦችና ሚሺነሪዎች ባወጡላቸው ስም ‹‹አቢሲኒያ›› ተብለው መጠራት አለባቸው ብሎ የሌላውን ማንነት በይኖ መከራከርና የሃይማኖት ተቋሙንም በዚያ መንገድ ሰይሞ ለማክፋፋት መሞከር ተገቢ አይመስለኝም፡፡ቅር ያሰኛል፡፡አንድ ሰው/ተቋም ራሱን በይፋ የሚጠራበትን የመዝገብ ስም ለውጦ በዚህ እነ እከሌ ባወጡልህ ነው የምጠራህ ማለት ለመደማመጥና ስንጠራራ ለመሰማማትም ያውካል፡፡ራሴን በማልጠራበት ቢጠሩኝ ‹‹አቤት›› አልልም፡፡በአምልኮ ደረጃም ‹‹እ/ሔር ሰውን በአምሳሉና በአርአያው ፈጠረ›› እንላለን እንጅ ‹‹ነጩን በአምሳሉ አንጽቶ፤ጥቁሩን በጥላው አጥቁሮ ፈጠረው›› አንልም፡፡‹‹ሁሉም ሰው በአምሳለ-ፈጣሪ ተፈጥሯል›› ተብሎ ነው በይሁዲውም ሆነ በክርስትናው የሚሰበከው፡፡ከዚህ ውጭ ኦርቶዶክሳዊት ቤተክርስቲያን ‹‹እ/ሔር ጥቁር ነው፤ነጭ ነው›› ብላ ለፈጣሪዋ ቅርጽና ቀለም የማውጣት ትውፊት የላትም፡፡እንዲያውም አብዛኞቹ በየአብያተ-ክርስቲያናቱ ያሉ ጥንታውያን ቅዱሳት ስእላት በቆዳቸው ነጭ ናቸው ተብለው የሚታመኑትን እመቤታችንን፣ጌታን፣ሐዋርያትንና ሰማእታትን ጠይም አድርገው በማቅረብ ትውፊታቸው የሚታወቁት፡፡የሐዲስ ኪዳን መርህኣችን ይኽ ነው፡- ‹‹አይሁዳዊ፡ወይም፡የግሪክ፡ሰው፡የለም፥ባሪያ፡ወይም፡ጨዋ፡ሰው፡የለም፥ወንድም፡ሴትም፡የለም፤ዅላችኹ፡በክርስቶስ፡ኢየሱስ፡አንድ፡ሰው፡ናችኹና››(ገላትያ ምዕራፍ 3 ቁጥር 28)፡፡
(6.3) ገመቹ መገርሳ ግን እንኳንስ ይሕን ሀቅ ወደመሬት ወርዶ ሊጽፍልን የሁሉም ክርስቲያኖች ሆነ ይሑዲዎች ወይም የሙስሊሞች የሃይማኖት መርህ ሐጋጊዎች (ደንጋጊዎች) የመካከለኛው ምስራቅ የፈካ ገጽታ ያላቸው (ነጮች?) ነቢያት/ሐዋርያት መሆናቸውን ሳያስተውል ክርስትናን እና ይሁዲን ከእስልምና ነጥሎ ስለ ‹ዋቃ ጉራቻ› ክብር ሲል ይሰዋቸዋል፡፡አናሲሞስ ወደ ኦሮሚፋ የተረጎመው መጽሐፍ ቅዱስ ከይሑዲ-ክርስቲያን ባሕል ውጭ ይመስል ጃሌ ገመቹ አቃቂር ይነቃቅሳል፡፡ምስጢሩ ዞሮ-ዞሮ የፈረደባትን ኦርቶዶክስ በተገኘው አጋጣሚ ሁሉ ነጥሎ ማነወር ነው!የዋቃ ጉራቻን የጠየመ ምስል ለማጉላት ክርስቶስን (ለስም አጠራሩ ክብር ይግባውና) እና አምላኪዎቹን ማሳነስ ነው!!ለነገሩማ ጥቁሩ አምላክ(Waqqa Guraacha) በጥቁረቱ ከተወደሰ፣ነጩ አምላከ-ሙሴ (እ/ሔር ወይም ኢየሱስ) በንጣቱ ከተወቀሰ ዘረኝነቱ አልሸሹም ዞር አሉ ነው፡፡ማን ነው የጥቁርን ዘረኝነት ቅድስና የሰጠው?!Is it not counter-racism? Is racism of black people against white brothers justifiable?
(6.4) የኦርቶዶክሳዊነት-እና-ኦሮሞነት ውኅደት በተግባር ይታይ ከተባለ የኢኦተቤክ በኦሮሞ ባሕላዊ ጭፈራዎች ታጅባ የታቦት ንግሦችንና ጥምቀትን ማክበሯን ጃንሜዳ፣ፉሪ ሃና፣የካ ሚካኤል እንዲሁም በአጠቃላይ ኦሮሞ ኦርቶዶክሳውያን ባሉባቸው አድባራት ሄዶ መታዘብ ይቻላል፡፡በተለይ በሸዋ ኦሮሞ ባሕላዊ አልባሳትን በማበረታታት፣በኦሮሚፋ መዝሙራት ባሕላዊ የሙዚቃ መሳሪያዎችን ብቻ በመጠቀም፣ጨፌ በየገዳማትና አድባራቱ በመጎዝጎዝ፣ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የእሬቻን ጤናማ ትርጉም በማጤንና በማጉላት ኦርቶዶክሳውያን የኦሮሞ ካሕናትም በአከባበሩ ተገኝተው በማክበር፣በኦሮሚያ በሚገኙ አብያተ-ክርስቲያናት (ደ/ሊባኖስ፣ቁልቢ፣ዝቋላ፣ወንጪ ቂርቆስ፣ደብረ-ፅጌ፣ዝዋይ ገዳማት፣ወዘተ…) መንፈሳዊ ጉዞዎችን በማካሄድ የሕዝብ ለሕዝብ ትስስር ሲደረግ ኖሯል፤አሁንም የበለጠ ለማዳበር ጥረት እየተደረገ ነው፡፡እነዚህ ድርጊቶች እንዴትም ቢተረጎሙ በኦሮሙማ ላይ አሉታዊ ጎን አላቸው ማለት አስቸጋሪ ይመስለኛል፡፡ኦሮሙማ እና ኦርቶዶክስ እንዳይጋጩ አድርጎ ማስቀጠል እንደሚቻል ኦርቶዶክሳውያን የቱለማ ኦሮሞዎች በበረከቱበት የሸዋ ምድር በድምቀት የሚከበሩት 2ቱ የፀደይና የበልግ እሬቻዎች ምስክሮች ናቸው፡፡
(6.5) ኦሮሙማን በማስተናገድ አቅሙ ኦርቶዶክስ በጥንታዊው የኦሮሞ እምነት ዋቄፋና እና በእምነቱ መሪ በአባ ሙዳ ዐይን ይገምገም ከተባለም ሌሎች የሃይማኖት ተቋማትና መሪዎቻቸው ስለ እሬቻ፣ቃሉ፣ቃሊቻ፣ጂላ፣ጨሌ፣ቦረንትቻ፣ዋቃ ጉራቻ፣ሀማቺሳ፣ወዘተ ያላቸው አተያይ፣እንዲሁም ለኦሮሞ አለባበስ፣ባሕል፣ሙዚቃ፣ሥነ-ልቦና ያበረከቷቸው አስተዋጽኦዎች በዝርዝር ተገምግመው ደረጃ ቢሰጠን ሸጋ ነው፡፡አሁን እየተደረገ ያለው በሕግ ተፈቅዶላቸው በኦሮሚያና በደቡባዊ ሀገሪቱ ክፍል ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ሚሽነሪዎች ሀገሪቱን በፈለግነው መጠን ፕሮቴስታንትና ካቶሊክ እንዳናደርጋት ተከላክላናለች የሚሏትን የኢኦተቤክ እያነወሩ የጻፉትን እንደወረደ እየገለበጡ በዋቄፋና ከለላነት ተጠልሎ ምሑራዊ ጥላቻ መዝራት ነው፡፡በውጤቱም ኦርቶዶክሳውያን ኦሮሞዎችን ሆድ እያስባሱ ወደ ፕሮቴስታንቲዝም ከማስኮብለል በቀር በኦሮሚያ የዋቄፋና ተከታዮች ቁጥር 4% እንኳ ሲደርስ አላየንም!

To be continued.......

Monday, October 5, 2015

ስለአንዳንድ በኢ.ኦ.ተ.ቤ.ክ ላይ…ከአንዳንድ የኦሮሞ ጸሐፍት የተሰነዘሩ…ያስቀየሙኝ ክታቦች!!


በአማን ነጸረ ፣ መስከረም 10 ቀን 2008 ዓ.ም

የታላላቅ ኦሮሞ ወንድሞቼን ቅሬታ የተጫናቸው ጽሑፎች አንብቤ ቅር አለኝ፡፡መነሻ የሆናቸውን ታሪካዊ በደል ለመረዳት አልሰነፍኩም፡፡ያም ሆኖ መስመር ያለፈና ባንድ ቦይ ብቻ የፈሰሰ በመሰለኝ ቅሬታቸው ቅር አለኝ፡፡ቅሬታዬ ቆየ፡፡ፈራሁ፡፡ከዚህ በላይ በሆዴ ከቆየ ቂም ይሆንና ይጎዳኛል ብዬ ፈራሁ፡፡ስፈራ ቅሬታዬን በረጅሙ (በፌስቡክ ስሌት ነው ርዝማኔው መጉላቱ) ጻፍኩት፡፡ሆኖም ስጽፈው ከ3 ችግሮች እንደማልነጻ አምኜ ነው፡፡አንድም በሁለንተናዬ ስላደኩበትና አሁን ድረስ በዕለት ኑሮዬ ስለሚደጉመኝ እንዲሁም የማኅበራዊ መደብ ጀርባዬ ስለሚመዘዝበት ተቋም ስናገር ንግግሬ ከሚዛናዊነት ይልቅ ወደ ተከላካይነት (advocacy?) እንደሚያጋድል ይታወቀኛል፡፡ሲቀጥል አማተር ነኝና የአጻጻፍና የማስረጃ ስደራ ችግር አያጣኝም፡፡እንዲያም ሲል ከሃይማኖት-ፖለቲካ ተዛምዶ አንጻር ያለኝ አረዳድና ንባብ ድኩም መሆኑን አልስተውም፡፡በተረፈ ‹‹አንዳንድ›› ብዬ የምጠራቸውን የኦሮሞ ጸሐፍት በስም ጠቅሻለሁ፡፡ጉዳዬ ስለክታባቸው ያውም ደግሞ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያንን (ከአሁን በኋላ የኢኦተቤክ) በማስመልከት ስለጻፉበት ነጥብ ብቻ ነው፡፡ከዚህ ውጭ እነሱም ሆነ ሌሎች ጸሐፍያን ስለሚያነሱዋቸው ተያያዥ ጉዳዮች መጻፍ የዚች ትሑት (ታናሽ) ጽሑፍ ዐላማ ስላልሆነ ተዛማጅ ጉዳዮችን አለመንሳቴን በአትሕቶ-ርእስ እገልጻለሁ፡፡
በዚች ጽሑፍ የማተኩርባቸው ቅሬታዎች፡- (1)የኢኦተቤክ ደባትር ‹‹ጋላ›› የሚለውን ቃል ሆን ብለው ኦሮሞን ለማሳነስ ፈልስፈዋል፣(2)የኢኦተቤክ ሥርዓት እኩልነትን አይቀበልም፣(3)አቶ አጽሜ እና አለቃ ታዬ የኢኦተቤክ ደባትር ናቸው፣(4) የኢኦተቤክ ለአፋን ኦሮሞ ጽዩፍ ናት፣(5)በኢኦተቤክ እልህ የተነሳ ወለጋ ፕሮቴስታንት ሆነ፤ጅማ፣ወሎ፣አርሲ እና ሐረር ሰለሙ፣(6)የኢኦተቤክ አስተምህሮ ከኦሮሞ ባሕል ጋር ተጻራሪ ነው፣(7)የኢኦተቤክ ካሕናት በሲሶ ገዥነት በኦሮሞ ምድር የመሬት ከበርቴች ነበሩ የሚሉ ናቸው፡፡አሁን ቀጥታ ወደታመቀው ክስና ሐተታዬ….

1-- ክስ አንድ፡- ‹‹ጋላ›› የሚለው ቃል የኢኦተቤክ ደባትር ፈጠራ ነው!!

‹‹ጋላ›› የሚለው ቃል ‹‹የአቢሲኒያ ቤተክሕነት ፈጠራ ነው›› ይላሉ እነ አባስ ሐጂ(ዶ/ር)፡፡‹‹ጋላ›› = መጻተኛ (stranger/outsider) የሚለው አገላለጽ የአቢሲኒያ ቤተክሕነት ፖለቲካዊና ርዕዮተ-ዓለማዊ አመክንዮ ያለው ፈጠራ ነው-- “fabricated by an Abyssinian clergy for politico-ideological reasons” ይሉናል (Mekuria cited in Being and Becoming Oromo: Re-examining the Galla/Oromo Relationship,p.105)፡፡ይቺን አገላለጽ በክብር እቃወማታለሁ፡፡ምክንያቱም በበኩሌ ‹‹ጋላ›› የሚለው ቃል በዚያ መልኩ በኢኦተቤክ የሃይማኖታዊ ሥርዓት መከወኛ መጻሕፍት ተጽፎ እና ተተርጉሞ አላገኘሁትም፡፡አውቃለሁ፡፡ብዙ የኦሮሞ ጉዳይ ጸሐፍት በ1960ዎቹ በ‹‹ራዕየ-ማርያም›› የወጣውን ስርዋጽ (ሆን ተብሎ በእኩያን የተጨመረ--ስረ-ወጥ--ከስር ያልነበረ) ጽሑፍ ይጠቅሳሉ፡፡እንደማመጥ፡-
(1.1) እሱ ስርዋጽ በኢኦተቤክ ደረጃ በሊቃውንትና በቅ/ሲኖዶስ ተመክሮበት ወይም በማናቸውም ከኢኦተቤክ አስተዳደር ጋር ግንኙነት ባለው አካል ፈቃድ/ትእዛዝ/ የወጣ አይደለም፡፡
(1.2) ስርዋጹ የኦሮሞን ብቻ ሳይሆን የሙስሊም፣የፈላሻ (ቤተ-እስራኤል) እና የሻንቅላ (ቤንሻንጉል-ጉሙዝ) ሕዝቦች ክብርንም እየጠቃቀሰ ኢ-ክርስቲያናዊ በሆነ መንገድ ያጎድፋል፡፡ታዲያ ያስተዋለ ሰው በግእዝ ቋንቋ ‹‹ሸ›› የሚባል ፊደል የማይታወቅ ሆኖ ሳለ በስርዋጹ ‹‹ፈላሻ እና ሻንቅላ›› የሚሉ ‹‹ሸ›› የበዛባቸው ቃላት በመታየታቸው ብቻ ተራ የእኩያን ጭማሪ (ስርዋጽ) መሆኑን መረዳት ይችላል፡፡እንዲህ ዐይነት ስርዋጽ ጽሑፎች ከዚህ በፊትም ከአንዳንድ ገድላትና ዜናመዋዕሎች ጋር ጎጃምን እንደ አገርና ሕዝብ በተለየ መልኩ ለማነወር በኵሸት ሕዝቡን ‹‹በላዕተ-ሰብእ (ቡዶች)››፤ሀገሩን‹‹ሀገረ-በላእተ-ሰብእ (የቡዶች ሀገር)›› የሚል ተቀጽላ ለመስጠት ተሞክሮ ሊቃውንቱ ታግለው ስርዋጹን ከኅትመት ከልተውታል፡፡ግብጻውያን በፍትሐ-ነገሥቱ ላይ የጨመሩት ‹‹የኢትዮጵያ አዋቂዎች ከራሳቸው ሊቅ ጳጳስ አይሹሙ›› የሚለውና በስንክሳር እስከዛሬ ለታሪክ ተመዝግቦ የሚገኘው ‹‹ኢትዮጵያውያን ከራሳቸው ሰው ጳጳስ ለመሾም ስላሰቡ መቅሰፍት ወረደባቸው›› የሚል ስርዋጽ በገቢር ከ1920ዎቹ ጀምሮ ቢሻርም ስርዋጹ ዛሬም አልተፋቀም፡፡እንዲህ ሲያጋጥም ለፍረጃ ከመሽቀዳደም ስርዋጹን ለማስተካከል ከመጣር በተጓዳኝ ገቢራዊነቱንም መፈተሽ፡፡
(1.3) ገቢሩ ሲፈተሸ ብዙኃን ኦሮሞ-ኦርቶዶክሳውያን ሊቃውንት ይህ ‹‹ጋላ ጋር የተኛ…›› የሚል ስርዋጽ ከመውጣቱ በፊት፣በወጣበት ጊዜ እና ከወጣም በኋላ በኢኦተቤክ ከተራ ካሕን እስከ መዓርገ-ጵጵስና ሲያገለግሉ ነበር፡፡አሁንም ያገለግላሉ፡፡ይሕም ስርዋጹ በምንም ተአምር ከኢኦተቤክ እንደማዕከላዊ ተቋም ታዝዞና ኃላፊነት ተወስዶ እንዳልገባ ገቢራዊ ማሳያ ነው፡፡ለነገሩ በ1960ዎቹ ብልጭ ብሎ የጠፋው ባለስርዋጽ መጽሐፍ አሳታሚና ማ/ቤቱም የኢኦተቤክ ንብረት አልነበሩም፡፡
(1.4) በምዕመን ደረጃ የኢኦተቤክ ብሔር ለይታ ‹‹እከሌን አግቡ፣እከሌን አታግቡ›› አትልም፡፡የመጣው ሁሉ ክርስትና ይነሳል፡፡ክርስትና ተነስቶ አቅመ-አዳም/ሔዋን የደረሰው ሁሉ ጋብቻው በሥርዓተ-ተክሊል ይፈጸምለታል፡፡ይሕ ድርጊት ብሔር አይለይም፡፡በዚህ መንገድ ቁጥራቸው አያሌ የሆነ ኦሮሞ ኦርቶዶክሳውያን በቅድስት ቤ/ክ እርስ በርሳቸውና ከፈቀዷቸው ብሔረሰቦች ተወላጆች ጋር በሥጋ ወደሙ ተወስነው ጋብቻ ሲፈጽሙ ኖረዋል፡፡እየፈጸሙ ነው፡፡ስለሆነም ከ‹‹ጋላ ጋር የተኛ›› እያለ የኵነኔ ፍርድ የሚሰጠው ስርዋጽ የኢኦተቤክ ያላትን አሰራር በቃልም በተግባርም አይገልጽም፡፡ምክንያቱም ጽሑፉ--ስርዋጹ የእርሷ ስላልሆነ!!
(1.5) እስከማውቀው በኢኦተቤክ የኦሮሞ ሕዝብ እና ታሪክ ከሌሎች ተለይቶ በአሉታ አይታይም፡፡ምክንያቱ ግልጽ ነው፡፡በቅርብ ዓመታት በአንዳንድ የኦሮሚያ አካባቢዎች ኦርቶዶክሳውያንን በጫና የማስለምና የማጰንጠጥ ሙከራዎች ብቅ ማለት ቢጀምሩም በረጅሙ የኦሮሞ ሕዝብ ታሪክ ሕዝቡ እንደ ሕዝብም ሆነ የአስተዳደር ሥርዓቱ (ገዳ) በሌላው ሕዝብ ላይ የሃይማኖት ማንነትን በኃይል የመጫን ባሕል አልነበረውም፡፡የ16ኛው ክ/ዘ የኦሮሞ ጦርነቶችም ሃይማኖታዊ ገጽታቸው ጎልቶ ሲነገር አልሰማንም፡፡ሃይማኖት ጫና ካልተደረገበት ደግሞ ሃይማኖታዊ ሰማዕትነት የለም፡፡ስለዚህ የዮዲት፣የሱስንዮስ፣የግራኝ መሐመድ፣የደርቡሽ፣የጣሊያን፣የደርግ እና የ20ኛው ክ/ዘመን የአክራሪ እስልምና ጥቃቶች በኢኦተቤክ መዛግብት በ‹‹ዘመነ-ሰማዕታትነት›› ሲመዘገቡ የኦሮሞ ታሪክ እንደ ብሔር በዚያ መልኩ አልተካተተም፤ድሮም አሁንም፡፡ስለሆነም ያን ያህል ብሔሩን ለማሳደድና የተለየ ስም ለመስጠት የሚያበቃ ቅራኔ በኢኦተቤክ በኩል አልነበረም፤የለም፡፡
(1.6) ወደ ቤተ-መንግሥቱ ደባትር እንሂድ፡፡እውነት ነው፡፡የቀድሞ ነገሥታት ዜና-መዋዕል ጸሐፊዎች በኢኦተቤክ የተማሩ ሊቃውንት ናቸው፡፡ቅብዐ-መንግሥት ቀብተው የሚያነግሡ አንጋሾችም የኢኦተቤክ ጳጳሳት (በዜግነት ግብጻውያን ጳጳሳት) ነበሩ፡፡ነገሥታቱ ኦርቶዶክሳውያን የነበሩ መሆናቸው እውነት ነው፡፡ነገሥታቱ በአገዛዛቸው ዘይቤ ኦርቶዶክሳዊነት የተጫነው religious nationalism አዝማሚያ እንደሚያሳዩና ለኢኦተቤክ አበው የተለየ ውዴታና ከበሬታ እንደነበራቸውም አይታበልም፡፡ኦርቶዶክሳውያን አበው (ጳጳሳት) ንጉሡ በእነሱ እምነት ማደሩን እና እስከ ፍጻሜ ዘመኑም በእምነቱ እንደሚጸና ቃል አስገብተው ይቀቡት እንደነበር እሙን ነው፡፡ይሄ አሰራር ይብዛም ይነስም በሁሉም ቀደምት የነገሥታት ሥርዓት በሰፈነባቸው አህጉር ያለ ነው፡፡በኦሮሞ ጥንታዊ የገዳ ባህልም ተሞክሮው ያለ ይመስላል፡፡ለአባ ገዳነት ለመብቃት ቅብዐተ-ቃሉ (በቃሉ መቀባት) ስለማስፈለጉ ታቦር ዋሚ ብሩ ጸጋዬን ጠቅሶ ሲጽፍ ‹‹…ለአባ ገዳነት ለመብቃትም ዋነኛው መመዘኛ የዋቄፈና ሃይማኖትን አክብሮና የሕዝቡን ወግና ሥርዓቶች ተከትሎ መገኘት ሲሆን…የሉባዎች ስልጣን የሚጸድቀው በቃሉ (አባ ሙዳ) የቡራኬ፣የምርቃትና መቀባት ሥርዓት ነው›› ይላል (ታቦር ዋሚ፡ገ.248)፡፡እርግጥ የአባ ገዳ ሲመት በዘር ሳይሆን በምርጫ መሆኑ ተራማጅ ያሰኘዋል፡፡
(1.7) ወደ ሐተታዬ ስመለስ ነገሥታቱ ለኢኦተቤክ እንደሚባለው ‹‹ሲሶ መንግሥት›› ባይሆንም መጠነኛ እርዳታ ሲያደርጉ መኖራቸውም እውነት ነው፤ኦፌሴላዊ ቋንቋቸውም ለረጅም ጊዜ የኢኦተቤክ መገልገያ የሆነው ግእዝ እንደነበረም እናውቃለን፡፡ያ!ማለት ግን ዜና-መዋዕል ጸሐፊዎች በግእዝ የሚጽፉት ሁሉ የኢኦተቤክ ዶግማና ቀኖና ነው፤ወይም የኢኦተቤክ የውዳሴና ቅዳሴ ዶክመንት ነው ማለት አይደለም፡፡ግእዝ ቋንቋ ነው፡፡እምነት፣ፍልስፍና፣ኑፋቄ፣ታሪክ፣ጥንቆላ፣…ይጻፍበታል፡፡ስለዚህ ይሄን ሳያስተውሉ የኢኦተቤክ በግእዝ ቋንቋ ለተጻፈ ዶክመንት ሁሉ (በተለይ ለነገሥታ ዜና-መዋዕል) ኃላፊነት አለባት ማለት በላቲን ፊደልና ቋንቋ ለተጻፈ ሁሉ ካቶሊኮች ተጠያቂ ናቸው፤ወይም ደግሞ በዐረብኛ ለተጻፈ ሁሉ እስልምና ተጠያቂ ነው እንደማለት ይሆናል፡፡
(1.8) ‹‹ጋላ›› ወደሚለው ቃል አጠቃቀም ልምጣ፡፡ዛሬ አንዳንድ ኦሮሞ ወንድሞቻችን ሚሽነሪዎች ‹‹ጋላ›› የሚለውን ቃል ስለማይጠቀሙ ወደ ወለጋ ያቀኑ ሚሽነሪዎች ተቀባይነት አገኙ ይሉናል፡፡ሸጋ፡፡ሚሽኖችን እንስማቸው፡፡<<The Missinories referred to the Oromo as the Hamitic [non-semetic] GALLAS who spoke GALLINYA.They used this condescending term…as late as 1973, nearly ten years after working with Oromo…>>ይላሉ(GilchrristII:73) (አጽንኦቱ የኔ ነው)፡፡የሚያሳዝነው እነዚህ የፕሮቴስታንትና የካቶሊክ ሚሽኖች ከ10 ዓመትና ከዚያ በላይ (ለምሳሌ፡- የMissio-Galla ባለቤቱ ካቶሊኩ አባ ማስያስ ከ145-1880 ዓ.ም ለ35 ዓመታት እንዲሁም የVicariatus Apostolici apud Gallas Commentarium Historicum ab erectione Vicariatus usque hodie ባለቤቱ አባ ጃሮሶ ከ1882-1938 ዓ.ም ለ46 ዓመታት) በኦሮሞ ሕዝብ መካከል ቋንቋውን (አፋን ኦሮሞ) እየተናገሩ ኖረው በእንግሊዝኛና ጣሊያንኛ ተጠቃሽ መጻሕፍቶቻቸው ‹‹ጋላ›› የሚል ቃል የሚጠቀሙት ‹‹በአቢሲኒያ ቄሶች›› ተጽእኖ እንደሆነ ለማስመሰል ይሞከራል፡፡ያሳዝናል፡፡መቼም ‹‹የአቢሲኒያ ቄሶች›› ተጽእኖ አውሮፓና አሜሪካ ድረስ ተጓጉዞ ለሚታተም የሚሽነሪ መጽሐፍ እንዴት ተጽእኖ ፈጣሪ እንደሚሆን እነሱና ደቀ-መዛሙርቶቻቸው ብቻ ናቸው የሚያውቁት!!
(1.9) ወደ ቤ/ክ መጻሕፍት እንመለስ፡፡ቢያንስ ስለቅኔ ቤት እና ዜማ ቤት ምስክር መሆን እችላለሁ--ስላለፍኩባቸው፡፡በነዚህ ጉባኤያት ‹‹ጋላ›› የሚል የግእዝ ቃል አልሰማንም፡፡በሌላ በኩል በውዳሴ ማርያም የአንድምታ ትርጓሜ የ1990 እትም ላይ በገጽ-86 እንዲህ የሚል ቃል ይገኛል ‹‹…በግብፅ የሚገኙ መነኮሳት በአመት ሁለት ጊዜ ያበስላሉ፡፡…ከአኃው [መነኮሳት] አንዱ ቢታመም ትኩስ እንጀራ የሚያመጣልኝ ባገኘሁ በቀመስሁት ነበር አለ፡፡ከዚህ በኋላ አንዱ የማን ወንድም ትኩስ እንጀራ እያለ ይሞታል ብሎ በመካከሉ <በርበር የሚባል ጋላ> ያለበት ነው፤ያንን አልፎ ሄዶ አምጥቼልሀለሁ ቅመስ አለው…›› እያለ ‹‹ጋላ›› ማለትን ለሽፍታ በርበር ሰጥቶ ይተርክልናል፡፡ በቅ/ያሬድ የኅዳር 29 የተፍጻሜተ ሰማዕት ቅ/ጴጥሮስ ድጓና በእለቱ ስንክሳር ‹‹ጋላት›› (በግእዙ ‹‹ላ›› ላልቶ ነው የሚነበብ) የሚል ቃል ይገኛል፡፡ቅ/ያሬድ በዐረብ ምድር በ4ኛው ክ/ዘ ስለተሰዋው ተፍጻሜተ - ሰማዕት ጴጥሮስ ሲያዜም ‹‹…አባ ጴጥሮስ ተፍጻሜ-ሰማዕት፣መጠወ ርእሶ ለ‹ጋላት›….›› ይለናል፡፡ቅ/ያሬድና የውዳሴ ማርያም መተርጉማን ቃሉን ለሰሜን አፍሪካ ኢ-ክርስቲያን የ3ኛው መቶ ክ/ዘ በርበሮች ሰጥተው ነው የሚናገሩት፡፡ከዚህ ውጭ እኔ ባጭር ዘመኔ ባነበብኳቸው የኢኦተቤክ መንፈሳዊ መጻሕፍት ‹‹ጋላ›› ስለሚለው ቃልና ስለብያኔው አላገኘሁም፤አልተማርኩም፡፡በቅኔ ቤት ‹ደብተራ› ተብለን የተማርንበት የእጅ ጽሑፍ ግስ (መዝገበ-ቃላቱን ግስ እንለዋለን) ‹‹ጋላ›› የሚል ቃል በፍጹም የለውም፡፡የእጅ ጽሑፉ ዛሬም በመጽሐፍ መደርደሪያዬ ያለ ነው፡፡
(1.10) ስለሆነም ይሕን ቃል ‹‹የኢኦተቤክ ደባትር ፈጠራ ነው›› በሚል ድምዳሜ ቤተክርስቲያኒቱንና ሊቃውንቷን በምልዐት ከሥርዓታቱ ጋር አላጥቆ ፈርጆ በጭፍን ከማሳደደድ በፊት ግራቀኙን ማየት አይከፋም፡፡ቢያንስ በተጓዳኝ የዚህን ቃል ምንጭ ዐማራን ጨምሮ በከፋ፣ሐዲያ፣ሲዳማ፣ጋሞ፣ትግራይ፣ሶማሌ….ከመሳሰሉ ብሔረሰቦች ቋንቋ ውስጥ ማሰስ፣ወደ ጎረቤት ሶማሊያና ኬንያ የታሪክ ጽሑፎች ጎራ ብሎ መጠየቅና ሰነድ ማገላበጥ፣ከሩቅ ዘመን ጀምሮ በምድረ-ኦሮሚያ ኖረው በአውሮፓ መጻሕፍትን ያሳተሙ የሚሽነሪ ጽሑፎችን በጥንቃቄ ማገላበጥ የተሻለና ሚዛናዊ መደምደሚያ ላይ ለመድረስ የሚረዳ ይመስለኛል፡፡Thomas Zitelman የተባለው ጸሐፊ በBeing and Becoming Oromo የጥናት መጽሔት Re-Examining the Galla/Oromo Relationship የተሰኘ ጽሑፉ ዘመናዊውና የታደሰው የኦሮሞ ማንነት ቅርጽ የያዘው በስዊድን ሚሽነሪዎች ነው የሚል ምልከታውን ገልጹዋል፡፡እንጥቀሰው <<During the late 19th C the Swedish Protestant missionray activities at Monkullo [Eritrea] provided a contextual frame for a modern reformation of being Oromo, by mixing Protestant zeal,romantic European nationalism and elements of Oromo past>> >>ይላል(Being and Becoming Oromo:p.108)፡፡እንጠርጥር ካልን ይቺ ጽሑፍ የሚሽነሪዎች ተጽእኖ በጎላባቸው የኦሮሚያ አካባቢዎች ሰባክያኑ ከስብከታቸው ጋር ‹‹የአቢሲኒያዎች ቤ/ክ ለኦሮሞ ‹ጋላ› የሚል አዋራጅ ስም ስላወጣች አትሆናችሁምና አዲስ ማንነት በፕሮቴስታንታዊነት ተላበሱ የሚል ብሔር-ተኮር ቅስቀሳ በወለጋ አካባቢ ሳይካሄድ እንዳልቀረ ታመላክታለች›› ብለን መጥርጠር ይቻላል፡፡ይቺ-ይቺ ፀረ-ተዋሕዶ የሚሽኖች ስብከት ተጠራቅማ የኦሮሞ ማንነትን በአዲስ እይታ ለመቅረጽ የተጉ ምሁራነ-ኦሮሞ የሆኑ ጸሐፍት ‹‹ጋላ›› የሚለው ቃል--“fabricated by an Abyssinian clergy for politico-ideological reasons” እያሉ ለጥጠው እንዲጽፉ አበረታታች፡፡ጥርጣሬዬ ነው!!!የሚሽነሪዎቹ ተደጋጋሚ ጸረ-ተዋሕዶ ምዕራባዊ ጽሑፎች የወለዱት ጥርጣሬ!!

2-- ክስ-ሁለት፡-የኢኦተቤክ መዋቅር እኩልተኛ ስላልሆነ ኦሮሞዎች አይጋሩትም!!

የታሪከ-ኦርቶዶክስ ሊቅ ተደርጎ በነመሐመድ ሐሰን (ዶ/ር) እና በነአባስ ሐጂ (ዶ/ር) እዚህም እዚያም የሚጠቀሰው መኩሪያ ቡልቻ (ዶ/ር) <<Oromo Orthodox Christians, though they share religion with Abyssinians, do not share the political/ideological orientation of the Ethiopian Church whose main interest was the preservation [of] structural inequalities enshrined in myths and legends>>ይሉናል(Mekuria cited in Abbas Haji:106)::ታድለው!እዚህ መደምደሚያ ላይ ለመድረስ <የታለ ያደረጋችሁት የመስክ ጉብኝት፣የታለ ለኦሮሞ ኦርቶዶክሳውያን የተደረገው ቃለ-መጠይቅ፣የታለ በየሃማኖቶቹ መካከል ለንጽጽር የሰራችሁት የዳሰሳ ጥናት?> የሚላቸው የለም፡፡የፈለጉትን ቢጽፉ ቋንቋው እንግሊዝኛ እስከሆነ ድረስ ‹‹የደብተራ ተረት›› አይባልባቸውም፡፡ታድለው!ከዚህም ከዚያም እያገጣጠሙ ለያዙት ዐላማ እና ለታደሙበት ድርጅት የሚሆን ታሪክ በልክ ይሰፋሉ፡፡ወደ ሕዝቡ ወርደው አያጠኑም፡፡ብቻ መርጠው ይተነትናሉ፡፡ታሪክ ማለት ትንታኔ፤ትንታኔ ማለት ታሪክ ይሆናል፡፡
(2.1) እስኪ የኢኦተቤክ አደረጃጀት ይታይ፡፡ጥንት ‹‹የሊቃውንት ጉባኤ/ማኅበረ-መነኮሳት/ማኅበረ-ካሕናት›› የተሰኘ የውስጥ ሃይማኖታዊ አስተዳደሩን፣ዶግማና ቀኖናውን የሚበይን አካል ነበረ፡፡ከ1951 ዓ.ም ጀምሮ የኢኦተቤክ ከግብፅ መንፈሳዊ የሞግዚት አስተዳደር ነጻ ወጥታ የራሷን ቅ/ሲኖዶስ ሰይማለች፡፡ፓትርያርኩ ከፋም ለማም ላለፉት 56 ዓመታት የሚሾመው በምርጫ ነው፡፡በአጥቢያ ደረጃ ባለው አደረጃጀት ከምዕመናንና ካሕናት የተውጣጣ ‹‹ሰበካ-ጉባኤ›› የተሰኘ አካል ከ1960ዎቹ መጀመሪያ ዓመታት ጀምሮ እስካሁን ድረስ በ3ቱም ሥርዓታተ-መንግሥታት ያለማቋረጥ እየተመረጠ ቤ/ክ’ንን በማስተዳደር ላይ ይገኛል--ከፋም ለማም፡፡በደርግም አልተቋረጠም፡፡መራጩ ምዕመኑና ካሕኑ ነው፡፡እርግጥ <ዲሞክራሲ፣አሴምብሊ፣ካውንስል፣…> የሚሉ ቃላትን ባለመጠቀማችን ዲሞክራሲ ላይ በኋላቀርነታችን ለሰራነው በደል ዘመናዊ ዲሞክራት ጸሐፊዎቻችንን መጠየቅ ይኖርብናል!!
(2.2) እገምታለሁ፡፡ይሕ የ40 እና የ50 ዓመታት ተሞክሮ የሃይማኖቱን ብሉይ ታሪክ አይገልጽም ይባል ይሆናል፡፡ገዳማቱ ይመርመሯ!!!በስተሰሜኑ ማዕከላዊ ኦሮሚያ ያለውን ገዳም እንምረጥ--የሰላሌውን ደ/ሊባኖስ!!የገዳሙ መሪ ጥንት ‹እጨጌ› አሁን ‹ፀባቴ› ይባላል፡፡ብቻውን በገዳሙ ላይ የማዘዝ መብት የለውም፡፡<ምርፋቅ> በሚል ስም የሚጠራ 12 ተመራጭ መነኮሳት የሚሰየሙበት የመማክርት ጉባኤ አለ፡፡መራጮቹ የገዳሙ አባላት (መነኮሳት) ናቸው፡፡ተመራጮቹ አጠቃላዩን የገዳሙን ሕግ ከጸባቴው (አስተዳዳሪው) ጋር በመሆን ይደነግጋሉ፤ያጠፋውን ቀኖና ይሰጣሉ፤የአባላትን ቅሬታ ይፈታሉ፤ፀባቴውን ይቆጣጠራሉ፤በገዳሙ ወጣ ያለ ባሕርይ የሚያሳይ መነኮስ ካለ ጾምና ስግደት በመበየን በገዳሙ ማረሚያ ቤት እስከመላክ የሚያደርስ የውስጥ ሕግ ነበረ፡፡የገዳሙ አባል መነኮሳት በምርፋቅ አባላት ላይ ቅሬታ ካላቸው እንዲሁ ቅሬታቸውን አቅርበው ምርፋቁን አውርደው በሌላ ምርፋቅ ይተኩታል፡፡ይሕ ሥርዓት ትናንት ነበረ፤ዛሬም አለ፤ወደፊትም እስከ ምጽአተ-ክርስቶስ ይኖራል ብለን እናምናለን፤አምነን እንናገራለን!!
(2.3) ይሕን አሰራር እነ መኩሪያ ቡልቻ ከሚያወድሱት የአባ ሙዳ አሰራር ጋር እናነጻጽረው፡፡መኩሪያ ቡልቻ <<The Office of Aba Muuda was…open to the Oromo people as a whole and was visited by delegates from every ‘gosa’ and from different parts of Oromo-land, but non-Oromos were not allowed to participate in rituals>>ይላል(Being and Becoming Oromo:53)::በተጨማሪም አባ ሙዳ ወይም ቃሉ (መራሄ-ዋቄፈና) ለመሆን የሚቻለው በዘር ማለትም ከአባት ወደ ልጅ በሚተላለፍ የተወላጅነት ሰንሰለት ብቻ እና ሲመቱም እስከ እድሜ ልክ (እንደ የኢኦተቤክ የፕትርክና ቀኖና) መሆኑን ታቦር ዋሚን ጨምሮ ብዙ ጸሐፍተ-ኦሮሞ አረጋግጠዋል (ታቦር ዋሚ፡ገ.221)፡፡እንግዲህ እኩልተኛ ሥርዓት ማለት ሁሉም እንዳቅሙ እንዲወዳደር የውድድር እድል (equal opportunity) የሚከፍት ማለት ከሆነ እንደ ኦሪት ሌዋውያን ዘርና ብሔርን (ኦሮሞን ብቻ!) መሰረት አድርጎ የሃይማኖት መሪነትን የሚያወራርሰው ዋቄፈና እየተወደሰ በሌላ በኩል ላመነ፣ለተጠመቀና መንፈሳዊውን እውቀት ለጨበጠ ሁሉ እንኳንስ ብሔር ዜግነት ሳይመርጥ ለሰብዓዊ ፍጡር ሁሉ ክፍት ሆኖ የኖረው ቤተመቅደስ በpreservation [of] structural inequalities ሲከሰስ መስማት ግራ ያጋባል፡፡ብቻ ግን በዛሬው የUNDHR ዘመን ‹‹ዘእምነገደ-ይሑዳም ሆነ፤ዘእምነገ-ሙዳ ጊዜውን የዋጁ ሥርዓታት አይመስሉም›› ብለን እንለፍ!!

3-- ክስ-ሦስት፡- አለቃ ታዬ እና አቶ አጽሜ የኢኦተቤክ ደብተራዎች ናቸው!!

እነዚህን ሰዎች (አለቃ ታዬንና አቶ አጽሜን) መሐመድ ሀሰን፣አባስ ሐጂ፣መኩሪያ ቡልቻ፣ታቦር ዋሚ በስፋት ጠቅሰው ጽሑፋቸውን ሲመቻቸው ግብዐት አድርገውታል፡፡በጽሑፎቻቸው ‹‹የራሷ የኢኦተቤክ ጸሐፍት አለቃ ታዬና አቶ አጽሜ እንዲህ አሉ›› ለማለት ከሰዎቹ ስራ ሐሜት ሐሜቱን ነቃቅሰው እንደማጠናከሪያ ተጠቀመውበታል፡፡ሳይመቻቸው ቤተክርስቲያኗን ከነአለቃ ታዬ ጋር እየደረቡ ጭምር ጽሑፋቸውን በአያሌው አጣጥለውታል፡፡እሱ ችግር የለውም፡፡መብታቸው ነው፡፡ችግሩ ሰዎቹ የቤተክሕነት ወኪልና የኢኦተቤክ ደባትር እንደነበሩ ተደጋግሞ መጠቀሱ ነው--ያልሆኑትን!!እስኪ ባጭሩ ታሪካቸውን ከሃይማኖት አንጻር ብቻ በጨረፍታ እንይ…
(3.1) አቶ አጽመጊዮርጊስ (1825-1907 ዓ.ም) የሰሜን ሸዋ ተወላጅ (ዐማራ?) ናቸው፡፡ስለ ኦሮሞ በታሪክም በጸያፍም ሊታይ የሚችል ታሪክ ጽፈዋል፡፡እሱ የኔ ማጠንጠኛ አይደለም፡፡የኔ ማጠንጠኛ የእሳቸው ጽሑፍ የኢኦተቤክ አቋም ተደርጎ መወሰድ እንደሌለበት ማስረገጥ ነው፡፡ምክንያቱም እሳቸው የኦርቶዶክሳዊት ቤ/ክ አባል አልነበሩም፡፡እንዲያውም እድል ባገኙ ቁጥር ኦርቶዶክስን የሚያጥላሉና የካቶሊክ ሚሲዮናውያን በስፋት ሀገሪቱ ላይ አለመንሰራፋት የሚያንገበግባቸው፣የነአባ ማስያስ ሚኒልክን ካቶሊክ ማድረግ አለመቻል የሚቆጫቸው፣የሱስንዮስ ዘመን የሚናፍቃቸው ሰው የነበሩ ስለመሆናቸው አንዳንድ ቃላቶቻቸው ያሳብቃሉ፡፡ጭልጥ ያሉ ካቶሊክ ነበሩ፤ያውም የኢኦተቤክ እና የካሕናቷ ከሳሽ፡፡ማስረጃ እናምጣ፡፡ፕ/ር ታምራት አማኑኤል በጻፉት ‹‹ስለኢትዮጵያ ደራሲያን›› የተሰኘ ምጥን መጽሐፍ በገጽ-14 ይኸንኑ የአቶ አጽሜን ጸረ-ኦርቶዶክስ አቋም ሲገልጹ ‹‹በካቶሊክ ሃይማኖት ያዲሱ ትውልድ ዘመን ሰው ስለነበሩ ለሃይማኖታቸው የነበረባቸው ቅንኣት በኦርቶዶክሳውያን ወገን ላይ ምክንያት ባገኙ ቁጥር ከልክ ያለፈ የተግሳጽ ቃል አስጽፉዋቸዋል፡፡አንዳንድ ጊዜም ታሪኩ መንገድ ሳይሰጣቸው በኦርቶዶክሳውያን ላይ የኃይል ቃል ለመጻፍ ምክንያቱን በግድ ፈልገው ያመጡት ይመስላል›› በሚል አስፍረዋል፡፡አቶ አጽሜ ለኦሮሞ የተቆረቆሩ መስለው የሚሽኖችን አለመምጣት በቁጭት ያነሳሉ፡፡የጦሩን መሪ ንጉሥ ምኒልክ ትተው በዐማራነት የፈረጇቸውን የኢኦተቤክ ካሕናትን ክፉኛ ይወርፋሉ፡፡የእሳቸውን የአጻጻፍ መንፈስ፣የውስጣቸውን ካቶሊካዊ ቅናትና መነሳሻ (motive) ያላጤኑ እንደነመሐመድ ሐሰን አይነት ጸሐፍት የእሳቸውን የጥላቻ ቃል እንዳለ እየወሰዱ ያጮሁታል (JOS:vol-7:p119)፡፡እነመሐመድ እና ጓዶቻቸው የካቶሊኮችን፣የሙስሊሞችንና ፕሮቴስታንቶችን ጽሑፎች ብቻ እየጠቀሱ ኦርቶዶክሳውያን ዶክመንቶችንና አማንያኑን ሳያመሳክሩ ስለኢኦተቤክ መጻፍን እንደልማድ መያዛቸውን ገና ወደፊትም በዚህ አጭር የዳሰሳ ጽሑፍ እናገኘዋለን፡፡አሁን ወደሌላው የኢኦተቤክ ደብተራ ወደተባሉት ጸሐፊ እንለፍ--ወደ አለቃ ታዬ ገብረማርያም!
(3.2) አለቃ ታዬ በ1853 ዓ.ም በጌምድር (ጎንደር)ተወለዱ፡፡ከአድዋ ዘመቻ በፊት (በ1872 ዓ.ም አካባቢ) ወደ ሐማሴን (ኤርትራ) ምንኩሉ የተባለ የስዊድን ሚሲዮናውያን ማረፊያ ሄደው ፕሮቴስታንት ሆኑ፡፡እዚያ ሳሉ ከምዕራባዊው ትምህርት ይልቅ ወደ ምስራቁ አዘነበሉ፡፡የግእዝ መጻሕፍት መመርመር ጀመሩ፡፡ለዚሁ እንዲረዳቸው ወደ ጎንደር ተመልሰው በ1875 ዓ.ም ቅኔ-ቤት ገቡ፡፡በ1877 ዓ.ም ቅኔ ተቀኝተው (ቤት ሞልተው ነው የሚባለው በባሕሉ) ተመለሱ፡፡በምንኩሉ ሚሲዮን አስተማሪ ሆኑ (ደማቆቹ፡ገ.57-68)፡፡ጥሩ የንባብ ተሞክሮ በቤተ-ፕሮቴስታንት ስላዳበሩ በእነሱ እርዳታ በ1889 ዓ.ም የግእዝ ሰዋስው አሳተሙ፡፡በሚሲዮናውያኑ የተልእኮ-ድጋፍ (ስፖንሰርሺፕ) ጀርመንኛ እና ፈረንሳይኛ አጥንተው በጀርመን የግእዝ አስተማሪ እስከመሆን ደርሰዋል፡፡ከዚያ መልስ በጎንደር ያባታቸው (አቶ ገ/ማርያም) ርስት ተፈቅዶላቸው እስከ 1903 ዓ.ም ይኖሩ ነበር፡፡‹‹...ይሁን እንጂ በደብረ ታቦር ሳሉ ‹ጻድቃን አያማልዱም› በሚል ክርክር ከካሕናት ጋር ስለተጋጩ ብዙ ጭቅጭ አገኛቸው፡፡በመጨረሻም በዚሁ ክርክር ምክንያት ወደ አዲስአበባ ተላለፉና ከአቡነ ማቴዎስ [ግብጻዊው] ፊት ቀርበው ነገሩ ከታየ በኋላ ከኢኦተቤክ [በውግዘት] ተለይተው የሚሲዮን ማኅበር አባል ሆነው ተቀመጡ፡፡›› (መርስዔኀዘን ወልደቂርቆስ፡ገ.146)፡፡ከዚህ ጊዜ ጀምሮ አለቃ ታዬ ከኢኦተቤክ ተገልለው እስከ እለተ-ሞታቸው ነሐሴ 15 ቀን 1916 ዓ.ም በመንግሥት ሠራተኛነት ታሪክ ሲጽፉ የነበረ መሆኑ አይካድም፡፡ነገር ግን ምንም እንኳ ከ19 ዓመታቸው ጀምሮ በፕሮቴስታንት እምነት በድብቅ ገብተው የኖሩ ቢሆንም የኢኦተቤክ ልጅነታቸው የታሪክ መጽሐፉን ከመጻፋቸው ከ13 ዓመታት በፊት (በኅቡዕ ፕሮቴስታንት መሆናቸው ከታወቀ ከ31 ዓመታ በኋላ) በ1903 ዓ.ም በይፋ ተቋርጡዋል፡፡ይሄው የብላታ መርስዔኀዘን መጽሐፍ በገጽ-147 ኅዳግ እንደሚተርከው አለቃ ታዬ በተወለዱ በ63 ዓመታቸው (ፕሮቴስታንት በሆኑ በ44ኛው ዓመት) በሞት ሲለዩም በኢኦተቤክ ለመቀበር ተናዝዘው ስለነበር አስከሬናቸውን ለማሳረፍ የቅ/ሥላሴ ካቴድራል ካሕናት በንግሥት ዘውዲቱ ሳይቀር ቢለመኑ ‹‹ይሕ ጸረ-ማርያም በቤተክርስቲያናችን አይቀበርብንም›› ሲሉ ተቃውሞ በማንሳታቸው የአለቃ ታዬ አስከሬን ወደ ጉለሌ ተወስዶ በፕሮቴስታንት መካነ-መቃብር ተቀብሯል፡፡እንግዲህ የኢኦተቤክ በቁም አውግዛ የለየችው፣በሞቱም ‹ሃይማኖት የለያየንን መቃብር አንድ አያደርገንም› ብላ ባመነበት አዲስ እምነት ካረፉ አዳዲስ አማንያን ወገኖቹ መቃብር ጎን እንዲያርፍ የጥምቀት ልጅነቱን ገፍፋ ቅጽሯን የዘጋችበት እና አንድም ጽሑፉን ያልተቀበለችው ዐለቃ ታዬ ነው ‹‹የኢኦተቤክ ደብተራ›› እየተባለ በየቦታው ከላይ በጠቀስኳቸው የኦሮሞ ጸሐፍት ስሟ የሚብጠለጠለው፡፡በዚህ አያያዝ ዛሬ ከኦሮሞ ብሔርተኞች ጋር ጽንፍ ረግጠው የሚወራከቡት ፕ/ር መስፍን ወ/ማርያም እና ፕ/ር ጌታቸው ኃይሌም ወደፊት ‹‹የኢኦተቤክ ደባትር›› ላለመባለቸው ዋስትና የለም!!

4-- ክስ-አራት፡- ኦርቶዶክስ ኦሮሚፋን ትጸየፋለች!

እውቁ የኦሮሞ ታሪክ ጸሐፊ መሐመድ ሀሰን በJOS (Journal of Oromo Studies.volume-7) ገጽ 118 ላይ በወጣ ጽሑፉ ጆቴ የተባለ ደራሲ ጠቅሶ <<The Amhara clergy failed to capture the hearts and minds of the Oromo by their total failure to use the Oromo language for their missionary work.Infact upto 1993, the Oromo language was considered too profane to be used by the Church>> ይለናል፡፡ሸጋ፡፡በምስማማበት ተስማምቼ ልጀምር፡፡የኢኦተቤክ ኦሮሚፋን ለስብከተ-ወንጌል ድሮም ሆነ አሁን (አሁን ላይ እጅግ መሻሻል ቢኖርም) በቅጡ ተጠቅማበታለች ብዬ አልዋሽም፡፡ነገር ግን ይሕ የሆነው መሐመድ እና ጆቴ እንደሚሉት ለኦሮሚፋ በተለየ መልክ ጽዩፍ (too profane) ሆና ነው ብየ አላምንም፡፡ላስረዳ፡-
(4.1) ዐማርኛ ራሱ በሊቃውንቱ ለቅዱሳት መጻሕፍት ትርጉም አገልግሎት መስጠት የጀመረው በጎንደር ዘመነ-መንግሥት ወቅት ያውም ካቶሊካውያንና ፕሮቴስታንቶች የሰሜኑን ሕዝብ በአካባቢው ቋንቋው እያስተማሩ ምዕመኑን ማስኮብለላቸው ባሳደረው ጫና ነው፡፡ዐማርኛ በተደራጀ መልኩ ለመጻሕፍት ትርጓሜ የዋለበትን (የወቅቱ የትርጓሜ መንገድ በራሱ የግእዝ ተጽእኖ እጅግ ቢበረታበትም) ትክክለኛውን ጊዜ ስናስቀምጠው በአጼ አድያም ሰገድ ኢያሱ ዘመን (ከ1674-1694) ስለመሆኑ በሚሊኒየሙ የታተመው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ከልደተ ክርስቶስ እስከ ፳፻ (2000ዓ.ም) መጽሐፍ በገጽ 187 አብራርቶ ያቀርብልናል፡፡ዐማርኛ በሥርዓተ-ቅዳሴ መካከል ለመነገር የበቃው ደግሞ ከ1913 ዓ.ም ወዲህ አባ ኪዳነማርያም በተባሉ የዋድላ (ወሎ) መነኩሴ አማካይነት ስለመሆኑ መርስዔኀዘን በገጽ 143 ተርከውልናል፡፡
(4.2) ከትርጉም ጋር በተያያዘ ጥቂት ግነት ያለበት ቢመስልም ሐቁን ያላጣውና ተስፋዬ ቶሎሳ በተባሉ አጥኚ የአፋን ኦሮሞን ጽሑፋዊ የታሪክ ሂደት የሚዳስስ የጥናት ወረቀት ገጽ-77 የተጠቀሰው የጀምስ ብሩስ አስተያየት ይታይ፡፡ብሩስ <<...there is an old law in this country (Ethiopia), handed down by tradition only, that whoever should attempt to translate the holy scripture into Amharic, or any other language his throat should be cut....>> በማለት ልማዳዊ ሕጉ ከግእዝ ውጪ ባሉ ቋንቋዎች ሁሉ ዐማርኛን ጨምሮ ይሰራ እንደነበር ይተርካል፡፡ልማዳዊ ሕጉ በአብዛኛው የሰሜን ኢትዮጵያ ኦርቶዶክሳዊ አሁን ድረስ ሕያው ነው፡፡ጸሎትና ቅዳሴው ለግእዝ ያደላ ነው፡፡በትግራይ፣በጎጃም፣በጎንደር፣በወሎ እና በሸዋ ግእዝ ጠቅሶ የማይሰብክ ሰባኪ እንኳንስ በካሕናቱ በምዕመናኑም የሚሰጠው ክብር እምብዛም ነው፡፡ሕዝቡ ለግእዝ ያደላል፡፡እዚያ በአማርኛ/ትግርኛ ብቻ ብትንደቀደቅ ‹‹ስብከቱ ጥሩ ነበር፤ግና ‹ቦለቲካ› በዛው›› ይልሀል፡፡
(4.3) ተስፋዬ ቶሎሳ በጥናቱ የቀደሙ ነገሥታትን የኦሮሚፋ ቋንቋን ጨቋኝነት በስፋት ቢገልጽም እ.ኤ.አ በ1877 ዓ.ም አለቃ ዘነብ (እኒህ ሰው የአጼ ቴዎድሮስን ዜና-መዋዕል የጻፉ የሸዋ ተወላጅ ሲሆኑ የጉራጌ ሕዝብ ከምኒልክ ጋር በተዋጋ ጊዜ ተገድለዋል--አለቃ ዘነብ) ለአጼ ምኒልክ መጽሐፈ-ኢያሱን፣መጽሐፈ-መሳፍንትን፣መጽሐፈ-ሩትን እና መጽሐፈ-ሳሙኤልን ወደ ኦሮሚፋ ተርጉመውላቸው በአውሮፓ ሊያሳትሙ ሲሉ ለማሳተም ቃል የገባላቸው ሚሲዮናዊው Krapf ከዚህ ዓለም በሞት በመለየቱ ኅትመቱ እንዳልተከናወነ የፓንክረስትን የ1976 እትም መጽሐፍ ጠቅሶ አስቀምጦታል፡፡‹‹ደማቆቹ›› የተሰኘ በመፍቀርያነ-ፕሮቴስታንት ጸሐፍት የተዘጋጀ መጽሐፍም ስለ አናሲሞስ ነሲብ ሲተርክ ይህንኑ የአለቃ ዘነብን ውጥን አንስቶታል (ደማቆቹ፡ገ.29)፡፡አናሲሞስን ከአጼ ምኒልክ ያገናኙት አቡነ ማቴዎስ እንደሆኑ፣አናሲሞስም ለአጼ ምኒልክ የኦሮምኛውን መጽሐፍ ቅዱስ እንዳበረከተላቸው፣ንጉሡም አናሲሞስን አጃቢ ባልደረባ ሰጥተው ወደ ወለጋ እንደላኩት ይኸው መጽሐፍ (ደማቆቹ) ይገልጻል፡፡የኢኦተቤክ ያላትን አስተምህሮ ሳይቃረን እንዲያስተምር ጳጳሱ አቡነ ማቴዎስ (ግብጻዊ) ራሳቸው ለአናሲሞስ ነግረውት ነበር፡፡ጳጳሱ ለወለጋው የወቅቱ አስተዳዳሪ በጻፉት ደብዳቤም ይሕንኑ አሳውቀዋል፡፡እንጥቀሰው ‹‹...እጅግ ለተከበርከውና ለተወደድከው ደጃዝማች ገብረእግዚአብሔር እንዴት አለህ?እኔ የማርቆስ አምላክ ይመስገን ደህና ነኝ፡፡ይሕ ከወደብ (ኤርትራ) የመጣው ኦኔሲሞስ ወደ እኛ መጥቶ እንዲያስተምር ጠይቆናል፡፡ከቤተክርስቲያናችን ትምህርትና እምነት የተለየ ጕዳይ አስተምሮ እንደሆነ እንድናውቀው አድርግ፡፡ነገር ግን ከኛ ትምህርትና እምነት ያላፈነገጠ ትምህርት የሚሰጥ ከሆነ ይቀጥል፤ማንም አንዳች አይበለው›› (ደማቆቹ፡ገ.33)፡፡እርግጥ ነው በኋላ ዘመኑ አናሲሞስ ችግር አጋጥሞታል፡፡ነገር ግን ችግሩ የገጠመው ኦሮሚፋን ተጠቅሞ በመስበኩ ሳይሆን የተሰጠውን መመሪያ ጥሶ ከኢኦተቤክ ዶግማና ቀኖና የሚጋጭ ፕሮቴስታንታዊ ትምህርት በማስተማሩ ነው፡፡ ይሕ ደግሞ በእሱ ላይ ብቻ ሳይሆን ቀደም ሲል ፕሮቴስታንታዊ ትምህርት ባስተማሩት ጎንደሬው አለቃ ታዬ፣ካቶሊካዊ ትምህርት ባስተማሩት ጎጃሜው አባ ገብረሚካኤል (በአጼ ቴዎድሮስ ታስረው ሳለ ስላረፉ ቫቲካን እንደ ብፁዕ ሰማዕት ነው የምታያቸው)፣በልዩ ልዩ የጸጋ-ተዋሕዶ-ቅባት ክርክሮች ወቅት በዐማራና በትግራይ ሊቃውንትም ዘንድ የደረሰ ነው--መሳደዱ፡፡ስለሆነም ዛሬ ላይ ቆሜ አንድ ሰው በእምነቱ የተነሳ መሳደድ እንደሌለበት በሙሉ ልቤ ባምንም ገና ወለጋ ለምኒልክ ሳይገብር በአካባቢው በሰፈነው የባርነት ንግድ በ1854 ዓ.ም (ምኒልክ በዚህ ጊዜ በመቅደላ እስር ቤት የአጼ ቴዎድሮስ እስረኛ ነበሩ) ተሽጦ ኋላ በሚሲዮናውያን አርነት ከወጣ በኋላ ለኦሮሚፋ ቋንቋ ታላቅ ውለታን የሰራው አናሲሞስ የተሳደደው በኦሮሞነቱ እና በኦሮሚፋው ነው ብዬ አላምንም፡፡የወቅቱ የኢኦተቤክ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ማቴዎስ ቋንቋ ሳይለዩ አናሲሞስ ስለኦርቶደክስ እንዲሰብክ የበኩላቸውን ጥረዋል፡፡ስብከቱን ለፕሮቴስታንታዊ ተልእኮ ሲጠቀምበት ግን ወቅቱ በፈቀደው ሕግና ሥልጣን ስብከቱን ለማገድ ተንቀሳቅሰዋል፡፡ይህ እንቅስቃሴያቸው ከሃይማኖት ነጻነት ጋር እንጂ ከቋንቋ ነጻነት ጋር አይገናኝም ብዬ አምናለሁ፡፡ሌላ ዋቢ እንጥራ!
(4.4) ከሆሮ-ጉድሩ ተማርኮ ኋላ በምድረ-ጎጃም ታላቅ ካሕን፣ጸሐፊ እና የተመሰገነ ሠዐሊ የነበረው አለቃ ተክለኢየሱስ (ነገሮ) ዋቅጅራ በ1891 ዓ.ም በኦሮሞ-ቤት (ሆሮ-ጉድሩ) ስለተካሄው የጎጃሙ ንጉሥ ተክለሃይማኖት ጉዞ (ጦርነቱ በ1871 ዓ.ም ተጠናቋልና ይሄኛው ጉዞ ለጦርነት አይደለም፤ለቤ/ክ ግንባታ እንጂ) እንዲህ ይተርካል ‹‹...የዚህ ጊዜ ንጉሥ ተክለሃይማኖት...ኦሮሞ ቤት ዲለሎ ከሚባል ቦታ ሲደርስ ቤተክርስቲያን ሲሰራ ባጀ፡፡...ኦሮሞውን ሁሉ አሳምኖ ብዙ ታቦት ተከለ፡፡ተሠሪ ሠራበት፡፡...[በ1871 ዓ.ም ከሆሮ-ጉድሩ ማርኮ] ያሳደጋቸውን ኦሮሞዎች ሁሉ ከዘመድ እያስተዋወቀ ለነሻቃ ይርባ [ሂርጳ?]፣ለነሻቃ ጉደታ፣ለነበጅሮንድ ናደው ከየአባታቸው ርስት ጉልት አድርጎ ሰጥቶ ቤት አሠራቸው፡፡...ከዲለሎ ሲመለስ አለቃ ተክለኢየሱስን ጠርቶ ዘመዶችህ እነሻቃ ይርባ [ሻቃ ሂርጳ የንጉሥ ተክለሃይማኖት ሰይፍ ጃግሬ ነበር] አገራቸው ገብተው ከዘመድ ተገናኝተው ለጉልት ሲበቁ ምነው አብረኸኝ ሳትሄድ አለው፡፡...ከርሞ የቀዎ ጊዮርጊስ ጌታ አደርግሀለሁ፡፡...እዚያው [ሥዕል] እየሣልክ ታሳምንልኛለህ፡፡ነገርግን የኦሮምኛ ቋንቋ እንዳይጠፋህ ይኹን አለው፡፡›› (አለቃ ተክለኢየሱስ፡ገ.198)፡፡ይቺ የተክሌ ሐተታና ‹‹እዚያው [ሥዕል] እየሣልክ ታሳምንልኛለህ፤ነገር ግን የኦሮምኛ ቋንቋ እንዳይጠፋህ ይኹን አለው፡፡›› የምትለዋ የንጉሥ ተክለሃይማኖት አገላለጽ በወቅቱ ዛሬ እንደሚባለው በኢኦተቤክ አካባቢ ኦሮሚፋ ‹‹ጽዩፍ›› የሚባል ቋንቋ እንዳልነበረ ፍንጭ ትሰጠናለች፡፡የንጉሥ ተክለሃይማኖት ዐላማም ጎጃም ማርኮ ያቆያቸውን ኦሮሞዎች ተጠቅሞ ሆሮ-ጉድሩን እና አካባቢውን በኦሮሚፋ እያስሰበከ በኦርቶዶክሳዊነት አሳምኖ ለማጥመቅ መሆኑን ይጠቁመናል፡፡
(4.5) የኢኦተቤክ በሰሜን በኩል ባሉ ብሔረሰቦች ውስጥ ሴሜቲክ በሚባሉት ዐማራና ትግራውያን (ሐማሴኖችን ጨምሮ) ብቻ ሳይሆን ሰሜናዊ ኩሽቲክ በሚባሉት አገዎች ዘመናትን የቀደመ ተጽእኖ አላት፡፡‹‹ላል-ይበላ›› የሚለው ስም አገውኛ ስለመሆኑና አገዎች ቤተመንገሥቱን 300 ዓመታት ተቆጣጥረውት እንደነበር ተደጋግሞ ተነግሯል፡፡ወደ ደቡብ ስንሄድ የከፋን ሕዝቦች ታሪክ የጻፈው በቀለ ወ/ማሪያም አዴሎ እንደሚነግረን የኢኦተቤክ በአካባቢው ከ600 እስከ 700 ዓመታት የቆየና የተመዘገበ ታሪክ አላት፡፡ለአብነትም በቀለ ወ/ማሪያም በ1532 ዓ.ም የተተከለው ባሃ ጊዮርጊስን ይጠቅስልናል፡፡(በቀለ ወ/ማሪያም፡ገ.122 እና 123)፡፡በወላይታም የደብረ-መንክራት ተክለሃይማኖት ቤ/ክ እድሜ ከ800 መቶ ዓመታት በላይ ይቆጠራል፡፡በ14ኛው ክ/ዘ በምድረ-ጉራጌ እነ አቡነ ዜናማርቆስ ያቋቋሙት የምሑር-ኢየሱስ ገዳም ዛሬም ከነግርማው አለ፡፡በጋሞዎች ምድር ያለችው ብርብር ማርያም ከንጉሥ ገብረመስቀልና ከንጉሥ ዘርዓያዕቆብ ጋር የተገናኘ የሺህ ዓመት ታሪክ ትቆጥራለች፡፡በሸዋ የኦሮሞ ምድር ያሉት የወንጪ(አምቦ) ቂርቆስ፣የዝቋላ/ጩቃላ አቦ፣የዝዋይ/ባቱ ደሴት ገዳማት፣የደ/ሊባኖስና የዐዳዲ ማርያም ገዳማት፣...የሚቆጥሩት እድሜ በትንሹ ከ500 ዓመታት በላይ ነው፡፡ሃይማኖቱ ከ6 ሀገራት ጋር ዶግማ ቀኖና ስለሚጋራ ከነዚህ ሀገራት የመጡ ቅዱሳን በኃላፊነት ጭምር እየተቀመጡ እስከቅርብ ጊዜ አገልግለዋል፡፡የዐረብኛ፣የሱርስት፣የግሪክ እና የእብራይስጥ ቋንቋ ሳይቀር ሊቃውንቱ እያጠኑ ቅዱሳት መጻሕፍትን ተርጉመዋል፡፡ላመነና ለተጠመቀ ሁሉ መድረኩ ክፍት ነበር፡፡እነ መሐመድ ሐሰን ይሄን ሳያጣሩ፣ወይም እያወቁ ሳያካትቱና ጥቂት እንኳ ለሚዛናዊነት ሳይጨነቁ ‹‹The Amhara clergy›› እያሉ ሃይማኖቱን የአንድ ብሔር በማስመሰል መጻፋቸው እጅግ ቅር ያሰኛል፡፡ሃይማኖቱ ለዐማርኛ ቋንቋ የሚባለውን ያህል ታሪካዊ የሥነ-ጽሑፍ ቦታ እንዳልነበረው እስኪ ቀ.ኃ.ሥ ይንገሩን፡፡
(4.6) ቀ.ኃ.ሥ በ‹‹ሕይወቴና የኢትዮጵያ እርምጃ›› የመጀመሪያ ክፍል መጽሐፋቸው ገጽ 136 በዘመናቸው ዐማርኛ የነበረበትን ዝቅተኛ የቤ/ክ አገልግሎት ሲገልጹ ‹‹...ቅዳሴው ሕዝቡ ሁሉ በማያውቀው በግእዝ ቋንቋ ስለነበር ብዙዎች የዜማውን ድምጽ ከመስማት በቀር ምስጢሩን የሚያስረዳ ቃል ሳይሰሙ በየቤታቸው ይመለሱ ነበር፡፡...›› ካሉ በኋላ በእሳቸው ዘመን ስለነበረው ጅማሮ ሲገልጹ ‹‹...አሁን ግን ጸሎተ-ቅዳሴው በአማርኛ ቋንቋ እንዲተረጎምና እንዲታተም አድርገን በየቤተክርስቲያኑ ስለታደለ ሕዝቡ መላውን እንኳ ባይሆን ዋና ዋናውን ቃል በቋንቋ ሲነበብ መስማት ጀምሯል፡፡ወንጌልና የሐዋርያት መልእክትም በአማርኛ ቋንቋ እንዲነበብላቸው ተደረገ፡፡›› ይሉናል፡፡በነገራችን ላይ መጽሐፈ-ቅዳሴ ከግእዝ ወደ አማርኛ በነጠላው የተተረጎመውና የታተመው በ1918 ዓ.ም ነበር፡፡ተርጓሚው መርስዔኀዘን ወልደቂርቆስ ነበሩ፡፡አማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ በነጠላ ትርጓሜ በ1832 ዓ.ም አባ አብርሃም (አባ ሮሜ) የታተመ ቢሆንም የተሟላና ሊቃውንተ-ቤተክርስቲያን የተሳተፉበት አማርኛ መጽሐፍቅዱስ የታተመው ግን በቅርቡ በ1953 ዓ.ም ነበር፡፡በዚህ ወቅት (ኧረ ቀደም ብሎ ነው!) መጽሐፍ ቅዱስን አናሲሞስ ነሲብ ወደ አፋን ኦሮሞ፤አለቃ ተወልደመድኅን ገብሩ ወደ ትግርኛ ተርጉመውት ነበር (የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ-ቃላት፡ገ.95)፡፡ድጋሚ ላስታውስ!የኢኦተቤክ በቀደመው ዘመን በስብከተ-ወንጌል ረገድ በየብሔረሰቡ ቋንቋ የመስበክ ብቃት ነበራት እያልኩ አይደለም፡፡አቋሜ የኢኦተቤክ የቋንቋ አጠቃቀም ውስንነት ልክ እስልምና ለዐረብኛ፤ካቶሊክ ለላቲን ቋንቋዎች እንደሚሳሱት (ኦሪጅናል ድርሰቶችና ዜማዎች በቋንቋዎቹ ስለተቀናበሩ) እሷም ለግእዝ ስሱ በመሆን እንጂ ኦሮሚፋን በተለየ ዐይን በማየት አይደለም የሚል ነው፡፡
(4.7) ይሕ በግእዝ ብቻ የመገልገል የኢኦተቤክ ልማድ መንበረ-መንግሥቱ በአክሱማውያን (ትግራውያን)፣በዛጉዌዎች (አገዎች) እጅ እና በየጁ ኦሮሞ ወረሴህ/ወራ-ሼክ እጅ በነበረበት ጊዜ (ለምሳሌ፡- ከየጁ ኦሮሞ የሚወለዱት ታላቁ ራስ ዓሊ ደብዳቤ ሲጽፉ ‹‹ጦማር ዘእምኀበ-ርእሰ-መኳንንት ዓሊ›› በማለት በግእዝ ነው አርእስታቸውን የሚጀምሩት)፤ኋላም ዙፋኑ በአጼ ዮሐንስ ተመልሶ ወደ ትግራይ ባመራበት ዘመን በኢኦተቤክ የግእዝ የበላይነት የጸና ነበር፡፡
(4.8) የቀደመው የግራኝና ደርቡሽ ሰቆቃ (አጼ ዮሐንስ በመተማ ተሰውተው ደርቡሽ ጎንደርን በወረራ ሲያጠፋ በሃይማኖቱ እውቀት ጫፍ የደረሱ ከ20 በላይ መምሕራንን አርዶ ነበርና) በወቅቱ ሀንጎቨሩ እንዳለ ሆኖ በተለይ ደግሞ የአጼ ሱስንዮስ ዘመን ካቶሊካዊ ፍልስፍና ኋላ ፊቱን ቀይሮ ጸጋ/ሦስት ልደት/-ቅብዐት-ተዋሕዶ/ካራ/ የሚል የውስጥ ክፍፍል በመፍጠር ሃይማኖቱ በውሳጣዊ ሽኩቻ ከመዳከሙም በላይ ከሊቃውንት ማዕከላቱ ትግራይ-ጎንደር-ጎጃም-ወሎ-ሸዋ ወጥቶ ወደሌሎች ብሔረሰቦች በስፋት በስብከተ-ወንጌል እንዳይደርስ ይሄው ሽኩቻ እስከ ዘመነ-መሳፍንት ፍጻሜ ዘልቆ ጎታች የነበረ መሆኑን ማስተዋል አይከፋም፡፡ እንጂ የኦሮሚፋ ስብከት ያልተስፋፋው መሐመድ ሐሰን እና ኦቦ ጆቴ እንደሚሉት ለኦሮሚፋ too profane በመሆን አይመስልም፡፡ጥያቄ ላንሳ፡፡ዶክቶር መሐመድ ወደ ኢኦተቤክ ከማለፉ በፊት እስልምና ለቁቤ እና አፋን ኦሮሞ ያበረከተውን ጸጋ ሊተነትንልን ይችል ይሆን?የአፋን ኦሮሞ ቁራን ነበረ?ቁራን በኦሮሚፋ ይቀራ ነበር?አዛንስ?ለንጽጽር እንዲመች ጥያቄዎቹ ቢብራሩ ሸጋ ነው!ስላደገበት እስልምና-እና-ኦሮሞነት ተዛምዶ ለመተንተን የተሻለ ግንዛቤ አለው ብዬ ነው!የእሱ የተጸውኦ(መጠሪያ) ስም ‹‹መሐመድ ሐሰን›› በኦሮሚፋ አይደል!!ይተርጉምልና!!
(4.9) እግረ-መንገድ እስኪ ከ100 ዓመት በፊት በኦሮሚፋ እና በዐማርኛ ቅልቅል (ፍርንዱስ) ሆኖ የግጥም ምጣኔው ‹ሥላሴ› የምንለው ከ3ኛው መስመር ጀምሮ ቤት እየመታ የሚሄድ ባለ 8 መስመርና ባለ 6 ቤት ቅኔ እንስማ፡፡የቅኔው ባለቤት አለቃ ዘወልዴ ይባላሉ፡፡ምናልባት በፕ/ር ታምራት ‹‹ፊተኛይቱና ኃለኛይቱ ኢትዮጵያ›› የሚል መጽሐፍ በተለየ አጻጻፍ ጽፈዋል የሚባሉትና መጽሐፋቸውን ያላገኘንላቸው ዘወልዴ ይሁኑ አይሁኑ አላወቅኩም፡፡ቅኔው የተደረገው በምኒልክ ጊዜ የነበረውን አስተዳደር በመተቸት ነው፡፡የተወሰደው በ1980 ዓ.ም በደርግ ጊዜ በአ/አ/ዩ አማካይነት ከታተመው ‹የግእዝ ቅኔያት የስነ-ጥበብ ቅርስ ክፍል-2› ከተሰኘ መጽሐፍ ገጽ-389 ነው፡፡የሊቁ ቅኔ እንዲህ ይነበባል..
አርካ-ኬቲ፡ሁንዱማ-ጨብሴ፤
ሌንጫ-ጎፍታኮ፡ኢጆሌ-ሌንጫ፤
አሁንም-የእውነት፡ግሩም፡አንበሳ፡የአንበሳ-ኮርማ፡የቢያ፣
በክንድህ-ሰበርኸው፡የሁሉን፡ሶማያ፣
ዱጉማ፡ጎፍታኮ፡ዱጉማ፡አሲ-መና-ኬቲ ገበያ፣
ሀሬ-ጉደቴ፡ፈርዳን-ፉለያ፣
ማሎ፡ማሎ፡ጎፍታ-ኪያ፣
መና-ፈርዳ፡ፉደቴ፡አህያ፡፡
ትርጉም፡- ‹‹አንበሳ የአንበሳ ልጅ፤ጌታየ ክንድህ ሁሉን ሰበረች፤አሁንም የእውነት አስፈሪ አንበሳ የአገር አንበሳ ኮርማ (አንተ)፤የሁሉን በትር በክንድህ ሰበርኸው፤እውነት ጌታዬ ከዚህ ገበያ ቤትህ እንደ አይጠ መጎጥ ፈረሶች ሲርቁ አህያ ከፍ ከፍ ተደረገች፤ምነው ምነው የእኔ ጌታ የፈረስን ቤት አህያ ወሰደች›› የሚል ነው፡፡
ምስጢሩ፡- ባለቅኔው የምኒልክን በባላባቶች ላይ የተገኘ አሸናፊነት አወድሰው ነገር ግን ‹‹በባህሉ ፈረስ እያለ አህያ ቀሚስ እንደማትለብስ እየታወቀ እስዎ ታላላቆችንና ምሁራኑን ትተው ለታናናሾች እና ላልተማሩት ቦታ (ስልጣን) እየሰጡ ነው›› በማለት የምኒልክን አስተዳደር በኦሮሚፋ የሚተች ነው፡፡በውዳሴ ጀምሮ በትችት መቋጨት ከቅኔ ባሕሪያት አንዱ ነዋ!

ይቀጥላል///////