Wednesday, July 22, 2015

" እርስ በርስዋ የምትለያይ መንግሥት ሁላ ትጠፋለች"

ፕሮቴስታንት፣ ካቶሊክ፣ ኦርቶዶክስ ብንባልም የእምነታችን ጀማሪና ፈፃሚ ግን ያው አንዱ ክርስቶስ ነው። በዚህ ዘመን ይቅርና በሐዋሪያት ዘመን እንኳ ክርስቲያኖች እርስ በእርስ በመከፋፈልና በመገፋፋት ያስቸግሩ ነበር። ጴጥሮስ (ኬፋ) ያስተማራቸው፣ ጳውሎስ ያስተማራቸው እንዲሁም ሌሎች ያስተማሩዋቸው ክርስቲያኖች ለየብቻቸው መደራጀታቸውና መራራቃቸው ሐዋሪያው ጳውሎስን አስመርሮት እንዲህ ብሎ ፅፎላቸው ነበር፦ 1ኛ ቆሮንቶስ 1፥ 10 "ነገር ግን፥ ወንድሞች ሆይ፥ ሁላችሁ አንድ ንግግር እንድትናገሩ በአንድ ልብና በአንድ አሳብም የተባበራችሁ እንድትሆኑ እንጂ መለያየት በመካከላችሁ እንዳይሆን በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም እለምናችኋለሁ። ወንድሞቼ ሆይ፥ በመካከላችሁ ክርክር እንዳለ ስለ እናንተ የቀሎዔ ቤተ ሰዎች አስታውቀውኛልና። ይህንም እላለሁ። እያንዳንዳችሁ። እኔ የጳውሎስ ነኝ፥ እኔስ የአጵሎስ ነኝ፥ እኔ ግን የኬፋ ነኝ፥ እኔስ የክርስቶስ ነኝ ትላላችሁ። ክርስቶስ ተከፍሎአልን? ጳውሎስስ ስለ እናንተ ተሰቀለን? ወይስ በጳውሎስ ስም ተጠመቃችሁን?"

በእኛ ዘመንም ቢሆን ክርስቶስ አልተከፈለም። በመካከላችንም ወይ በፕሮቴስታንት ወይ በኦርቶዶክስ ወይ በካቶሊክ ስም የተጠመቀ የለም። የተሰቀለውም አንድ ሲሆን፣ በታዘዝነው መሰረት በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ሁላችን ተጠምቀናል። ክርስትና አንድ ሲሆን አብያተክርስቲያናት ግን እንዳመለካከታችን መጠን ብዙ ናቸው። ልዩነት ችግር የሚሆነው እኛ ስናደርገው ነው፣ ካወቅንበት ግን ዉበት ነው።

============================
አለም ላይ እንዳለው ብዛት እና ተፅዕኖ የመፍጠር አቅም የትና የት መድረስ ይችል የነበረው የተከበረው ሐይማኖታችን፣ በኋላቀር አስተሳሰባችንና እኔ ብቻ ልደመጥ ባይነታችን እርስ በእርሱ ተጠላልፎ ወደ ፊት ዳዴ እንኳን ማለት ተስኖታል። ለዚህ ሁሉ ተጠያቂ እኛው ነን። ጥፋታችንን ሳንቀበል መፍትሄ ማምጣት አይቻልም። ወላጆች እንደሌላቸው ልጆች በየቦታው ተበታትነናል። ለአንድ ዓላማ ልንቆምለት የምንችለው ትልቅ ሐይማኖት እና እውነት ይዘን፣ ነገር ግን እንደ ህፃናት በተገኘችው ጥቃቅን ቀዳዳ ሁሉ መበጣበጥ በጣም አሳዛኝ ነገር ነው። ተልኮአችንን ረስተነዋል። ውጪ ያሉትን ለክርስትና መማረክ ሲገባን የራሳችንን ወንድም በመታገል ጉልበታችንን እዛው ቤት ውስጥ እያፈሰስነው ነው። የራሳችንን ቤት እኛው እያፈረስነው ነው። ወደ ፍቅር እንመለስ!!

==========================
ማቴዎስ 12፥ 25 " እርስ በርስዋ የምትለያይ መንግሥት ሁላ ትጠፋለች፥ እርስ በርሱ የሚለያይ ከተማም ሁሉ ወይም ቤት አይቆምም።"

===========================
መዝሙረ ዳዊት 133 ፥ 1 "ወንድሞች በኅብረት ቢቀመጡ፥ እነሆ፥ መልካም ነው፥ እነሆም፥ ያማረ ነው።"

===========================
ዮሐንስ 17፥ 20-23 "ሁሉም አንድ ይሆኑ ዘንድ፥ ከቃላቸው የተነሣ በእኔ ስለሚያምኑ ደግሞ እንጂ ስለ እነዚህ ብቻ አልለምንም፤ አንተ እንደ ላክኸኝ ዓለም ያምን ዘንድ፥ አንተ፥ አባት ሆይ፥ በእኔ እንዳለህ እኔም በአንተ፥ እነርሱ ደግሞ በእኛ አንድ ይሆኑ ዘንድ እለምናለሁ። እኛም አንድ እንደ ሆንን አንድ ይሆኑ ዘንድ፤ እኔም በእነርሱ አንተም በእኔ ስትሆን፥ በአንድ ፍጹማን እንዲሆኑ፥ የሰጠኸኝን ክብር እኔ ሰጥቻቸዋለሁ፤ እንዲሁም ዓለም አንተ እንደ ላክኸኝ በወደድኸኝም መጠን እነርሱን እንደ ወደድሃቸው ያውቃል።"

===========================
ስለ ክርስቲያኖች አንድነት ብዙ የተባለ ቢኖርም ለዛሬ እነዚህን አይተናል። ስህተትን ማረም ከሁሉም ይጠበቃል። በየአብያተክርስቲያናቱ ያሉ መሪዎችም ራሳቸውን መፈተሽ እና ከሚከፋፍል እና ከጥላቻ የራቀ ትምህርት ማስተማር ይኖርባቸዋል። እንዲያ ካልሆነ ግን እግዚአብሔርን ማገልገልም ሆነ መከተል ከንቱ ነው። የፍቅርና የአንድነት አምላክ እንጂ የጥላቻ እና የመከፋፈል አይደለምና። ወንድሙን ጠልቶ እግዚአብሔርን እወዳለሁ የሚል እራሱን ያታልላል።

እያልኩ ያለሁት ያሉንን አብያተክርስቲያናት አፍርሰን አንድ ቤተክርስቲያን እናቋቁም ሳይሆን፣ በያለንበት ህብረት ማድረግ ይቻላል። ከልዩነቶቻችን በላይ አንድነታችንን እናጉላው የሚል ነው።

እንግዲህ በመካከላችን ያለውን አላስፈላጊ ርቀት እናጥብብ፣ ህብረት እናድርግ፣ እንፈላለግ፣ ይቅር እንባባል። አንድነት ውስጥ ያሉ የአመለካከት ልዩነቶች ውበት ናቸው እንጂ በራሳቸው ችግር አይደሉም። መንገዳችንንም እናስተካክል፣ እግዚአብሔርንም በአንድነት እንፈልግ።

===========================
መጽሐፈ ዜና መዋዕል ካልዕ 7፥ 14 "በስሜ የተጠሩት ሕዝቤ ሰውነታቸውን አዋርደው ቢጸልዩ፥ ፊቴንም ቢፈልጉ፥ ከክፉ መንገዳቸውም ቢመለሱ፥ በሰማይ ሆኜ እሰማለሁ፥ ኃጢአታቸውንም ይቅር እላለሁ፥ ምድራቸውንም እፈውሳለሁ።"
===========================

በዚህ መልእክት የምትስማሙ መልእክቱን ለሌሎች ወንድሞችና እህቶች ሃሳቡን ለሌሎች አካፍሉ። እንዲህ ባለው ሀሳብ ደስተኛ የማይሆኑ አንዳንድ ግለሰቦች በየአብያተክርስቲያናቱ ቢኖሩ ለጊዜው ነው ተዋቸው፣ እግዚአብሔርን በሚገባ እስኪያውቁት ነው።


Lewi Ephrem's

Thursday, July 9, 2015

የኦሮሞ ኢስላሚስቶች ለአረፋ በዓል ሄደው በሳዑዲ ያደረጉትን ይመልከቱ!

  
    በኦሮሚያ ክልል የተነሱ የአብዱል ወሀብ ጥራዝ ነጠቅ  ተከታይ ወሀቢስቶች በጅማ፤ በኢሉባቦር፤ በአርሲና በባሌ የተለያዩ ቦታዎች በኦፊሴል የተነገረና ያልተነገረ የሽብር እንቅስቃሴ ሲያደርጉ ቆይተዋል። በአማራ ክልል ደግሞ የወሎ አክራሪ ወሀቢስቶች ቤተ ክርስቲያን ከማቃጠል አንስቶ ሰው እስከመግደል መድረሳቸውን በማስረጃ የተረጋገጠ እውነት ነው። በስልጤና ወራቤ የከተሙ አሸባሪ ፋናቲኮች ተመሳሳይ ድርጊት ላይ ተሰማርተው መገኘታቸውም ፀሐይ የሞቀው፤ ሀገር ያወቀው ጉዳይ ነው። እነዚህ ሱሪያቸውን የሚያሳጥሩ፤ ካልሲያቸውን የሚያሳዩ፤ የአፍንጫቸውን ስር ጸጉር ሙልጭ አድርገው በመላጨት ጢማቸውን የሚያሳድጉ፤ ግንባራቸው ላይ የተነቀሱ እስኪመስል ድረስ ከመሬት ሲጋጩ የጠቆረ ሰውነት ከማንነት ጋር የተሸከሙ አክራሪዎች የሌላውን መብት እስካልነኩ ድረስ ተቃውሞ የማይቀርብበት ቢሆንም የድርጊታቸው ዋነኛ ምስክር ግን ለማሸበር ልዩ ምልክታቸው ሆኖ መገኘቱ ነው። ወሀቢስቶች ከሱኒና ከሱና ውጪ ያለው ሁሉ ካፊርና ከሀዲ ነው።          ለዚህም ዓላማ ግብ መንታት መታገል፤ መዋጋትና መግደል ብሎም መሞት ጂሀድ ነው። በዚህ ዓላማ ላይ መሞት በጀና/ ገነት/ ልዩ ዓለም የሚያስገኝ ሲሆን 72 ደናግላን ሴቶች ድንግላቸውን በጂሀድ ለሞተው አሸባሪ ለማስረከብ በጥቋቁር ቀሚስ ተሸፋፍነው እንደሚጠብቋቸው ያምናሉ።
ከዚህ በታች የሚታየው ቪዲዮ በሳዑዲ የአረፋ በዓል ለማክበር የሄዱ አክራሪዎች የወቅቱ የኢትዮጵያ ባንዲራ የሆነውን ዓርማ ከተሰቀለበት አውርደው የኦነግን ባንዲራ ሲሰቅሉ ያሳያል። «ሱባንአላህ» የሚለው የኦሮሞ ኢስላሚስት አክራሪ የአማራ ባንዲራ ወርዶ የኦሮሞ መንግሥት በቅርቡ በኦሮሚያ ይቋቋማል ይላል። በዚህ ዓይነት ኦነግ አሸባሪ አይደለምን?
እንግዲህ እነዚህ የመሳሰሉ አሸባሪዎች ናቸው፤ ኢትዮጵያ ተመልሰው ሕዝብን ከሕዝብ፤ ሃይማኖትን ከሃይማኖት ሲያጋጩ የሚስተዋለው።
ደግመን ደጋግመን የምንለው እውነታ ቢኖር ኢትዮጵያ ውስጥ ምቹ ሁኔታ ጠፍቶ እንጂ ለቁጥር የሚያታክቱ አሸባሪዎች አሉ። «አስቀድሞ ነበር፤ መጥኖ መደቆስ፤
አሁን ምን ያደርጋል፤ድስት ጥዶ ማልቀስ»
እንዳይሆን ሰላምን፤ ፍቅርን፤አንድነት፤ ኅብረትንና በጋራ አብሮ መኖርን በሚፈልጉ የእስልምና እምነት ተከታዮች በኩል አካባቢንና ውስጥን የማጥራት ሥራ ከታችኛው እርከን አንስቶ እንዲደረግ ከዚህ በፊት ስንለው እንደቆየነው ሁሉ አሁንም ደግመን ለማስታወስ እንወዳለን።


Tuesday, June 30, 2015

ክርስትናን አጋድመው ያረዱት..."


(ያሬድ ሹመቴ)

ከዚህ በታች የማስነብባችሁን ጽሁፍ ከዚህ ቀደም በጨርቆስ ተገኝቼ የሰማውትን በዚሁ መገናኛ መድረካችን ላይ አስነብቤያችሁ ነበር።
ከሰሞኑን በአሜሪካን ሀገር በግብረ ሰዶም ተግባር ላይ እጅግ አስነዋሪ የጋብቻ ህግ መጽደቁን ተከትሎ ልንነጋገርበትና መንፈሳዊ ምግብ እንሰንቅበት ዘንድ የመጋቢ ሀዲስ እሸቱን ስብከት ከመድረኩ የሰማውትን ለንባብ እንዲመች አድርጌ በማቀናበር በድጋሚ እነሆ ብያለው።
"ሰው ብቻ አትሁኑ" መ.ሀ.እሽቱ
"...ሰው ብቻ ማለት ምንድን ማለት ነው? ብዬ ሳስብ፤ የሚበላ፣ የሚጠጣ፣ በሚለብሰው ልብስ፣ በሚነዳው መኪና የኑሮን ስኬት የሚለካ ማለት ነው። እስከ ሞት የሚኖር ማለት ነው፦ እንደ እንስሳ።
"...ታላቁ ሊቅ ዮሀንስ አፈወርቅ እንዲህ ይላል 'ሰው እግዚአብሄር ሲለየው' ይላል። ሰው እግዚአብሄ ሲለየው፤ ጠባዩ እንደ አራዊት፤ አመጋገቡ እንደ እንስሳ፣ ሆኖ መልኩ ብቻ የእግዚአብሄር ሆኖ ይቀራል። በጣም ቀለል ባለ አገላለጽ ሲም ካርዱ የወጣ ሞባይል ማለት ነው። ጥሪ የማይቀበል። ለጉትቻ ማንጠልጠያ ብቻ የተሰራም ጆሮ አለ።"
"...እኔ በዕውነቱ ከተማው ፈርሶ እየተሰራ ነው እየተባለ አይናማዎቹ ሲያወሩም ሲያስወሩም እሰማለው። ፈርሶ መሰራት ያለበት የሰዉ አስተሳሰብ ነው።... የሰዉ አስተሳሰብ ፈርሶ ካልተሰራ፤ የተሰራ ከተማ ይፈርሳል። ጃፓንና ቻይና ሀገራቸውን ያለሙት መጀመሪያ አስተሳሰባቸውን አልምተው ነው። አስተሳሰቡ ያልለማ ህዝብ የለማውን ያወድማል።"
"...ምንድነው አሁን ያሳየሁዋቹ? (ትንሽ ጣታቸውን አውጥተው ወደላይ እያሳዮ) ይህች ጣት ብትታምም ሀኪም ቤት ብቻዋን ነው የምትሄው?... የማይመለከታቸው እነ ጉበት፣ እናፍንጫ፣ እነ እግር፣ አብረው ነው የሚሄዱት።"
"...ከረባት የሚታሰረው የት ላይ ነው?... አንገት ላይ የታሰረ ከረባት አካሄድን ይቀይራል። አሁን እግር ምን አገባው እውነት ለመናገር? (ከፍተኛ ሳቅ) ውድ መነጽር አይናቸው ላይ ያደረጉ ሰዋች አካሄዳቸውን ሁሉ ነው የሚቀየረው። አይን መነጽር ያደረገው መላ የሰውነት አካላትን ተክቶ ነው። ለዚህ ነው ታላቁ ሊቅ ዮሀንስ አፈወርቅ "እኛ የሰውነት ክፍሎች ነን ክርስቶስ ግን ራስ ነው" ያለው። ሰው እጁ ተቆርጦ ይኖራል፤ አይኑ ጠፍቶ ትኖራል። እራሱ ተቆርጦ ግን አይኖርም። እራስ ክርስቶስ ነው። እኛ ብንሞት (የሰማይ ህይወት) ይቀጥላል። የክርስትናው እራስ ክርስቶስ ስለሆነ።"
"ቤታችሁ ገብታችሁ እንድታጤኑት ነው። እነዛ... (ምንትስ) የምንላቸው ክርስቲያኖችን አርደዋል... ምዕራባውያኑ ደግሞ ክርስትናን እራሱን አርደውታል።....ወንድ ለወንድ፣ ሴት ለሴት፣ በቤተክርስቲያናቸው እያጋቡ፤ ክርስትናን አጋድመው ያረዱ ምዕራባውያን ናቸው። (ይህን ሁሉ ያመጣውም) የምዕራባውያን ልክ ያጣ ነጻነትና ገደብ ያለፈ ዝርክርክነት ነው።"
"እንደምታዩት እኔ አይነ ስውር ነኝ። ቀላል አይደለም.... እንክዋን ዘውትር ዓይን አጥቶ አንድ ቀን መብራት ሲሄድ ስንት እንደምታማሩ ታውቅታላችሁ። አንድ ቀን ግን አልቅሼ አላውቅም። ከሞት ወዲያ መብራት አለ። ከመቃብር በላይ መብራት አለ። ... ወደ መቃብር ሲወርድ ማንም ዓይነ ስውር ነው። ማንም አይኑ እያየ የተቀበረ የለም። ተስፋችን ግን ምንድን ነው? ከሞት ወዲያ ህይወት አለ። ከሞት ወዲያ ብርሀን አለ።"
"...አንድ አንድ ጊዜ እመኛለሁ። እማይረባ እማይረባ ነገር ስናይ (ዓይናችንን) የሚያጠፋ ቆጣሪ ቢኖር... መልካም ነገር እስክናይ ድረስ ለጊዜው የሚያጠፋ ቆጣሪ ቢኖር።
"አሁን እንደው ጆሮ በካርድ የሚሰራ ቢሆን ሀሜት እንሰማ ነበር?(ከፍተኛ ሳቅ)... የምንፈልገውን (ብቻ) አውርተን ስዊች ኦፍ እናደርገው ነበር። ስንት ዞማ ጸጉር ይዞ አስተሳሰቡ የከረደደ አለ።
"ጀርመን ሀገር ሄጄ ሲነግሩኝ፤ ባለ አምስት ኮከብ የውሻ ሆቴል አለ ተባለ። እኛ ሀገር አምስት ኮከብ ሆቴል ገብተው የበሉ ትንሽ ዝና (ሀብት) እና ትንሽ ስልጣን ያላቸው ናቸው። ማን ይገባል ከነሱ ውጪ። ግን ሰዋች ነን። የጀርመን ውሻ ዛሬም ውሻ ነው ለዘላለምም ውሻ ነው። እኛ ግን ሰው ነን።
እንደ ሰው አስቡ (ምዕመናን) በማርያም።"
" እስኪ እንደው ትዳራችሁን ገምግሙት ደስተኛ ናችሁ? እንደሰው እየኖራችሁ ነው? ሚስቶቻችሁን ታከብራላችሁ? ፖለቲከኞቹ የኪነጥበብ ሰዎቹ (እዚህ) አላቹ ሲባል ሰምቻለሁ። ቆም ብላችሁ ልታስቡ ይገባል።"
" እኛም የሀይማኖት ሰዎች ሰበክን ሰበክን፤ ስብከቱ የህዝቡን አመለካከት መቀየር ትቶ የኛን ኑሮ ቀየረ።(ከፍተኛ ሳቅ)... የሰበክነው ክርስቶስ ሳይታወቅ እኛ እንታወቃለን። ማስታወቂያ ሰርተው ዝነኛ የሆኑ ሰዎች አሉ። ምርቱ ተሽጠ? ወይስ አልተሸጠም?" (ከፍተኛ ሳቅ)
" ተርቦ ያበላን፣ በክራይ ቤት እየኖረ እኛን በቪላ ቤት ያኖረን፣ እሱ በግሩ እየሄደ ለኛ መኪና የገዛልንን፤ ዝነኛ ያደረገንን ህዝብ እኛ አመለካከቱን ልንቀይረው ይገባል። አለባበስን መቀየር ቀላል ነው አስተሳሰብን መቀየር ግን ዋጋ ያጠይቃል።"
"የግሪክ ፈላስፎች እነ ሶቅራጥስ የህዝቡን አመለካከር ለመቀየር ደከሙ። ዛሬ በኢኮኖሚ ውድቀት የምትንገላታ ግሪክ ናት፦ የነ ሶቅራጥስ ሀገር። 'ሀገር ሲያረጅ ጃርት ያፈራል' ይባላል። እኛ እንክዋን ይክበር ይመስገን ኢትዮጵያውያን ነን።"
"አሁንም ደግሜ እናገራለው። ይሄን ችግር ያደረሱብን ኢትዮጵያውያን አይደሉም። (እዚህ ያሉት) ጎረቤቶቻችንን እነ መሀመድ እነ ከድጃ... ስጋዎቻችን፣ ደሞቻችን፣ አካሎቻችን ናቸው።"
"ልብ ካለ ሊቢያ ሄዶ እናዛን መፋለም ነው። '... ቢያሸንፈው ወደ ሚስቱ ሮጠ' ይባላል። አንድ አንድ አባ ወራ አለ ቡና ቤት ሄዶ ከዚያ መልስ ቅዳ (ሂሳብ በኔ ነው) ይላል። (ሚስቱ) የወር ወጪ ስትጠይቀው፤ ጥጦ እንደተነጠቀ ህጻን የሚያለቅስ።"
"...ወቀሳ አበዛሁ?(የተሰበሰበው ህዝብ ከሳቅ ጋር አላበዙም አለ) ማርያምን?... ኮሶ የሚጠጣው ስለሚጣፍጥ አይደለም ስለሚያሽር(ስለሚያድን) ነው። ለመጣፈጥማ ስኩዋር ይሻል ነበር ግን ወስፋት ነው ትርፉ።" (ሳቅ)
"...የንጉሰ ነገስቱ የክርስቶስ አልጋ ወራሾች ነን... የደስታችሁ ልኬት የደስታችሁ ሚዛን ምግብና መጠጥ አይሁን፤ መኪናና ቤት ዝናንም አታርጉ። እኛ መለኪያችን ጽድቅ ነው። መከኪያችን መንግስተ ሰማያት ነው። ያ የምንገባበት ቤት ደግም የተዋበ፣ የደመቀ፣ መብራት ውሀ የማይሄድበት፤ 24 ሰኣት ክርስቶስ የሚያበራበት፤ 24 ሰኣት የህይወት ውሀ የሚጠጣበት፤ ሀብታም፤ ደሀ፣ተራሰው የማይባልበት፣ እገሌ ግባ እገሌ ውጣ የማይባልበት ቦታ ነው። ደህና እደሩ"
መጋቤ አዲስ እሸቱን ቃለ ህይወት ያሰማልን...
አሜን!

Sunday, June 28, 2015

" ጥበበኞች ነን ሲሉ ደንቆሮ ሆኑ፥" (ሮሜ 1:22)

my finger to you? (blogger)


                                ፍቅር ፍቅር ነው” ኦባማ

" እንዲሁም ወንዶች ደግሞ ለባሕርያቸው የሚገባውን ሴቶችን መገናኘት ትተው እርስ በርሳቸው በፍትወታቸው ተቃጠሉ፤ ወንዶችም በወንዶች ነውር አድርገው በስሕተታቸው የሚገባውን ብድራት በራሳቸው ተቀበሉ።" " እግዚአብሔርን ለማወቅ ባልወደዱት መጠን እግዚአብሔር የማይገባውን ያደርጉ ዘንድ ለማይረባ አእምሮ አሳልፎ ሰጣቸው"
ሮሜ1፣27-28

ወንድ ከወንድ፤ ሴትም ከሴት ጋር ጋብቻ መፈጸም ይችላሉ፤ ለእነርሱ የጋብቻ ሠርቲፊኬት መከልከል ሕገመንግሥቱን ይጥሳል በማለት የአሜሪካው ጠቅላይ ፍርድ ቤት የተመሳሳይ ጾታ ያላቸው መጋባት እንደሚችሉ ወሰነ፡፡ ለጋብቻ ቅድስናና ክቡርነት የሚከራከሩ “የእግዚአብሔርን ሕግ ምድራዊ ፍርድ ቤት ይህን መለወጥ አይችልም” በማለት ውሳኔውን አጥብቀው ተቃውመዋል፡፡ በምንም መልኩ ይገለጽ ፍቅር ፍቅር ነው በማለት ፕሬዚዳንት ኦባማ ውሳኔውን ደግፈዋል፡፡

 ዋናውን (ዓቃቤ ፍትህ) ጨምሮ ዘጠኝ የፍትህ ዳኞች የያዘው የአሜሪካው ጠቅላይ ፍርድ ቤት በዚህ የሰዶማውያን ጋብቻ ላይ ውሳኔ እንዲያስተላልፍ ጉዳዩ ከቀረበለት ጊዜያት ተቆጥረዋል፡፡ በአሜሪካ የፍትሕ ሥርዓት ምዕራፍ ከፋች የተባለለት ውሳኔ አርብ ዕለት ሲተላለፍ የፍትሕ ዳኞቹ በአምስት ለአራት በመወሰን ነው ያጸደቁት፡፡ ይህ ጠባብ ልዩነት የታየበት ውሳኔ ሲተላለፍ አምስቱን ደጋፊዎች ወክለው አስተያየታቸውን የጻፉት የፍትሕ ዳኛ አንቶኒ ኬኔዲ ናቸው፡፡ እርሳቸውም ሲጽፉ “ከጋብቻ አንድነት የሚበልጥ የለም፤ ምክንያቱምታላቅ የሆነ ፍቅር፣ ታማኝነት፣ መስዋዕትነትና ቤተሰብን ያካተተ በመሆኑ ነው፡፡ ሁለት ከመሆን ይልቅ አንድ በመሆን የሚገኘው ኅብረት ይበልጣል በማለት ሰዎች የጋብቻ ኅብረት ይፈጥራሉ” ብለዋል፡፡ ሲቀጥሉም “ይህንን ጉዳይ በተመለከተ አቤቱታቸውን ያቀረቡት እንዳሳዩት ጋብቻ ማለት ሞትን አልፎ የሚሄድ ፍቅር መሆኑን ነው፤ … እነዚህ ሰዎች የጋብቻን ክቡርነት ያቃልላሉ ማለት እነርሱን አለመረዳት ነው፤ እንዲያውን እነርሱ ጋብቻን እንደሚያከብሩ ነው በመማጸን የሚናገሩት፤ ጋብቻን በጣም ስለሚያከብሩ ነው ተፈጻሚነቱን በእነርሱ ህይወት ማየት የሚፈልጉት፤ ጥንታዊ ከሆኑ ተቋማት አንዱ ከሆነው ጋብቻ ተገልለውና በብቸኝነት ተኮንነው ላለመኖር ነው ተስፋቸው” በማለት አስተያየታቸውን ሰጥተዋል፡፡

 ውሳኔውን ከተቃወሙት የአራቱን በመወከል አስተያየት የጻፉት ዓቃቤ የፍትሕ ዳኛው ዮሐንስ ሮበርትስ ናቸው፡፡ እርሳቸው ውሳኔው በርካታዎች ሊያስደስት ይችላል ካሉ በኋላ ሲጽፉ “አብላጫውን ድምጽ የሰጡት ውሳኔ በጥልቅ ልብን የሚነካና ተስፋ የሚያስቆርጥ ነው፤ ጋብቻ በአንድ ወንድ እና በአንዲት ሴት መካከል የሚፈጸም ኅብረት ነው የሚለው ዓለምአቀፋዊ ትርጉም በምንም ዓይነት መልኩ ታሪካዊ አጋጣሚ አይደለም፤ ጋብቻ በፖለቲካ ትግል፣ በግኝት መልክ፣ በበሽታ፣ በጦርነት፣ በሃይማኖታዊ ሥርዓተ ሕግ ወይም አንዳች የዓለምን ታሪክ ባናወጠ ኃይል የተከሰተ አይደለም፤ እንዲሁም ወንድና ወንድ ወይም ሴትና ሴት ተጋቢዎችን ለማግለል ተብሎ የተደረገ የቅድመታሪካዊ ውሳኔ ውጤትም አይደለም” ብለዋል፡፡ ሲቀጥሉም “ጋብቻ የተከሰተው ወሳኝ የሆነን ፍላጎት ለማሟላት ነው፤ ይህም ደግሞ ከእናትና አባት ልጆችን በመውለድ እነርሱን በተረጋጋ ሁኔታ ለማሳደግ ራስን አሣልፎ በመስጠት የህይወት ሙሉ ውሳኔ በማድረግ ነው” ብለዋል፡፡

የውሳኔው እንደምታ

የጋብቻን ክቡርነት የሚሰብኩና ጋብቻ በአንድ ወንድና በአንዲት ሴት መካከል መወሰን አለበት የሚሉ ወገኖች በዚህ የጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ውሳኔ ክፉኛ ሃዘን ገብቷቸዋል፤ የወደፊቱም ሁኔታ አስግቷቸዋል፡፡ ውሳኔውን ተከትሎ የሚከሰቱት ነገሮች ማኅበረሰቡን በእጅጉ የሚበጠብጡ እንደሚሆኑም ካሁኑ እየተነገረ ነው፡፡
ፍርድ ቤቱ ውሳኔውን ሲያሳልፍ የጋብቻን ሃይማኖታዊ ገጽታ አልተመለከተም የሚሉ ወገኖች በተለይ መጽሐፍ ቅዱስ ሰዶማውያንን በተመለከተ የሚናገረውን ከሮሜ መጽሐፍ አንደኛው ምዕራፍ ላይ ያለውን ይጠቅሳሉ፡፡ “እግዚአብሔርን እያወቁ እንደ እግዚአብሔርነቱ መጠን ስላላከበሩትና ስላላመሰገኑት የሚያመካኙት አጡ፤ ነገር ግን በአሳባቸው ከንቱ ሆኑ የማያስተውለውም ልባቸው ጨለመ። … ስለዚህ እርስ በርሳቸው ሥጋቸውን ሊያዋርዱ እግዚአብሔር በልባቸው ፍትወት ወደ ርኵስነት አሳልፎ ሰጣቸው፤ ይህም የእግዚአብሔርን እውነት በውሸት ስለ ለወጡ በፈጣሪም ፈንታ የተፈጠረውን ስላመለኩና ስላገለገሉ ነው፤ … ስለዚህ እግዚአብሔር ለሚያስነውር ምኞት አሳልፎ ሰጣቸው፤ ሴቶቻቸውም ለባሕርያቸው የሚገባውን ሥራ (ከወንድ ጋር መገናኘት ትተው) ለባሕርያቸው በማይገባው (እርስ በርሳቸው በማድረግ) ለወጡ፤ እንዲሁም ወንዶች ደግሞ ለባሕርያቸው የሚገባውን ሴቶችን መገናኘት ትተው እርስ በርሳቸው በፍትወታቸው ተቃጠሉ፤ ወንዶችም በወንዶች ነውር አድርገው በስሕተታቸው የሚገባውን ብድራት በራሳቸው ተቀበሉ። እግዚአብሔርን ለማወቅ ባልወደዱት መጠን እግዚአብሔር የማይገባውን ያደርጉ ዘንድ ለማይረባ አእምሮ አሳልፎ ሰጣቸው፤ … ጥበበኞች ነን ሲሉ ደንቆሮ ሆኑ”፡፡

ይህ ብቻ ሳይሆን በዚህ ውሳኔ ምክንያት በርካታ ግለሰቦችና ተቋማትም አደጋ ላይ እንደሚወድቁ እየተነገረ ነው፡፡ ለምሳሌ በጋብቻ ሥርዓት ላይ አገልግሎት የሚሰጡ የሠርግ ኬክ ጋጋሪዎች፣ አበባ አዘጋጆች፣ የሠርግ ዕቅድ አውጪዎች፣ ፎቶግራፍ አንሺዎች፣ ወዘተ በእምነታቸው ምክንያት ለሰዶማውያን ጋብቻ አገልግሎት አንሰጥም በሚሉበት ጊዜ በሰብዓዊ መብት ጥሰት ቅጣት የሚቀበሉ ይሆናሉ፡፡ በኮሎራዶ ጠቅላይ ግዛት አንድ ኬክ ጋጋሪ እንዲሁም በኒውዮርክ ግዛት የገጠር ቤታቸውን ለሠርገኞች የሚያከራዩ ለሰዶማውያን አገልግሎት አንሰጥም በማለታቸውና ግዛቶቹ የሰዶማውያንን ጋብቻ ያጸደቁ በመሆናቸው ፍርድቤት ቀጥቷቸዋል፡፡ ከጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ውሳኔ በኋላ ግን በየትኛውም ግዛት ቅጣቱ ተፈጻሚ ይሆናል፡፡ ምክንያቱም ከአምሳዎቹ የአሜሪካ ግዛቶች 14ቱ በሰዶማውያን ጋብቻ ላይ ዕገዳ ያደረጉት ከአርቡ የጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ውሳኔ በኋላ ዕገዳቸውን ማንሳት አለባቸው፡፡


“ተመሳሳይ ጾታ” ብሎ “ጋብቻ” የሚለው ቃል አብሮ አይሄድም በማለት የሚከራከሩ ወገኖች ጋብቻ የሚለው ቃል የሚውለው ለተቃራኒ ጾታ ብቻ ነው ይላሉ፡፡ ከዚህም ሲያልፍ የተቃራኒ ጾታዎች ግንኙነት ብቻ ነው ልጆችን ማፍራት የሚችለው ይላሉ፡፡ ሰዶማውያን ወይም ተመሳሳይ ጾታ ያላቸው ሲጋቡ የሚያፈሩት ልጅ የለም፡፡ ሴቶቹ ተጋቢዎች የወንድ ዘር ከዘር ባንክ በመግዛትና ውስጣቸው በህክምና በማስጨመር ቢወልዱም ወንድ ተጋቢዎች ግን በጉዲፈቻነት ሌሎች በተቃራኒ ጾታ ግንኙነት የፈጠሩትን ልጅ ወስደው ነው የሚያሳድጉት፡፡ ስለሆነም ሁለቱ ተጋቢዎች በተፈጥሮ ለመውለድ የማይችሉ በመሆናቸው በጥቅሉ ከሚታወቀው ጋብቻ እኩል ተደርጎ መወሰድ የለበትም ይላሉ፡፡ እንዲያውም የሰዶማውያን ጋብቻ የሰው ዘር እንደ ብርቅዬ እንስሳ እንዲጠፋ ድጋፍ የሚሰጥ ነው እስከማለት አጥብቀው ይከራከራሉ፡፡

ይህንን ውሳኔ ተከትሎ ካሁን በኋላ ሰዶማውያን የፈለጉትን ልጅ በጉዲፈቻነት ለማሳደግ ልክ እንደ አንድ ባልና ሚስት ፈቃድ ማግኘት ይችላሉ፡፡ ይህ ፈቃድ በሰዶማውያን “ወላጆች” አድጎ በነርሱ መስመር የሚቀጥል ልጅ ለማሳደግና ሰዶማዊነት እንደ መደበኛ ተግባር እንዲቆጠር ለማድረግ በር ከፋች ይሆናል፡፡ ይህ ብቻ አይደለም ከሃይማኖታቸው አንጻር የሰዶማዊነትን ትክክለኛ አለመሆን የሚሰብኩ ካህናት በሰብዓዊ መብት ረገጣ እስር ቤት የሚጣሉበት ቀን ሩቅ አይሆንም፡፡ በየአምልኮ ቦታው የሚሄዱ ሰዶማውያን ልጆችን ከማስተማር ጀምሮ በአምልኮ ቤቶቹ አገልግሎት እንዳይሳተፉ መከልከል አይቻልም፡፡ በመሆኑም መጪው ትውልድ ከሥነምግባር አኳያ በትምህርት ቤት ብቻ ሳይሆን በአምልኮ ሥፍራዎችም የሰዶማውያን ጋብቻ ትክክል ነው በማለት እያመነ እንዲያድግ ይቀረጻል፡፡

የፍርድ ቤቱ ውሳኔ እንደተሰማ ተቃውሟቸውን ያሰሙት የሉዊዚያናው አገረ ገዥ ቦቢ ጂንዳል ሲሆኑ እርሳቸውም ዘለግ ያለ መግለጫ አውጥተዋል፡፡ ለመጪው የፕሬዚዳንታዊ ምርጫ የሚወዳደሩት ጂንዳል “ውሳኔው ሰዶማዊነትን በመቃወም ሰዎች የሃይማኖት ነጻነታቸውን በገሃድ እንዳይለማመዱ ጥቃት የሚሰነዝር ነው” ብለውታል፡፡ ሲቀጥሉም “ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ውሳኔውን ያስተላለፈው የሕዝብ አስተያየትን በመከተል መሆኑ የሚያስደንቅ አይደለም፤ ሆኖም ውሳኔው ጠቅላይ ግዛቶች በሚያስተዳድሯቸው ግዛቶች ላይ የሚፈልጉት ሕግ እንዳያወጡ ወይም እንዳይቃወሙ መብታቸውን የሚረግጥ ነው፤ በመሠረቱ በአንድ ሰውና በአንዲት ሴት መካከል ጋብቻ እንዲሆን የመሠረተው እግዚአብሔር ነው፤ ማንኛውም ምድራዊ ፍርድ ቤት ይህን መለወጥ አይችልም” ብለዋል፡፡


የጠቅላይ ፍርድቤቱ ውሳኔ እንደተሰማ ፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ በሰጡት መግለጫ ደስታቸውን ገልጸዋል፡፡ “ፍቅር ፍቅር ነው” በማለት የተናገሩት ኦባማ የግብረሰዶማውያን ጋብቻ ሕጋዊ እንዲሆን በተለይ በሁለተኛው የአስተዳደር ዘመናቸው ጥረዋል፡፡ ውሳኔው “ለአሜሪካ ድል ነው” በማለት በወጣትነት ዘመናቸው ሰዶማዊ ነበሩ ተብለው በአንዳንዶች የሚታሙት ኦባማ በካሜራ ፊት አውድሰውታል፡፡


ኦባማ የሰዶማውያን መብት በአገራቸው ብቻ ሳይሆን በአፍሪካም እንዲከበር አበርትተው ሲሰሩ ቆይተዋል፡፡ ባለፈው ምዕራብ አፍሪካን በጎበኙበት ወቅት ይህንኑ ጉዳይ አንስተው ያደረጉት ንግግር በአፍሪካውያን ዘንድ ተደማጭነት ያጣ ብቻ ሳይሆን የከረረ ተቃውሞም ገጥሞት ነበር፡፡ ሆኖም ግን በተገኘው አጋጣሚ ሁሉ የአሜሪካ ሸሪክ በመሆን የአሜሪካንን ጥቅም ጎረቤት አገርን በመውረርም ሆነ ወታደራዊ ቤዝ በመስጠት የሚያስከብሩ የአፍሪካ አገራት በዚህ የሰዶማውያን መብት ጥበቃ ወጥመድ ውስጥ ይወድቃሉ የሚለው አስተያየት ሲሰማ ይደመጣል፡፡ አሜሪካ የበጀት ድጎማ የምታደርገውም ሆነ አምባገነኖችን በጭፍን የምትደግፈው በምላሹ የምታገኘውን በማሰብ እንደሆነ የሚናገሩ ወገኖች አሜሪካ ገንዘቧ ሰጥታ ይፈጸምልኝ የምትለውን ሳታገኝ የምትቀርበት ምንም ምክንያት አይኖርም ይላሉ፡፡
ከዚህ አንጻር በኢትዮጵያ ውስጥ እየተስፋፋ በመጣው የወሲብ ልቅነትና የሰዶማውያን ሁኔታ ሳይንሳዊ መረጃ ማቅረብ የሚያዳግትበት ቢሆንም ከውጭ ድጋፍና ተጽዕኖ ጋር የተሳሰረ እንደሆነ ይነገርለታል፡፡ የዛሬ ሁለት ዓመት በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ሆነው የተሾሙት ፓትሪሽያ ሃስላክ የሹመት ጥያቄያቸውን ለአሜሪካው የሕግ መወሰኛ ምክር ቤት በማቅረብ በውጭ ጉዳዮች ኮሚቴ ፊት ቀርበው ሲመሰክሩ እንዲህ ብለው ነበር፤ “(የአምባሳደርነት ሹመቴ) ከጸደቀ በጾታ ላይ የሚደረግን ጥቃት እንዲሁም በግብረሰዶማዊያን ኅብረተሰብ ላይ የሚፈጸመውን መድልዖ አስመልክቶ እኛ (አሜሪካውያን) የምንከተለው የፖሊሲ አቅጣጫና ጥረት (በኢትዮጵያም እንዲሆን) የሚቻለኝን ሁሉ ለማድረግ ቁርጠኛ መሆኔን እገልጻለሁ”፡፡


በሐምሌ ወር ማገባደጃ አካባቢ ባራክ ኦባማ ኢትዮጵያን እንደሚጎበኙ ባለፈው ሰሞን መነገሩ ይታወሳል፡፡


(Golgul web news)

Monday, May 25, 2015

የጴንጤዎቹ እንደዶክሌ ቀልደኛው ዳዊት ሞላልኝ የሰው ሕጋዊ ሚስት ቀማ!!

ጌታ ለእኔ የማይፈርደው እስከ መቼ ነው? የእግዚያብሔር ቤተሰቦች የእውነት ቃል በእናንተ ካለ እስቲ ፍረዱ !
ፓስተር ዳዊት ሞላልኝ የተባለ ግለሰብ ህጋዊ የትዳር አጋሬን ባለቤቴን በቁሜ ነጠቀኝ::
አቶ ግርማ ዱሜሶ








ይህንን ጽሁፍ እራሳቸው አዘጋጅተው ከእነ ፎቶግራፋቸው የላኩት ግለሰብ ነዋሪነታቸው በሰሜን አሜርካ በአትላንታ ጆርጂያ ግዛት የሚኖሩት አቶ ግርማ ዱሜሶ የተባሉ ግለሰብ ህጋዊ ባለቤቴን ወ/ሮ ትግስት አበበ ደምሴን ፓስተር ዳዊት ሞላልኝ የተባለ ግለሰብ አስነውሮብኝ ትዳሬን አፍርሶታል:: እኔም እነዚህ ሁለት ግለሰቦች ባደረሱብኝ ከባድ የህይወት ወንጀል በተደጋጋሚ ሁለቱም ግለሰቦች በቤተክርስትያን በኩል እንዲጠየቁልኝ እና ክርስቲያናዊ ይቅር እንድንባባል በተደጋጋሚ አሜርካ ውስጥ ለሚገኙ የኢትዮጵያናውያን ቤተክርስትያኖችን ጠይቄ ከቤተክርስትያኖቹ ምላሽ አጥቼያለሁ ስለሆነም ውድ የእግዚያብሔር ቤተሰቦች የሆናችሁ እውነተኛ ክርስቲያኖች ይህንን እውነተኛ ታሪኬን አንብባችሁ ፍርዳችሁን እንድትሰጡኝ በጌታ ኢየሱስ ስም እማጸናችኋለሁ

ቀን 03/16/2015

ለቄስ ዶ/ር ቶሎሳ ጉዲና

አትላንታ ጆርጂያ (USA )

ጉዳዩ ፡ በኔና በትዳሬ ላይ የደረሰውን በደል ፤ ነውርና ጥቃት ይመለከታል!

በእግዚአብሔር የተወደድክና በጣም የማከብርህ መንፈሳዊ አባቴ ( ፓስተሬ ) ነህና “አንተ “ ብልህ እንደ ድፍረት እንደማትቆጥርብኝ ተስፋ አደርጋለሁ ። ተወልጄ ባደኩበት ማህበረሰብና እንዲሁም በእግዚአብሄር ቃል ውስጥም ቢሆን ሰው ፈጣሪን የሚያህል አምላኩና የሥጋ ወላጅ አባቱን “አንተ “ እንጂ “እርስዎ አምላኬ ሆይ “ ብሎ ስጣራ አልሰማሁም ።

በመሆኑም በሚገባኝ መንገድ ከልቤ በሆነ አክብሮት የጌታ ሰላም ፤ ምህረት ፤ጥበቃና ቸርነት እየተመኘሁልህ ፤ እንዲሁም ረጂም ዕድሜና በረከት ይብዛልህ ለማለት እወዳለሁ።

ፓ/ር ፡

ምንም እንኳን አንተን ማድከምና ማሰልቸት ቢሆንም ከዚህ ቀደም በአካልና በሰልክ ደጋግሜ ያጫወትኩህን (በሰፊው የተነጋገርንብትን ) እና አሁንም ድረስ የተቸገርኩበትን ብርቱ ጉዳዬን ከዚህ እንደምከተለው እንደገና ልገልጽልህ ወደድኩ ። ያም ጉዳይ ቀደም ሲል አንተም የሚታውቀውና በቅርቡም በቢሮህ ተገኝቼ በዝርዝር ገልጬልህ በተነጋገርነው መሰረት ሚስቴ የነበረችው ወ/ሮ ትግስት አበበ ደምሴና ፓ/ር ዳዊት ሞላልኝ አበጋዝ የሚባሉ ግለሰቦች ያደረሱብኝን በደልና ጥቃት የሚመለከት ነው ፡፤

እነዚህ ግለሰቦች እንደ ሌሎቹ ቅዱሳን አማኞች መልካምና ጥሩ ስነ-ምግባር ያላቸው እውነተኛ አገልጋዮች መስለውኝ አመንኳቸውና በቅንነትና በየዋህነት በልበ-ንጽህና ቀረብኳቸው እንጂ ከኋላዬ ዞረው ፈጣሪን በመዳፈር ለብቻቸው የተደበቀ እና ስውር የሆነ የግል ሚስጢርና ግንኙነት ኖሮአቸው ነውርን በትዳሬ ላይ ሊሰሩ ይችላሉ ብዬ ለማሰብ አንዳች ስጋትና ግምት አልነበረኝም ፤ ትዳሬን አፍርሰው ህይዎቴን አደጋ ላይ ይጥሉኛል ፤ ለከፋ ብስጭትና ኪሳራ ይዳርጉኛል ፤ ያዋርዱኛል ብዬ ጨርሶ አላሰብኩም ነበር ።

ይሁን እንጂ የቤተክርስቲያን አገልጋዮች በመሆናቸው እምነት ጥዬባቸው ሳለ በገርነቴና በቀናነቴ በነዚህ በእግዚአብሔር አገልጋይ ተብዬዎች በደል ደረሰብኝ ፤ ተጎዳሁ ፤ ተጠቃሁ ።በዚህ በተፈጸመብኝ በደል የተነሳ እጅግ በጣም አዝኛለሁ ። በዋናነት የበደለኝም ብልጣ-ብልጡ አፈ-ጮሌ ፤ አስመሳይ መንፈሳዊ ሰው መሳይ ዳዊት ሞላልኝ የተባለ የ “FBI “ ቤተክርስቲያን ፓ/ርና መሪ ግለሰብ ነው ።

ይህ ያለንበት ዘመን በተለያየ ስፍራ በሃይማኖታዊና በመንፈሳዊነት ስም የምመላለሱ መንፈሰዊ ዱሪዬዎች እጅግ የበዙበት ወቅት በመሆኑ በእግዚአብሄርና በአገልግሎት ስም እያመኻኙ ባለቤቱ የከደነውን አለፈቃድ የሚከፍቱ ፤ ያስቀመጠውን አንስተው የሚወስዱ ፤ የሰውን ኑሮ የሚያናጉ ንጹሕ ፍቅር ባላቸው ጥንዶች መካከል እየገቡ በሰላምና ደስታ ፋንታ ጭቅጭቅንና ሃዘንን የሚያደርሱ የፍቅርና የቅድስና ጠላት የሆኑ ጉዶች የፈሉበት ጊዜ ነው ቢባል ያጋነንኩ አይመስለኝም ።

ፓ/ር ዳዊት ከዚህ ቀደም ማንንም ገጥሞት በማያውቅ ሁኔታ በሃይማኖት ተጀቡኖ ፤ በአገልጋይነት ሰበብ ተሸፍኖ፤ በእግዚአብሄር ስም እየነገደ ፤ በንቀት ድፍረት ተሞልቶ የሥጋ ፊላጎቱን ማርኪያና መደሰቻ ሲል ትዳሬን አፈራርሶታል ።ይህንንም ያደረጉት በተጋባን ዕለት ካረፍንበት ሆቴል ሙሽሪት( ወ/ሮ ትግስት) ቬሎ ልብሷን ቀይራ እኔን በሆቴል ውስጥ ጎልታኝ ሁለቱ ግን የግል ሥጋዊ ፊላጎታቸውን ለመፈጸም አንዴ ብቻ ሳይሆን ሁለቴ የድፍረት ሙከራ ፈጽመውብኝ አክሽፈዋለሁ ፤በመቀጠልም በቤተዘመድ በታላቅ እህቴ ቤት በተዘጋጀልን የመልስና ቅልቅል ጥሪ ላይም በዕለቱ የተጠሩት የሥጋ ዘመዶቼ እንኳ ሳይታደሙ በሚያስደነግጥ ሁኔታ እኔን (ሙሽራውንም) ሆነ ዘመዶቼን በንቀት ተመልክተውን ከምንም ሳይቆጥሩን አሳዝነውን እና አሳፍረው ግብዣውን አቋርጠው ተያይዘው መሄዳቸው ፤ በሌላ ቀን ደግሞ ወደ አረፍንበት ሆቴል ድረስ በራሱ መኪና ልወስዳት ሲመጣ ፈቃደኛ አለመሆኔን ለመግለጽ ቢሞክርም ጉልቤው ዳዊትና ሚስቴ ራሷ “ አንተን ያወቅንህ ገና ቅርብ ጊዜ ነው ፤ እኛ ግን የቆዬ ጓደኝነትና የጋራ አገልግሎት አለን ፤ ስለዚህ ከተስማማህ እረፍና ቁጭ በል ካልተመቸህ የራስህ ጉዳይ “ ብለው ዓይኔ እያየ ያለፈቃዴ ሚስቴን ነጥቆኝ ሄዷል ።

እንዲሁም ሌላ ጊዜ ደግም አብረን በአውሮፕላን እየተጓዝን ሳለን እኔን ባሏን “ አንተ መጽሐፍ አንብብ ፤ ዳዊት ብቻውን ነውና እሱ ወደ ተቀመጠበት ወንበር ሄጄ ላጫውተው “ በማለት በአውሮፕላን ውስጥም እንኳ ለብቸኝነት ዳርጋኛለች ። በአንድ ወቅት ደግሞ አንድ

ከተማ ውስጥ አብሬን በተመሳሳይ ሆቴል ውስጥ ባደርንበት ጊዜ (ዕለት) “ከዳዊት ጋር የአገልግሎት ጉዳይ የሆነ የሚናወራው ነገር አለን “ በማለት lab top computer ይዛ ያረፍኩበትን ሆቴል መኝታ ክፍል በር ዘግታብኝ ከሄደች በኋላ የት እንዳደረች ሳላውቅ በ2ኛው ቀን ምግብ መመገቢያው ውስጥ ከግለሰቡ (ዳዊት ) ጋር ቁርስ ስበሉ ለዚያውም ከሩቅ እስካ አየኋቸው ሰዓት ድረስ የትና ምን ሲሰሩ እንዳደሩ እግዚአብሔርና እነሱ ብቻ ናቸው የሚያውቁት ።

በሌላውም የምሳና የእራት ፤ እንዲሁም የቁርስና ቡና ሰዓታት እሷ ሁሌ ከሰውዬው (ዳዊት ) ጋር በመሆን ለብቻቸው ተጣብቀው ስላሉ (ስለምቀመጡ ) ከሙሽራዋ ሚስቴ ጋር ማዕድ ለመቆረስ እንኳ አልታደልኩም ነበር ።የስልክ አጠቃቀሟም ቢሆን ባለሁለት ቀፎ ስለሆነ ከዳዊት ጋር በስልክ ስታወራ ከኔ ርቃ ወይም መኝታ ቤት ገብታ ዘግታ በመቆለፍ ስለሆነ አብሬያት በቆየሁባቸው ጥቂት ወራት የብቸኝነትን ህይዎት ነበር የተጋፈጥኩት ።

አትላንታ ከተማ ተመልሰን በገዛ ቤታችን በእንግድነት ሰውዬውን ( ዳዊትን ) ባስጠጋነው ወቅትም ቢሆን እኔን ሳሎን ( ምግብ ቤት ውስጥ) ትተውኝ “ ስለ አገልግሎት የምንመካከረው ጉዳይ አለን” ወዘተ .. በማለት በራሴ መኝታ ቤት ወይም እንዲተኛበት በሰጠነው መኝታ ክፍል ውስጥ ቢያንስ ለ2 እና ከዚያ በላይ ሰዓታት ያህል በር በመቆለፍ ያደረጉትን አገልግሎት ፈጣሪ ብቻ ይመልከተው ከማለት ሌላ ለማውራት የማይቻለኝ የሚቀፍና ህሊናን የሚያደማ ነገር ነው ።

ይህ ብቻም ሳይሆን ባጋጣሚ እኔ አስቀድሜ ወደ መኝታ ቤቴ ውስጥ ከገባሁ ደግሞ ሌላ ሰበብ ይፈጥሩና “ ከዳዊት ጋር የሚንሰራው አጣዳፊ ጉዳይ አለኝ “ በማለት ኮምፒዩተሯን ይዛ እስከ እኩለ-ሌልት አንዳንዴም እስኪነጋ በሌላው ክፍል ወይም በሳሎናችን ውስጥ አብረው ያድሩ እንደነበር እነሱ ራሳቸው (ዳዊትና ትግስት ) ባሉበት ያንተ ረዳት ፓስተሮችም በተገኙበት ቢሮህ ውስጥ ለበርካታ ሳዓታት ( 7 ሰዓት ) ሙሉ በግልጽ ስንነጋገር አለመካዳቸው የሚታወስ ነው ።

ይህ ድንበርና ገደብ የለሽ መንፈሳዊ ሽፋንና ሃይማኖታዊ ሰበብ ከባል ስልጣንና ፈቃድ ውጪ የተሰወረ ሚስጢራዊ አገልግሎት ሊደረግ ሲታሰብ ምን ሊሆን እንደሚችል ፍርዱን ለፈጣሪና አመዛዛኝ ህሊና ላለው ሰው ሁሉ ትቻለሁ ።

ሌላው ደግሞ በአጋጣሚ እንኳ እግሯን አንድ ነገር ስያደናቅፋት ፤ ዕቃ ስወድቅባት እና ድንገት የሆነ ድንጋጤ ስሠማት በቁልምጫ “ዴቭ ድረስልኝ “ ስትል መስማት፤ እንዲሁም ከወላጆቿ ፤ከሥጋ ዘመዶቿና አብሮ አደግ ጓደኞቿ እንዲሁም ከኔና እሷ ፎቶግራፎች ይልቅ የዳዊትን ፎቶዎዎች በመኝታዬ ራስጌና ግርጌ ፤በሳሎን ቤትና የማድ ቤት ( ኩሽና ) ማቀዝቀዣ ላይ ዘወትር ማየት አዕምሮን የሚያደማና ህሊናን የሚያቆሽሽ ትዕይንት ነበር ። እስቲ አትታዝቡኝና በሷ ልብና አምሮ ውስጥ ይህ ዳዊት ምኗ ይሆን ? እኔስ ምኗ ነበርኩ ?

በአጋጣሚ ይህንን ደስ የማይል ታሪክና ዜና ለሚሰሙትም ሆነ እሮሮዬን ለሚያነቡት ሁሉ ለማለት የሚፈልገው ነገር ቢኖር 1ኛ እንዲህ ያለው እልህን ጭሮ ለከፋ ወንጀል የሚገፋፋው አደናጋሪና አጠያያቂ ክፉ ፈተና በገዛ ቤቴ ስለገጠመኝ እንኳን መሸከምና መታገስ ቀርቶ ለመስማትም ሆነ ለማውራት የማይቻለው የስቃይ ጦርነት እየተፈራረቀብኝ በእግዚአብሔር ጸጋ እስካሁን ድረስ በህይዎት መኖሬ እኔን እራሴ ስገርመኝና ስደንቀኝ የሚኖር የጌታ ጥበቃና ውለታ ነው ። እግዚአብሔር አምላክ የማይቻለውን አስችሎ ከክፉ ሁሉ ጠብቆ ነፍሴን ስላኖራት ክብር ምስጋና ይህንለት እላለሁ ፤ 2ኛ የተወደደች ፤ እግዚአብሔርን የሚታውቅ ፤ የምትፈራ ፤ በቃሉም የምትመራ ፤ ለፈጣሪ ፤ ለባሏ ፤ለህሊናዋ ፤ለኑሮዋ ታማኝ የሆነች መልካም ሴት ( ሚስት ) አግኝቶ አዕምሮው ካልተቃወሰ ( የጤና ችግር ከላጋጠመው ) በቀር ማን በዋዛ ሚስቱን ይጥላል ? ( ይተዋል ) ? ያልታደልኩትን እኔን ካልሆነ በቀር እንዲህ ዓይነቱ ውንብድና ፤ ሃፍረት የሌለው ጥቃት በማን ላይስ ደርሶ ያውቃል ?

ይህ ከመሆኑ በፊት ምንም እንኳን በውቅቱ የገባሁበት አጣብቂኝ ለማውራትም እንኳ የሚቀፍ ፤ ውስብስብ ፤ የከረፋ ቆሻሻና ጸያፍ ከመሆኑ የተነሳ ልታገሱት የማይቻል ቢህንም ፤ ለብዙ ዘመን ተጠምቼ ፤ ተመኝቼና በትዕግስት ጠብቄ ያገኘሁት ፤ ብዙ ዋጋ የከፈልኩበት ትዳሬ ስለሆነ ሙሉ ለሙሉ ከመበላሸቱ በፊት እስቲ ይሁን ብዬ ፤ ይቅር ለእግዚአብሔር በማለት ሁሉን ረስቼ ፤የማይቻለውን ችዬ ፤የማይረሳውን ረስቼ ፤ ነገን ብቻ ተስፋ በማድረግ እንደገና ጠጋግኜ ለማዳን የሞከርኩት ትዳሬ አፈር ድሜ በልቷል ።

እንዲህም እንኳን ሆኖ ወዲያውኑም ውዬ ሳላድር ባንድም ሆነ በሌላ ፤ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ በኔ ሰበብ የእግዚአብሔር ቤት መጠቋቋሚያና መሳለቂያ ከሚሆን ፤ሌሎች ቅዱሳንና እውነተኛ ታማኝ የሆኑ አገልጋዮችና መሪዎች ስም በመጥፎ ምሳሌ አብሮ ከሚነሳ ( ከሚጠፋ) ፤አገልግሎታቸው ከሚተች ፤ራዕያቸው ፤ ዓላማቸውና ትጋታቸው ዋጋ እንዳያጣ ፤ሳይጣን ከሚደሰት ፤ ሁላችንም የዓለም አጀንዳ ከሚንሆን፤ እግዚአብሔርንና መንፈሱን ከማሳዘን ፤ በተለይም በእምነታቸው ያልበረቱ አዳዲስ አማኞች ግራ እንዳይጋቡ እኔው ደግሜ ደጋግሜ ልጎዳና የሚቻል ከሆነ እስቲ እንደገና ትዳሩን ወደ ነበረበት ልመልሰው በማለት ያሰብኩት ቀናነት ዋጋና ትኩረት ተነፈገው።

ይህ ሁሉ ሆኖ ሰውየው ( ፓ/ር ዳዊት ) ይህንን ለፈጸመበት ጥፋትና አስነዋሪ ተግባር እስካሁን አልተገሰጸም ፤ አልተወቀሰም ፤ አልተከሰሰም ይቅርታም አልጠየቀም ። ነገር ግን የከበረውን ትዳሬን አፍርሶ እሱ ግን ዛሬም እያሾፈ በሰላም ይኖራል ፤ እንዳውም ይባስ ብሎ ቤተክርስቲያንን ይመራል ፤ የእግዚአብሄርን ቃልና ፈቃድ አስተምራለሁ ፤ የክርስቶስን ዓላማ እያራመድኩ፤ እያስፈጸምኩ ነኝ ይላል ።ግብረ አበሩ የሆነችውም ወ/ሮ ትግስት የራሷን ትዳር ንዳ ዛሬም አብረው በመሆን ሥፍራና ጊዜ እየቀያየሩ በየአብያተክርስቲያናቱ ዘንድ የተለመደውን ተራ ግርግር እየፈጠሩ መንፈሳዊ አገልጋይ ለመባል እየጣሩ ናቸው ። በኔ ላይ በለመዱት ዓይነት አኳኋን በተመሳሳይ ሁኔታ የኔ ዓይነቶቹን ሌሎች የእግዚአብሔር ህዝብ መተራመስ የለበትምና ድርጊቱ ተገላልጦ የማያዳግም ትምህርት ተሰጥቶ ህዝበ-እግዚዝብሔር ከመታለልና ተመሳሳይ ሰለባ ከመሆን መዳን አለበት ።

እነዚህ ፌዘኛ ግለሰቦች ፤ እጥቤ አሿፊ ጩሉሌዎች ሃፍረትና ይሉኝታ የሌላቸው ደንታ-ቢስ ባይሆኑ ነው እንጂ እንኳን በቤተ-እግዚአብሔር ውስጥ ካህን የሆነ ሰው ቀርቶ በዓለም ያሉቱ ካሃዲዎች ዘንድም እንኳ እንዲህ ዓይነቱን ወንጀል ስፈጽሙ ተሰምቶና ተደርጎ አይታወቅም ። እኔ ተራ እቃ ( ንብረት ) ብቻ አይደለም የጠፋብኝ ፤ ገንዘብና ጊዜ ብቻ አልነበረም የባከነብኝ ።ነገር ግን ትዳሬ እኮ ነው የፈረሰው ፤ መተኪያ የሌለውና የዚህ ምድር አስፈላጊ እና እግዚአብሔር ባርኮ ከፈቀደልን እድሎችና መብቶች አንዱ ነው ትዳር::

በሌላ አባባል ትዳር ከእግዚአብሔር ቃልና መመሪያ ውጪ ሌላ ፎርሙላ የለውም ፤ “ ሰው እናት አባቱን ይተዋል ከሚስት (ከባል ) ጋር አንድ ይሆናል፤(ይጣበቃል) “ እንደሚል አንድ ሥጋ ፤አንድ አካል ፤አንድ መንፈስ በመሆን አንድ ዓላማ ይዘው ጥንዶች በፍቅር የሚጣመሩበት ነው ። በዚህ ዓላማ የተጣመሩ ጥንዶች አንዳቸው ከሌላኛው የተለየ ፊላጎት እና የተደበቀ ልዩ ሚስጢርና ፊላጎት ሊኖራቸው አይገባም ፤

ነገር ግን ያልታደለው የኛ ትዳር ግን ገና ስፈጠር ከአጀማመሩ በጨቅላነቱ በአጭር የቀጩት ቢሆንም ትዳሬ ለኔ ህይወትና የከበረ የአምላኬ ስጦታ ነበር ። ትዳር አንዴ ብቻ ነው ፤ ማፍቀርም የምቻለው አንዲትን ሴት ፤ ለዚያውም ከተቻለ አንዴ ጊዜ ብቻ ። ዳስታም ቢሆን ሁሌ የለም፤ በየዓመቱ ሠርግ ለማድረግም የማይታሰብ ነው ። የሆነው ሆኖ ለአንዲት ደቂቃ ( ዕለትም ) እንኳ ቢሆን ያፈቀርኳትን ሴትና የከበረውን ትዳሬን በቀላሉ በፓ/ር ዳዊት ሞላልኝ ምክንያት አጥቻለሁ ።

ስለዚህ የከበረና የናፈቅኩት ፤ የተመኘሁት ጅምር ደስታዬ በእንጭጩ ከመቅጽበት በመቀጨቱ ወደ ሃዘንና ውርደት ተቀይሮ አንገት አስደፍቶኛል ፤እልሀኛ ፤ ቂመኛና በምሬት የተሞላሁ ተናዳጅ አድርጎኝ ሄዷል ።ነገ ደግሞ ምን እንደሚሆንና ምን እንደሚገጥመኝ እርግጠኛ አይደለሁም ።

ይህ ግለሰብ (ዳዊት) ግን ኑሮዬን አፍርሶ ፤ ህይዎቴን አበላሽቶ እንዲህ እንደ ቀልድ እያሾፈ ሊኖር ነው ? ካደረሰብኝ ብርቱ ፈተና የተነሳ በህይወት ለመኖር የማያስችል ፤ ለወንጀል የሚገፋፋ ፤ ለከፋ በሽታና ጥልቅ ሃዘን የምዳርግ ነው የገጠመኝ ። አረ ለመሆኑ በትዳርና በርስት ቀልድ አለ ? በዓይንና በሚስትስ መጫወት ይፈቀዳል ? እንኳን ግፍና በደል በግልጽ በቤቴ ተፈጽሞብኝ ቀርቶ ድርጊቱ ደግሞ ከጥርጣሬ ያለፈ የአደባባይ ጥቃት መሆኑ ይቅርና እንዲሁ በጥርጣሬም እንኳን ቢሆን በሚስቴ የልቅነት ድርጊት የተነሳ የመቅናትም ሆኔ የተጣመመውን የማቅናት መብቱ ለኔ የሚገባኝ ህጋዊ ባል (አባወራ ) አይደለሁምን ?

እስቲ ፍረዱኝ አንድ መንፈሳዊ አገልጋይ በአገልግሎት አሳቦ የራሱን ሚስት እቤቱ አስቀምጦ “ዘመዴ( ካዝኔ) ናት “ እያለ አንዲትን ሌላ ሴት እንደ ኮሮጆ ሸክፏት ፤ እንደ ሻንጣ እየጎተተ ከሀገር ሀገር ፤ ከከተማ ወደ ከተማ በየሆቴሉ ሁሉ አስከትሎ ስጓዝ ትንሽ እንኳን ይሉኝታ አይዘውም ? ያቺስ ሴት ብትሆን የ”ሶሎ ዘማሪ ፤ የሙዚቃ መሳሪያ ተጫዋች ፤ ወይም በመድረክ ላይ የቋንቋ አስተርጓሚ (ሰባኪ ) ሳትሆን የራሷን መደበኛ ኑሮ ትታ እንደ ጭን ገረድ በየሀገሩና መንደሩ የማንንም ወጠምሻ ጎሮምሳ ተከትላው እየዞረች አብራው በየሆቴሉ አብራው ስታድር ሁለቱም ህሊና የላቸውም ዎይ ?

ሁለቱም በገዛ ህሊናቸው ባይኮረኮሩ ፤በመንፈስ ቅዱስ ለምን አልተወቀሱም ? አዕምሮ ቢደነዝዝ ፤ ህሊናቸው የማይወቅሳቸው ፤ የአውዋቂን ምክርና ተግሳጽ የማይሰሙ ፤የህዝብን ትዝብትና ግልምጫን ከምንም የማይቆጥሩ ቢሆኑም ከነአካቴው ሁሉም ይቅርብኝ እንጂ እኔ ግን ትዳሬን በማንም ማስነካት ፤ ሚስቴንም ከማንም ጋር መጋራት ስላልፈለኩ ሳልወድ በግድ ከመካከላቸው ወጣሁ ።በዚህም በዘመኔ ሁሉ የማልረሳ የህይዎት ጠባሳ እና ስብራት ትቶልኛል ፤ አንዳንዴ ቁጭ ብዬ እያሰላሰልኩ ሳስብ ባልጠፋ ሰው ከነዚህ ቅንነት ከጎደላቸው ሰዎች ጋር እኔ ስገጣጠም እግዚአብሔር ለምን ዝም አለኝ ? ይህ ሁሉ ጉዳት ፤ መቁሰል ፤ መድማት ፤ መፈራገጥ ፤መላላጥ ብሎም ለብርቱ ሃዘን መጋለጥ ለማን ይጠቅም ይሆን ? ማንስ ይከብርበት ይሆን ? ማን ከስሮ ቀርቶ ማንስ ያተርፍ ይሆን ? እንዳው ባጭሩ ይህ ዳዊት የሚባል ሰውዬ እንዲህ አቃጥሎኝ አዋርዶኝ እስከመጨረሻው የሚሳካለት መስሎት ይሆን ? ደስታዬን እንዲህ በአጭር

አጨልሞ እሱ ግን እንደ ፈነጨ ሊኖር ? ለማንኛውም የመጨረሻውን ውጤትና ድምዳሜ በያንዳንዷ ሰኮንድና ደቂቃ ከአምላኬ በትዕግስት እጠብቃለሁ ።

ዶ/ር ፡

ፓ/ር ዳዊት የበደለኝ በብዙ አቅጣጫ ነው ፤ለምሳሌ አስቀድመን በጋራ በተስማማነው መግባባት መሰረት በራሱ ቤተክርስቲያን (FBI ) ባለሙያዎች ተቀርጸው የተሰሩትን የሠርጌን ቪዲዮና ከ5000 በላይ የሆኑ ፎቶግራፎችን ኮፒም ሆነ ኦሪጂናል ቅጂዎችን እስከ ዛሬ ድረስ እንዳለገኝ ከልክሎ በማስቀረቱ እንኳን ለዘመድ አዝማድ ፤ ጎደኞቼና ጎረቤቶቼ ፤ የስራ ባልደረቦቼ ፤ ለአብሮ አደጎቼ ይቅርና እኔ ራሴ የጉዳዩ ባለቤት የሆንኩት የሠርጌን ማስታወሻ የማየትና በታሪክነቱ ለማስቀመጥ ዳዊት ከልክሎኛል ። የጋብቻ ወረቀቴንም (Marriage Certificate ) እስካሁን ድረስ በጉልበቱ አስቀርቶታል ።

እኔ ብቻ ሳልሆን መልካም ትዳር እንዲገጥመኝ ተመኝተውልኝ ለጋብቻችን መሳካት የጸለዩ ፤ የለፉ ወገኖች ፤ የረዱን እና በብዙ የደከሙልን ፤ እሩቅና የተሻለ ደረጃ ላይ እንዲንደርስ ከልባቸው ያማጡ ጓደኞችና የስጋ ዘመዶቼ ሁሉ ጭምር በደረሰብኝ ሁኔታ አፍረዋል ፤ አዝነዋል ፤ተበሳጭተዋልም ።

በቆየው የሀገራችን አባባል “ከምርት እንክርዳድ አይጠፋም” እንዲሉ ጥቂት ግለሰቦች (የነዳዊት ግብረአበሮች ) ካላቸው ተመሳሳይ ሥነምግባር እና ባህሪ፤ የግል ጓደኝነት ፤ ውለታና ቀረቤታ የተነሳ ግድፈትና ነውራቸውን ሊያስተባብሉ ፤ እርኩሰትንና ቅጥፈትን አድበስብሰው ነጻ ናቸው ለማለት ደፋ ቀና ሲሉ ፤ የጥፋተኛውን ወንጀል ሸፋፍነው ነውረኛውን በጉያቸው ወሽቀው በመደበቅ ፤ሃቅን በሃሰት በመጨፍለቅ ፤ እኔን በማግለል ለነገራችን ቅርበት የሌላቸውን ንጹሃንን በማታለል ፤ እውነትን በማፈን ፍትህን ለማዛባት ትርምስ ፈጥረው ቅዱሳንን ግራ ለማጋባት ሞክረው ነበር ።

ነገር ግን እኔን የገረመኝና ያናደደኝ “ በሰው ቁስል እንጨት ስደድበት “ ዓይነት አባባል ካልሆነ በቀር የገጠመኝ መከራና ፈተና ከመርግ ይልቅ እጅግ የሚከብደው ውርደትና ሃዘን ፤ ጥቃት ሁሉ እነሱን ገጥሞ ቢሆን ኖሮ ( ራሳቸው በኔ ቦታ ቢሆኑ ኖሮ ) ያለማጋነን ነፍሳቸውን በዛፍ ላይ የሚያንጠለጥሉ ፤ ምናልባትም አዕምሮያቸውን ስተው ፤ ጨርቃቸውን ጥለው የሚያብዱ ወይም ደግሞ በንብረትና በሰው ህይዎት ላይ ከፍተኛ ጉዳት ሊያደርሱ እንደሚችሉ አልጠራጠርም ። ፓ/ር ዳዊት ራሱ እኔን የገጠመኝ ዕጣ-ፋንታ ገጥሞት ቢሆን ኖሮ ምን ይውጠው ነበር ? ሁሉም ቢጤዎቹ ካንድ ጉድጓድ የተቀዱ ፤ አንድን ጽዋ በጋራ የጨለጡ አሳፋሪዎች እና selfish ስለሆኑ ታዘብኳቸው ።

መቼም ቢሆን እንደ ሰው ያልሆነ እግዚአብሔር ጻዲቅና መልካም አምላክ ነውና ምህረት ፤ ቸርነት ፤ ጥበቃው ፤ ፍቅሩ ፤ ርህራሄው ያማያልቅበት ፤ ወረት የሌለው በመሆኑ ራራልኝና አጽናንቶ የማይቻለውን እንዲችል ረዳኝና ከክፉው ሁሉ ጠብቆ እስካሁን በህይዎት አኖረኝ እንጂ የተጋራጠብኝ ፈተና ማንም ብርቱ ነኝ ባይ ልታገሰውና ልቋቋመው የማይቻል ከባድ አደጋ ነበር ። የራራልኝ እግዚአብሄር ይመስገን ፤ ነገንም በርሱ ፈቃድ እኖራለሁ ፤ አሜን ።

ለመሆኑ በማንአለብኝነት ይህንን ሁሉ ጥቃት የሚፈጽም ይህ ጉልቤ ጀብደኛ (ዳዊት ) ማን ነው ? “ከወፈሩ አይፈሩ” ነው ነገሩ ? ወይስ ምንን ተማምኖ ? ይህንን ሁሉ በደልና ግፍ ሰው አይቶ ባይፈርድልኝ እግዚአብሔርስ ይወደዋል ዎይ ? ይህ ግድየለሽ ሰላሜን አደፍርሶ ፤እና ህይዎቴን አበላሽቶ ፤ ኑሮዬን አናግቶ እሱ ግን ልፈነጭ ? አይደረግማ !!

የፈጸመውን ድርጊት ተናግሮ ፤ ጥፋቱ ተዘርዝሮ ስህተቱ ተብራርቶ ነውርና ድፍረቱ ተገልጦ ለአደባባይ መቅረብ አለበት ። ምናልባት በመንፈሳዊ አገልግሎት ሽፋንና ሰበብ ያካባተው ሃብት ፤ ያተረፈው ዝናና ክብር አለኝ ብሎ ስለምያስወራ ፤ እንዲሁም የጥፋቱ ተባባሪ ቢጤዎች ፤ ጓደኛና ምኑንም በውል ያልተረዱ ቅንና የዋሆች ያለእውቀት ደጋፊዎች ልኖሩ ስለምችሉ ከሰው ዘንድ እውነተኛ ፍርድ ላላገኝ እችላለሁ ፤ ቢሆንም ከቲፎዞ (ደጋፊ) ብዛት የተነሳ የፍትህ ዳኛና ሃቀኛ ምስክር ስለማይገኝ ፤ ትዳሬ ፈርሶ ፤ህይዎቴ ተበላሽቶ ፤ ራዕዬ ተጨናግፎ ፤ ተስፋዬ ጨልሞ ከአቅሜ በላይ የሆነ አበሳና ውርደት ተሸክሜ ለመኖር ለኔ እጅግ ከባድ ነው ።

ፓ/ር፡

ከዚህ ቀደም ውድ ጊዜህን ሰውተህ ከረዳቶችህ ጋር በመካከላችን ተገኝተህ ለበርካታ ሰዓታት እኛን ( ዳዊት ፤ ትግስትንና እኔን ) ስታወያየን አንተ ራስህ ሰምተህ ፤ አይተህ ፤ግንዛቤ እንዳገኘሀው (እንዳረጋገጥከው ) ፓ/ር ዳዊት እኔና ሚስቴን ባጋባበት ዕለት ወዲያውኑ ከመቅጽበት ከሚስቴ ጋር እንዲንለያይ ዋና ምክንያት ሆኗል፤ ለዚያውም አንዴ ብቻ ሳይሆን ሁለቴ ሦስቴም እንጂ ።

ይህ ድርጊት በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ በአበሻ ታሪክ በኔ ብቻ ካልሆነ በቀር የት ሀገር ? መቼ ? በነማን ላይ ደርሶ ያውቃል ? እነዴትስ በጫጉላ ሽርሽር ወቅት ( honey moon time ) ሙሽሪት ሙሽራውን ትታ ፓስተሯን ለመዝናናት በሚል ሰበብና ድፍረት የቃል ኪዳን ሙሽራ ባሏን በሆቴል ውስጥ እንዲሁም በሌላ ጊዜ ደግም በባዶ መኖሪያ ቤት ውስጥ ጥላ ፤ጨርቋን ጥላ እና አዕምሮዋን ስታ ለ7 ቀንና ሌሊት ያህል የምትጠፋው ? በገዛ ቤታችን ውስጥስ ቢሆን ባልን ሳሎን ውስጥ ትቶ ከፓ/ር ጋር መኝታ ቤት ገብቶ በር በመቆለፍ ለሰዓታት ያህል አገልግሎት ላይ ነን ማለትና…ወዘተ ጸያፍና ድፍረት የተሞላባቸው አሳፋሪ ድርጊቶችን መፈጸም የጤና ነው ? ወይስ የእብደት ?

እንዲህ ዓይነቱ ነውርና ልቅ የሆነው ጥፋት ከልክ ያለፈ ፤ መረን የለቀቀ ፤ሚዛኑን የሳተ ፤ ከድንበርም የዘለለ ስለሆነ ልሸከመው የማልችለው በቤቴ ፤ በትዳሬ እየተፈጸመ ነውና የከፋ ነገር ከመምጣቱ በፊት ይታሰብበት በማለት በግልጽ ውይይትና ምክክር አድርገን እናስወግድ ፤ መፍትሄ በመፈለግ እርማት እንውሰድበት የሚል ገንቢ እና ቀና ሃሳብ እንደ አገልጋይ ክርስቲያንና አማኝ በአክብሮት ያቀረብኩላቸው አቤቱታ ና ጥያቄ “ ጌታ ይገስጽህ ! ይህ ሰው (ፓ/ር ዳዊት ) በእግዚአብሔር የተቀባ ፤ የተለቀለቀ መንፈሳዊ ሰው ነው ፤ ስለዚህ ጌታ በቀባው ላይ እጅህን አታንሳ ፤ “ ተብዬ ተኮነንኩ ። ራሱ ዳዊትም ቢሆን “ ያቀረብከው ጥያቄ ለኔ የሚመጥን አይደለም “ በማለት ናቀኝ እንጂ ጆሮውን እንኳ ለጥቂት ለደቂቃ ያህል ልሰጠኝ አልፈለገም ፡፡ በዚህም ተግባሩ የኔን መብት ለራሱ አደረገ ፤ እኔን ግን ለውርደት ለጭንቀት ፤ ለሃዘንና ለኪሳራ ዳረገ። አሁን በዚህች ደቂቃና ሰከንድ ይህንን ደብዳቤ በማዘጋጅበት ሳምንት (ቀናት ) በሀገር ቤት ኢትዪኦጵያ ውስጥ ከዚህቺው ሴት ጋር አብረው ናቸው ። ጨርሰው ልላቀቁ ስላልቻሉ በረቀቀ ሚስጢር ያለሀፍረት አሁንም አብረው እንደተጣበቁ ናቸው ።

ፓ/ር ፡

ምናልባት “ድፍረት ፤ ንቀት ፤ ትዕቢት ወዘተ…የተባሉትን ዓረፍተነገሮች (ቃላት) ለምን ተጠቀምክ ? ለምንስ ደጋገምክ ? ትለኝ ይሆን ?በጣም የሚያናድደው ፤የሚያስገርመውና አሳፋሪው ነገር ይህ ግለሰብ ራሱን ነቢይ እያስባለ መገለጥ ቢጤ እያቀነባበረ የእግዚአብሔርን ቃል እየጠቃቀሰ “ የዓዞ እንቧ “ እንደተባለው የሀገራችን አባባል “ኢየሱስ ያድናል “ ወዘተ….በሚል ቋንቋ የዋሁን ህዝበ-እግዚአብሔር ፊት በእግዚአብሔር ፑልፒት ላይ እየተንጎራደደ መፈክር እያሰማ የትዳርን ክቡርነት ፤ የባልና ሚስትን ህጋዊ ግንኙነት (አብሮነት) ከፈጣሪ የሆነና የተቀደሰ ቃል ኪዳን መሆኑ እንደት ተሰወረበት ? የራሱን ሚስት እቤቱ አስቀምጦ በአፍላ ፍቅራችንና ጅምር ትዳራችን ወስጥ እንደ እርጎ ዝንብ ጥልቅ ብሎ ለምን ገባብን ?

ለነገሩማ ቀድሞውንም ቢሆን ሴራቸው ስላልገባኝ የእግዚአብሔር አገልጋዮች ናቸው በሚል አምኜ ቀረብኳቸው እንጂ እነሱ ግን ያኔም ቢሆን ማስመሰል በተሞላበት የህሰት ትንቢት አደንቁረውኝ ፤በመገለጥ አዋክበውና አጣድፈውኝ ለስውር ዓላማቸውና የግል ጥቅማቸው ማሟያ አቅደው ለይስሙላ ከአጠገባቸው ሊያስቀምጡኝ ፈለጉ እንጂ ያኔ ያላወቅኩት ቆይቼም ቢሆን በኋላ እንዳረጋገጥኩት ለ5 ዓመታት ያህል ዘልቆ የቆየ ግነኝነትና አሳፋሪ ቃል-ኪዳን ነበራቸው ።

በሀገራችን አባባል “ የአይጥ ምስክር ዲንቢጥ ናት “ እንደተባለው ካልሆነ በቀር እነዚያ ቢጤዎቹስ ቢህኑ “ እሱ ዳዊት የፈጸመብህ ድርጊት አግባብ ባይሆንም ጸጥ ፤ ለጥ ብለህ ተቀበልና ዝም በል ። አለበለዚያ ትቀሰፋለህ ፤ ወደ ሲኦል ትገባለህ፤ ለሳይጣን አሳልፎ ይሰጥሃል ፤ ትረገማለህ “ ወዘተ.. እያሉ አስፈራርተው ሲያሸማቅቁ ፤ በሌላ በኩል ደግሞ “ የሚናከብረውና በጌታ የተቀባ ፤የተለቀለቀ ፤በመገለጥና ጥበብ ብሎም የፈውስ ጸጋ ስጦታ አገልግሎቱ እጅግ የጠለቀ ፤ የመጠቀ ነውና የተደረገብህን ድርጊት ሁሉ አሜን ብለህ አርፈህ ኑር” በሚል ማባበል እኔን አታሎ ለማዘናጋት ለሃጥያት ሲተባበሩ ፤በሃሰት ሲመሰክሩ ፤ አንዳች ፈጣሪን ባይፈሩ ፤ለማንም ባይራሩ ፤ ለሃቅ ባይቆረቆሩ ፤ በእግዚአብሔርም ሳይጠሩ ለክብራቸው ፤ ለዝናቸው ፤ ለጥቅማቸውና ለእንጀራቸው ያንን ያህል በድርቅና ከተከራከሩ ትዳሬ ደግሞ ለኔ ከእንጀራና ሆድ የሚበልጥ ፤ ከዝና ፤ ከክብርና ጊዜያዊ ጥቅም ያለፈ ህይዎትና ኑሮዬ መሆኑን ለማወቅ እንዴት ተቸገሩ ?

ስለዚ ይህ መቼም “ በሰው ቁስል እንጨት ስደድበት “ እንዲሉ ንቀት ፤ ትዕቢት፤ ድፍረትና “ ነጌ በኔ” አለማለት ካልሆነ በቀር ሌላ አንዳችም ምክንያት ሊኖር አይችልም እንዳውም በኔ ቦታ ሆኖ ካዩት ከድፍረት ያለፈ ጭካኔ ነው እላለሁ ። እኔ ደግሞ ተበድዬ ፤ ተጎድቼ ፤ ተጠቅቼ ፤ ተደፍሬና ተንቄ ሽንፈትን አሜን ብዬ በውርደትና በሃዘን የተሞላ ህይዎት ለመኖር ስለማልፈልግ አንድ ስፍራ ላይ ባንድ ወቅት

ባንዴ መቋጨትና መቆረጥ አለበት ። ያንን ለማምጣት ደግሞ እስከ ህይዎቴ ፍጻሜ ድረስ ዋጋ ለመክፈል ዝግጁ ነኝ ፤ የእውነት አምላክ ፤የቅኖች ወዳጅ ፤ የምስኪኖች አለኝታ የሆነው ፈጣሪዬ ደግሞ ለአረመኔዎችና ለነውረኞች አሳልፎ ስለማይሰጠኝ ፤ ጥቃቴንም ስለማይወድ በሱ እየታመንኩ ላደርገው የወሰንኩትን በአርሱ ታምኜ እፈጽማለሁ ።

አዎን ከዚህ በላይ ያልኩት ሁሉ በኔ ላይ የተፈጸመ እውነት የሆነ ዓይን ያወጣ ጥርሱን ያገጠጠ ብልግናና በቃላት የማይገለጽ ከባድ በደልና ግፍ ነበር ። ዛሬ ዛሬ በየቦታው አፈ-ጮማ አተራማሽ መተተኛና ፈጣጣ ጋጠ-ወጥ ጮሌ ሁሉ የእግዚአብሔርን ቤት እያጥለቀለቀ የስንቱ ምስኪኖች ትዳር ደቀቀ ? አረ የፍትህ ያለህ ! የጽድቅ ያለህ ! የቅድስና ያለህ ! አለቅን ፤ ደቀቅን !! እባካችሁ ድረሱልን !!!

ለመሆኑ ትዳርን ማፍረስ ቤተክርስቲያንን ማፍረስ አይደለምን ? ለዚያውም የቤተእምነት መሪና አገልጋይ ሆኖ የንጹሃንን ትዳር እያረከሱ ፤ ቤተሰብን እያፈረሱ ቤተክርስቲያንን እያስወቀሱ “የተቀባ ፤የበቃ “ ወዘተ … አገልጋይ መሆን ይቻላል ? ትንቢት እየተናገሩ መገለጥ እየቀበጣጠሩ የትዳርን ክቡርነት እንዴት ዘነጉ ? ሚስት ለባል ፤ ባልም ለሚስት ብቻ መሆናቸውን ለማረጋገጥ ለነሱ ብቻ ሲባል ሌላ ነቢይ መቅጠር ( ልዩ መላዕክት ከሰማይ ማስመጣት ) አለብን ዎይ ? “እግዚአብሔር እንዲህና እንድያ ብሎሃል” እያለ ሌት ተቀን እየሰበከ እራሱ ግን ለምን አልኖረበትም ? ራሱ ልፈጽመው ያልቻለውን በጉልበት ልያሽክመን ለምን ይጥራል ?

ደግሞስ የኔ አንዲቷ ነጠላ ህይዎት (ነፍስ) ቤተክርስቲያን አይደለችምን ? የእግዚአብሔር መንፈስ ማደሪያ ፤ የክብሩም መገለጫ ቤተክርስቲያን አይደለሁም ዎይ ? ይህ ዓይኑን በጨው የታጠበ ደፋር ግለሰብ ህይዎቴንና ዕድሌን አበላሽቶ ደስታዬን ወደ ሃዘን ለውጦ ቤተክርስቲያንን ሊመራ ?ህዝብን ሊያገለግል ? “ It is not fair “ (ፍትሃዊና አግባብ አይደለም ) ፤ እሷስ ወ/ሮ ትግስት ብትሆን ልማደኛ ባትሆን ኖሮ ከበፊተኛው ስህተቷ ለምን አልታረመችም ? ከኔ በፊት ጀምሮ ነጋ ጠባ የትዳር ቀበኛና ጸር “Allergy “ (የፓስተሮች ቀማሽ ) ይመስል በበፊቱ ነውርና ስህተቷ ትምህርትም ሆነ ምክር ችግርና ግሳጼው ሁሉ መታረም ስገባት እንዴት እንደገና ለአግልግሎት በቃች ? ከኔ በፊት የነበራትን ትዳሯንም እንዲሁ በተመሳሳይ ተግባር ከሌላኛው ፓስተሯ ጋር በዝሙት ተጠርጥራ ትዳሯ እንደፈረሰ ከኔ በቀር ሁሉም የአከባቢያችን መንፈሳዊ መሪዎች የሚታውቁት የቅርብ ጊዜ ታሪክ ነው ። የራሷን ጽንስ (የኑሮ ጅምር ) አጨናግፋ (አኮላሽታ ) ፤ በተለያየ ጊዜና ወቅት ካገባቻቻው ባሎቿ መካከል አንዱንም እንኳ በአግባቡ ይዛ የራሷ ለማድረግ አቅቷት ሁሉንም በየተራ በየቦታው በአደባባይ እያፈረጠች ፤ እንደገና አዘናግታ ከሌሎች ተረኞች ጋር የምትከንፍ ያልሰከነች ሴት አሁን ከሰሞኑ ደግሞ ስፍራና ቤተክርስቲያን ቀይራና ለዋውጣ አዳዲሶቹን መሪዎች ጥብቅ ብላ የቤተእምነቱን ቁልፍ እንዴት ተረከበቻቸው ?

ለማስመሰልና ለጉራ፤ ብሎም ለዝና ብሎም ለድብቅ ዓላማ ካልሆነ በስተቀር የራሱን ቤት ያቃተው ሰው የእግዚአብሔርን ቤት ለመጠበቅና ለማገልገል እንዴት ተገባው ? ለማጭበርበር ካልሆነ በቀር የራሱን ጽንስና ራዕይ ገሎ የሰው ቤት ሄዶ የሌላውን ልጅ ተንከባክቦ ለማስተማር ቀርቶ ጉንጭ እንኳን ለመሳም ሃላፊነት የሚጣልበት ስበእና አለው ለማለት አያስችልም ።እንዲህ ዓይነቱ ሰው ካለ ራዕይ ለመጠበቅ ከቶ አይቻለውም ፤ ምክንያቱም እውነተኛ አገልግሎትና ታማኝነት ከራስ ቤትና ትዳር መጀመር ስለምገባው ። እውነተኛዋ የክርስቶስ ቤተክርስቲያን ካለች እንዲህ ዓይነቱን ዓይን ያዋጣ ድፍረትና ተራ ቁማር መዋጋት ተጋቢ ይመስለኛል ።

ምክንያቱም በኔ በኩል የችግሩ ሰለባ ከመሆኔም በላይ እንደ ባለ አዕምሮ ሳሰላስል እነዚህ እና ቢጤዎቻቸው ባለቤቱ የከደነውን ያለፈቃድ የሚከፍቱ ፤ አንዱ የገነባውን የሚንዱ ፤በፈጣሪ ስም ፤ በሃይማኖት ሰበብ ተገቢ ያልሆነን ተግባርን የሚሰሩ ፤ለማንም የማይራሩ ከስህተታቸው የማይማሩ ፤ የራሳቸውን ትተው የሰውን ሚስት ( ባል ) ለመቅመስ ሌት ተቀን የሚዞሩ ፤ ለከበረው ትዳርና ጤነኛ ፍቅር እንቅፋት ብቻ ሳይሆኑ ለሰሩት ጥፋትና ስህተት በንቀት ጆሮ ዳባ ብለው (ችላ ባይ ከመሆናቸው የተነሳ )ጉዳቴ ዕለት በዕለት ይበልጥ እየተሰማኝ ስለሆነ የሚወስነው ውሳኔ እየክፋ እንደመጣ ተገንዝቤያለሁ ።

በመሆኑም ስማቸው ከዚህ በላይ በተደጋጋሚ የጠቀስኳችው ግለሰቦች (ፓ/ር ዳዊትና ግብረ አበሩ ወ/ሮ ትግስት ) እንዲሁም ቢጤዎቻቸው በሰው ላይ በደልና ነውር እያደረሱ ፤የንጹሃንን ትዳር እያፈረሱ በእግዚአብሔር ቤትና በቅዱሳን መካከል መሽገው ፤ሃጥያታቸውን ሸሽገው ሚስኪኖችን አንገት እያስደፉ ፤ የሰላማዊ ኑሮን ጣዕምና ትርጉም እያጠፉ መላውን ቅድዱሳን በሃሜትና በአሉባልታ እያተራመሱ ቤተ-እምነቶችን መነጋገሪያ ፤ መሳለቂያ እያደረጉ መቀጠል ተገቢ አይደለምና ጉዳዩን ለህዝብ ሚዲያ እና ለመላው አብያተ-ክርስቲያናት ለማቅረብ ወደድኩ ።

አዎን ፤ በቃ ፤ የእግዚአብሔር ቤት ይህንን ከመሳሰለ የነውር ተግባር ከነዚህ ዓይነቶቹ አስመሳይ ነውረኞች ልጠራ ይገባል ፤እኔም ከእንግዲህ ጥፋተኛው ቅጣቱን እስኪቀበል ፤ ነውረኛው በነውሩ እስኪጸጸት ፤ እግዚአብሔርን ፤ ህዝቡንና ተበዳዩን ይቅርታ እስኪጠይቅ ፤ ቁስሌ እስኪጠገን ፤ህመሜ እስኪፈወስ ፤ ምናልባት ተመሳስለው እና ተደብቀው በየቦታው የተሸሸጉ ነውረኞች ካሉ ያጨለሙት

ተስፋዬ እስኪታደስ ፤ ሃላፊነት የጎደላቸው መንፈሳዊ ጀብደኞች ያኮላሹት ራዕዬ እስኪመለስ ፤ የጌታ ፈቃዱ ሆኖ በህይዎት እስካለሁ ይህንን ስድ አልለቀውም ።

ሌላው ቢቀር እንኳ የዚህን ጨዋ መሳዪ ተግባር ሰው ሁሉ ይስማውና ባላጌዎች ይፈሩበት ፤ ጥፋተኞች ይታረሙበት ፤ ትውልድ ይማርበት ፤ያፈለገው ንሰሃ ይግባበት ፤ዱሪዬዎች አደብ ይግዙበት ፤ ዝንጉዎች ይጠንቀቁበት ፤የተጎዳው አእምሮና መንፈሴ ይታደስበት ፤ እግዚአብሔር ይክበርበት ።

እንዲሁም ተመሳሳይ በደልና ግፍ በሰውር በቅዱሳን የግል ኑሮና ቤተሰብ ህይዎት ላይ እየተፈራረቀባቸው በአጓጉል ኋላ ቀርና በሃይማኖት ስም ማስፈራሪያነት ከደረሰባቸው በደልና ጥቃት ጋር ተሸማቀው “ታሪኬ ከበደለኝ ሰው ጋር አብሮ ከሚጋለጥ ጥቃቱን ተሸክሜ ፤የጎዱኝን ነውረኞች አበሳ ደብቄ ልኑር “ የሚሉት ሳይቀሩ ሌባውን ሌባ ፤ነውረኛውን ነውረኛ ፤ዋሾ አስመሳዩን ቀጣፊ ፤ወዘተ…እያሉ በድፍረት ተናግረው ለማጋለጥ ጉልበት ያግኙበት።

በሌላ በኩል ሰውዬው ( ፓ/ር ዳዊት ) ብልጣ-ብልጥ ፤ አስመሳይ ጮሌ ፤ ምላሱ ቅቤ ፤ልቡ ጩቤ ስለሆነ ፤የገነነ ዝና ፤ እውቅና ፤ ገንዘብና ብዙ ቢጤዎች ስላሉት ብቻ እኔው ተጠቅቼ ፤ፍትህ አጥቼ ፤ በቀሪ ዘመኔ ሁሉ ተቀጥቼ አልኖርምና ሃቀኛ ዳኛ ፤አመዛዛኝ ህሊና ፤ ከአድልዎ የጸዱ ፍትህን የሚያስከብሩ ፤ ለእግዚብሔርና ቤቱ የሚቆረቆሩ ፤ ህዝበ-እግዛብሔርን የሚያፈቅሩ፤ በጽድቅ የሚኖሩ ፤ለሚስኪኖች የሚከራከሩ ፤ነውረኛ ጥፋት ፈጻሚዎችን በድፍረት በመገሰጽ የሚመክሩ የሚያስተምሩ በፍቅር የሚገሩ ፤ ነውርንና እርኩሰትን የሚጸየፉ እውነተኛ የእግዚአብሔር አገልጋይ ዳኞች አሁንም በአምላኬ ቤት ልኖሩ እንደሚችሉ እርግጠኛ በመሆን ይህንን ጉዳቴን ፤ አበሳዬንና ገበናዬን ዘርዝሬ አቅርቤያለሁ ።

ፓ/ር፡

ይህንንም ሳደርግ አንተ ብቻ ሳትሆን ሌሎች የእግዚአብሔር ሰዎች ፤ የጌታ አገልጋዮች ፤መንፈሳዊ መሪዎችና መላው ቅድሳን ሁሉ “ እኛ በቦታው አልነበርንም ፤ አልሰማንም ፤ አላየንምና አንዳች ነገር ከቶ አያገባንም” ወዘተ… እንዳይሉ ይህንን ደብዳቤና የከዚህ ቀደሞቹን ዝርዝር ጉዳዮች የያዙ ኮፒዎችን ሁሉም በያሉበት አድራሻ በተከታታይ የሚልክላቸው (የማሰራጭ ) መህኑን አልሸሽግም ።

ለዚህም ዋና ምክንያቴ ኪሳራዬ ባይካስም ፤ጉዳቴ ስብራቴ ባይጠገንም ፤ ቁጭት እልሄ በርዶ ቁስሌ ባይፈወስም ትዳሬን እንደሆነ እስከመጨረሻው ያጣሁ፤ የፈራረሰ እና ያከተመለት ፤ የሞተ ነገር ቢሆንም እኔ ተጎድቼ ፤ተዋርጄ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ሌላው ትውልድ ዘላቂ መፍትሄና ያማያዳግም ትምህርት ያገኝበታል ብዬ በመገመት ነው ፤ አዎን ከተቻለ የኔ ትዳር ተኮላሽቶ ታሪኬም ተበላሽቶ ከእንግዲህ ግን የምስኪን ወገኖቼን ትዳርና ኑሮ ከሚያኮላሹና ከሚያበላሹ አገልጋይ ተብዬ መንፈሳዊ ዱሪየዎች ለመታደግ ነው።

ፓ/ር ፡ እጅግ በጣም የማከብርህ ትልቅ የእግዚአብሔር አገልጋይና መሪ ነህ ። ፓስተሬ እንደ መሆንህ መጠን በአከባቢዬ አንድ የእግዚአብሔር ሰው የሚለው እና የጉዳዬን ዝርዝር ታሪክ በቅርበት የሚያውቅ ካንተ የበለጠ ከእግዚአብሔር በቀር ሌላ ማንም የለም ።

ከመነሻው እስከሁን ያለውን ታሪኬን ከሞላ-ጎደል ታውቀዋለህ ፤ በተለይም ጉዳቴን ፤ ስብራቴን ፤ሃዜኔና እንባዬን ፤ እንዲሁም ጥልቅ ቁጭቴን መገመት ከቶ አያቅትህም ብዬ አስባለሁ ። ስለሆነም ከዚህ ቀደም ከአንዴም ሁለቴ በኛ ጉዳይ እንባህን ስታፈስ ደጋግሜ አይቸሃለሁ ።በሌሎች ቅዱሳን ዘንድም ቢሆን የነዚህ ነውረኞች ነውርና ቀልድ ከማንም የተሰወረ አይደለም ፤ ያለንበት ወቅት ከምንጊዜውም በለይ በእርኩሰትና በክፋት የተሞላ ሆኗል ፤ ክህደት በመብዛቱ ቅጥፈት ነግሶ ዘመኑ እጅግ ከባድ ሆኖብናል ።

ስለዚህ እውነት ታፍኖ ሃቅ በመታነቁ ምክንያት ፍትህን አስከብሮ ለጽድቅ የሚፈርድ ዳኛ ይቅርና የቅርብ የሆነ ታማኝ ጓደኛ የታጣበት አስደንጋጭ ወቅት ላይ ደርሰናል። እኔ ያለእግዚአብሔር በቀር ሃብት ፤ ዘመድ፤ ወገንና ደጋፊ የለኝም ።

በዚህ ቁርጥና ፈታኝ ወሳኝ ወቅት አንተ ግን እንደ አባት ፤ የእምነት ሰው ፤ የቤተከርስቲያን መሪና የህዝብ አገልጋይ የመፍትሄ ምክርህ ፤ እገዛህ ፤ አስተያየትና ውሳኔህ ምንድን ነው ?

በተጨማሪም የተፈጸመብኝ በደል ፤ ግፍና ጥቃት ዘርዝሬ ከላይ በጠቀስኩት መሰረት ለሚዲያዎችም ጭምር ለማሰራጨት የወሰንኩ መሆኔን በክብሮት እየገለጽኩ ከፈጣሪዬና ካአንዲት ነፍሴ በቀር አንዳች ለሌለኝ ለኔ ለብቸኛውና ምስኪኑ ሰው አሁንም እንዲትጸልይልኝ ጭምር በጌታ አደራ እላለሁ ።

በጌታ እወደሃለህ

እጅግም አከብርሃለሁ

እግዚአብሔርና ቃሉ ብቻ እውነትና ትክክል ናቸው !

ከእንግዲህ በዘመኔ ሁሉ ማንንም አላምንም !!

እውነት ብትቀጥን እንጂ ጨርሳ ተበጥሳ አታውቅም !!!

ግርማ ዱሜሶ

Email; gelgela09@yahoo.com

ግልባጭ ፡

ለኢትዮጵያ ወንጌላዊያን አብያተ ክርስቲያናት በሙሉየእግዚአብሔር ቅዱሳን ሁሉ በያሉበትአበሻ ነክ ለሆኑ የኢትዮጵያዊያን ሚዲያዎችና ድህረ-ገጾች በሙሉ ።

Wednesday, May 13, 2015

I.S የተባለው ሽብርተኛ ቡድን አቀንቃኝ ኢትዮጵያ ውስጥ አለ!

በደቡብ ክልል በስልጤ ዞን ተደጋጋሚ የሃይማኖት ጥቃት ሲፈፀም ቆይቷል። ችግሩ እየተባባሰ እንጂ እየቀነሰ ሊሄድ አልቻለም። የኦሮቶዶክስ እምነት ተከታዮች እየተሰቃዩ ነው። ቤተ ክርስቲያናቸው ተቃጥሏል። የግለሰቦች ንብረት ወድሟል። "ሀገሩን ለቃችሁ ካልሄዳችሁ እንፈጃችኋለን"ማለት ከተጀመረ ሰነባብቷል። የመከራውን ገፈት ቀማሾች ለአቤቱታ በሄዱበት መንግስታዊ እርከን ሁሉ የሚጠብቃቸው ሹም ራሱ የሽብር አስፈጻሚ አካል ነውና "ከሚገድሏችሁ ለቃችሁ ሂዱ" የሚል ምላሽ እየሰጡ ይገኛሉ።
ከእግዚአብሔር በታች የሕዝብ ከለለሰ መንግሥት ነው። ሕግና መንግሥት ባለበት ሀገር ሕዝብ የመኖር ዋስትናውን በአሸባሪዎችና ለሽብርተኞች ከለላ በሚሰጡ አመራሮች ህልውናውን ሊያጣ አይገባም። ኢህአዴግ ለእንደዚህ ዓይነት ተግባርና አመራር ትእግስት ሊኖረው እንደማይገባ አበክረን እንጠይቃለን። " ሳይቃጠል በቅጠል" እንዲሉ አፋጣኝ እርምጃ በመውሰድ የህዝብ አለኝታነቱን ሊያሳይ ይገባል። ሕዝቡ የድረሱልን ጥሪውን በደብዳቤ አቅርቧል።
" የመንግሥት ያለህ!!!"

Friday, May 8, 2015

የዘንድሮው የግንቦቱ የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባዔ ቶሎ ተጠናቀቀ።

ለወትሮው ብዙ አጀንዳ ቀርጾ ረጅም ቀናት ይወስድ የነበረው የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባዔ ከወትሮው በተለየ ሁኔታ በጥቂት ቀናት ውስጥ መጠናቀቁ ተሰምቷል።
በምክንያትነት ተወስዷል ተብሎ ከውስጥ አዋቂ ምንጮች የቀረበው መረጃ እንደሚያስረዳው የ2007ቱ ሀገር አቀፍ የምርጫ  ሁኔታ ሲሆን የጉባዔው ቀናት መርዘም ከምርጫው ጊዜ ጋር እንዳይደራረብና በጉባዔው ሊነሱ የሚችሉ ሰፊ ክርክሮች በመራጭነት በተመዘገቡ የቤተ ክርስቲያኒቱ ተከታዮች ላይ ሊፈጥር የሚችለው ተጽእኖ ቀላል ባለመሆኑ በአስቸኳይ ጉዳዮች ላይ ብቻ በመነጋገር ሌሎች አጀንዳዎችን ለማሸጋገር መገደዱን ለማወቅ ተችሏል።
  ከዚሁ በተጨማሪ ለጉባዔው ሰፊ አጀንዳዎች ለቀጣይ ጉባዔ መሸጋገር  በምክንያትነት ተያይዞ የቀረበው ጉዳይ በጥቅምቱ ጉባዔ ላይ በቅዱስ ሲኖዶስ የተላለፉት ብዙ ውሳኔዎች በአፈጻጸም ድክመት ተወዝፈው ስለቆዩ ለአፈጻጸሙ ምክንያት የሆነው ጭብጥ እንደሚያስረዳው  ጉዳዩ ቢነሳ ለሰፊ ክርክርና ጭቅጭቅ ስለሚያበቃ ጊዜ ወስዶ ለማየት የጥቅምቱ ጉባዔ በፓትርያርኩ መመረጡን ተያይዞ የደረሱን መረጃዎች ያስረዳሉ።
  በአባ ማቴዎስና አባ ሉቃስ ተወዝፎ ምንም ያልተነካው የሲኖዶስ ውሳኔዎች አካል የሆነው ጉዳይ ማኅበረ ቅዱሳን የእስከዛሬ ገቢና ወጪውን በቤተክርስቲያኒቱ ባለሙያዎች የማስመርመር፣ በህጋዊ የቤተክርስቲያን ሞዴል መጠቀም፣ ማኅበሩ በሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ስር ሆኖ በየአመቱ በሚታደስ አዲስ ደንብ እንዲተዳደር ማድረግና ያለውን ሀብትና ንብረት ማስመዝገብን የተመለከቱ ውሳኔዎች በጭራሽ እስካሁን አለመነካታቸውንና በሁለቱ ጳጳሳት ከለላ ስር ውሳኔው ተዳፍኖ መቆየቱ ይነገራል። ቅዱስ ፓትርያርኩ አጽንኦት ሰጥተው ሲናገሩ የነበረው የማኅበሩ ልቅ እንቅስቃሴ ተወስኖ በተሰጠው ምህዋር ላይ ብቻ እንዲንቀሳቀስ  የሚያደርገው አዲስ የመተዳደሪያ ደንብ እንዲቀረፅ ብዙ የተናገሩለት በጳጳዳቱ ዳተኝነት ጭራሽ የታሰበበት አይመስልም።
 ይልቁንም (የማኅበረ ቅዱሳን ሲኖዶስ) አባላት የሆኑት አባ ማቴዎስ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ሥራ አስኪያጅ: አባ ሉቃስ የሲኖዶሱ ፀሐፊ፣ አባ ቀሌምንጦስ የሀገረ ስብከቱ ሊቀጳጳስ የያዙትን ቁልፍ ቦታ ለማኅበረ ቅዱሳን በሚጠቅም መልኩ ለማከናወን ቢጥሩም በፓትርያርኩ እምቢ ባይነት ባለመሳካቱ ወጣቶችን በማስተባበር በሽፋን ባቀረቡት አቤቱታ እንደተነገረው በቀጥታ ፓትርያርኩን በመወንጀል አቡነ ጳውሎስ ላይ የተደረገውን ዘመቻ ለማስቀጠል ተዘጋጅተው የነበረ ቢሆንም የዘመቻ ጽሁፍ ተቀባይነት ከማጣቱም በላይ አባ ቀሌምንጦስን ፓትርያርኩ እንደገሰጿቸው ታውቋል።  ይህን ዘመቻ በይደር ለጥቅምት በማቆየት በማኅበረ ቅዱሳን ላይ የተላለፉት ውሳኔዎች ሊታዩ የሚችሉት የሰንበት ት/ቤት ወጣቶች ያቀረቧቸው ጠያቄዎች ምላሽ ሲሰጣቸው ብቻ መሆን እንዳለበት ዱለታው የተጠናከረ ሲሆን ከዚህ ዱለታ ጀርባ ሌሎች ጳጳሳትም እንዳሉበት ተያይዞ ይነገራል።
 የማኅበረ ቅዱሳን ቅምጥ ኃይል የሆነው የወጣቶቹ ኅብረት ለአደጋ ጊዜ እንደሽፋን የሚያገለግል ኃይል ሲሆን በቀጥታ የማኅበሩ አባል ጳጳሳትንና ማኅበሩን ከተጠያቂነት ለማዳን ለሽፋን ያገለግላል።
በወጣቶች ደም ለመነገድ መሞከር ወንጀል ነው።

Sunday, April 26, 2015

ኢትዮጵያ ውስጥ የተዳፈነ አክራሪነት አለ!

ወደድንም ጠላንም ኢትዮጵያ ውስጥ በእምነት ተከባብሮ የመኖር የቆየውን ልምድ በተቃራኒው የሚፈታና የሚመለከት የፍጅት፤ የእልቂት፤ የሁከትና ኢስላማዊ መንግሥት የማቋቋም የተዳፈነ አክራሪ ኃይል አለ። ይህንን ጉዳይ ጠበቅ አድርገን መናገራችን እርስ በእርስ አለመተማመንን እንዲኖር ሳይሆን በመሬት ያለውን እውነታ ደብቀን «የኢስላሚክ ስቴት ሽብርተኛ ቡድን እኛን አይወክለንም» የሚለው ወቅታዊ መፈክር የችግሩን አደገኛነት ስለማይለገልጽ ላይ ላዩን ማውራቱ ለአብሪነት በቂ መልስ መሆን ስለማይችል ብቻ ነው። በተለይ መንግሥት ከቀበሌ አንስቶ በሀገር አቀፍ ደረጃ ሕዝቡን እያወያየ ያለውን የአክራሪ ኃይል በተለይም ወጣቱን በማሳተፍ ስር ነቀል መፍትሄ ካልሰጠበት ውሎ አድሮ አደጋውን መቀልበስ ከማይቻልበት መድረሱ አይቀርም። ይህንን ሐቅ ከሚያረጋግጡልን ማስረጃዎች አንዱ «ጀማል ሀሰን አሊ ይመር» የተባለ ከሙስሊም ቤተሰብ የተገኘ ኦርቶዶክሳዊ፤ በሙስሊም ቤተሰቦቹና ጓደኞቹ መካከል ያለውን ችግር ከተወለደበት መንደር ባሻገር እየተከሰተ ያለውን የአክራሪነት አደጋ በዓይን ምስክርነት እንዲህ ያወጋናል።

ሦስት መልዕክቶች አሉኝ!
መልዕክቶቹም ክርስቲያኑንና ሙስሊሙን ኅብረተሰብ እና መንግሥትን ይመለከታሉ፡፡

መልዕክት አንድ-ለሙስሊም ወገኖቻችን፡-በፎቶው ላይ በቀኝ በኩል ያለው የሥጋ ወንድሜ "አህመድ ሀሰን" ሲሆን በግራ በኩል ያለሁት ደግሞ እኔ ጀማል ሀሰን ነኝ፡፡ ነገር ግን ስመ ጥምቀቴ ገብረ ሥላሴ ነው፡፡ ሁለቱ ሴቶች ደግሞ ወላጅ እናቴና አኅቴ ሲሆኑ ከእኔ ጋር በልጅነት የተነሳው ነው፡፡ ሙስሊም የሆነው የሥጋ ወንድሜ አህመድ ከደቡብ ወሎ ወደ አዲስ አበባ እኔን ክርስቲያን ወንድሙን ሊጠይቀኝ መጥቶ 3 ሳምንት እኔ ጋር ከርሞ ከሄደ ዛሬ ገና 8ኛ ቀኑ ነው፡፡
ጁምዓ ጁምዓ አህመድን አንዋር መስጊጂድ አድርሼው እኔ ራጉኤል ቤተ ክርስቲያን እገባ ነበር፡፡ የሙስሊም ሥጋ ቤት ሄደን ገዝተን እቤት ሄደን እኔው ራሴ ሠርቼ አህመድ ሲመገብ ነው የቆየው፡፡ እኔ ደግሞ አባቴን ሀሰን ዓሊንና ሌላውንም ሙስሊም ቤተሰቤን ልጠይቅ ወሎ ስሄድ ለብቻዬ በግ ያርዱልኛል፡፡ በአጠቃላይ ከእኔም ቤተሰብ አልፎ ወሎ ስሄድ የማየው የክርስቲያኑና የሙስሊሙ ፍቅርና ተቻችሎ መኖር እንዴት ያስቀናል መሰላችሁ!!! ቤተ ክርስቲያን ሲሠራ ሙስሊሞቹ በገንዘብም በጉልበትም ሲረዱ በዓይኔ ተመልክቻለሁ፡፡ መስጂድም ሲሠራ ሕዝበ ክርስቲያኑ አብሮ ከሙስሊሞች ጋር ሠርቷል፡፡
ነገር ግን ይህ እጅግ ያስቀና የነበረው የክርስቲያኑና የሙስሊሙ ፍቅርና መተሳሰብ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እየደበዘዘና መጥፎ ጥላ እያጠላበት መጥቷል፡፡

ባለፈው መስከረም ወር ላይ ግሸን ማርያም ደርሼ በዚያው ቤተሰቦቼን ጠይቄ እስከ ቦረና አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫና አባ ጽጌ ድንግል ገዳማት ድረስ በእግሬ ለ7 ሰዓት ተጉዤ ሄጄ ነበር፡፡ አጎቴ ሼህ እንድሪስ ምን አሉኝ መሰላችሁ? "እናንተ ከከተማ የምትመጡ ልጆቻችንኮ ልታስቀምጡን አልቻላችሁም" አሉኝ፡፡ ሼኹን ለምን እንዲህ እንዳሉ ስጠይቃቸው ወደ ዐረብ ሀገራት ሄደው የተመለሱ የሙስሊም ወንዶች ልጆቻቸው ጉዳይ በጣም እንዳሳሰባቸው ነገሩኝ፡፡ ምክንያቱም ሁሉም ከዐረብ ሀገራት የተመለሱት ልጆቻቸው በዚያ በሰፈራቸው ክርስቲያኖች መኖር የለባቸውም የሚል ጽኑ አቋም አላቸው፡፡ ዕድሜ ጠገብ ቃልቻዎችንና ሼኾችን "እናንተ ሙስሊም አይደላችሁም" ይሏቸዋል፡፡ የዋሐቢዝምን ጽንፈኛ አቋም ካላራመዱ ማለትም ከክርስቲያኖች ጋር ቡና ከጠጡና በችግርና በደስታ ከተረዳዱ ሙስሊም እንዳልሆኑ ይነግሯቸዋል፡፡ ወጣቶችን እየሰበሰቡ ጥላቻን ይሰብኳቸዋል፡፡ ሲመክሩ ውለው የሚያድሩት እስልምናን በኃይል ስለማስፋፋትና ክርስቲያኖችን ስለማጥፋት ነው፡፡ ዕድሜ ጠገብ ቃልቻዎቹና ሼኾቹ ደግሞ በዚህ ፈጽሞ አይስማሙም፡፡ "እንደቀድሞው ተዋደንና ተቻችለን እንኖራለን" የሚል ጽኑ አቋም አላቸው፡፡ አጠቃላይ የወጣቶቹ ሙስሊሞች ሁኔታቸው ሼህ እንድሪስንም ሆነ ሌሎቹን ታላላቅ ሽማግሌዎች በጣም አሳስቧቸዋል፡፡ እነሱ ካለፉ በኃላ ተረካቢውና መጪው ትውልድ ያስፈራቸዋል፡፡

ሼኹ እውነታቸውን ነው፡፡ እኔም በዘዴ ቀርቤ የዋሐቢዝምን ጽንፈኛ አቋም የሚያራምዱ ሙስሊም ወጣቶችን ሳናግራቸው የሰጡኝ መልስ እውነትም አስፈሪ ነው፡፡ "ክርስቲያኖችን እናጠፋለን ኢትዮጵያንም እንገዛለን" የሚል ጽኑ አቋም አላቸዉ፡፡ እኔ በዚያው ቦረና ወግዲ አባ ጽጌ ድንግል ገዳም ስሄድ ያየሁትን ልንገራችሁ፡፡ መነኮሳቱ ከገዳሙ ወጥተው ገበያ እንኳን መሄድ አይችሉም፡፡ ሲሄዱ ጠብቀው መንገድ ላይ በድንጋይ ይመቷቸዋል፡፡ ሴቶቹ መነኮሳት ብቻቸውን ወደ ወንዝ ወርደው ውኃ መቅዳት አይችሉም ምክንያቱም የመደፈር አደጋ ላይ ይወድቃሉ፡፡

ውድ ሙስሊም ወገኖቻችን፡- ሰሞኑን የISIS ጽንፈኛ ኢስላማዊ አሸባሪ በክርስቲያኖች ላይ የፈጸመውን እጅግ ዘግናኝ ድርጊት ከልብ አውግዛችሁ ቂርቆስ ሰፈር የታረዱት ሰማዕታት ቤተሰቦች ዘንድ መጥታችሁ አብራችሁን ስታለቅሱ አይቻለሁ፡፡ ምስጋናዬንና አድናቆቴን ሳልገልጽ አላልፍም፡፡ ግን በተቃራኒው ዋሐቢዝምን የሚያራምዱ ልጆቻችሁ በዘመናዊው መገናኛዎች አማካኝነት "እሰይ ታረዱ" ሲሉ እያየናቸውና እየሰማናቸው ነው፡፡ በየፌስቡኩ አስተያየታቸው ላይ አንድ ሙስሊም እንኳን "አላህ ነፍሳቸውን ይማር" ብሎ ምኞቱን የገለጸ የለም፡፡ ከተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች ባገኘነው መረጃ መሠረት "ሀዘናችንን በጋራ እንግለጽ ድርጊቱንም በጋራ እናውግዝ" ተብሎ ለሁለቱም እምነቶች በየዩኒቨርሲዎቹ ግቢ ውስጥ በተዘጋጀው መርሀግብር ላይ ሙስሊም ተማሪዎች አልተገኙም፡፡ ይህ ምን ማለት እንደሆነ መገመት ይቻላል፡፡ እኔ ግን የድርጊቱ ደጋፊዎች መሆናቸውን ነው የምረዳው፡፡ በየዩኒቨርሲዎቹ ግቢ ውስጥ ሙስሊሙና ክርስቲያኑ ተማሪ በጠላትነት ነው የሚተያየው፡፡ ይህንንም ከዩኒቨርሲዎች የወጣን ሁላችን በተግባር አይተነዋል፡፡ በአንድ ትልቅ የመንግሥት መ/ቤት ውስጥ አብሮኝ የሚሠራ ሙስሊም ጓደኛዬም ከዚህ በፊት እነ አልቃይዳ እውነኛዎቹ ሙስሊሞች እነርሱ መሆናቸውን ሽንጡን ገትሮ ሲከራከረኝ ነበር፡፡

ወደ መፍትሄው እንምጣ........
ውድ ሙስሊም ወገኖቻችን! እንደቀድሞው እንዳማረብን እንዴት ተከባብረንና ተዋደን እንኑር??? መፍትሄው ቀላል ነው፡፡ ይሄኛው መልዕክት መንግሥትም ይመለከታልና ባለሥልናት ሁላችሁ ስሙ፡፡ መንግሥት እንኳን ለህልውናህ ስትል ሳትወድም ቢሆን በግድ ትሰማለህ ንጹሐን ሙስሊም ወገኖቻችን ግን የድሮውን መዋደድና መተሳሳብ ብሎም መቻቻል እንዳለ ይዘን መቀጠል ከተፈለገ ለጉዳዩ አጽንኦት በመስጠት ችግሩን በግልጽ መነጋገር አለብን፡፡
የችግሩ የመጀመሪያው መፍትሔ ችግሩ መኖሩን አምነን እንቀበል! የአጎቴ የሼህ እንድሪስ ሀሳብ በጣም ትክክል ነው፡፡ ዋሐቢዝምን የሚያራምዱ "አዳዲስ ዘመነኛ ሙስሊሞች" የነገዎቹ አልቃይዳዎችና ISISዎች ናቸው፡፡ እኔ በዚህ 101% እርግጠኛ ነኝ! በየመስጂዱ ውስጥ ለወጣቶቹ ሙስሊሞች ምን ዓይነት ሥልጠናና ትምህርት እንደሚሰጥ እኔው ራሴ እምነቱ ውስጥ በነበርኩበት ወቅት ያየሁትንና የተማርኩትን ነው እየመሰከርኩ ያለሁት፡፡ መንግሥት ሆይ! ንጹሐን ሙስሊም ወገኖቻችን ሆይ! ችግሩን በየሚዲያው በቀን ሺህ ጊዜ "ISIS እስልምናን አይወክልም" በሚል ፉከራና ሽለላ ችግሩን መቅረፍ እንደማይቻል እመኑ፡፡ ጥቂት የማይባሉ የነገዎቹ አልቃይዳዎችና ISISዎች በሀገራችን ሞልተዋል፡፡
በኢትዮጵያ ውስጥ የሩቁን ትተን በቅርቡ በጂማ፣ በስልጤ፣ በኢሉባቡርና በሌሎቹም ክልሎች ጽንፈኛና አክራሪ ሙስሊሞች ቤተ ክርስትያን ውስጥ እየገቡ በጸሎት ላይ የነበሩትን ክርስቲያኖች በገጀራ ሲቆራርጧቸው ያኔ isis አይታወቅም ነበርኮ! "isis የትኛውንም ሃይማኖት አይወክልም" የሚል ባዶ ፉከራ እያሰማችሁ የምታጃጅሉን ለምንድነው? ክርስቲያኖችን በገጀራ እየቆራረጠ ቤ/ክንን ሲያቃጥል ደነበረው ያ ሁሉ ኢትዮጵያዊ ሙስሊም ከነ ገጀራው ማንን ነበር የሚወክለው? የዛኔ የትኛው ሙስሊም ነው በአደባባይ ወጥቶ እኛን አይወክልም ያለው? የisis ዘግናኝ ድርጊት እኛ ሀገር ከተጀመረ ቀየኮ!
isis ዛሬ የፈጸመው አረመኒያዊና እጅግ ዘግናኝ ተግባር በዓይነቱም ሆነ በይዘቱም ከዚ በፊት በሀገራችን ከተፈጸመው ጋር ምንም ልዩነት የለውም። "እውነኛዎቹ ሙስሊሞች እነ አልቃይዳ ናቸው" ያለኝ ያ የመንግሥት መ/ቤት ጓደኛዬ ሁኔታዎች ቢመቻቹለትና አጋጣሚውን ቢያገኝ እኔንም አጋድሞ እንደሚያርደኝ እርግጠኛ ነኝ፡፡ በየገጠሩ ያሉ ጽንፈኛ አክራሪዎች ሁኔታዎች በተመቻቹላቸው ጊዜ ምን እንዳደረጉ አይተናል፡፡
ኢትዮጵያው ውስጥ የሚገኙ ሙስሊም መምህራን በተለያየ ጊዜ የአመጽ ቅስቀሳ ሲያደርጉ የተቀረጸውን ቪዲዮ ማየት እንችላለን፡- "በዚህ ማንም ክርስቲያን አንገቱን ቀና አድርጎ አይሄድም፡ በሜንጫ ነው አንገታቸውን የምንላቸው" "ኪዳነ ምሕረት ቤ/ክንን እናቃጥላታለን..." ሲሉ የነበሩ አመጸኛ አክራሪዎች አጋጣሚውን ቢያገኙና ሁኔታዎች ቢመቻቹላቸው የተናገሩትን ተግባራዊ ማድረጋቸው አይቀርም፡፡ ደግሞም ተግባራዊ አድርገውት አሳይተውናል፡፡

እውነታውን አንሸፋፍን! የመጀመሪያው መፍትሔ ይሄ ነው፡፡ ጉዳዩ የማይመለከታችሁ ንጹሐን ሙስሊም ወገኖቻችንና መንግሥት ችግሩን አምናችሁ ተቀበሉና ወደ መፍትሔው በጋራ እንምጣ፡፡ ዝም ብሎ በአፍዓ ብቻ አክራሪነትን እንቃወም ማለት ብቻ ሳይሆን በሀገራችን ያሉ አክራሪዎቻችንን በተግባርም እንቃወማቸው፡፡ የጽንፈኛዎቹን እንቅስቃሴዎቻቸውን ተከታትሎ ለሕዝብ ይፋ ማድረግና ግለሰቦቹንም ለይቶ መረጃ አጠናክሮ ለሕግ ማቅረብ ቀጣዩ ተግባር ይሁን፡፡ ንጹሐን ሙስሊም ወገኖቻችን ይህን ማድረግ ስትችሉ ነው isis እንደማይወክላችሁ የምናውቀው፡፡ "isis እስልምናን አይወክልም" ስትሉን ሳይሆን "እኛ የ isis ን ድርጊት እንጸየፋለን" ስትሉን ነው የምናምናችሁ፡፡ እናንተ የጽፈኛ አሸባሪዎችን ድርጊት በጽኑ የምትቃወሙ መሆናችሁን በተግባር አሳዩን እንጂ ጽፈኛ አሸባሪዎቹን እስልምናን አይወክልም አትበሉን፡፡ ጽንፈኛ ኢስላማዊ አሸባሪዎቹ "ክርስቶስን ክዳችሁ አላህን ብቻ አምልኩ..." እያሉ ነው ሰማዕታት ወንድሞቻችን ያረዱብን፡፡ ሰያፊዎቹ ቢያንስ እነሱ ለራሳቸው ሙስሊሞች ናቸው እናንተ በግድ "ሙስሊም አይደላችሁም እስልምናንም አትወክሉም" ልትሏቸው አትችሉም፡፡ እነሱ ሃይማኖት ለአላህ ብቻ እስከሚሆን ድረስ ነው እየገደሉና እያረዱ ያሉት፡፡

ስለዚህ ንጹሐን ሙስሊም ወገኖቻችን ፖለቲካኛውን አስተሳሰብና አነጋገር ተውትና በጎረቤትኛና በዘመድኛ አስተሳሰብ እንተሳሰብ፡፡ በፍቅርና በመውደድኛ ቋንቋ እንነጋገር፡፡ "isis እስልምናን አይወክልም" ስትሉን ሳይሆን "እኛ የ isis ን ድርጊት እንጸየፋለን" ስትሉን ነው የምናምናችሁ፡፡ እናንተ የጽፈኛ አሸባሪዎችን ድርጊት በጽኑ የምትቃወሙ መሆናችሁን በተግባር አሳዩን እንጂ ጽንፈኛ አሸባሪዎቹን እስልምናን አይወክልም አትበሉን፡፡ የድርጊቱ ፈጻሚዎች ተጸየፏቸውና ተቃውሞአችሁን አብራችሁን ሆናችሁ በተግባር አሳዩን፡፡ አቤት ያኔ ፍቅራችን ሲደረጅ........

መልዕክት ሁለት-ለክርስቲያን እኅት ወንድሞቼ፡- ከዚህ ከሊቢያው ሰማዕታት ወንድሞቻችን ምን ተማርን??? የትኛውም ሐዋርያ በክብር ዐረፈ የሚል ገድል የለውም፡፡ ሁሉም ሐዋርያት "ተዘቅዝቆ ተሰቀለ፡ አንገቱን በሰይፍ ተቆረጠ፡ በእሳት ተቃጠለ፡ ቆዳው ተገፈፈ..." የሚል ገድል ነው ያላቸው፡፡ ሰማዕታት ሁሉ በሐዋርያት መንገድ ተጉዘው ሰማዕትነታቸውን ፈጸሙ፡፡ በስንክሳሩ መጽሐፍ ላይ ስናነበው የኖርነውን የሐዋርያትንና የሰማዕታትን ታሪክ ወንድሞቻችን ዛሬ በዚህ በ21ኛው ክፍለ ዘመንም በተግባር አሳዩን፡፡ ወንጌልን በተግባር ሰበኩልን፡፡ ክርስቶስን ክደው የአንገታቸውን ክር በጥሰው ቢሆን ኖሮ ማንም አይነካቸውም ነበር፡፡ ሦስት ቀን ሙሉ በረኀብ አሠቃይተዋቸው እስከ መጨረሻው ድረስ በጽናት ቆይተው አንገታቸውን በጸጋ ለሰይፍ ሲሰጡ ስናይ ከጥልቅ ሀዘን ባለፈ ምን ተሰማን በእውነት!?
እኛስ በቃል ሰይፍ ብቻ ታርደን የክብር ባለቤት መድኀኔዓለም ክርስቶስን የካድን ስንቶቻችን እንሆን?
አንድ ዐይን ያለው ሰው በአፈር አይጫወትም፡፡ ሐዋርያው "ለቅዱሳን አንድ ጊዜ ፈጽሞ ስለተሰጠች አንዲት ሃይማኖት እንድትጋደሉ እየመከርኋችሁ እጽፍላችሁ ዘንድ ግድ ሆነብኝ" ያለው ለዚህ ነው፡፡ ይሁ 1፡3፡፡ ሞት እንደሆነ ሰው በዝሙት ይሞታል፡ በመኪና አደጋ ይሞታል፡ በትንታ ወይም የሚበላው እህል አንቆትም ይሞታል፡፡ ምን!... በኃጢአት ላይ ኃጢአት ለመጨመርና እህል ለማመላለስ ተኖረ አልተኖረ!....፡፡ ክርስቶን እንዲህ ሞቱን በሚመስል ሞት አክብሮ ሰማዕት ሆኖ መሞት ምንኛ መታደል ነው!!! ሰማዕታት ወንድሞቻችን ዛሬ ክርስቶስን ትንሣኤውን በሚመስል ትንሣኤ ተባብረውት በእቅፉ ውስጥ ናቸው፡፡ ክርስቶስን በሞታቸው ያከበሩት የሰማዕታቶቻችን በረከታቸው ይደርብን በእውነት!!! አባቶችን በገዳም ሰማዕታትን በደም ያጸና አምላክ እኛንም በሃይማኖት በምግባር ያጽናን!

ታስታውሳላችሁ አይደል አሁን በወጣቱ ዘንድ ያለውን የክርስትናውን መነቃቃት የተፈጠረው በበሻሻ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ በተሰየፋ ክርስቲያኖች አማካኝነት ነው፡፡ ዛሬም እነዚህ 30 የሊቢያ ሰማዕታት ወንድሞቻችን የለኮሱት የእምነት ችቦ በእያንዳንዳችን ልብ ውስጥ እየተቀጣጠለ ክርስትናችንን በዓለም ዙሪያ አጠንክሮ እንደሚያስፋፋው ሳይታለም የተፈታ ነው!!! ነገር ግን አካሄዳችን ሁሉ በፍጹም ፍቅርና በትዕግስት ይሁን፡፡ ለሙስሊም ወገኖቻችን ፍቅር እንስጥ፡፡ እንደቀድሞው ተዋደንና ተቻችለን እኑር፡፡ በፍቅር የሚሞትለት አንጂ በጥላቻ የሚገደልለት አምላክ እንደሌለን ፍቅር ሰጥተን እናሳያቸው፡፡ በቀል የእኔ ነው ያለ አምላካችን ለእኛ ግን "ጠላቶቻችሁን ውደዱ" የሚል መመሪያ ነው የሰጠን!!!

መልዕክት ሦስት-ለቤተ ክህነትና ለቤተ መንግሥት፡- እግዚአብሔር አምላክ ከሁለቱም ወገን በአንድ ጊዜ ቀንድ ቀንዱን ነቅሎ ሲወስድ አይታችሁ ያልተማራችሁ አሁን ሰው ነግሯችሁ ልትሰሙ ስለማትችሉ ምንም አልልም! ዝምምምም.....

ohhh ሙስሊሞች አንድ የረሳኃት መልዕክት ትዝ አለችኝ! ጀማል የሚባል ልጅ አብሮ ተሰይፏል እያላችሁ ነው መረጃ ግን አልተገኘም፡፡ እስቲ ቤተሰቦቹን ጠቁሙንና አብረን ሄደን እናስተዛዝን??? እስካሁን ጀማል የሚባል የተሰየፈ ከሌለ ግን ምናልባት ወደፊት እኔ ተሰይፌ ያኔ "ካፊሩ ጀማል ተሰየፈ" የምትሉበት ጊዜ ከመጣ እሰየው ነው!