Monday, March 10, 2014

ማኅበረ ቅዱሳን የፓትርያርኩን እጅ የመጠምዘዝ፤ እምቢ ካሉም የማስወገድ ትግሉን አጠናክሮ ቀጥሏል!! (ከማን ጋር ሊሰሩ ነው? » አባ ኤልሳዕ


የአሀዳዊ መዋቅር ምንጭ በሆነው ሲኖዶስ የምትተዳደር ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ማኅበረ ቅዱሳን ምኗ ነው? 
በአንድ ወቅት ሟቹ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ «በመንግሥት ሌቦች እጃችን ታስሯል» ማለታቸው አይዘነጋም። ከትንሹ በቀቀን ካድሬ አንስቶ እስከ ትልቁ ዓሳ ነባሪ/አንበሪ/ ሹመኛ ድረስ የመዋጥ፤ የመሰልቀጥ ተግባሩን ተመልክተው «የመንግሥት ሌባ እጃችንን አስሯል» ማለታቸው ይህንን ሁሉ በአንዴ ለማስቆም አለመቻላቸውን መግለጻቸው ብቻ ሳይሆን ከስፋቱ አንጻር ለማስቆም መሞከር ውጤቱ አደገኛ ሊሆን መቻሉን ለማመልከት« እጃችን ታስሯል» በማለት የችግሩን ስር መስደድ በአጭር ዐረፍተ ነገር ለመግለጽ ሞክረዋል። እዚያ አደገኛ ደረጃ ላይ የተደረሰው ግን በአንድ ጀምበር ሳይሆን ቀስ በቀስ አንዱ አንዱን እየዋጠና እየፋፋ እንደመሆኑ መጠን እጅ ከመታሰሩ በፊት አስቀድሞ ትንሽ በትንሹ እርምጃ ቢወሰድ ኖሮ አስጊነቱ ያን ያህል ባላሳሰበ ነበር።  ስርቆት ምንጊዜም ከክፉ ሰዎች ልቡና በሚመነጭ ሃሳብ የሚፈጸም ተግባር ነው። ክፉ ሰዎች ደግሞ ሰውን ከመግደል ወደኋላ አይመለሱም። እግዚአብሔርን ማወቅ ከሰዎች ኅሊና ውስጥ ሲጠፋ ጭካኔ ይስፋፋል። እርግማን፤ ግዳይ፣ ስርቆት፤ ደም ማፍሰስ ይበዛል።
በአንድ ወቅት የእስራኤል ልጆች ኃጢአት በመብዛቱና የካህናቱ ርኩሰት መጠን ከማጣቱ የተነሳ እግዚአብሔር አዝኖ የሥራቸውን ዋጋ ይቀበሉ ዘንድ ጥፋት እንደተዘጋጀባቸው መጽሐፍ ቅዱሳችን ይነግረናል።( ሆሴዕ ምዕ 4 እና 5) ሌብነትን መዋጋት ህግን እንደማስከበር ብቻ ሳይሆን መታየት ያለበት ደም ለማፍሰስ የማይመለሱ ሰዎችን ከኅብረተሰቡ ውስጥ እንደማውጣት ይቆጠራል።
እንደዚሁ ሁሉ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ከፓትርያርኩ ጀምሮ እስከ አጥቢያው አገልጋይ ካህን ድረስ እጃቸውን ወደኋላ አስሮ በቤተ ክርስቲያኒቱ ስም እየነገደ የፈረጠመውና በመዋቅሩ የዓሳ ነባሪ ያህል የገዘፈው ማኅበረ ቅዱሳን መሠረታዊ ጥቅሙን ለማስከበር ሲል ብቻ ከዚህ በፊት ለፓትርያርኩ ይሰጥ የነበረውን የምስጋና ካባ አውልቆ እጃቸውን ወደመጠምዘዝ ተግባር መሸጋገሩን እየተመለከትን እንገኛለን። የዚህ ሁሉ ዋናው ምክንያት በጥቅሙ መስመር ላይ የሚቆም ማንም ሰው የጥቅሙ ጠላት በመሆኑ አስቀድሞ እጁን በመጠምዘዝ ወደቀድሞ አስተሳሰቡ ለመመለስ በየትኛውም መልኩ መታገል፤ ካልተቻለ ደግሞ ከቆመበት የጥቅሙ መስመር ላይ ማጥፋትና ማስወገድ የጥቅመኛ መዳረሻ ግቡ ነው። ምን ጊዜም በማግበስበስ የበለጸጉ ሰዎች ጥቅማቸውን የማያስጠብቀውን አመራር ለማስወገድ እረፍት የሌላቸው መሆኑ ታሪክ ያስተምረናል። ሰሞኑን  የማኅበረ ቅዱሳንና የተባባሪ ጳጳሳቱ ጩኸት አቶ መለስ እንዳሉት የፓትርያርኩን እጅ የመጠምዘዝና ወደኋላ በማሰር ወደቀድሞ የማኅበሩን ጥቅም የማስከበር መስመር የመመለስ ትግል ተጠናክሮ መቀጠሉን እያየን ሲሆን ችግሩ በዚህ የማይፈታ ከሆነና ከቀጠለ ፓትርያርኩን የማስወገድ እርምጃ እንደሚከተል ሳይታለም የተፈታ ነው። እንዴት ይፈጸማል? የሚለውን ወደፊት የምናየው ሆኖ መጽሐፍ ቅዱስ እንደሚናገረው ግን ክፉ ሰዎች / ክፉ መሪዎች/ ክፉ ሀገራት/ ወዘተ ምን ጊዜም የማይስማማቸውን ከመግደል እንደማይመለሱ በእርግጠኝነት ልንናገር እንችላለን።
«ክፉ ካላደረጉ አይተኙምና፤ ካላሰናከሉም እንቅልፋቸው ይወገዳልና» ምሳሌ 4፤16
በዚሁ አጋጣሚ የምናሳስበው ነገር እውነተኛን የሚጠብቅ እግዚአብሔር እንደማያንቀላፋ ቢታወቅም  በተሰጠን ልቡና ራሳቸንን እንዳንጠብቅ የሚያዘናጋን ባለመሆኑ ፓትርያርክ አቡነ ማትያስ በሚበሉት፤ በሚጠጡትና በሚለብሱት ሁሉ ጥንቃቄ ማድረግ እንዳለባቸው ማስገንዘብ እንወዳለን።  እውነት ነው! «ሥጋንም የሚገድሉትን ነፍስን ግን መግደል የማይቻላቸውን አትፍሩ፤ ይልቅስ ነፍስንም ሥጋንም በገሃነም ሊያጠፋ የሚቻለውን ፍሩ» ማቴ 10፤28 በማለት እንደተናገረው የእግዚአብሔርን ፈቃድ ብቻ በሕይወታችን በማስቀደም ማገልገል እንደሚገባ እንጂ የሚያሳስበን በስጋ መሞት እንደማያስፈራን ይታወቃል።
ፓትርያርክ ማትያስ ከማኅበረ ቅዱሳን እስራት ነጻ ሰው መሆናቸውን መግለጽ በጀመሩ ማግስት፤ እስራታቸውን አምነው እንዲቀበሉ የማኅበሩ እስረኝነታቸውን ያረጋገጡ ጳጳሳት ቢቻል በምክር ሽፋን እጃቸውን እንዲሰጡ አለሳልሰው በማባበል፤ ፓትርያርኩ የአቋም ሰው በመሆን ከቀጠሉ ግፋ ሲል ደግሞ ወደፊት በማስፈራራት፤ አድማ በመምታትና በስመ ድምጽ ብልጫ የፓትርያርክነቱን ሥልጣን በመቀማት እግር ተወርች የማሰሩ ዘመቻ በእርግጥ ይቀጥላል። አባ ጳውሎስንም እንዲሁ ነበር ያዋከቡት።
ፓትርያርክ አቡነ ማትያስ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ እንጂ የማኅበረ ቅዱሳን ፓትርያርክ የመሆን ግዴታና ውል የለባቸውም። እኛም እንደተለመደው የምንጠይቀው ነገር ቢኖር አንድና አንድ ብቻ ነው።
የአሀዳዊ መዋቅር ምንጭ በሆነው ሲኖዶስ የምትተዳደር ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ማኅበረ ቅዱሳን ምኗ ነው? የሲኖዶስ አባላት ጳጳሳቱ የሚያገለግሉት ለማኅበረ ቅዱሳን ወይስ ለቤተ ክርስቲያን?

Saturday, March 8, 2014

«እውነትንም ታውቃላችሁ እውነትም አርነት ያወጣችኋል» ዮሐ 8፤32


ሐዋርያቱ ጌታችንን ከጠየቁት አስደናቂ ጥያቄዎች አንዱ «የመምጣትህና የዓለም መጨረሻ ምልክቱስ ምንድር ነው?» በማለት ያቀረቡለት ጥያቄ ነው። ከክርስቶስ ዳግም መምጣት በፊት የሚሆነውን የዓለሙን ነገር ከተናገራቸው መካከል አንዱ ደግሞ የመንግሥት ወንጌል በዓለሙ ሁሉ እንደሚሰበክ የተናገረው ይገኝበታል። ማቴ 24፤14
መንግሥተ ሰማያት የሚያስገባውና ዳኝነት የሚያሰጠው የሕግ መጽሐፍ ወንጌል በመሆኑ ማንም ቢሆን ይህንን ቃል እንዲሰማ በመጨረሻውና በክርስቶስ መምጫው መዳረሻ ላይ ወንጌል በዓለሙ ሁሉ እንደሚሰበክ የተናገረው ምልክት እነሆ በዓለሙ ሁሉ ከመቼውም ጊዜ በላይ ከአጽናፍ እስከ አጽናፍ እየተሰበከ መገኘቱ እውነት ነው። በንግግር፤ በጽሑፍ፤ በምስል፤ በድምጽ፤ በምልክትና የተለያዩ መገናኛ ዘዴዎች ወንጌል እየተሰበከ ይገኛል። በእርግጥ ወንጌልን የሚሰብኩ ሁሉ እውነተኞች፤ እንዲሁም ወንጌል የሰማ ሁሉ ይድናል ማለት አይደለም። የተጠሩ ብዙዎች፤ የተመረጡት ግን ጥቂቶች በመሆናቸው ለመዳንም ይሁን በፍርድ ለመውደቅ ድርሻው የእያንዳንዱ ሕይወት ከወንጌል ቃል መስማማቱ ነው። ወንጌል ሕጋችን ነው የሚሉ እነዚህ በሁለት ይመደባሉ።
1/ ወንጌል የሚናገረውን የእውነት ቃል አምነው እንደቃሉ የሚኖሩ
2/ ወንጌል የሚናገረውን የእውነት ቃል አምነው እንደራሳቸው የሚኖሩ ናቸው።
ወንጌል የሚናገረውን የእውነት ቃል አምነው እንደቃሉ የሚኖሩ በመልካም መሬት ላይ እንደተዘራ ዘር የወንጌልን ቃል አፍርተው ለብዙዎች መዳንና ወደእውነት መድረስ መንገድ የሚሆኑ ናቸው። ለዚህ አብነት ሆኖ የሚጠቀስ የመልካም መሬት ዘር ሐዋርያው ጳውሎስ ነው። ሐዋርያው መንፈሳዊ ትግሉ ምንጊዜም ሰዎች የክርስቶስ ብቻ ሆነው መልካም ፍሬ ያፈሩ ዘንድ ይተጋ ነበር።
«እንዲሁ፥ ወንድሞቼ ሆይ፥ እናንተ ደግሞ በክርስቶስ ሥጋ ለሕግ ተገድላችኋል፤ ለእግዚአብሔር ፍሬ እንድናፈራ፥ እናንተ ለሌላው፥ ከሙታን ለተነሣው፥ ለእርሱ ትሆኑ ዘንድ» ሮሜ 7፤4
እኛ በወንጌል አምነን በቃሉም የምንኖር ለሕግ ሞተን፤ ለክርስቶስ የሆንን የሌላ የማንም ፍሬ አይደለንም። የተክልዬም አይደለንም። የአቦዬም አይደለንም። የሚካኤልም አይደለንም። የማርያምም አይደለንም። የማንም ጻድቅ አይደለንም። የየትኛውም ቅዱሳን አይደለንም ማለት ቅዱሳንን እንደማቃለል አድርገው የሚመለከቱ አሉ። ከክርስቶስ በቀር የሞተልን፤ ከሞት የታደገንና ያዳነን ማንም የለም ማለት ነው። ጳውሎስ እንደተናገረው «ከሙታን ለተነሳው ለእሱ ትሆኑ ዘንድ» እንዳለው የእግዚአብሔር ብቻ እንደሆንን ይነግረናል። ወንጌል በክርስቶስ ብቻ ድነን የክርስቶስ እንሆን ዘንድ ሲያዘን ለቅዱሳን ያለንን ክብር የገለጽን እየመሰለን በማኅበራዊ ድረ ገጾችና በመረጃ መረቦች ላይ «እኔ የማርያም ነኝ፤ እናንተስ? እኔ የተክልዬ ነኝ፤ እናንተስ? ያለድንግል ማርያም አማላጅነት ዓለም አይድንም! የሚል ጥሪ ወንጌልን አመንን ከሚሉ ነገር ግን የወንጌል ቃል ተቃራኒ ድምጾች ይስተጋባሉ።  እውነቱን ስንነጋገር ዓለም የዳነው መቼ ነው? ዓለሙን ሁሉ ያዳነው ማነው? እግዚአብሔር አብ ዓለሙን ለማዳን አንድያ ልጁን ሲልክ የማን አማላጅነት እረፍት ስለነሳው ነው?
በጣም አሳዛኝና ወንጌልን የሚጻረር ድምጽ እየሰማን እንገኛለን። ቅዱሳንን በማክበር ሽፋንና ቅዱሳን በመቀበል ከለላ «ዓለም ያለቅዱሳኑ አማላጅነት አይድንም» ማለት ፈጽሞ ክህደት ነው ።  የእግዚአብሔር ፍርዱን ማን ሊመረምር ይችላል? ጳውሎስ እንዳለው።
«የእግዚአብሔር ባለ ጠግነትና ጥበብ እውቀቱም እንዴት ጥልቅ ነው፤ ፍርዱ እንዴት የማይመረመር ነው፥ ለመንገዱም ፍለጋ የለውም።የጌታን ልብ ያወቀው ማን ነው?ወይስ አማካሪው ማን ነበር? ወይስ ብድራቱን ይመልስ ዘንድ ለእርሱ አስቀድሞ የሰጠው ማን ነው?ሁሉ ከእርሱና በእርሱ ለእርሱም ነውና፤ ለእርሱ ለዘላለም ክብር ይሁን፤ አሜን» ሮሜ 11፤33-36
ወንጌልን አምነው ነገር ግን  እንደራሳቸው ቃል የሚኖሩት ደግሞ የራሳቸው የሆነ ፍሬ አላቸው። ፍሬአቸው ከወንጌል ቃል ጋር ፈጽሞ አይስማማም።  ለአብነትም ይህንን እውነት ከታችኛው ምስለ ድምጽ በማስረጃ ያመሳክሩ!!







Monday, March 3, 2014

ግብፅ ስትደነፋ መለስ ዜናዊ ናፈቁኝ!! When I hear Egypt's Rhetoric over Nile, I miss Meles Zenawi


ፎቶ፦ ናሳ ሳተላይት    
  ጽሁፍ በአማኑኤል ዊንታ
በሌሊት የተነሱ የግብፅ የሳተላይት ፎቶዎችን በአትኩሮት ብታዩ ፍንትው ያለና የማያወላዳ እውነትን ይጋፈጣሉ ከታላቁ የአስዋን ግድብ በካይሮ አድርጐ እስከ ሜዲትራንያን ባህር ድረስ 84 ሚሊዮን የሚጠጋው አጠቃላይ የግብፅ ህዝብ በጣም በሚገርም ሁኔታ የአባይን ዳር ለዳር ተጠግቶ ይኖራል፡፡ ይህም ግብፅን በአለም ላይ ካሉ ሀገራት ሁሉ እራሷን ሙሉ በሙሉ ለጥፋት አደጋ ያመቻቸች ብቸኛ ሐገር ያሰኛታል፡፡
ታላቁ የአስዋን ግድብ ያቋተው ውሃ የናስር ሐይቅ የሚባለውን ሰው ሰራሽ ሐይቅ ለመፍጠር ምክንያት ሆኗል፡፡ የናስር ሰው ሰራሽ ሐይቅ 547 ኪ.ሜ ርዝመት 35 ኪ.ሜ ስፋትና 110 ሜ ከፍታ አለው፡፡ ይህ የተፈጥሮ ሐይቅ ቢመታና ውሃው ቢፈስ በሰዓታት ውስጥ ግብፅ ያለምንም ጥርጥር ከጫፍ እስከ ጫፍ ተጥለቅልቃ ትጠፋለች ይህ ሳይንሳዊ ሐቅ ነው፡፡

በቅርቡ የካይሮና የአዲስ አበባ መሪዎች የተለያዩ የተካረሩ ቃላቶችን ሲወራወሩ አይተናል ሰምተናል፡፡ እንደማንኛውም ኢትዮጵያዊ ውስጤን ቆፍጠን! በሸቅ! ነደድ! የሚያደርግ ነገር ወረረኝ፡፡ አይ ወይኔ ይሄኔ ነበር የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስቴር መለስ ዜናዊ በኖሩልን ብዬ  የተመኘሁት በደንብ አርገው ግብፅን ያቀምሱልኝ ነበራ፡፡ አሐ እሳቸው እንዲሁ ነብሳቸውን ይማርና እንኳን የግብፅን የአሜሪካና የአውሮፓ ድንፋታንም ከቁብ አይቆጥሩት እኔ በግሌ የእሳቸው ፓርቲ አባል አይደለሁም ፓለቲካም አልወድም አባቴ ይሙት! ጀግና ናቸው እረ በጣም አዋቂም ናቸው፡፡ ናፈቁኝ ከምር ናፈቁኝ፡፡ ምን ዋጋ አለው “የማንም ልቅምቅም የሰው ልክ አያውቅም!” አለ ያገሬ ሰው፡፡ ግብፆች ደነፋብን የግብፅ ኘሬዝዳንት ሙሐመድ ሙሪሲ ለህዝባቸው የሚከተለውን ድስኩር አሰሙ፡፡
“በእውነቱ እኔ ጦርነት ይጀመር እያልኩ አይደለም ግን በእርግጠኝነት ቃል እገባላችኋለው የግብፅ የውሃ ፍላጐት በማንም በምንም አደጋ ላይ አይወድቅም! አሉ ቀጠሉናም
“የግብፅ የውሃ ፍላጐትና ደህንነት መቸም ቢሆን ጥያቄ ውስጥ አይገባም በማንም አይሞከርም እንደ ግብፅ ኘሬዝዳንትነቴ እማረጋግጥላችሁ ነገር ቢኖር ሁሉም አማራጮች ክፍት ናቸው ይተገበራሉም!” አሉ
ከዛም ቀጠሉና ተረት ተረት የሚመስለውን ግን እርር ድብን ያረገኝን ቀጣዮቹን ሁለት ንግግሮች ቀጠሉ “ግብፅ የአባይ ስጦታ ናት ካልን አባይም የግብፅ ስጦታ ነው!” በማለት ከድሮ ጀምሮ ሲባል የነበረውን አባባል በቴሌቪዥን ሕዝባቸውን ሆ አስባሉበት ቀጠሉናም ደነፉ፡፡
“የግብፃውያን ሕይወት ከአባይ ጋር ብቻ የተያያዘ ነው…. እንደ አንድ ታላቅ ህዝብ ደግሞ አንዲት ጠብታ ውሃ ከአባይ ላይ ሳትመጣ ብትቀር አማራጫችን አንድና አንድ ነው ደማችን ይፈሳል!” አሉና ፈገግ ጀነን ደንደን አሉ፡፡
እኔም እርር ድብን! ቆጣ! በስጨት! አልኩና ለማን ልተንፍሰው? ኮከቤ ደግሞ ታውረስ በሬው ነውና ለመዋጋትም፣ ይለይልን ኑ ውጡ! ለማለትም አማረኝ ግን አንድ ኢትዮጵያዊ ግለሰብ መሆኔ ሁሉንም አገደኝ ግን ከምር አንድ ግብፃዊ መንገድ ዳር ላይ ባገኝ ያን ቀን በስሱ በቴስታ ነበር አፍንጫውን ብየ ደም እያሉ ኘሬዝዳንት ሙርሲ የደነፉበትን ደም የማየው በእውነት ምን ችግር አለው በስሱ አንድ ቴስታ ባቀምሰው? ምንም፡፡
ኘሬዝዳንት ሙርሲም ሲያጠቃልሉ “ግብፅ ሁሉንም የአባይ ተፋሰስ ሐገራት ኢትዮጵያንም ጨምሮ በወንዙ ላይ ለሚሰሩት የልማት ኘሮጀክቶች ተቃውሞ የላትም፡፡ ነገር ግን የልማት ኘሮጀክቶች የግብፅን ህጋዊም ሆነ ታሪካዊ መብቶች የሚነኩም የሚያስተጓጉሉም መሆን የለባቸውም፡፡” አሉና ፖለቲካቸውን ቦተለኩ፡፡
የግብፅ የተለያዩ ፖለቲከኞችም የሙርሲን አባባል እያነሱ እያወደሱ በቴሌቪዥን መስኮት ብቅ ብቅ እያሉ እንዳውም ታላቁን የኢትዮጵያ የሕዳሴ ግድብ ከፍ ሳይል ባጭር እንቅጨው የጦር እርምጃ እንውሰድበት እያሉ ቀባጠሩ፡፡
ታዲያ መለስ ዜናዊ ቢናፍቁኝ ትፈርዱብኛላችሁ? አሃ ሌሎችንማ አየናቸው እኛ ላይ ሲሏችሁ ነው እንጂ የምትደነፉት ጠላት ሲመጣማ ጭጭ ምጭጭ፡፡ ባይሆን በኢቲቪ ወጣ ብላችሁ “ግብፅ ብትደነፋም በኩርኩም ነው የምንላት!” ምናምን እያላችሁ አታፅናኑንም? ድንቄም ፖለቲከኛ! እኔ በእውነት በጣም ተሰምቶኛል ወይ ደግሞ አንዳንድ ጊዜ ፖለቲከኞቻችን መድረሱን ለጀግኖች ለመከላከያ ሰራዊታችን ለቀቅ አድርጉላቸውና በሚዲያችን ዛቻና ድንፋታ እንስማበትና ወንዱ! አንበሳው! እንባባል፡
እውነቱን እንነጋገር ከተባለ ይህንን ሁሉ ችግር የፈጠረው የእኛ የፖለቲከኞች ችግርና ጥበብ ማነስ ነው ግድቡ የኢህአዴግ ብቻ ይመስል ለግንቦት 20 በአል አከባበር ታላቅ ድምቀት ብላችሁ የልደት ኬክ ይመስል አባይን ቦታውን አስቀይሳችሁ በሌላ አቅጣጫ እንዲፈስ አደረጋችሁ ወይም በሳይንሳዊ አገላለፁ (Diversion) ተሰራ፡፡ ግን ይሄ መሆን ያለበት የግብፅም ሆነ ሌሎች የአባይ ተፋሰስ ሐገራት ቅድሚያ አውቀውትና ተስማምተው መሆን አለበት፡፡ ምክንያቱም ግድቡ ሲጀመርም እኮ አብዛኞቹ ሐገራት ተስማምተዋል፡፡ መመካከር ማንን ይጐዳል? ነው ወይስ አባይን ለፖለቲካ ቅስቀሳ ጥቅም ብቻ ነው የገነባችሁት? አባይ የዚህ ወይም የዛ ፓርቲ አባል ነው የሚል ፓርቲ ካለ ከግብፅ ጐን መሰለፍ ይችላል፡፡ አባይ በተለይም ጥቁር አባይ የኢትዮጵያዊያን በሙሉ ነው፡፡ ለዛም ነው ህዝቡ በጉልበቱም በገንዘቡም ሆ ብሎ እየገነባው ያለው የሚገነባውም! እና እንደ ምክር ወይ እንደተግሳፅ ፖለቲከኞቻችን እዩትና እባካችሁ ለሐገራችን የሚጠቅመውን አድርጉ አዋቂና ጥበበኞችም ሁኑ አንብቡ ተማሩ ተመራመሩ፡፡ መለስ የናፈቁኝ አንባቢ መሪና ተመራማሪ ስለነበሩ ነው፡፡ እንደውም አሁን አሁን በየቀበሌው በየቢሮው የመለስን ራዕይ እናሳካለን እያላችሁ በለጠፋችሁት ወረቀት ስር ይህንንም የምንተገብረው እንደሳቸው በማንበብና በመፃፍ በመማርና በመመራመር ነው በሉበት፡፡ በእውነት እውነቴን ነው፡፡ እኔ ይህንን ጽሑፍ ለመፃፍ ያነሳሳኝ የፖለቲካ ፓርቲ አባል ወይም ስልጣን ፈላጊ ሆኘ አይደለም ሐገሬን አንድ ግብፃዊ ስነ-ህዝቡ በአደባባይ ሲዘልፋት ሰምቸ ተናድጀና ተቆጥቸ እንጅ አንድ ተራ ሰላማዊ ዜጋ ነኝ ግን እንደኔ ይህንን ስሜት የሚጋሩ ብዙ ኢትዮጵያዊያን አይጠፉምና አስቡበት፡፡
ከዚህ ቀጥሎ ግብፅ በ2011 ላይ ደርሶባት ስለነበረው የእርስ በእርስ ግጭትና የግብፅን የአሁን ሁኔታ በመላው አለም ላይ ተሰራጭቶ የተለያዩ ኤክስፐርቶች አስተያየት የሰጡበትን መረጃ በመመርኮዝ ለሐገራችን ሕዝቦች ለመንግስታችንና ለሐገር መከላከያ ሰራዊታችን አቀርባለሁ፡፡
ልብ በሉ ግብፅ በታሪኳ ብዙ ጦርነቶችን አድርጋለች ታላላቅ ጦርነቶችን ግን ተሸንፋለች፡፡ በአሁኑ ሰዓት የጦር ኃይሏ በአፍሪካ አንደኛ በአለም አስረኛ ነው፡፡ በአሜሪካ የጦር መሳሪያ ድጋፍ ከሚያገኙ ሐገራት ከእስራኤል ቀጥሎ ሁለተኛ ናት፡፡ አሜሪካ የእኔ ብቻ ናቸው ሌላ ሐገራት ቴክኖሎጂውን እንዳይሸጡት በሽያጭ አላቀርባቸውም የምትላቸው የብቻዋ ቴክኖሎጂ የሆኑ የተለያዩ ቀላልና ከባድ የጦር መሳሪያዎች ሄልኮኘተርና ጀቶችን ጨምሮ ግብፅን አስታጥቃታለች፡፡ በአጭሩ ግብፅ በአፍሪካ ቁንጮ ላይ ከአቅሟ በላይ የታጠቀች ጉረኛ ሐገር ናት ማለት ይቻላል፡፡
በአንድ ቀላል ምሳሌ እንኳን ለማስረዳት እስራኤልን ከምድረ ገፅ አጠፋለሁ ብላ ከሶስት ሐገራት ጋር ተባብራ በታሪክ የ“6 ቀኑ ጦርነት” የሚባለውን ልትተገብር ስትነሳ፣ ገና ሳይነሱ እስራኤል አጋየቻቸው እንጅ 300 የጦር አውሮኘላኖችን ቦምብና ሚሳኤል አስታጥቃ እስራኤልን ልትወርና ልታጠፋ የሞከረች ሐገር ናት፡፡ ይህም ምን ያህል ድንፋታም ነገር ግን ጥበብ የጐደላት ሀገር መሆኗን በቀላሉ ያስረዳል፡፡
ብዙ አወራሁ ወደ ተሰራጨ ያልኳችሁ ፅሑፍ ልግባና በመፅሐፍ ቅዱስ ትንቢተ ሕዝቅኤል ምዕራፍ 29 እና 30 ላይ የግብፅን ቅጣት ስለሚያትተው ትንቢት የተሰራጨ አንድ ጽሑፍ ነበር ጽሑፉንም የተለያዩ ታዋቂ ሰዎች አስተያየታቸውን አስፍረውበት ነበር ከአስተያየቶቹ መካከልም አይ ይህ ትንቢት እኮ ድሮ ገና ድሮ ከእየሱስ ክርስቶስ ልደት በፊት በ572 ቅ.ል.ክ አካባቢ በናቡከነፃር ጊዜ ተፈፅሟል ያሉም ነበሩ፡፡ በዚህ አሁንም ድረስ እያነጋገረ ባለ ፅሑፍ ተነስተን እስኪ በደንብ ትንቢቱን በጥሞና እንየው፡፡
በደንብ መታየት ያለበት ነገር የግብፅ የቅርብ ጊዜ እርስ በእርስ መባላት በየአደባባዩ ጐራ ለይቶ መወራወር ከቱኒዚያ በተነሳው የጐዳና ላይ ግጭት ቀጥሎ የአለምን ትኩረት የሳበ ነበር፡፡ የግብፃዊያኑ አመፅ ዋናው አላማም ለ30 አመት ግብፅን አንቀጥቅጦ የገዛውን የሆስኒ ሙባረክን መንግስት መገልበጥ ነበር፡፡ በአሜሪካ መንግስትና በአንዳንድ የምዕራቡ ሐገራት ባለስልጣናት ግፊትም ሆስኒ ሙባረክ ስልጣናቸውን በፌቡራሪ 12 ቀን መልቀቂያ ጠይቀው ለግብፅ ጦር ሰራዊት አስረከቡ፡፡ ከዛ ጊዜ ጀምሮ እስከ አሁኗ ደቂቃ ድረስ በግብፅ ውስጥ ከፍተኛ የሆነ የስልጣን ሽኩቻና ብጥብጥ ተፋፍሟል ዋናው ግፊትም ያለው ግብፅ በሐይማኖት መሪዎች የምትመራ ጠንካራና እስላማዊ ሐገር ሆና እንድትቀጥል ለማድረግ የሚደረግ ጥረት ነው፡፡
ተራማጅ እስላም በሚል መፈክር ስርም ከጀርባ ሁኖ ማርሹን በመቀያየር የሚገኘው “ሙስሊሞቹ ወንድማማቾች” (Muslim brotherhood) የሚባለው ድርጅት እንደሆነ የአደባባይ ሐቅ ነው፡፡ ቀስ በቀስም በጥበብ ቁልፍ የስልጣን ቦታዎችን እየያዘ ገና እየወጣ የሚገኝ ፓርቲ ነው ዋናው አላማውም ግብፅን ጠንካራ የሙስሊሞች ሐገር እንድትሆን ማስቻል ነው፡፡ በቅርቡ የሚታየው ሁኔታ እንደሚያመለክተውም የሙስሊም ወንድማማቾች ፓርቲ በግብፅ ጦር ውስጥ ያሉ ቁልፍ ሰዎችን እያዳከመና ወደ ፓርቲው እየቀላቀለ ስልጣኑን ሙሉ በሙሉ ለመቆጣጠር ቀን ከሌት እየሰራ ይገኛል፡፡
ባጭሩ የፖለቲካ ተንታኞች እንደሚገልፁት በጣም የጦፈ የስልጣን መያዝ ፉክክር እንደሚደረግና የሙስሊም ወንድማማቾች ፓርቲ እንደሚያሸንፍና ተራማጅ እስላም ስልጣን ላይ እንደሚሆን ይገልፃሉ፡፡
ሙባረክ ስልጣኑን ባስረከቡ ማግስት ነው እንግዲህ እስራኤላውያን ነቃ ብለው የግብፅን ሁኔታ በጥሞና ማዳመጥ የጀመሩት የስለላ ኤክስፐርቶቻቸውንም ያሰማሩት፡፡ ምክንያቱም እ.ኤ.አ ማርች 31,1979 ጀምሮ ከ30 አመታት በላይ ያስቆጠረ የሰላም ስምምነት ከሙባረክ ጋር እስራኤል አድርጋ ነበር ሙባረክ ሲወድቅም ስምምነቱ ተቋረጠ፡፡ ባለፉት 30 አመታት ምንም እንኳ ግብፅ በጨቋኙ የሆስኒ ሙባረክ አገዛዝ ስር ብትሆንም እንኳ ግብፅ ለእስራኤል ደቡባዊ ድንበር መጋጋት የሆስኒ ሙባረክ ወታደሮች ከፍተኛ ጥበቃ ያደረጉ ነበርና ነው፡፡ ነገር ግን አሁን ያ አስተማማኝ ጥበቃ የለም ስለዚህ እስራኤል ሆየ ነቃ! ብላ ነገሩን መከታተል ጀመረች፡፡
ይህ የእስራኤል ስጋትም ሳይውል ሳያድር እውን መሆኑ ተረጋገጠ ሁለቱ በተባበሩት መንግስታት አሸባሪ ተብለው የተፈረጁትና እስራኤልን ከምድረ ገፅ ለማጥፋት ሙሉ ጊዜአቸውን ሰውተው የሚንቀሳቀሱት የአሸባሪ ቡድኖቹ የሐማስና የፋታህ መሪዎች ሳይውል ሳያድር ግብፅ ካይሮ ላይ በሚያዚያ 26 ተገናኙና ጦራቸውን አንድ በማድረግ እስራኤልን ለመዋጋት ተፈራረሙ፡፡
የአሸባሪ ቡድኑ ፋታህ ኘሬዝዳንት ሞሐመድ አባስም ንግግራቸውን አሰሙ፡፡
“እኛ ፍልስጤማውያን ከዛሬ ጀምሮ ያንን ጥቁር የልዩነት ዘመናችንን አጠናቀናል! ሐማስ የፍልስጤም ሕዝብ አባልና አካል መሆኑን አውጀናል፡፡ እንግዲህ እስራኤል ከሰፈራ ኘሮግራም ወይም ከሰላም አንዱን መምረጥ አለባት!” ሲሉ ተኮፈሱ፡፡
አሁን በእርግጠኝነት ለመናገር ከዚህ በኋላ በእስራኤልና በፍልስጤም መካከል የሚደረግ የሰላም ስምምነት ሊኖር አይችልም፡፡ ቀዩ መስመር ይሉሐል ይሄኔ ነው! ፍልስጤም የምትባል ሐገርን ለማቋቋምና እውቅናን ለመስጠት ፋታህ እና ሐማስ መሞከራቸው አይቀሬ ነው ከዚች ቀን ደቂቃና ሰከንድ ጀምሮም ነበር እስላሞቹ ወንድማማቾችና እስራኤል አይጥና ድመት የሆኑት፡፡
እንግዲህ ቅድም የገለፅኩት የግብፃዊያን ትንቢት በትንቢተ ሕዝቅኤል ላይ ቁልጭ ብሎ ተቀምጧል ያልኩት ከፅሑፉ ተነስቸ ነው፡፡ ምክንያቱም ሕዝቅኤል በግልፅ ግብፆች የሚቀጡት ከእስራኤል ጋር አልተባበርም በማለታቸው ነው ይላል፡፡ “ግብፅ ለወደፊቱ አይቀጡ ቅጣት ነው የሚደርስባት ፍርዱም የቆሻሻ መጣያ ቦታ እስክትመስል በግብፅ ይታያል እያለ ቃል በቃል የሚከተሉትን የመፅሐፍ ቅዱስ ጥቅሶች ያትታል፡፡

 ሕዝቅኤል 29 (6:12)
በግብፅም የሚኖሩ ሁሉ ለእስራኤል ቤት የሸንበቆ በትር ሆነዋልና እኔ እግዚአብሔር እንደሆንሁ ያውቃሉ”
“በእጅ በያዙህ ጊዜ ተሰበርህ ጫንቃቸውንም ሁሉ አቆሰልህ በተደገፈብህ ጊዜ ተሰበርህ ወገባቸውንም ሁሉ አንቀጠቀጥህ”
“ስለዚህ ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል እነሆ ሰይፍ አመጣብሃለሁ ሰውንና እንስሳንም ከአንተ ዘንድ አጠፋለሁ፡፡”
“የግብፅ ምድር ባድማና ውድማ ትሆናለች እኔም እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ ያውቃሉ አንተ ወንዙ የእኔ ነው የሰራሁትም እኔ ነኝ ብለሀልና”
“ስለዚህ እነሆ በአንተና በወንዞችህ ላይ ነኝ የግብፅንም ምድር ከሚግዶል ጀምሮ እስከ ሴዌኔና እስከ ኢትዮጵያ ዳርቻ ድረስ ውድማና ባድማ አደርጋታለሁ፡፡”
“የሰው እግር አያልፍበትም የእንስሳም ኮቴ አያልፍባትም እስከ 40 አመትም ድረስ ማንም አይኖርባትም፡፡”
“ባድማም በሆኑ ምድሮች መካከል የግብፅን ምድር ባድማ አደርጋታለሁ ባፈረሱትም ከተሞች መካከል ከተሞችዋ 40 አመት ፈርሰው ይቀመጣሉ ግብፃውያንንም ወደ አህዛብ እበትናቸዋለሁ በአገሮችም እዘራቸዋለሁ፡፡”

 በአሁኑ ሰአት ያለምንም ጥርጥር ግብፅ እስራኤልን ለማጥፋት ለብዙ አመታት ቀን ከሌሊት ሲማስኑ ከኖሩ ሙስሊም አሸባሪዎች ጋር ህብረት ፈጥራለች፡፡
ይህ የአሸባሪነት ትብብርም በቅርቡ እንደ ሰደድ እሳት መቀጣጠሉና ብዙ አሸባሪዎችን በህብረት አሰባስቦ እስላማዊ ወንድማማቾችን አሁን ጊዜው ደርሷል እስራኤል ትወረር ማስባሉ የማይቀር ሐቅ ነው፡፡
ብዙ ሰዎች ከላይ የጠቀስኩትን የሕዝቅኤል 29 ትንቢት ገና ወደፊት አለም ስትጠፋ የሚፈፀም ትንቢት ነው እንጅ አሁን ጊዜው ገና ነው እያሉ ይቃወማሉ፡፡
አንዳንዶቹ ደግሞ ትንቢቱ እኮ ድሮ ገና ድሮ በባሊሎናዊያን ጊዜ ተፈፅሟል ይላሉ፡፡ ነገር ግን አብዛኞቹ ልብ ያላሉት ነገር ቢኖር የሕዝቅኤል ትንቢት ስለፍፃሜው ሲተነብይ እሚያወራው ሴዌኔ ስለሚባል ቦታ የሚደርስበትን የወደፊት መከራ ነው የሚዘረዝረው፡፡ በዛ ላይ ደግሞ ከላይ የዘረዘርኩት የመፅሐፍ ቅዱስ ቃል እንደሚያትተው ግብፅ በታሪኳ መቸም ቢሆን ለ40 አመታት ያህል ሰው የሌለባት ምድረ በዳ ሆና አታውቅም ይህም ትንቢቱ ገና ወደፊት ለመሆኑ ትልቅ ማስረጃ ነው፡፡
ለብዙ አመታት ስናምንበት የኖርነው የሕዝቅኤል ትንቢት በተፈጥሮው ቅኔያዊ ይዘቱ ያይላል፡፡ ይህንን ለማለት ያስቻለኝ ምክንያትም ሕዝቅኤል ትንቢቱን ሲፅፈው በዛ ጊዜ “የሴዌኔ ማማ” የሚባል ነገር ወይም ቦታ የለም አልነበረም እንደውም እ.ኤ.አ እስከ 1967 ጊዜ ድስ ይህ ቦታ አልተሰራም በ1967 ግን ይህ ቦታ በሚደንቅ ሁኔታ ታላቁ የአስዋን ግድብ ሆኖ ብቅ አለ፡፡ በግብፅ ደቡባዊ በኩል አባይን ተከትሎ ተገነባ፡፡ “ሴዌኔ” የሚለው ስም የመጣው ሲቭኔ ከሚለው የሒብሩ ቃል ሲሆን ትርጓሜውም “መግቢያ” ወይም “ቁልፍ” ማለት ሲሆን ይህም ስም የጥንት ግብፃውያንን መግቢያ ያመላክታል፡፡ ከደቡባዊ ግብፅ ወይም ከኢትዮጵያ ተነስቶ አንድ ሰው ወደ ግብፅ ሲገባ የሚያየውን መግቢያ ወይም ቁልፍ በግልፅ ያትታልና፡፡
በጣም ብዙና የተለያዩ ታሪካዊ መረጃዎችን ብናገላብጥ የመፅሐፍ ቅዱስ ሴዌኔ በእርግጥም አስዋን ግድብ ነው ይላሉ፡፡ ከነዚህ መረጃዎች መካከል አንዱ በ1966 እ.ኤ.አ በኬል እና ዳልሽ የተፃፈው የብሉይ ኪዳን ጥናትና አስተያየት የሚለው መፅሐፍ ይገኝበታል፡፡ ግንኙነቱንም ሲያጠናክረው በግሪኮች “ሴዌኔ ብሩዳሽ” እንደፃፈው “ሴርቱዋጅንት” ወይም የመጨረሻዋ የግብፅ ደቡባዊ ከተማ ከኩሽ ማለትም ኢትዮጵያ አቅጣጫና ጐን ናት ይላል፡፡ አሁንም ድረስ ከአባይ ምስራቃዊ ቦታዎች አካባቢ የሚታዩ ኢትዮጵያዊ የሆኑ አንዳንድ የጥንት ስልጣኔ መገለጫዎች በግብፅ ደቡባዊ አዋሳኝ ከተማ ሴርቱዋጅንት አካባቢ ይገኛሉ፡፡
የሚገርመው ነገር ኬል እና ደልሽ በ1866 የብሉይ ኪዳን ጥናትና አስተያየት ሲፅፉ አስዋን ላይ ምንም አይነት ማማ አልነበረም ሕዝቅኤል ትንቢቱን በ570 ቅ.ክ.ል በፊት ሲፅፈውም ምንም አይነት ማማ አልነበረም፡፡ እውነታው ግን ታላቁ የአስዋን ሐይድሮ ኤሌክትሪክ ግድብ በግብፃውያንና በራሻውያን ተሰርቶ በ1967 እ.ኤ.አ እስከሚጠናቀቅበት ቀንና ደቂቃ ጊዜ ምንም አይነት ማማ በአስዋን ላይ አልነበረም፡፡
አሁን ግን ይህ ግድብ ሲጠናቀቅ በአካባቢው ያለው ብቸኛ ማማና ወደ ላይ የተራራ ያህል ገዝፎ የሚታየው የአስዋን ግድብ እራሱ ነው፡፡ ለዛም ነው ይህ “ሴዌኔ” እየተባለ በትንቢት ሲገለፅ የነበረው ቦታ በአሁኑ ሰአት አስዋን እየተባለ የሚጠራው ቦታ መሆኑን አጋግጠናል የሚሉት፡፡ ግብፃውያኑ የራሽውያንን ቴክኖሎጂ ተጠቅመው ግድባቸውን በተሳካ ሁኔታ ሙሉ በሙሉ ሲያጠናቅቁም ተኮፈሱና እስከ ዛሬ ድረስ የሚመፃደቁበትን አባባላቸውን ለልጅ ልጅ እንዲወረስ እያደረጉ እንደ ምሳሌያዊ አነጋገር ይጠቀሙበታል፡፡

“ወንዙ የእራሴ ነው የሰራሁትም እኔ ነኝ” ግብፃውያን

 ሕዝቅኤል 29 (2-5)
“የሰው ልጅ ሆይ ፊትህን በግብፅ ንጉስ በፈርኦን ላይ አድርግ በእርሱና በግብፅ ሁሉ ላይም ትንቢት ተናገር፡፡”
“እንዲህም በል - ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላላ በወንዞች መካከል የምትተኛና ወንዙ የእኔ ነው ለራሴም ሰርቸዋለሁ የምትል ታላቅ አዞ የግብፅ ፈርኦን ሆይ እነሆ በአንተ ላይ ነኝ፡፡”
“በመንጋጋህ መቃጥን አገባብሃለሁ የወንዞችህንም አሶች ወደ ቅርፊትህ አጣብቃለሁ ከወንዞችህም መካከል አወጣሀለሁ የወንዞችህም አሶች ሁሉ ወደ ቅርፊትህ ይጣበቃሉ፡፡
“አንተና የወንዞችህን አሶች ሁሉ ወደ ምድረ በዳ እጥላለሁ በምድርም ፊት ላይ ትወድቃለህ እንጅ አትከማችም አትሰበሰብም መብልም አድርጌ ለምድር አራዊትና ለሰማይ ወፎች ሰጥቼሃለሁ፡፡”
ትንቢቱ ዝም ብሎ በመጀመያ ሲታይ የሚመስለው ለግብፅ ንጉስ ፈርኦን ፓሮህ የተፃፈ ይመስላል ቀስ እያላችሁ በደንብ መፈተሽ ስትጀምሩ ግን ትንቢቱ የተፃፈው “በባህር ላይ ስለሚኖረው” ታላቅ አዞ መሆኑን ታውቃላችሁ፡፡
ቀጥሎም አንተና የወንዞችህ ወይም የአባይ አሳዎች ሁሉ ወደ ምድረ በዳ እጥላለሁ ለምድር አራዊትና ለሰማይ ወፎችም መብል አደርግሃለሁ እያለ ያትታል፡፡
አባይ በየአመቱ እየተንደረደረ በከፍተኛ ሙላት ነበር ወደ ግብፅ የሚገባው ነገር ግን ግድቡ ከተሰራ በኋላ ሰጥ ለጥ ብሎ ነው ግብፅ ውስጥ የሚጓዘው በትንቢቱ እንደተገለፀው አባይን እንደገና በከፍተኛ ሙላት እያስጋለቡ በግብፅ ውስጥ ለማስጓዝ ብቸኛው መንገድ አንድ እና አንድ ብቻ ነው ግድቡን ማፍረስ፡፡
ሌላው አስደናቂ ነገር ይህ ታላቅ ግድብ የተገነባው በጣም በትልልቅ ብረቶችና ኮንክሪቶች ተጠፍጥፎ ከመሆኑ የነሳ የዘርፉ ባለሙያዎች የአስዋን ግድብ በምንም አይነት ቦምብ ቢመታ ሊፈርስ አይችልም፡፡ ከኒውክሌር ቦምብ በቀር ማለታቸው ትንቢቱን ገና ያልተፈፀመ ስለመሆኑ ያረጋግጣል፡፡ ኒውክሌር ቦምብ የአሁን ቴክኖሎጂ ነውና፡፡

 እስራኤላዊያን ጠበብቶች ምን አሉ?

በ2002 የእስራኤል የፓርላማ አባል የነበረ አቪጐር ሊበርማን የተባለ ሰው ነው ለመጀመሪያ ጊዜ ይህች በየጊዜው ለእስራኤል ችግር መነሻ እየሆነች ላስቸገረችው ግብፅ የምትባል ሐር ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ የሚሆን መፍትሄ አግኝቻለሁ ብሎ ንግግሩን ያሰማው፡፡
“እስራኤል በቀላሉ ግብፅን በአንድ ኒውክሌር ቦምብ ድምጥማጧን ማጥፋት ትችላለች አለ” ልብርማን ስለ ግድቡ በደንብ ነበር ያጠናው ያሰማራቸው ረዳቶችም አስዋን ግድብ በጣም ትልቅና ግዙፍ ከመሆኑ የነሳ በተራ ቦምብ እንደማይፈርስ ተረድቶ ነበርና ኒኩሌየር ቦምብ ብቸኛ አማራጭ መሆኑን ተንትኖ አስረዳ፡፡
ሌላኛው የፓርላማ አባል ይጋል አሎን ቀጠለና ይህንን ጥሩ ዜና የምስራች ለእስራኤላዊያን በአደባባይ አበሰረ፡፡ እነዚህ ሁለት ጀግኖች አብዛኞቹ እስራኤላዊያን የሚያውቁትን ነገር ግን በውስጣቸው አምቀው የያዙትን እውነት በአደባባይ ያበሰሩ ጀግኖች አደረጋቸው፡፡ ሊበርማን ከእስራኤል የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እስከ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስቴርነት ድረስ፣ ይጋል ደግሞ ለሰባት አመታት በሚኒስቴርነት ሐገራቸውን አገልግለዋል፡፡
ሊበርማንና ይጋል እስከ አሁኗ ደቂቃ ድረስ ግብፃውያን አንገታቸውን ደፍተው እድሜልካቸውን መፍትሄ የማያገኙለትን የቤት ስራ ሰጥተዋቸዋል፡፡
እነኚህ ሁለት እስራኤላዊያን ሲናገሩም የእስራኤል የማንነት ጥያቄ በግብፃውያን ወረራ የሚስተጓጐል ከሆነ ጨዋታው የሚሆነው እንደዛ በምትመፃደቁበት ግድባችሁ ላይ ይሆናል በማለት አስረገጡ፡፡
“በኑክሊር ቦምብ አስዋንን እናፈርሰዋለን፡፡ በውሃውም በሰዓታት ሰምጣችሁ ታልቃላችሁ አርፋችሁ ቁጭ በሉ፡፡ “ይኸው እነሱም አርፈው እስከ ዛሬ ቁጭ ብለዋል፡፡

 የሚከተሉት የማጠቃለያ የመፅሐፍ ቅዱስ ጥቅሶች በመጨረሻው ቀን ላይ ያተኩራሉ ልብ ብላችሁም አስተውሉ የሴዌኔ ማማም ተጠቅሷል፡፡

 (ሕዝቅኤል 30 1፡6)
“የእግዚአብሔርም ቃል ወደ እኔ እንዲህ ሲል መጣ የሰው ልጅ ሆይ ትንቢት ተናገር እንዲህም በል”
“ጌታ እግዚአብሄር እንዲህ ይላል” ዋይ በሉ ለቀኑ ወዮ ቀኑ ቅርብ ነው የእግዚአብሔር ቀን ቅርብ ነው የደመና ቀን የአህዛብ ጊዜ ይሆናል፡፡
“ሰይፍ በግብፅ ላይ ይመጣል ሁከትም በኢትዮጵያ ይሆናል የተገደሉትም በግብፅ ውስጥ ይወድቃሉ ብዛትዋንም ይወስዳሉ መሰረቷም ይፈርሳል፡፡”
“ኢትዮጵያና ፋጥ ሎድም የደባለቀም ሕዝብ ሁሉ ኩብም ቃል ኪዳንም የገባችው ምድር ልጆች ከእነሱ ጋር በሰይፍ ይወድቃሉ፡፡”
“እግዚአብሄር እንዲህ ይላል ግብፅን የሚደግፉ ይወድቃሉ የሐይሏም ትእቢት ይወርዳል ከሚግዶል ጀምሮ እስከ ሴዌኔ ድረስ በእርስዋ ውስጥ በሰይፍ ይወድቃሉ ይላል ጌታ እግዚአብሄር፡፡”

ለዚህም ነው ግብፅ ለመኖሪያ የማትመች የተንኮለኞችና የእግዚአብሔር ቃል ተቃዋሚዎች ሐገር በመሆኗ ለ40 አመት ያህል ማንም የማይኖርባት ምድረ በዳ አደርጋታለሁ ያለው፡፡ የእግዚአብሄር ቃል በሕዝቅኤል 38 ላይ እስራኤልን ተባብረው ከሚያጠቋት የጐግ ሐይሎች ጋር ግብፅ ያልተጠቀሰችውም እኮ ስለማትኖር ነው እንጂ ብትኖርማ የመጀመያ ቋሚ ተሰላፊ ነበር እኮ የምትሆነው፡፡
በራዲዮአክቲቭ ንጥረ ነገር በተበከለ ውሃ የተጥለቀለችን አንድ ሐገር ለማፅዳት የሚፈጀውን ሐይልና ገንዘብ አስቡትና ምን ያህል አስቸጋሪ ነው ብላችሁ እራሳችሁን ጠይቁ፡፡ ወይም ከመጨረሻው ቀን በኋላ በእግዚአብሄርና በተከታዮቹ የሚፀዳው ቦታ ግብፅ ይሆነ ይሆናል፡፡ ማን ያውቃል? እባካችሁ ኢትዮጵያዊያን ጀግኖችም በዚህ ጉዳይ ላይ አንድ ነገር በሉ “ግብፅ ሆይ አርፈሽ ቁጭ በይ! በእሳት አትጫወች! ግድባችንን እንዳንሰራ ወንድ የሆነ ያስቆመናል! አለዛ በደህና ጊዜ የሰራሽውን የአስዋን ግድብ መጥፊያሽ ይሆናል! አሁን ያለው ኢትዮጵያዊ ትውልድ ከምታስቢው በላይ ነቃ ያለ ነው እንኳን ለወደፊቱ ድሮ ለሄደብን አፈርም ካሳ መጠየቁ አይቀርም” እኔስ እችን ፅፌ ትንሽ ንዴቴ ተንፈስ አለልኝ! እናንተስ?

 የምወዳትን ኢትዮጵያ እግዚአብሔር ይባርካት፡፡

                              አመሰግናለሁ፡፡

                       አማኑኤል ዊንታ

                   ባህር ዳር ሰኔ 2005

Sunday, February 23, 2014

ጾም


(ነብዩ ዮናስ በነነዌህ የሥዕል ምንጭ ባይብል ጌት ዌይ)
(የጽሁፍ ምንጭ፦ የዲያቆን አሸናፊ መኮንን ገጽ)

ጾም ለመንፈሳዊው ዓለም የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ነው፡፡ በእግዚአብሔር ፊት ቁርጥ ልመናን ለማቅረብ፣ እውነተኛ ንሰሐን ለመፈጸም፣ የዕንባ መሥዋዕትን ለማቅረብ፣ በትሕትና ጸጋን ለመቀበል ጾም አስፈላጊና ግዴታ ነው፡፡
ጾም አዋጅና በአዋጅ ሊደረግ የሚገባው ነው፡፡  በስውር የሚደረግ ጾም አለ፡፡  ግለሰቡ ጉዳዩን ለእግዚአብሔር የሚያቀርብበት፣ መጾሙንም የማያሳውቅበት ነው፡፡  የማኅበር ጾም ግን በአዋጅ የሚደረግ፣ ስለ አገርና ስለ ወገን የእግዚአብሔር ማዳን የምንጠባበቅበት ነው፡፡  ጾምን ሰው ለራሱ ያውጃል፣ ቤተ ክርስቲያንም ታውጃለች፡፡
ጾም ራሳችንን በእግዚአብሔር ፊት የምናዋርድበት ነው፡፡  በተሰበረ ልብ የሚቀርብ ልመና ግዳጅን ይፈጽማል፡፡  ፈጽሞም መልስ ያገኛል፡፡  ጾም ለትሑት ጸሎት እጅግ ይረዳል፡፡  ሥጋን በማድከም ወደ ነፍስ ልዕልና የምንቀርብበት ምሥጢር ነው፡፡  ጾም የርኅራኄ መገኛ፣ የዕንባ ምንጭ፣ የትሕትና መፍለቂያ ናት፡፡  ራሳችንን በጾም ስናዋርድ እግዚአብሔር ከፍ ያደርገናል፣ ምሪትን ይሰጠናል (ዕዝ. 8÷21)::
ጾም አዋጅን የሚሽር አዋጅ ነው፡፡ በመጽሐፈ አስቴር ላይ እንደምናነበው በአይሁድ ላይ የታወጀው የሞት አዋጅ ወደ ሹመትና ክብር የተለወጠው በጾምና በጸሎት ነው (አስቴ. 4÷3)፡፡  የተዘጉ ደጆች እንዲከፈቱ፣ በአገር በወገን ላይ የመጣ የክፉ አዋጅ ማለት ሞት፣ መከራ፣ በሽታ እንዲወገድ ጾም ጸሎት ትልቅ መሣሪያ ነው፡፡  የጾምና የጸሎት ትጥቅ አይታይም፣ የሚታየውን ጠላት ግን ያሸንፋል፡፡  
ጾም ይቅር ብለን ይቅርታ የምንለምንበት ነው፡፡  እግዚአብሔር ከመሥዋዕት ይልቅ ምሕረትን (ይቅርታን) ይወዳል (ማቴ. 9÷13)፡፡  በጾም በጸሎት የእግዚአብሔርን ይቅርታ ስንለምን ይቅር እያልን፣ በረከቱን ስንለምን ለተራቡት እያበላን ሊሆን ይገባዋል፡፡ አማኝ ከጫጫታ ስፍራ ገለል ብሎ፣ ከዘፈን ይልቅ ዝማሬን መርጦ፣ ከወሬ ይልቅ በጸሎት ተጠምዶ እንዲባረክ ጾም ቀስቃሽ ደወል ነው፡፡
ዘፈንና ዝሙት እንዲሁም ስካር በአገር ሲበዛ ቀጥሎ ትልቅ ጥፋትና ልቅሶ ይኖራል፡፡  "የዘፈን ቤት ሳይፈርስ አይቀርም" እንዲሉ ዘፈን ሲበዛ መጾምና ማልቀስ ይገባል፡፡ እግዚአብሔር የሚፈልገው ጾም የበሬ ሥጋን ከመብላት መከልከልን ብቻ ሳይሆን ከሰው ሥጋም እንድንርቅ ነው፡፡  ያለ ቢላዋ በሐሜት የሰውን ሥጋ መብላት ጾምን እንደ መግደፍ ነው፡፡  እኛ ግን የበሬ ሥጋ እንጂ የሰው ሥጋ አንተውም፡፡ ሠራተኞቻችንን እያስለቀስን፣ ደመወዛቸውን እየበላን፣ ቂምን በልባችን ሞልተን የምንጾመው ጾም የረሃብ አድማ እንጂ ጾም አይባልም (ኢሳ. 58÷5-6)፡፡ የጾም መሰናዶው ነጠላን ማጽዳት ሳይሆን ልብን ማጽዳት፣ በየልኳንዳ ቤት ደጆች መሰለፍ ሳይሆን ንስሐ መግባት፣ ዕቃን ማጣጠብ ሳይሆን ከቂም መጽዳት ነው፡፡  የጾምን መረቁን እንጂ ሥጋውን አልበላንምና ከንቱ ልፋተኞች ሆነናል፡፡ ምክንያቱም ለጾማችን የምናደርገው ዝግጅት ሜዳዊ እንጂ ውስጣዊ አይደለምና፡፡ ትልቁ ጾም ከኃጢአት መከልከል ነው፡፡  ቅበላና ፋሲካ የሌለው ጾም ኃጢአት ነው፡፡  በአገራችን በጾም መግቢያና መውጫ ስካርና ዝሙት ይደራል፡፡  ቅበላውና ፋሲካው በኃጢአት በመሆኑ ከጾም የሚገኘውን በረከት ማግኘት አልቻልንም፡፡
ጾም ለእግዚአብሔር እንጂ ለታይታ አይደለም (ዘካ. 7÷5)፡፡  ከማኅበረሰቡ ላለመለየት፣ ሆዳም ላለመባል፣ ዶሮ ለመባረክ መጾም ከንቱ ጾም ነው፡፡ የምንጾመው ከእግዚአብሔር ዋጋ ለማግኘት እንጂ ጾመኛ ለመባል መሆን የለበትም፡፡ የጾምና የጸሎት ዋጋ ያለው ከእግዚአብሔር ዘንድ ነው፡፡ “በጾም አፌ ክፉ አታናግሩኝ” ለማለት መጾም አይገባንም፡፡  ባንጾምም ክፉ መናገር አይገባንም፡፡  በጾማችን የሚታየን እግዚአብሔር ነው?  ራሳችንን መጠየቅ ይገባናል፡፡
ጾም እውነትና ሰላም ያለበት ነው፡፡  በጾማችን ወራት ከድሆች ጋር ማሳለፍ፣ ብድር መመለስ ለማይችሉ ቸርነት ማድረግ ይገባል፡፡ እኩያን ሲጠሩ መኖር እውነተኛነት አይደለም፡፡ ከእኛ ባነሰ ኑሮ ለሚኖሩት እጅን መዘርጋት ግን የጾም መገለጫው ነው፡፡  ጾም ሁለት እጆች አሏት፡፡  አንደኛው የጾም እጅ ጸሎት፣ ሁለተኛው የጾም እጅ ምጽዋት ነው፡፡  ጾም ሁለት አንደበት አሏት፡፡  አንደኛው ቃላችን ሲሆን ሁለተኛው ዕንባችን ነው፡፡ ጾም እውነትን ትፈልጋለችና ለተጨቆኑ ምስኪኖች፣ ፍርድ ለተጓደለባቸው እስረኞች፣ በግፍ ከገዛ አገራቸው ለሚሰደዱ አቤት የምንልበት፣ ግፍ አድራጊዎችን በቃችሁ ብለን የምንገስጽበት የእውነት ሰይፍ ነው፡፡ ጾም ሰላም ስለሆነ ግለሰብ ከግለሰብ፣ ማኅበራት ከማኅበራት፣ አገር ከአገር ጋር የሚታረቁበት፣ እንዲታረቁም ጥረት የምናደርግበት ሊሆን ይገባዋል፡፡ እርቅን የጠሉና የገፉ የሃይማኖት አባቶች ጾምን የማወጅ አቅም የላቸውም፡፡ ስለዚህ ታርቀው የሚያስታርቁበት እንዲሆን ሊያስቡ ይገባቸዋል፡፡ የጾም የመጨረሻው ውጤት ወይም በዓሉ እግዚአብሔር በሚሰጠን መልስ ሆታና ደስታ ነው፡፡  መልስ እንዲመጣ ግን እውነትና ሰላም መርጋት አለባቸው፡፡ ግፈኞች፣ የሌላውን ድርሻ እየነጠቁ የሚበሉ፣ ለሀብታም እያደሉ በድሃ የሚፈርዱ ሊገሰጹ፣ ንስሐ ሊገቡ ይገባል፡፡  ያ ሲሆን የጾም ዳርቻው ተድላና ደስታ ይሆናል (ዘካ. 8÷19)፡፡
 የነነዌ ሰዎች ምሕረትን የተቀበሉት በሦስት ቀን ጾምና ጸሎት ነው፡፡  የመጣው መዓት የተመለሰው፣ የራቀው ምሕረት የቀረበው በአንድ ልብ ሆነው አቤት በማለታቸው ነው፡፡  እኛ ግን ዓመት ሙሉ እየጾምን ለምን በረከት ራቀን? ብለን ጠይቀን አናውቅም፡፡ 

እንደጸሎታችን መብዛቱ ረሃብና ቸነፈር፤ ስደትና እንግልት፤ የሰላምና ፍቅር እጦት፤ አንድነትና ኅብረት አለመኖር የሚያጠቃን ለምንድነው? የጾም ጸሎት ምላሹ ይህንን ለማስቀረት ካልሆነ የጾምና የጸሎታችን ጉዞ የተተከለ ደንብ ከመፈጸም ውጪ ከእግዚአብሔር ሀሳብ ጋር አልተገናኘም ማለት ነው። ስለዚህ ይህን ዐቢይ ጾም ስንጾም፡-
    1.     ርዕስ ልንይዝ
    2.    ይቅር ልንባባል
    3.    ንስሐ ልንገባ ይገባናል፡፡
ብዙ አንገብጋቢ ርዕሶች አሉን፡፡ የቤተ ክርስቲያን ለሁለት መከፈል፣ በመንፈሳዊ ቦታ መንፈሳዊ ያልሆኑ ሰዎች መቀመጣቸው፣ እርቅን የማይወዱ ሰዎች መሙላታቸው፣ በአገር ያለው የኑሮ ውድነት፣ ድሆች በደንብ እየደኸዩ መሆናቸው፣ ፍትሕና ፍቅር መጥፋቱ፣ የገንዘብ ጣኦት በምድራችን መቆሙ፣ የዝናብ መታጣት፣ የበሽታ መበርከት፣ የአንድነት መጥፋት፣ የትዳር መናጋት፣ የልጆች ዋልጌነት፣ የሐሰት መምህራን መብዛት፣ እግዚአብሔርን መርሳት…….  ይህ ሁሉ የጾምና የጸሎት ርዕሳችን ነው፡፡  ክርስቲያን መንፈሳዊ ኃይልን አጥተóል፡፡  በየደረሰበት ውጊያ አሸናፊ ሳይሆን ተሸናፊ ሆኗል፡፡
ይኸውም፡-
    -      ቃሉን ስለማያጠና
    -      የጸሎት ሰዓቱ ስላልተከበረ
    -      ጾምና ጸሎትን ስለተወ
    -      ምጽዋትን ስላስቀረ
    -      የእግዚአብሔርን ለእግዚአብሔር መስጠት ስላልቻለ …. ነው፡፡
በእውነት ጾመን በዓሉ ተድላ እንዲሆን፣ በጾም ዘርተን በፈውስ እንድናጭድ እግዚአብሔር ይርዳን!

Sunday, February 16, 2014

ዕርቅና ሰላም፤ የሕይወት ቅመም


የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን እንደውለታ ቢስ ለሚቆጥሩ ወገኛ ሁሉ መልስ የሚሆን ጽሁፍ እነሆ!
በፕሮፌሰር ጌታቸው ኃይሌ 
 
   አንድ ጥናት ሳነብ፥ ምናልባት እናንተም አንብባችሁት ይሆናል፥ የተፈጥሮ ሀብት ባላት ሀገር ውስጥ የሚኖሩ ሰዎች ከተራቡ፥  የማሰብ ችሎታቸው ዝቅተኛ ቢሆን ነው ሲል አገኘሁት። "ጥልቀት የሌለው ረጋ-ሠራሽ ጥናት ነው" ብዬ ጣልኩት። ኢትዮጵያ የተፈጥሮ ሀብት ባለጠጋ መሆኗን እርግጥ ባለሞያዎች የመሰከሩት ነው። ማዳበሪያ የማያስፈልገው መሬት ታርሶ አያልቅም። የወንዞቿ ውሀ ለጎረቤት አገሮች ሳይቀር ይተርፋል። ይኸንን እውነታ በቀጥታ ከተመራማሪዎቹ  አፍ ለመስማት የፈለገ ፕሮፌሰር ስዩም ገላየን ማዳመጥ ይችላል።  
   እንዲህ ከሆነ፥ ትኩረቱ በኢትዮጵያውያን የማሰብ ችሎታ ላይ ሊሆን ነው። እውነት የኢትዮጵያ ሕዝብ ተመጽዋች ሆኖ የቀረው የማሰብ ችሎታው ዝቅተኛ ሆኖ ነው? አይመስለኝም።  ሰውየው ጥናቱን ማስተካከል አለበት። አለዚያ፥ ከዚያ ቀጥሎ፥ "አንድ ሰው እሱቁ ውስጥ ከመስተዋቱ በስተኋላ ድፎ ዳቦ እያየ ከተራበ የአስተሳሰብ ችሎታው ዝቅተኛ ቢሆን ነው" ሊለን ነው። ምንም ከፍተኛ የማሰብ ችሎታ ቢኖረው፥ ዳቦውን እንደማያገኘው ለማንም ግልጽ ነው። 
  እርግጥ ነው፥ በአስተሳሰብ ደከም የሚል ሰው ሊጎዳ ይችላል። ሌላው ቢቀር፥ የብልሁ ጓደኛውን ያህል አይደላውም።  ግን በከፍተኛ ደረጃ የማሰብ ችሎታ ያለው ሰውም ሊቸገር ይችላል።  ስንቶች ናቸው ኢትዮጵያ ውስጥ በችግር የሚኖሩ፥ መውጫ ቢያገኙ ግን ለሌላው ሳይቀር የሚተርፉ? በአፍሪካ፥ በአውሮፓ፥ በአሜሪካ ዩኒቨርስቲዎች ውስጥ በማስተማርና በምርምር ላይ ያሉ ኢትዮጵያውያን ቊጥር ቀላል አይደለም። በንግዱ ዓለምም ቢሆን፥ "የሺ ብር ጌቶችን" ጓዳ ይቊጠራቸው። 
የለም፥ የተፈጥሮ ሀብት ባለጠጋ የሆነች ኢትዮጵያ ብልሁ ሕዝቧ ለምን እንደሚራብ የተከበረ ጥናት መደረግ አለበት። ዋና ዋናዎቹን ምክንያቶች ፕሮፌሰር ስዩም ገላየ ደርድሯቸዋል። አንዱ፥ የመሬት ይዞታ መበላሸት ነው ይለናል። "የመሬት ላራሹ" ጩኸት ውጤቱ "መሬት ለነጋሹ" ሆኗል፤ ለገበሬው የታሰበውን መሬት ወያኔ ወሰደው። የዱሮ ንጉሣዊ ገዢዎቿ ቤተ ሰቦች ስለነበሩ በቊጥራቸው ማነስ ምክንያት እነሱን በማር ግብር ለማጥገብና በሰላም ለመኖር ቀላል ነበረ። የዛሬዎቹ ገዢዎች ብሔረ ሰቦች ስለሆኑ እነሱን ሁሉ በሚሊዮን ዶላር ማጥገብ መራቆትን አስከትሏል። ሌላው፥ አገሪቱ በክልል መከፋፈል ነው። ማንም ሰው በገዛ ሀገሩ ከመሰለው ክፍለ ሀገር ሄዶ በሰፊው ማረስ አይችልም። ዛሬ ኢትዮጵያ ለአንድ ኢትዮጵያዊ ሙሉ በሙሉ አገሩ አይደለችም። ኢትዮጵያ ለልጆቿ እናትነቷ በሙሉ ሰውነቷ እንዳይሆን ተከልክላለች። 
 የታሪክ ተመራማሮዎችም ያዩት ምክንያት ይኖራቸዋል። ክርስቲያኖችና እስላሞች፥ ኦሮሞዎችና ሌሎች መሆናችንን ዐውቀን በብልህነት አለማስተናገዳችን ጒዳት እንዳመጣብን ይናገራሉ። ሁላችንም የአንድ ሃይማኖት ተከታዮች፥ አንድ ቋንቋ ተናጋሪዎች ብንሆን ኖሮ ከምሰሶ ጋር በእግር ብረት እንደተቈራኘ ሰው እጃችንን ብቻ ወደ እግዚአብሔር እያደረስን አንድ ዘመን ላይ ቆመን አንቀርም ነበር ይላሉ።  
  በሃይማኖት አንድ ባለመሆናችን ያስከተለውን ጕዳት ለማሳየት የአክሱምን ሥልጣኔ ያከሰመውን የጉዲትን አመፅና የአምሐራን ("የአማራን" ማለቴ አይደለም)ሥልጣኔ እሳት የለቀቀበትን የግራኝን ወረራ ይተርካሉ።

እነዚህ ሁለት ሥልጣኔዎች ኢትዮጵያን በዚያ ዘመን ከገነኑ አገሮች እኩል አስሰልፈዋት ነበረ፤ ጠፉ፤ ባለንበት ቆመን ቀረን። 
ዛሬ ስለሁለቱ ሥልጣኔዎች የምናውቀው ከመጥፋታቸው በፊት ከተጻፈው ታሪካቸውና ከጥፋት ካመለጠው  ርዝራዣቸው ነው። ሀገሪቱ ከግራኝ ምች ልታንሰራራ አልቻለችም። የግራኝ ምች የምለው እስላሞች በዓሥራ ስድስተኛው ምእት ዓመት በክርስቲያኖች ላይ ያደረሱትን ጒዳት ነው;ታሪኩን ክርስቲያኖቹ በሐዘን፥እስላሞቹ በደስታ መዝግበውታል፤ ዛሬም በዚያው ስሜት ያስታውሱታል። የደረሰው የሰውና የንብረት ጥፋት ሁሉ የሚያሳዝን ቢሆንም፥ሁልጊዜ የሚታወሱኝ ቅጂ ያልተገኘላቸው ስማቸው ብቻ የቀረልን ብርቅ ድርሰቶች ናቸው።
እስላሞቹ ክርስቲያኖቹን ለማጥፋት ከጂሃድ በቀር ሌላ ምንም ምክንያትአልነበራቸውም። መንግሥቱን ተወደደም ተጠላ ያቋቋሙት ክርስቲያኖቹ  ነበሩ። ከሀገሪቱ ክፍል ሱማሌዎችና ይፋቴዎች እንደሚኖሩባቸው አንዳንድ ክፍሎች ሲሰልሙ፥ በኢትዮጵያ ስር ሆነው ራሳቸውን በራሳቸው እንዲያስተዳድሩ ሙሉ ሥልጣን ተሰጥቷቸው ነበረ። በዛሬው ዓይናችን እንኳ ስናየው፥ የንጉሣዊው መንግሥት ከዚህ የተሻለ ሌላ ምን አማራጭ አገዛዝ ነበረው? የጂሃዱ መንሥኤ ኦርቶዶክሱን ሕዝብ በሞላ አስልሞ በሸሪዓ ሕግ መግዛት  ነበር። 
እስላሞቹ፥ "መንግሥቱን ወስደን፥ ክርስቲያኖቹ ራሳቸውን እንዲያስተዳድሩ እናደርጋለን" ቢሉ እንኳን ያባት ነበር። ኦሮምኛ ተናጋሪዎችና ሌሎች መሆናችን ያስከተለውን ጕዳት ለማሳየት ደግሞ የኦሮምኛ ተናጋሪ ጎሳዎችን ወደማህል ኢትዮጵያ የመፍለስ ታሪክ ይተርካሉ። ለአባ ባሕርይና የዘመኑን ነገሥታት ታሪክ ለጻፉ፥ በተለይም ለተክለ ሥላሴ ጢኖና ለተክለ ኢየሱስ ዋቅጂራ ምስጋና ይድረሳቸውና የኦሮሞ ጎሳዎች ወደማህል ኢትዮጵያ ፍልሰት ያስከተለው የሥልጣኔ ውድመት ከብዙው በጥቂቱ ተመዝግቧል። ኦሮምኛ የሚናገሩ ጎሳዎች የእስላሞቹ አመፅ በተገታ ማግስት ፈልሰው፥ ከእስላሞቹ የተረፈውን የሥልጣኔ ምልክት ጠራረጉት። ጋዳ በሚሉት ሁሉን ለጦርነት በሚያሰልፍ የማፊያ ሥርዓት በውትድርና ተደራጅተው፥ በግብርና፥ በንግድ፥ በድብትርና ("በዕውቀትና በምርምር"ማለቴ ነው) የሚተዳደረውን ሰላማዊ ሕዝብ አረዱት፤ ንብረቱን አወደሙት። በእርሻው፥ በሰብሉ ላይ ከብታቸውን አስሠማሩበት። በባህላቸው መሠረት፥ ክርስቲያን ያልገደለ በቅማል ይሰቃያል እንጂ ራሱን አይላጭም ነበር። ሸዋን፥ ጎንደርን፥ ጎጃምን፥ አምሐራን (የዛሬውን ወሎ) ደመሰሷቸው።  
እስላሞቹ የክርስቲያኖቹን ሥልጣኔ አጥፍተው በራሳቸው ሥነ ጽሑፋዊ ሥልጣኔ ሊተኩት አስበው ነበረ። ኦሮምኛ ተናጋሪዎቹ ግን እረኞች ስለነበሩ ሥልጣኔን በሥነ ጽሑፋዊ ሥልጣኔ የመተካት ግዴታ አልነበረባቸውም። ግን በባህል ረገድ ከወረሩት ሕዝብ አብዛኛውን እንደነሱ ኦሮምኛ ተናጋሪ፥ የቀረውን ገበር (አሽከር) አደረጉት። እስላሞቹና ኦሮምኛ ተናጋሪዎቹ ሰውና ቅርስ ባወደሙበት ቦታ ሁሉ ሐውልት ቢቆም ሀገሪቱ "ሀገረ ሐውልት" ትሆን ነበረ።  
  ከግድያቸው ሰለባቸው ይብስ ነበረ። ባለቅኔው፥ "ጃዊ ቀደደ ሆድ ሆድሆዶሙ ወሰለቦሙ እስከ ሕምብርት" (ጃዊ ሆድ ሆዳቸውን ቀደደው፤ እምብርታቸው ድረስ ሰለባቸው) ያለው በጎንደር ዘመነ መንግሥት የደረሰውን መቅሠፍት አይቶ ነው። የሆነውን በታሪክ ዓይን አይቶ በማለፍ ፈንታ፥ ዛሬ አቻው እንዲሆን ታስቦ ያልሆነ፥ ያልተደረገ የአረመኔነት ታሪክ ለራስ ጎበና ዳጨ ወታደር መፍጠር፥ ግፋ ቢል ሞኞችን በሞኝነታቸው እንዲኖሩ ከማድረግ የበለጠ አገልግሎት አይኖረውም። ውሸት ታሪክ አይሆንም።  
  ማንም መጥቶ ኢትዮጵያ ውስጥ ቢሰፍር የኢትዮጵያ ነገሥታት አይከለክሉም ነበር። ሰው የሌለበት ሰፊ ቦታ ስለሞላ ማንም ከዚያ ቢሰፍር ማን ነህ የሚለው አልነበረም። ችግሩ፥ ኦሮምኛ  ተናጋሪ ጎሳዎች ከአንድ ቦታ ፈልሰው ከባዶ ቦታ በመስፈር ፈንታ፥ ሌሎች ያቀኑትን ቦታና ያተረፉትን ቅርስና ውርስ እንንጠቅ ማለታቸው ነበር። በዚያ ላይ፥ ማህል ኢትዮጵያን ከያዙ በኋላ፥ ለኢትዮጵያ መንግሥት አንገብርም ማለትን አመጡ። በዚህ ጊዜ የንጉሣዊው መንግሥት ምርጫ ምን መሆን ነበረበት?  

  
ያምናው በሽታ፤ 

  በዚህ እኛ ባለንበት ዘመን፥ እስላሞች ቤተክርስቲያን ሲያቃጥሉ፥ አንዳንድ ኦሮምኛ ተናጋሪዎች ሰላማዊውን ሰው በሕይወት ገደል ሲሰዱ፥ በ ዩቲዩብ  (youtube) ሳይ፥ ሰውየው፥ "ኧረ እናንተ ሰዎች ሰው አይድንም ታሞ፤ ያምናው በሽታየ አገረሸ ደግሞ፡" ያለው ትዝ አለኝ። በሽታውን ማስገርሸት አንዱን ጠቅሞ ሌላውን አይጐዳም። ሁሉም ተጐጂ ነው የሚሆነው። ሁል ጊዜ ሳይሞቱ መግደል አይቻልም። 
ሌላውን የሚገድሉት እየሞቱ ነው። በዚያ ላይ በማህል ቤት የሚሆነውን ማንም አያውቀውም። ለምሳሌ፥ የኦሮሞን አመፅ ይመሩ የነበሩ የወለጋ ፕሮቴስታንቶች እንደነበሩ ይታወሳል። አሁን አመፁን ከነሱ ተቀብለው በኦሮሞ ስም የሚያካሂዱት፥ "ከኦሮሞው ሕዝብ አርባ በመቶው እስላም ነው" የሚሉ የኦሮሞ እስላሞች ናቸው። ቊጥራቸውን ቢያጋንኑትም፥ እስላሞቹ ከፕሮቴስታንቶቹ መብለጣቸው አያጠራጥርም።  እንግዲህ፥ የፕሮቴስታንት ክርስቲያኖች በኦርቶዶክስ ክርስቲያኖች መንግሥት  ላይ  ያካሄዱት ትግል በፍትሐ ነገሥት ቀርቶ በሸሪዓ ሕግ በሚያምኑ ወገኖች ለመተዳደር ሊሆን ነው።  የግብጽ ክርስቲያኖች የመለካውያን ክርስቲያኖችን የበላይነት በመጥላት አገሪቷን ዐረቦች እንዲወስዷት ረድተው፥ ዋጋ ከሌለው ጸጸት ላይ እንደወደቁ የምናየው ነው። 


 የመጀመሪያው እርምጃ፤ 

ከላይ እንደገለጥኩት፥ እስላሞችና ኦሮምኛ ተናጋሪ ጎሳዎች ኢትዮጵያን እንዴት እንዳቈረቈዟት ታሪኩ እንዳይፋቅ ሆኖ ተጽፏል፤ የሚፈለገው ግን ዕርቅና ሰላም እንዲወርድ ነው።ዕርቅና ሰላም የሚወርድ ከሆነ፥ታሪኩ ባይፋቅም ተከቶ ከድንቊርናና ከረኀብ የምንላቀቅበትንና ከፍተኛ የማሰብ ችሎታ እንዳለን የምናስመሰክርበትን ብልሀት ልንፈልግ እንችላለን።ለዚህም መሆን ያለበት የመጀመሪያው እርምጃ አባቶቻችንን እንወክላለን የሚሉ እስላሞችና ኦሮሞዎች የአባቶቻቸውን ጥፋት ከመቀጠል አባቶቻችው በኢትዮጵያ ላይ ላደረሱት መጠን አልባ ጥፋት የኢትዮጵያን ሕዝብ ይቅርታ መጠየቅ ይሆናል። 
የጥፋቱን ታሪክ ጸሐፊዎቹ ለወገኖቻቸው እያዳሉ ጽፈውታል እንዳይሉ፥የጻፉት ራሳቸው እስላሞቹ እነሽሀብ እዲን ዐረብ ፈቂህ፥ የአማራውና የኦሮሞ ተወላጆች እነ አባ ባሕርይ፥ እነ ተክለ ሥላሴ ጢኖ፥ እነ ተክለ ማርያም ዋቅጂራ ናቸው። ታሪካችንን ደብተራዎች አይጽፉትም የሚሉ ካሉ፥ የጸሐፊዎቹን ማንነት ባለማወቅ ሊሆን ይችላል። የሌሎችም ታሪክ ጸሐፊዎች ስማቸውና ሥራቸው "የአባ ባሕርይ ድርሰቶች፤ ኦሮሞችን ከሚመለከቱ ሌሎች ሰነዶች ጋራ"  በተባለው መጽሐፌ ውስጥ ተዘርዝሯል።  ይህን መጽሐፍ ብዙ ሰው ስለሚፈልገው፥ ማንም ሰው  እያወረደና እያተመ  እንዲያነበው በማሰብ፥ www.ethiopiawin.net or www.ethiopiawin.org  ብለን ካቋቋምነው ድረ ገጽ ላይ ተለጥፏል። ኢትዮጵያን ለማገልገል ላቋቋምነው ድርጅት እርዳታ የሚሆን በፈቃድ ከሚሰጥ ገንዘብ በቀር የመጽሐፉን ዋጋ አንጠይቅም።  

ሁለተኛው እርምጃ፤ 

ሁለተኛው እርምጃ ኦሮምኛ ተናጋሪዎችን የሚመለከት ነው፤ አፄ ምኒልክና ራስ ጎበና ዳጨ ስፍር ቊጥር በሌለው ጎሳ የተበታተኑትንና እርስ በርሳቸው የሚባሉትን ኦሮምኛ ተናጋሪዎች አንድ ያደረጉበትን ቀን በየዓመቱ ማክበር አለባቸው። ግን ሁሉንም አንድ ያደረጉት በአንድ ቀን ድል ስላይደለ፥  የትኛውን ቀን እንደሚያከብሩ በጨፌያቸው ሊወስኑት ይችላሉ። ሆኖም በአፄ ምኒልክ ሐውልት ስር አበባ ማስቀመጥ የበዓሉ ክፍል መሆን አለበት። ራስ ጎበና ሐውልት ስለሌላቸው፥ ሳይውል ሳያድር ከተከበረ አደባባይ ላይ የጎላ ሐውልት እንዲተከልላቸው ባለውለታዎቹ መገፋፋት ይኖርባቸዋል።        

ሶስተኛው እርምጃ 

ሶስተኛው እርምጃ አስተሳሰብን ከሰብአ ትካት አስተሳሰብ ወደ ሰብአ ዘመን አስተሳስብ ማራመድ ነው። '"ሰብአ ትካት" በእንግሊዝኛ  primitive people የሚባሉት ናቸው። አስተሳሰባቸው ከመንደራቸው ርቆ አይሄድም፤ የዚያኛው መንደር ሰው ጠላታቸው ነው፤ የዚያኛው ብሔረ ሰብ አባል ባለጋራቸው ነው። "ሰብአ ዘመን" modern man ነው። መንደሩ ጠቅላላዋ ሀገር ነች። በሰብአ ዘመን አስተሳሰብ የዚያ መንደር ወይም የዚህ መንደር ነባር መሆንና የዚያ ቋንቋ ወይም የዚህ ቋንቋ ተናጋሪ መሆን ዋጋ ሊሰጠው የማይገባ አጋጣሚ ነው። የሰብአ ዘመን አስተሳሰብ ከዚያም መጥቆ ሄዶ ዓለም አቀፍ ላይ ይድርሳል። በሰብአ ትካት አስተሳሰብ ያሉ ብሔርተኞችን በአንድ ጊዜ ወደዓለም አቀፍ አስተሳሰብ ይሸጋገራሉ ብለን አንገምትም፤ ለጊዜው ፍላጎታችንም አይደለም። ግን በሰላምና በብልጽግና ለመኖር ከብሔርተኛነትና ከሰብአ ትካት አስተሳሰብ ወጥቶ ዲሞክራት መሆን አማራጭ የሌለው እርምጃ ነው። በአካል የሰብአ ዘመን አባል ሆኖ በአስተሳሰብ ሰብአ ትካት መሆን፥ "የሚራቡት የማሰብ ችሎታቸው ዝቅተኛ ቢሆን ነው"  ለሚለው ጥናት ማስረጃ መሆን ነው። እንደማየው፥ ብሔርተኞች ከዲሞክራሲ ጋር ያላቸው ግንኙነት በፍቅርና በጥላቻ የተሳሰረ ነው። የዲሞክራሲ ዋና መለዮ ሰብአዊ መብቶችን ማስከበር ነው። በአሁኑ ሰዓት ከገዢዎቹና ከደጋፊዎቻቸው በቀር ይኸንን የማይቀበል ያለ አይመስለኝም። እዚህ ላይ ብሔርተኞችና ዲሞክራሲ ፍቅረኞች ናቸው። ግን  ሰብአዊ መብቶች የሚባሉት የግለሰብ ብቻ ናቸው ወይስ ማኅበሮችና ብሔረ ሰቦችም ሰብአዊ መብቶች አሏቸው? የላቸውም ከተባለ፥ ብሔርተኞች ዲሞክራሲን አይቀበሉም።  

መብት በመሠረቱ የግለሰብ ነው። ሆኖም ብሔረሰቦች በደፈናው መብት የላቸውም አይባልም። አቅም ካላቸው ቋንቋቸውንና ሌላ ሌላ ባህላቸውን ማዳበር መብታቸው ነው። ይኸንን በሥራ ላይ ለማዋል ሲሰበሰቡ ጸጥታቸውን መንግሥት ያስከብርላቸዋል። የአንድ ሀገር ሕዝብ ሆኖ ብሔረሰባዊ  ፓርቲ መመሥረት ግን ከሌላው ብሔረ ሰብ ጋር የጋራ ጥቅም የለንም ማለት ይሆናል። የፓርቲ መሠረቱ የግለሰብን ሕይወት በኢኮኖሚ እድገት ማሻሻል ነው። ለዚህ ዓላማ ፓርቲው ጉራጌ፥ አደሬ፥ ጉጂ፥ ወዘተ መሆን የለበትም።  ሆኖም፥ የብሔረሰብ አባላት በይፋ አድመው ድምጻቸውን ይጠቅመናል ለሚሉት ፓርቲ ሊሰጡ ይችላሉ። በዲሞክራሲ አስተዳደር ብሔርተኞች ብሔራቸውን የሚጠቅሙት በዚህ መንገድ ብቻ ነው።            
 
 

Saturday, February 15, 2014

ፓትርያርኩ ማኅበረ ቅዱሳን የጠራውን ሀገራዊ የሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ጉባዔ ማገዳቸው ትክክል ነው!!


«መታገድ» የሚለውን ቃል በአሉታዊ ምልከታ ለማራገብ ካልተሞከረ በስተቀር ባለእባብ ዓርማው ማኅበረ ቅዱሳን የጠራውን ስብሰባ መታገድ በተመለከተ የሚያሳየው  የትርጓሜ እውነታ ግን በትክክለኛነቱ ተቀባይነት ያለው ውሳኔ ነው። ለዚህም ከበቂ በላይ ምክንያቶች አሉን።
1/ ማኅበረ ቅዱሳን የተባለውን ማኅበር ቤተ ክርስቲያኗ ያላቋቋመችውና ከብላቴ ጦር ምላሽ በጎ ፈቃደኞች የመሠረቱት ሲሆን የቤተ ክርስቲያኗ የውክልና ድርሻ ስለሌለው የትኛውንም የቤተ ክርስቲያን አባል በመጥራት መሰብሰብ አይችልም።
2/ ማኅበረ ቅዱሳን በጥቂት ደጋፊዎቹ ተነስቶ የሲኖዶስ አባል የሆኑትን ጳጳሳት በመጠምዘዝ፤ በማስፈራራትና በጥቅማ ጥቅም በማታለል ለራሱ ብቻ የሚጠቅመውን መተዳደሪያ ደንብ በማስጸደቅ ቤተ ክርስቲያንን ተለጥፎ በሕይወት ለመቆየት ከመቻሉ በስተቀር የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን እንደልማት ማኅበር ወይም እንደ በጎ አድራጊ ድርጅት ወይም እንደመንፈሳዊ ተቋም የመሠረተችው አይደለም። ስለዚህ አሀዳዊትና ሐዋርያዊት በሆነችው የክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ሌላ ማኅበር ሊኖር ስለማይገባው ማኅበረ ቅዱሳን ማንንም የቤተ ክርስቲያን አባል በማደራጀት መንቀሳቀስ አይችልም።
3/ ቤተ ክርስቲያኒቱ ከቅዱስ ሲኖዶስ አንስቶ በሊቃነ ጳጳሳት የሚመራ የሀገረ ስብከት ጽ/ቤቶች በተዋረድ ያላት ተቋም ሆና ሳለ በሽብልቅ የገባው ማኅበር ይህንን የመዋቅር ሰንሰለት በጥሶ ለራሱ ዓላማና ግብ በመንፈሳዊ ካባ ተጠልሎ ስብሰባ የማካሄድ፤ የመጥራት፤ የማደራጀት፤ የመምራት ስልጣን የለውም።

4/ ማኅበረ ቅዱሳን በልማት ማኅበር ወይም በእርዳታ ድርጅት ወይም ራሱን በቻለ መንፈሳዊ ተቋምነት ወይም በሌላ መሰል ስያሜ የሀገሪቱ ሕግ በሚፈቅደው አግባብ እውቅና አግኝቶ የተፈቀደለትንና የሚችለውን ሀገራዊና መንፈሳዊ ዓላማ ከማከናወን በስተቀር በሲኖዶስና በማኅበር የሚመራ ሁለት አስተዳደር ቤተ ክርስቲያኒቱ መሸከም የለባትም። ስለሆነም የፓትርያርኩ እግድ የስልጣን ተዋረድንና ኃላፊነትን ያገናዘበ በመሆኑ ትክክለኛ ውሳኔ ነው።
5/ ለወደፊትም ቢሆን ቁርጡ በታወቀ ቁመና የማኅበረ ቅዱሳን ማንነት መታወቅ አለበት። ስለሆነም እጅ እየጠመዘዘ ያስጸደቀው መተዳደሪያ ደንብ ቀሪ ሆኖ በራሱ ግዘፈ አካል፤

   ሀ/ በሰንበት ትምህርት ቤቶች አወቃቀር የቤተ ክርስቲያን መንፈሳዊ ማኅበር ለመሆን ከፈለገ ያለውንና ያፈራውን ሀብትና ንብረት ለቤተ ክርስቲያኒቱ በማስረከብ ለሰንበት ተማሪዎች በተሰጠው የቤተ ክርስቲያኒቱ ተቋማዊ መመሪያ መሰረት መተዳደር አለበት።
  ለ/ የሰንበት ትምህርት ቤቶችን ለማደራጀት በወጣው ህገ ደንብ የመተዳደር ፈቃደኝነቱ ከሌለው የአባልነት ምልመላ፤ የገንዘብ አቅምን የማጎልበት፤ አስተዳደራዊ መዋቅሩን የመዘርጋትና የማንነት አቅም ማጎለበቱ ከቤተ ክርስቲያኒቱ መዋቅር ውጪ የመሆን አዝማሚያ እንዳለው እያየን ነውና ሀገሪቱ በምትሰጠው መብት በፍትህ ሚኒስትር ተመዝግቦ ሊንቀሳቀስ ይገባዋልና ቅዱስ ፓትርያርኩ የጀመሩትን መልክ የማስያዝ ጅማሮ ከፍጻሜ እንዲያደርሱ እንጠይቃለን።

Monday, February 10, 2014

አዲሱ የሃይማኖት ህግና የሀገሪቱ ህገመንግስት!



 ( ጽሁፍ በሰሎሞን )
(ማስታወሻ ከደጀ ብርሃን) አንዳንዶች እንደሚሉት ሳይሆን ኢትዮጵያ ከሉላዊው ዓለም ውጪ ካለመሆኗም በላይ በአፍሪካ ቀንድ እንደመገኘቷና ካላት የረጅም ዘመን ታሪክ አንጻር ከአሸባሪነት አደጋ ነጻ አይደለችም የሚለውን ሚዛናዊ ስፍር እንቀበላለን። በተለይም ሃይማኖታዊ ፍልስፍና በሚንጠው የክፍለ ዘመኑ የጽንፈኝነት አተያይም ለሀገራችን የሚበጀውን የሰላም ጎዳና ሁሉ መደገፋችን እውነት ነው። ይህንን ሀገራዊ ሰላም ለማስጠበቅ መንግሥት የሚያከናውናቸው ከእምነት ተቋማት ጋር የሚያደርገው የውይይት፤ የመረዳዳትና የጋራ ግንዛቤን የመያዝ የጋራ ኃላፊነት ስምምነቶችንም በበጎነቱ እንጠቅሳለን። ከውይይትና ከጋራ ግንዛቤ ስምምነቶቹም ባሻገር ሕጋዊ ማዕቀፎችን በማዘጋጀት ጽንፈንነትንና አክራሪነትን ለመከላከል የሚያስችሉ የሕግ አግባቦችንም መቅረጹ ከአስፈላጊነቱ የሚጠቀስ እንደሆነም እንረዳለን። ነገር ግን ፍርሃትን ለማስቀረትና ጽንፈኝነትን ለመዝጋት እንችላለን በሚል ጥቅል እሳቤ የተነሳ መንግሥት ብቻውን ይበጀኛል የሚለውን የሕግ አግባብ ለመቅረጽና ለመተግበር የሚያደርገው ጥረት አያዋጣም ብቻ ሳይሆን ውጤቱ እጅግ አደገኛ ሊሆን እንደሚችል አስቀድሞ አለመገመቱ ያሳስበናል። ሕግ የሚቀረጸው በህጉ ተጠቃሚ የሚሆነውን ሕዝብ ሰላምና ደህንነት በማረጋገጥ ማኅበራዊ ዋስትናውን ማስቀጠል እስከሆነ ድረስ ከዚያ ሕዝብ በተለይም ስስ ከሆነው የሕዝብ የእምነት ስሜት ውጪ ሕግ ለማውጣት መሞከር ከጠቃሚነቱ ጎጂነቱ ስለሚያመዝን መንግስት የሃይማኖት ተቋማትን አስመልክቶ ያወጣውን ሕግ ለማጽደቅ የሚያደርገውን መጣደፍ ቆም ብሎ እንዲመለከት ለማሳሰብ እንወዳለን። በሁሉም ነገር ላይ የሁሉም ስምምነት ይኖራል ተብሎ ባይጠበቅም ሃይማኖትን በተመለከተ የሚወሰዱ የህግ አግባቦች ግን የእምነቱ ባለቤቶች ያደረጉት አብላጫው የጋራ ውይይትና ስምምነት ይበልጥ ውጤታማ ስለሚሆን ሕግ ከማጽደቅ በፊት ውይይቱ ይቅደም እንላለን።)  ከዚህ በታች ያለው ጽሁፍ «በኢትዮ-ክርስቲያን መረጃ መረብ በአቶ ሰሎሞን የቀረበና የእምነት ተቋማትን የመመሪያ ረቂቅ በህገ መንግሥቱና በማኅበረሰባዊ ምልከታ ያለውን የፍትህ ሚዛን ያሳያልና ሳይሰለቹ እንዲያነቡት ጋብዘንዎታል።
መንግሥት ሕገ-መንግስቱን ሊያከበር ይገባል! (ከእምነት ቤቶች) 
  በፌደራል ጉዳዮች ሰብሳቢነት ከተለያዩ ቤተእምነቶች የተሰባሰቡ ተወካዮች በጉዳዩ ላይ እንድንወያይ ስንጠየቅ ይህ  የሀገሪቱን ህገመንግስት ይቃረናል እኛም እዚህ ተወክለን የመጣነው ለሌላ ጉዳይ እንጂ በህግ ላይ ህግ ለማውጣት አይደለም ብለን አጀንዳው እንዲመለስ አድርገናል(ከተስባሲቢዎች አንዱ) 
“ኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች መርጠው በላኳቸው ተወካዮቻቸው አማካይነት ሕዳር 29 ቀን 1987 ዓ.ም  የኢትዮጵያ  ፌደራላዊ  ዲሞክራሲያዊ  ሪፐብሊክ  ሕገ  መንግስትን  በአዋጅ  ቁጥር  1/1987 ያጸደቁት”  ሕገ  መንግሥትን  መንግሥት በተለያዩ  ጊዜያት  እየጣሰ  መሆኑን  የሀገሪቱ  የተለያዩ ህብረተሰቦችና ተቋማት መናገር ከጀመሩ ሰነባብተዋል፡፡  
 በቅርቡ  ደግሞ  “በፌደራል  ጉዳዮች  ሚኒስቴር  የተዘጋጀ  የሃይማኖት  ድርጅቶች  እና  ማኅበራትን” አስመልክቶ የወጣው “መመሪያ” የተጠቃሻቹ የሃይማኖት  ድርጅቶች  እና  ማኅበራትን  በበቂ  ሁኔታ ሃሳባቸው  ሳይሰማና  በማያውቁት  ሁኔታ  ሥራ  ላይ  በማዋሉ  ምክንያት  የሃይማኖት  ድርጅቶችና ተቋማትን   በተለይም  ደግሞ  የክርስትና  እምነት ተከታዩ ኅብረተሰቡን በእጅጉ የማጉረምረሚያ ሃሳብ ከመሆን አልፎ መንግሥት መመሪያውን በድጋሚ እንዲያስብበት በመጠየቅ ላይ ይገኛሉ፡፡ ኢትዮጵያና  ሃይማኖት  የአምስት  ሳንቲም  ግልባጮችና  ፈጽሞ  ሊለያዩ  የማይችሉ  መሆኑን  መንግሥት በ1997 ዓ.ም ያወጣው  እስታስቲክስ  62.8  ከመቶ  ክርስቲያን፣  33.9  ከመቶ  ሙስሊም  ፣  2.7  ከመቶ ባህላዊ እምነት ተከታይ  ፣ 3.3 ከመቶ ሌሎች  እና ስለ እምነታቸው መልስ ያልሰጡ ደግሞ 0.6 ከመቶ መሆኑን ባሳየው  እስታስቲካዊ  መረጃ  አረጋግጣአል፡፡ ይህ እስታስቲካዊ  አሃዝ እንደሚያሳየው  በሀገሪቱ ውስጥ  ያለእምነት  የሚኖር  ከቁጥር  የማይገባ መሆኑንና  በአጠቃላይ  በሃገሪቱ  የሚኖሩ  ዜጎች  100 ፐርሰንት  ሃይማኖተኛ  እንደሆኑ ያሳያል፡፡ በመሆኑም ኢትዮጵያን  ማለት  ሃይማኖተኛ  የበዛባት ሃገር ማለት ሳትሆን ራሷ ሃይማኖት ማለት ናት  ብንል የምንሳሳት አንሆንም፡፡ ስለዚህ መንግሥት ሃይማኖትን  አስመልክቶ የሚያወጣቸው መመሪያዎች ከፍተኛ  ጥንቃቄ የታከለበትና ከሕገመንግሥቱ ሃሳብ ጋር የማይቃረን ማድረግና በሕገ መንግስቱ ውስጥ የተገለጡትን ሃይማኖታዊ መብቶች የማክበርና የማስከበር ኃላፊኑን ካልተወጣ  ሀገሪቱን ወዳልታሰበ ቀውስ ውስጥ ሊከታት ይችላል ብለው ያሳሰባቸው ጥቂቶች አይደሉም፡፡  
 ሕገ መንግሥቱ  በአንቀጽ 27 በግልጽ  ለሕዝቡ ያረጋገጠለትን  ተፈጥሯዊ  የሃይማኖት  ነጻነቱን  ወንጀል እስካልፈጸሙ  ድረስ  ሊያከብርለትና  ሊያስከብርለት  ይገባል  እንጂ  ሊሸራርፍ  የሚችል  ሕግ  ወይም መመሪያ ሊያወጣ በምንም መልኩ ሕገ መንግስታዊ መሠረት የለውም፡፡  
 በአሁኑ ጊዜ ከረቂቂነት አልፎ የሃገሪቱ መመሪያ በመሆን ሥራ ላይ የዋለው የሃይማኖት ድርጅቶችንና ማኅበራትን  አስመልክቶ  የወጣው  መመሪያ  በሚኒስቴሩ  መስሪያ ቤት  የተዘጋጀ  መሆኑንና  መጠቀሻውም “የሃይማኖት  ድርጅቶችን  እና  ማኅበራትን  ለመመዝገብና  ተዛማጅ  አገልግሎቶችን  ለመስጠት  የወጣ መመሪያ  ቁጥር  1/2005 ተብሎ  ሊጠቀስ”  እንደሚችል  “ክፍል  አንድ  ጠቅላላ”  ከሚለው  አንቀጽ  ሥር በንዕስ  አንቀጽ  ሁለት  ላይ  ይናገራል፡፡  ይሄው  መመሪያ  በዘጠኝ  ክፍል  ተከፋፍሎ  45  አንቀጾች  ያሉት ሲሆን በእያንዳንዱ አንቀጽ ሥር ከ 2-15 ንዑስ አንቀጾችን ያቀፈ ነው፡፡  
ወደዚህ  መመሪያ ዝርዝር  ይዘቱ  ከመምጣታችን  በፊት  በሕገ  መንግሥቱ  በአንቀጽ  11 “የመንግሥትና የሃይማኖት  መለያየት”  በሚለው  አንቀጽ  ሥር  ንዑስ  አንቀጽ  1-3  የተቀመጠውን  ብንመለከት “መንግሥትና   ሃይማኖት   የተለያዩ   ናቸው፡፡   መንግሥታዊ   ሃይማኖት   አይኖርም፡፡   መንግሥት በሃይማኖት  ጉዳይ  ጣልቃ  አይገባም፡፡  ሃይማኖትም  በመንግሥት  ጉዳይ  ጣልቃ  አይገባም፡፡” በሚል በግልጽ መንግስትና ሃይማኖትን የማይገናኙ እንደሆኑ ይናገራል፡፡ 
እንደገናም ይሄው ሕገ መንግሥት በአንቀጽ 27 “የሃይማኖት፣ የእምነትና የአመለካከት ነጻነት”በሚለው አንቀጽ ሥር ንዑስ አንቀጽ1 እና 2 የተቀመጠው ብንመለከት “ማንኛውም ሰው የማሰብ  ፣ የሕሊና እና የሃይማኖት  ነጻነት  አለው፡፡  ይህ  መብት  ማንኛውም  ሰው  የመረጠውን  ሃይማኖት  ወይም  እምነት የመያዝ  ወይም  የመቀበል  ሃይማኖቱንና  እምነቱን  ለብቻ  ወይም  ከሌሎች  ጋር  በመሆን  በይፋ  ወይም በግል የማምለክ የመከተል የመተግበር የማስተማር ወይም የመግለጽ መብትን ያካትታል፡፡ በአንቀጽ 90 ንዑስ  አንቀጽ 2  የተጠቀሰው  እንደተጠበቀ  ሆኖ  (ስለአስኮላ ትምህርት  ቤት የትምህርት ይዘታቸው በሚመለከት የሚናገር አንቀጽ ነው) የሃይማኖት ተከታዮች  ሃይማኖታቸውን ለማስፋፋትና ለማደራጀት የሚያስችላቸው  የሃይማኖት  ትምህርትና  የአስተዳደር  ተቋማት  ማቋቋም  ይችላሉ”  ይላል፡፡(ጽሑፉን ያወፈርንና ያሰመርንበት ልብ ይሉት ዘንድ እኛው ነን) እንደገናም  አንቀጽ  ዘጠኝ በ “ሕገ  መንግስት  የበላይነት” በሚለው  አንቀጽ  ሥር  ንዑስ  አንቀጽ 4 ላይ “ኢትዮጵያ  ያጸደቀቻቸው  ዓለም  አቀፍ  ስምምነቶች  የሃገሪቱ  ሕግ  አካል  ናቸው፡፡”  በሚል  ተቀምጧል፡፡ በዚህም መሰረት ኢትዮጵያ ያጸደቀቻቸው ዓለም አቀፋዊ ሕጎችና ቃልኪዳኖች እኤአ የ  1966 የሲቪልና የፓለቲካ መብቶች ዓለም አቀፋዊ ቃልኪዳን ስምምነቶች ውስጥ ሃይማኖታዊ መብትን እውቅና ይሰጣል፡፡ ስለዚህ በሕገ መንግሥቱ በአንቀጽ 27 ንዑስ አንቀጽ 5 በግልጽ እንደተቀመጠው “መንግሥት ሃማኖትና እምነትን  የመግለጽ  መብትን  ሊገድብ  የሚችለው  የሕዝብን  ደህንነት፣  ሰላም፣  ጤናና  ትምህርት፣ የሕዝብን የሞራል  ሁኔታ የሌሎችን ዜጎች መሠረታዊ መብቶች፣ ነጻነቶች እና መንግሥት ከሃይማኖት ነጻ  መሆኑን  ለማረጋገጥ” ካልሆነ በቀር በምንም መልኩ የሃይማኖትን  የትምህርትና የአስተዳደር ተቋማዊ ቅርጾቻቸውን ሊወስንላቸው፣ደንብ ሊቀርጽናቸው፤ እኔ  በምፈልገው  መልኩም  ተደራጁ ሊላቸውና  በመካከላቸውም ጣልቃ እየገባ እንደ አወቃቀራቸውን ሊወስንላቸው አይችልም፡፡  ሃይማኖተኞቹ በሚያምኑት መንገድ መዋቀር ሳይሆን መንግስት በሚፈልገው መንገድ ለመዋቀር ማመን አለባቸው ማለት ነው።
 ይሁን እንጂ መመሪያው እነዚህን ተፈጥሯዊና ሕገ መንግስታዊ የሃይማኖት መብት ክፉኛ የሚጥስ ብቻ ሳይሆን ዕውቀት ጎደል መሆኑ ጭምር ጥቂት ክፍሎችን ብቻ ለዋቢነት እየጠቀስን እንመልከት፡፡            
 በአንቀጽ  5  የሚንስቴሩ  ስልጣንና  ተግባር  በሚለው  ርእስ  ሥር  በንዑስ  አንቀጽ  2  ላይ “በድርጅቶቹ ወይም በማኅበራቱ በሚቀርብ  ደንብ  ላይ  የማሻሻል  አስተያየት  መስጠት፣ ማጽደቅና መመዝገብ”የሚንስቴሩ ሥልጣንና ተግባር  እንደሆነ ይናገራል፡፡  ይህ ማለት ሃይማኖታዊ ድርጅቶችም ሆኑ ማኅበራት በሚኒስቴሩ ለመመዝገብ በሚቀርቡበት ወቅት እነርሱ ከሚከተሉት ሃይማኖታዊ  አስተምህሮ አንጻር የቀረጹትን ደንባቸውን ከመቀበልና ከመመዝገብ ይልቅ ሚኒስቴሩ ደንባቸውን እርሱ በሚፈልገው መሰረት እንዲያሻሽሉ ሃሳብ ያቀርብባቸዋል ማለት ነው፡፡ ይህ “የማሻሻያ አስተያየት መስጠት” የሚለው ቃል  ሚኒስቴሩ  ለሃይማኖት  ተቋማቱ  የሚያቀርበው  “የማሻሻያ  አስተያየት”  ምን  አይነት  አስተያየት እንደሆነ  ግልጽ  ያልሆነ፣  ገደብ  የሌለው  በራሱ  ህሊናና  በራሱ  ፈቃድ  ላይ  ብቻ  የተመሠረተ  በመሆኑ ለራሱ  የሚመች  ሃሳብ  አቅርቦ  ደንባቸውን  ቀርጸው  እንዲያመጡ  ሊያስገድዳቸው የሚችልበት እድል የሰፋ ከመሆኑም በላይ ሃይማኖታዊ ድርጅቶችንና ማኅበራትን ወደፈለገው መስመር ለማስገባት የሚከለክለው ምንም ነገር የለም፡፡ ከነባራዊው የህብረተሰብ አኗኗርና ልምድ ያላፈነገጠ፤ ከሀገሪቱ ሕገ መንግስትና ተዛማጅ ሕጎች በተጻራሪ ያልቆመ መሆኑን ከማረጋገጥ በስተቀር ሃይማኖት ተቋማት ለራሳቸው በሚቀርጹት ደንብ ላይ ሚኒስትር መስሪያ ቤቱ የማሻሻል ወይም የማስተካከል ስልጣን ከተሰጠው  መንግስት ጣልቃ አይገባም የሚለው ህግ ዋጋ የሌለው ይሆናል።
 ይህም  አንድ  ሃይማኖት  የሚከተል  ተቋም  ወይም  “ሃይማኖታዊ  ድርጅትና  ማኅበራት” ባቀረቡት  ደንብ ላይ ካስተካከለና ከጠመዘዘ አለዚያ ያቀረበላቸውን “አስተያየት” አንቀበልም ካሉ መመዝገብ እንደማይችል ከገለጸ  በሕገ  መንግሥቱ  አንቀጽ  11  እና  27  ንዑስ  አንቀጽ  2  የተቀመጠውን  በተለይም  ደግሞ መንግሥት  በሃይማኖት  ትምህርትና  በአስተዳደር  ተቋማት  ላይ  አይገባም  የሚለውን  ይጥሳል  ማለት ነው፡፡ ሃይማኖቶዊ  ድርጅትም  ሆነ  ማኅበር  የሚወለደው  የሃይማኖቱ  ተከታዮች  ከሚያምኑበት  ሃይማኖታዊ እሳቤና  ምንጭ  አንጻር  በመሆኑ  እምነትና  ማኅበር  ወይም  ሃይማኖትና  ድርጅታዊ  አወቃቀር  የአንድ አካል  ክፍሎች በመሆኑ በመነጣጠል በተለይም ደግሞ እነርሱ የሚተዳደሩበት ደንብ ቀርጾ ማውጣትም ይሆን ባወጡት ላይ “የማሻሻያ አስተያት” እንዲቀበሉ ማድረግ መንግሥት ሃይማኖት ውስጥ አልገባሁም የሚልበት  ምክንያት  አይኖረውም፡፡  ስለዚህም  “የማሻሻያ  አስተያየት”  ከሰጠበት  ደቂቃ  ጀምሮ  ሕገ መንግስቱን ይጥሳል ማለት ነው፡፡   
    ሌላው  በዚሁ  በአንቀጽ  5  የሚንስቴሩ  ስልጣንና  ተግባር  በሚለው  ርእስ  ሥር  በንዑስ  አንቀጽ  9 ላይ “ሞዴል መተዳደሪያ ደንቦች የማዘጋጀት” ስልጣንና ተግባር የሚኒስቴሩ እንደሆነ ይናገራል፡፡ ይህ ደግሞ የሃይማኖት  ድርጅቶችም  ይሁኑ  ማኅበራቱ  ደንብ  ይዘው  ሲመጡ  “የማሻሻያ  አስተያየት”  ከመስጠት አልፎ ደንብ የሚያዘጋጅላቸውም እራሱ እንደሆነ ይናገራል፡፡ “ሞዴል መተዳደሪያ ደንብ” ማለት እርሱ በሚፈልገው መልኩ የተቀረጸ ይዘት ያለው ሆኖ የተዘጋጀ ማለት ነው፡፡  
 በመሆኑም  ደንብ  የየሃይማኖቱ  ከሚከተሉት  እምነት  አንጻር  ለራሳቸው  የሚመች  የሚያወጡትና የሚከተሉት  እንጂ  ሚኒስቴር  መስሪያ  ቤቱ  የሃይማኖት  ተቋማትና  መተዳደሪያ  ደንብ  ማውጣትና መቅረጽ አይችልም፡፡ የመንግሥት ሚና የፖለቲካ ወይም ሃይማኖቶች ራሳቸው በራሳቸው እንዲዋቀሩና እንዲመሩ  መንገድ  መክፈት  እንጂ  ደንብ  የመቅረጽና  በሚፈልገው  መልኩ  እንዲያምኑና  እንዲዋቀሩ ማድረግ አይደለም፡፡         
 ሌላው  በዚሁ  በአንቀጽ  5  በንዑስ  አንቀጽ 10 ላይ ሚኒስቴሩ  ባወጣው በዚሁ  መመሪያ መሰረት “ለሚሰጣቸው ለምዝገባና ተዛማጅ አገልግሎቶች ክፍያ እንደሚያስከፍል” ያናገራል፡፡ እንዲሁም በአንቀጽ 6 በንዑስ አንቀጽ 5 ላይ ደግሞ “ህጋዊ የምዝገባ ፈቃድ ሳያገኝ በምስረታ ላይ እያለ ከመስራች አባላት በስተቀር  ህዝብን  በመጥራት  ሃይማኖታዊ  ስብሰባ  ማካሄድ  ማስተማር  ወይም  መስበክ  እና  ሌሎች ተመሳሳይ  ድርጊቶችን  መፈጸም  አግባብነት  ባለው  ሕግ  የሚያስጠይቅ  ይሆናል”  ይላል፡፡  በመሆኑም መክፈል  ሳይችሉ  ቀርተው  መመዝገብ  ያልቻሉ  ሃይማኖቶች  በግልም  ይሁን  በቡድን  ሃይማኖታቸውን ማራመድ፣  መስበክ፣  መሰብሰብ፣  ማስተማር  ወይም  ሌላ  ተመሳሳይ  ሃይማኖታዊ  ድርጊት  መፈጸም እንደማይችሉ  የሚናገር  ብቻ  ሳይሆን  ይህን  ያደረጉ  ድሆች  ሃይማነተኞች  በሕግ  የሚጠየቁ  ይሆናሉ ማለት ነው፡፡ ይህም ተፈጥራዊና ሕገ መንግስት የሰጣቸውን አንቀጽ 27 ንዑስ አንቀጽ 1 በግልም ይሁን በቡድን በመሆን በይፋ የማምለክ፣ የመከተል፣ የመተግበር፣ የማስተማር ወይም የመግለጽ መብታቸውን በመንጠቅ ሕገ መንግሥቱን ይጥሳል ማለት ነው፡፡ 
 በሌላ  መልኩም  ይህ  አንቀጽ  6  በንዑስ  አንቀጽ  5  የተቀመጠው    “ህጋዊ  የምዝገባ  ፈቃድ  ሳያገኝ በምስረታ  ላይ  እያለ  ከመስራች  አባላት  በስተቀር  ሕዝብን  በመጥራት  ሃይማኖታዊ  ስብሰባ  ማካሄድ ማስተማር  ወይም  መስበክ  እና  ሌሎች  ተመሳሳይ  ድርጊቶችን  መፈጸም  አግባብነት  ባለው  ሕግ  የሚያስጠይቅ  ይሆናል” የሚለውን  ስንመለከት  አንድ  የግል  እምነት ያለው  ዜጋ  የሚያምነውን  እምነት ለሌሎች  በመስበክ  በማስተማርና  ተከታይ  በማፍራት  ወደ  ሃይማኖታዊ  ማኅበርነት  ስለማይቀየር ሃይማኖቱን  በነጻ  የመግለጽ  ብሎም  የማስፋፋት  ተፈጥሯዊና  ሕገ  መንግስታዊ  መብቱን  ያፍናል ይገድባል፡፡  እርሱን  ብቻ  አይደለም  በንዑስ  አንቀጽ  6  ደግሞ  ይሄ  እንደማኅበር  መመዝገብ  ደረጃ  ላይ ያልደረሰ ዜጋ እርሱ ለሚያደርገው የመስበክ የማስተማር ወይም ሌሎች ሃይማኖታዊ ድርጊት “የደገፈና መሰል ትብብሮችን ያደረገ ማንኛውም ሰው በተመሳሳይ አግባብነት ባለው ሕግ የሚጠየቅ” እንደሚሆንም መመሪያው  ይገልጻል፡፡  ይህም  ሕገ  መንግሥቱን  ሳይጥሱ  ጤናማ  ሃይማኖታዊ  ሥራ  ሲያካሂዱና ሲደግፉ  የነበሩትን  በወንጀል  መጠየቅ  ከሕገ  መንግስታዊ  ድንጋጌዎች  መንፈስ  የሚጻረርና  ወንጀል ባልተፈጸመበት ወንጀል እንደመፍጠር ነው፡፡    ሕገ መንግስቱ በግል የማምለክና የማመን፤ የማስተማር ነጻነትን ሲሰጥ በሃይማኖት ድርጅቶች ማቋቋሚያ ደንብ ላይ ግን በግል ማመን ቀርቶ በማኅበር ወደመደራጀት ብቻ ከፍ ብሏል። ግለሰብ የሚያምነውን ለሌሎች በማካፈል፤ ተከታይ ለማፍራት ካላስተማረ ራሱን እንደማኅበር ቆጥሮ ህጋዊ ፈቃድ ያገኝ ዘንድ የሚገደድበት አግባብ ትክክለኛ አካሄድ አይደለም።
 እንዲያውም  ሃይማኖታዊ  ድርጅቶችና  ማህበራት  ዓለማቀፋዊ  ግንኙነት ለማድረግና  ምቹ  መንገድ እንዲኖራቸው  ራሳቸው  ከማሰብ  አንጻር  ሊመዘገቡ  ወደ  ሚኒስቴሩ  ይሄዳሉ  እንጂ  ካልተመዘገበችሁ ሃይማኖት አይደላችሁም ማለት ተገቢ አይደለም፡፡ እነዚህ ሃይማኖታዊ አገልግሎቶች የሕገ መንግሥቱን ድንጋጌ እስካልጣሱ ድረስ ሊከለከሉ አይገባም፡፡  
 ሌላው ይሄው መመሪያ በአንቀጽ ሰባት “አደረጃጀት” በሚለው ሥር በንዑስ አንቀጽ 1 ላይ “ማንኛውም የሃይማኖት  ድርጅት  ወይም  ማኅበር  በመተዳደሪያ  ደንብ  መሠረት  ጠቅላላ  ጉባኤ፤  የስራ  አስፈጻሚ / አመራር  ቦርድ  ፣  ስራ  አስኪያጅ  /  ፕሬዝዳንት  ፣  ዳይሬክተር  ፣  ኦዲተር  ፣  ሂሳብ  ሹምና  ሌሎች እንደድርጅቱ ወይም ማኅበሩ አደረጃጀት አስፈላጊ የሆኑ የሥራ ክፍሎች ሊኖሩት ይገባል ይላል፡፡” ይህም የሃይማኖት  ድርጅቶችና  ማኅበራት  ከሚከተሉት  እምነትና  ከመንፈሳዊ  መርህ  አንጻር  አደረጃጀታቸውን ያወጣሉ እንጂ መንግሥት አደረጃጀታቸውንና የስልጣን ተዋረዳቸውን እንዲሁም የማዕረግ ስሞቻቸውን ሊያወጣላቸው  አይችልም፡፡  ለምሳሌ  የኢትዮጵያ  ኦርቶዶክስ  ተዋህዶ  ቤተክርስቲያንን  ብንወስድ ሃይማኖቷዊ ቀኖናዋና የራሷ ሕገ ቤተክርስቲያን እንደሚያዘው ቀድሞ በፓትሪያሪኩ የበላይ ጠባቂነትና አመራር  ሰጪነት  በኋላም  ተሻሽሎ   በብጹዐን  ሊቃነ  ጳጳሳት  ምልዐተ  ጉባዔ  እንድትመራ  ከወሰነችበት እለት ጀምሮ አሁን በዚሁ እየሄደች ያለችን ቤተክርስቲያን  ፣ ወደ ፊትም ቤተክርስቲያኗ እንደ ቀኖናዋ መሰረት  እንዳመቻትና  ለራሷ  በምታምነው  አደረጃጀትና  አስተዳደራዊ  መዋቅር  ዘርግታ  ብትሄድ መንግሥት  ጣልቃ  ገብቶ  እንደ  ሃይማኖት  ድርጅት  ወይም  ማኅበር  ተዋቅረሽ  ጠቅላላ  ጉባኤ፤  የስራ አስፈጻሚ /  አመራር  ቦርድ  ፣  ስራ  አስኪያጅ /  ፕሬዝዳንት  ፣  ዳይሬክተር  በሚል  መዋቅር  ውስጥሽን ካላደራጀሽ ሃይማኖት አይደለሽም ሊላት እንደሆነ ይሄው መመሪያ ያስረዳል ማለት ነው፡፡  
ይህ መመሪያ የያዘው እነዚህ ስያሜዎች ማለትም ጠቅላላ ጉባኤ፤ የስራ አስፈጻሚ / አመራር ቦርድ  ፣ ስራ  አስኪያጅ /  ፕሬዝዳንት  ፣  ዳይሬክተር  ፣  ኦዲተር  ፣  ሂሳብ  ሹምና  ሌሎች  ተብለው  የተቀመጡት መዋቅራዊ ስያሜዎች በራሳቸው “ዓለማውያን” ቋንቋዎችና ትርጓሜዎች ያሏቸው እንጂ ሐይማኖታዊ ቋንቋዎች ለመሆናቸው በራሱ አነጋጋሪ ጉዳዮች ናቸው፡፡  
 ሌላም   እንደምሳሌ   የወንጌላውያን   አብያተክርስቲያናትን   ይዘትና   አወቃቀር   ብንመለከት   አንዱ ቤተክርስቲያን  ከሌላው  በመሰረታዊ  ክርስትና  አስተምህሮ  አንድ ቢሆንም  በአስተዳደራዊ  አወቃቀሩ  ግን የተለያየ  ሲሆን  አንዳንዱ  በ “ሐዋርያዊ  አመራር”  የሚያምንና  የተዋቀረ  ሌላው በ “ሽማግሌያዊ አስተዳደር”  የሚያምንና  የተዋቀረ  ሌላው  ደግሞ  በ “ፓስተራል  አስተዳደር”  የሚያምንና  የተዋቀረ ወዘተርፈ  በመሆኑ እነዚህን በአንድ አስተምሯቸውን ተከትሎ  ካዋቀሩት አስተዳደራዊ  አደረጃጀት አውጥቶ  እንደልማት ማኅበር  ጠቅላላ  ጉባኤ፤  የስራ  አስፈጻሚ  /  አመራር  ቦርድ  ፣  ስራ  አስኪያጅ / ፕሬዝዳንት፣  ዳይሬክተር ብላችሁ ተደራጁ ብሎ በ “ማሻሻያ  ሃሳቡ”  ጠምዝዞ  ካላዋቀራቸው አትመዘገቡም  እንደሃይማኖትም  መንቀሳቀስና ማስተማር  መስበክ  አትችሉም  ሊል  እንደሚችል  በግልጽ ያሳያል፡፡  ይህም “መንግስት  በሃይማኖት  አይገባም”  የሚለውንና  “የሃይማኖት  ተከታዮች ሃይማኖታቸውን  ለማስፋፋትና  ለማደራጀት የሚያስችላቸው  የሃይማኖት  ትምህርትና  የአስተዳደር ተቋማት ማቋቋም ይችላሉ” የሚለውን በአንቀጽ  11 ንዑስ አንቀጽ 3 እና አንቀጽ 27 ንዑስ አንቀጽ 2የተቀመጠውን የራሳቸውን መብት በመንጠቅ ሕገ መንግሥቱን የሚጻረር መሠረታዊ ስህተት መሆኑን ያሳያል፡፡ 
 ለነገሩ  ወንጌላውያን  አብያተክርስቲያናት  ይህ  አዲሱ  መመሪያ  ከመውጣቱም  በፊት  በነበረው  መመሪያ መሠረት እንደልማት ተቋማትና ድርጅት ይመዘገቡና ስራቸው ሃይማኖታዊ ይሁን ልማታዊ ሳይታወቅ የስራና  የሂሳብ  ሪፖርታቸውን  እንዲሁም  የቀጣይ  የበጀት  ዓመት  የሥራ  እቅዳቸውን  ጭምር ካላቀረቡ በቀር  የሥራ  ፈቃድ  ስለማያገኙ  ይህን  ለማቅረብ  ይገደዱ  ነበር፡፡  መንግስትም  የሃይማኖት  የስራ ሪፖርትና  እቅድ  የበጀት  አስተዳደራቸውንም  ጭምር  የማየትና  የመቀበል  በውጭ  ኦዲትርም እንዲመረመሩ  የማድረግ  ምንም  ሕገ  መንግስታዊ  ሥልጣን  የሌለው  ቢሆንም  ለረጅም  ዘመናት ሲያካሂድባቸው  ኖሯል፡፡ይህም  መንግስት  በሃይማኖቶች  ውስጥ  በትምህርታቸውም  ሆነ  በአስተዳደር ስልጣናቸውና  አወቃቀራቸው  ውስጥ  ገብቶ  እንደነበረ  በሚንስትሩ  የሃይማኖትና  የእምነት  ዳሬክቶሪት የተጨናነቁ መዝገብ  ቤትን ማየት  በቂ  ምስክር  ነው፡፡  በዚህም  በመንግስት  ጣልቃ  ገብነትና የአወቃቀር ውሳኔ ምክንያትና የወንጌላውያን አብያተክርስቲያናት እርስ በርሳቸው በመዋቅሩ እንዳይስማሙ የመካሰስ የመለያየት  እንዲሁም  አላግባብ  የቤተዘመድ  አመራር  እንዲፈጥሩ  ወዘተ  ጭምር  ተገደው  እንዲገቡ ተደርገዋል፡፡          
ከዚሁ ጋር ተያይዞ ሌላው መነሳት ያለበት ነጥብ በዚሁ መመሪያ በአንቀጽ 3 “ትርጓሜ” በሚለው ሥር በንዑስ  አንቀጽ  6 ላይ  “መንፈሳዊ  አገልጋይ  ወይም  ሰባኪ  ወይማ  ዳኢ  ማለት  በሃይማኖት  ድርጅቶቹ ወይም  ማኅበራት  ውስጥ  እውቅና  ኖሯቸው  በክፍያ  ወይም  ያለክፍያ  የሃይማኖት  ትምህርት የሚያስተምሩ  ወይም  የሚሰብኩ  አገልጋዮችን  ያጠቃልላል፤”  ይላል፡፡  እዚህ  ላይ  መመሪያው በየሃይማኖታዊ  ድርጅቶችና ማህበራት  ውስጥ ያሉትን  ልዩ  ልዩ ስያሜዎችና የአገልግሎት ማዕረጋትን በአንድ  መጠቅለሉና  መጥራቱ  መሠረታዊ  ስህተት  ነው፡፡  ይህ  ጠቅልሎ  የመጥራት  ሥራና  ኃላፊነት የየሃይማኖቱ  ድርጅቶችና  ማኅበራት  ተግባርና  ሥልጣን  እንጂ  እንዴትስ  እንዲህ  ብሎ  መጠቅለልና መጥራት ይችላል? የሚሉ ብዙዎች ናቸው፡፡ በተለያዩ የሃይማኖት ተቋማት ውስጥ የተለያየ ስምና ማዕርግ ያላቸው፤ ሃይማኖታዊ ተቋሙ የሚፈቅደውን መጠሪያ ይዘው የሚሰብኩ፤ የሚያስተምሩ በዚህ ጥቅል ስያሜ መሰረት ቀሪ ሆኗል ማለት ነው።
 ሌላው  አነጋጋሪ  ጉዳይ  በዚሁ  መመሪያ  አንቀጽ  13 “የውጭ  ዜጎችን  ማሰማራት”   በሚለው  አርእስት ሥር ንዑስ አንቀጽ 5 ላይ  ሃይማኖታዊ ድርጅቱ ወይም ማኅበሩ “ ያሰማራው የውጭ ዜጋ ከመጣበት ዓላማ  ውጪ  በመንቀሳቀስ  ለሚፈጽመው  ጥፋት  በተናጠልና  በጋራ  በሀገሪቱ  ህግ  ተጠያቂ  ይሆናል” የሚለው  ነው፡፡  ይህም  ማለት  አንድ  ፈረንጅ  ከሃይማኖታዊ  ተቃሙ  ወይም  ማህበሩ  ጋር  በመሆን መንፈሳዊ  ሥራ  ለመስራት  ተስማምቶ  በመግባት  መንፈሳዊ  ሥራው  ጋር  ባልተገናኘ  ሁኔታ  ባለው ትርፍ  ጊዜም  ሆነ  በግሉ  ሌላ  ወንጀል  ቢሠራ  ለፈጸመው  ወንጀል  ተቋሙ  ወይም  ማኅበሩ በወንጀል መጠየቁ  አግባብ  አይደለም፡፡  ሃይማኖታዊ  ድርጅቱ  ወይም  ማኅበሩ  ላለው  ሃይማኖታዊ  ተግባር ተስማምቶ አሰማራው እንጂ ሌላ የግል ስህተቱን ሁሉ ተቋሙን ወይም ማኅበሩን ተጠያቂ ማድረግ ከህግ አስተሳሰብ ጋር ፈጽሞ የሚገናኝ አይደለም፡፡ 

 ከዚህ ዓይነቱ ጅምላ ተጠያቂነት ለመዳን ግለሰቡን ለማስተማር ወይም ለማሰራት ያስመጣው ተቋም ሰውየው ለመስራት ከተዋዋለበት ሰዓት ውጪ ያለውን ጊዜ የትም እንዳይንቀሳቀስ የሚጠብቁ ፖሊሶች ወይም አጃቢዎች መመደብ ወይም ጉዳዩን ከጨረሰበት ደቂቃ አንስቶ ባመጣው መንገድ አፍኖ ወደ መጣበት የመመለስ ግዴታ አለበት ማለት ነው።
 በአንቀጽ  18  “የተከለከሉ  ተግባራት”  በሚለው  ርእስ  ሥር  ንዑስ  አንቀጽ  8  ደግሞ  ብንመለከተው መመሪያው ሌላ አስገራሚ ነገርንም ይዟል፡፡ “ከሚመለከተው አካል ፈቃድ ሳያገኙ ከአምልኮ ቦታ ውጪ ሰዎችን  በማሰባሰብ  ባልተፈቀደ  ቦታ  የሃይማኖት  ትምህርት ማስተማር  ወይም  መስበክ” በንዑስ  ቁጥር 12  ደግሞ  ከሌሎች  ጋር  “አብሮ  መስራት”  ፣    በንዑስ  አንቀጽ  13  ደግሞ  “የሃይማኖት  ተግባርን ከበጎአድራጎት ዓላማና ተግባር ጋር ቀላቅሎ መሥራት” ይከለክላል፡፡ 
 ይህም ማለት እንደምሳሌ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን እምነትና አስተምህሮን  ብናይ ለረዥም ዘመናት ሲወርድ ሲዋረድ የመጣውን የህዝቡን የቤት ለቤት ጽዋ ማህበራት ያለፈቃድ ሰብስቦ እንደወትሮው  ማስተማር  መስበክና  ሃይማኖታዊ  ተግባራት  መፈጸም  ይከለክላል  ማለት  ነው፡፡  የታቦት ንግስ፤ በዓል፤ መንፈሳዊ ጉዞ የመሳሰሉ የቆዩ ልምዶች ሁሉ ዝግ ናቸው ማለት ነው። ቄሱም የነፍስ ልጆቻቸው ከአምልኮ ቦታ (ከቤተክርስቲያን ቅጥር ጊቢ) ውጭ ሰብስቦ ቢሰብክ ቢያስተምር በሕግ ያስጠይቀዋል  ማለት  ነው፡፡  ይህ  ብቻ  አይደለም  የአደባባይ  ክብረ  በዓላትንም  ጭምር  ያለ  መንግስት ፈቃድ እንደወትሮ ቢያካሂዱ መሰብሰብ በዓላቱንም ማካሄድ አይችሉም ማለት ነው፡፡ ይህን ሃይማኖታዊ  ነጻነታቸውን ከሚመለከተው የመንግስት ቢሮ ሄደው “ይሁንታ” ማግኘት ይጠበቅባቸዋል፡፡ ካላገኙም ቀረ ማለት ነው፡፡ 
ወደ  ካቶሊኩም  ወደ  ወንጌላውያኑም  ተመሳሳይ  እጣ  ፈንታ  ይገጥመዋል፡፡  ከተፈቀደላቸው  የአምልኮ ቤቶች   (ይህም  ተከራይተው  የሚያመልኩበትን  ቤት  ያካትት  አያካት  መመሪያው  ግልጽ  አያደርግም  ) ውጭ  የቤት  ለቤት  ጸሎት  ፕሮግራሞች፣  መጽሐፍ  ቅዱሳዊ  የጥናት  ፕሮግራሞች  በሀዘንና  በደስታ ወቅትም በሚያደርጉት የቤትና የድንኳን አገልግሎቶች ሁሉ የተከለከሉ ይሆናሉ ማለት ነው፡፡
ሌላው ሃይማኖት የሚወልደው ለሌሎች በጎ የማድረግ የመደገፍ ተግባር ነጥሎ እናንተ እንደ ሐይማኖት መጸለይ  ብቻ  ይገባችኋል  እንጂ  ሃይማኖትን  ከምግባር  አታቀላቅሉ  ብሎ  የሚገልጸው  መመሪያ ለክርስቲያኑ ህብረተሰብ “ተርቤ አብልታችሁኛል  ፣ ተጠምቼ አጠጥታችሁኛል፣ ታምሜ ጠይቃችሁኛል፣ ታስሬ  ወደ  እኔ  መጥታችኋል  ብሎ  ጌታ  በመጨረሻ    በማቴወስ  ወንጌል  25፡34-46  እንደተገለጸው የሚጠይቀውን ቃልና “ከሥራ የተለየ እምነት የሞተ  ነው” የሚለውን የያዕቆብ መልእክት ምዕራፍ 2፡18-26ን  የእምነት  መሠረት  የሚጥስ  አሊያም  ነጣጥሎ  በዚህ  መልኩ  ሥጡ  ብሎ  ያለ  እምነት መሰረታቸው  አካሄድ  መግለጹ  ሲሆን  ለእስልምና  እምነት  ተከታይም  ከአምስቱ  የእስልምና  ማእዘናት ውስጥ  በሦስተኛ  ደረጃነት  “ዘካት”  መስጠትን  የሚከለክል  ወይም  ይህንን  እንዴት  መፈጸም እንደሚገባቸው ከሐይማኖታዊ አስተምህሯቸው ውጪ መንግስት መመሪያ እየሰጠ በመሆኑ መንግሥት ሕገ መንግስቱን ጥሶ በሐይማኖት ጣልቃ መግባቱን ያሳያል ፡፡                     
 እንግዲህ  ሕዝቡ  ይህ  ሃይማኖትን  በነጻነት  የመቀበል፣  በግልና  በጋራ  የማራመድ  የማስፋፋትና የማደራጀት  ሕገ  መንግስታዊ  መብቱን  የገፈፈው  መመሪያ  ለውይይት  ለመጀመሪያ  ጊዜ  መንግስት የሃይማኖት  ተቋማትን  በጠራና  ሃሳቡን  በገለጸ  ጊዜ  የኢትዮጵያ  ኦርቶዶክስ  ተዋህዶ  ቤተክርስቲያን “አይመለከተኝም”  ብላ  ስብሰባውን  ረግጣና ጥላ  እንደወጣች  ካቶሊክም  “እኔ  አለም  አቀፋዊ  አወቃቀር እንጂ  ብሔራዊ  ብቻ ስላልሆንኩ አለም አቀፉን ቤተክርስቲያኗን ጠይቁ”ብላ ጥላ  እንደወጣች፣ እስልምናም  በተመሳሳይ “አይመለከተኝም”ብለው ሲወጡ ጥቂት  ፕሮቴስታንት  አካላት  ብቻ ቆይተው የመንግሥትን  ይህን  ሃሳብ  እንዳዳመጡ  የውስጥ ምንጮች ይገልጻሉ፡፡ይሁን እንጂ እነዚህ የእምነት ተቋማት ባይቀበሉትም ቅሉ መመሪያው ጸድቆ እንደመመሪያ እየተተገበረ ሲሆን ብዙዎችን ግራ እያጋባ ይገኛል፡፡             

      

Thursday, February 6, 2014

ቅድስት ድንግል ማርያም ላይ መዋሸት ይቁም! -


By Mesy Yegetalij (facebook)
ሁሉ በጌታ በኢየሱስ ስም አድርጉት" ቆላ 3፤17
ቅድስት ድንግል ማርያም ጸጋን የተሞላች፣ በትሕትናዋ፣ በእምነቷ በቅድስናዋ ተወዳዳሪ የሌላት፣ አስደነቂውን መለኮታዊ ምሥጢር በልቧ በመጠበቅ እስከ መስቀል ድረስ የተገኘች ብቸኛዋ እናታችን ናት።
ቅድስት ድንግል ማርያምን በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በእምነታቸው ከተመሠከረላቸው ቅዱሳን ሁሉ ልዩ የሚያደርጋት እምነቷ መለኮትን በማሕጸኗ መሸከሟ እና ምሥጢር ጠባቂነቷ ነው። ያለወንድ ዘር ልጅ ትወልጃለሽ፣ ይህን ለማድረግ እግዚአብሔር አይሳነውም ተብሎ ሲነገራት እንደ ቃልህ ይሁንልኝ በማለት አመነች። እጅግ አስደናቂ እምነት ነው፣ ኤልሳቤጥ በመንፈስ ቅዱስ ተሞልታ ከእግዚአብሔር ዘንድ የነገሩሽን ቃል የምታምኚ አንቺ ብፅእት ነሽ በማለት አክብሮቷን ገለጠች።
ቅዱስ ገብርኤልም የተላከበትን ምክንያት ከመናገሩ በፊት በእግዚአብሔር ፊት ያላትን ክብር ከሰማይ ያየውንና የሰማውን በመለኮታዊው ዙፋን ዘንድ ያላትን ሞገስ ነበር ያበሠራት። ቅዱስ ገብርኤል በእግዚአብሔር ፊት የሚቆም መልአክ እንደመሆኑ መጠን ድንግል ማርያም በሥላሴ መለኮታዊ ክብር የታሰበች መሆኗን ተረድቷል፣ ስለዚህ በርሷ ላይ ያለው የጌታ ክብር ነውና ተጠንቅቆና ተንቀጥቅጦ ነበር የቀረባት። መልአኩ ወደ ድንግል ማርያም ሲቀርብ በታላቅ ትህትና ነበር። ምክንያቱም እግዚአብሔር ከርሷ ጋር ነውና ልኳን እና መጠኗን ይረዳል። እርሷ በመለኮታዊ ክብር ተሸፍና በመንፈስ ቅዱስ ጸጋ ተሞልታለች።
ድንግል ማርያም መልአኩ ካበሠራት ጀምሮ በእርሷ እየተካሄደ ያለውን ምሥጢር ታውቃለች፣ አካላዊ ቃል ከሰማይ ወርዶ በማሕጸኗ አድሮ ተጸንሷል። በዚህ ጊዜ እራሷን በጌታ ፊት ዝቅ አድርጋ "ነፍሴ ጌታ እግዚአብሔርን ታከብረዋለች መንፈሴ በአምላኬና በመድኃኒቴ ሐሴት ታድርጋለች እርሱ በእኔ ታላቅ ሥራ አድርጓልና" ስትል እግዚአብሔርን አከበረች
ድንግል ማርያም እጅግ አስደናቂው ውበቷ ያለው እዚህ ላይ ነው። ነገሩን በልቧ ይዛ ትጠብቀው ነበር እንጂ ለማንም አላወራችም። የጌታን ምሥጢር ያለጊዜው መግለጥ አልፈለገችም፣ ከተጸነሰ ጀምሮ እስከ ሞቱ ድረስ በምሥጢር ያዘችው ። ለሰላሣ ሦስት ዓመት ያህል ዝም በማለት እግዚአብሔርን ጠበቀች፤ ይህ ነው ቅድስተ ቅዱሳን የሚያሰኛት ድንግል ማርያምን "ከሴቶች ሁሉ ተለይተሽ የተባረክሽ ነሽ" ያሰኛምት ይህ ነው። ድንግል ማርያም ከአእምሮ በላይ የሆነ ትግሥት አሳይታለች፤ እውነትም ጸጋን የተመላች ናት የድንግል ማርያም እንደዚህ የመቀደስ ዋና ምክንያት ግን እግዚአብሔር ከርሷ ጋር ስለሆነ ነው።
"አላዋቂ ሳሚ ንፍጥ ይለቀልቃል" እንደተባለው፣ ድንግል ማርያምን እናከብራለን ያሉ ሐሰቶኞች በድንግል ማርያም ላይ የተናገሩትና አሁንም እያስተማሩ ያሉት ግን በመጽሐፍ ቅዱስ የምናውቃት ድንግል ማርያምን አትመስልም። መናፍቃን በድንግል ማርያም ላይ የፈጸሙትን ስም ማጥፋት ጥቂት እንመልከትና እኛም ድንግል ማርያምን ያከበርን እየመሰለን በርሷ ላይ ሐሰትን ከመናገር መቆጠብ አለብን።
በተዓምረ ማርያም የተጻፈውን ውሸት እውነት በሆነው በእግዚአብሔር ቃል እንመርምር፦t

"ዘከመ ጸለየት እግዝእትነ አመ አሠርቱ ወሰደስቱ ለየካቲት እምድህረ እርገቱ ለእግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ ወዘከመ ነሥአት ኪዳነ ምሕረት ዘኢይትሄሰው"
ትርጉም "ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ካረገ በኋላ እመቤታችን እንደጸለየችና የካቲት አሥራ ስድስት ቀን የምሕረት ቃል ኪዳን እንደተቀበለች"
"ኢያንተገት ገዪሰ ወጸልዮ ኀበ መቃብረ ወልዳ ዘውእቱ ጎልጎታ"
ትርጉም "ወደ ልጇ መቃብር እየሄደች መጸለይን አቋርጣ አታውቅም፣ ይኸውም ጎልጎታ ነው"
ይህ ታምር ነው ከተባለ ደራሲው ሊል የሚፈልገው ጌታ ካረገ በኋላ የካቲት አሥራ ስድስት ቀን፣ ጎልጎታ በሚገኘው የጌታ መቃብር ስትጸልይ፣ ጌታ ተገልጦ ቃል ኪዳን እንደሰጣት፣ እመቤታችንም ጌታ ከሞተ ጀምሮ መቃብሩ ላይ ቆማ መጸለይን አቋርጣ እንደማታውቅ፣ ጌታም ሁልጊዜ ይጎበኛት እንደነበር ነው።
ጌታ የተሰቀለው መጋቢት ሃያ ሰባት ሲሆን የተነሣው ደግሞ መጋቢት 30 እንደሆነ የቤተ ክርስቲያን ታሪክ ያስረዳል። እንግዲህ እመቤታችን ኪዳን የተቀበለችው የካቲት አሥራ ስድስት ቀን ከሆነ አንድ ዓመት ሙሉ ወደ ጌታ መቃብር ስትመላለስ ነበር ማለት ነው። ይህ ታሪክ የመቤታችንን ስም ያጠፋል፣ ምክንያቱም እመቤታችን በመንፈስ ቅዱስ የተሞላች በእግዚአብሔር የሆነውን ነገር ሁሉ የምታምን ቅድስት ናት። የጌታን ትንሣኤ አይታለች፣ እርገቱንም ተመልክታለች፣ እርሱ ዓለምን ለማዳን ከእርሷ እንደተወለደ፣ የእግዚአብሔር ልጅ እንደሆነ፣ ለዘለዓለም ሕያው እንደሆነ፣ ከስም ሁሉ በላይ የሆነ ስም እንዳለው፣ በፍጥረት ሁሉ በላይ ከፍ ያለ ጌታ እንደሆነ፣ በዙፋኑ ላይ የተቀመጠ ልዑል፣ ዳግም ለፍርድ እንደሚገለጥ ከማንም በላይ የተረዳች እናት ናት።
ታዲያ ሞቶ እንደቀረና እንዳልተነሣ፣ በአብ ቀኝ በዙፋኑ እንዳልተቀመጠ፣ በማሰብ መቃብሩ ላይ ዕለት ዕለት እየተገኘች እንዴት ልታለቅስ ቻለች? የጌታን ትንሣኤና እርገት በዓይኗ አይታ በደስታ በመሞላት እንደርሷ ያለ ከየት ይገኛል? ኢየሱስ ክርስቶስ ኃጥአንን ሊያድን እንደመጣ ከርሷ በላይ ማን ሊያውቅ ይችላል? ቅድስት ድንግል ማርያም የጌታን እርገት ያየች ስለሆነ በመቃብሩ ላይ ታለቅስ ነበር የሚለው አባባል የደብተራ ተረት ነው።
መጽሐፍ ቅዱስ ጌታ ካረገ በኋላ እመቤታችን ትጸልይበት የነበረውን ሥፍራ እንዲህ ሲል አስቀምጦታል።
"በዚያም ጊዜ ደብረ ዘይት ከሚባለው ተራራ ወደ ኢየሩሳሌም ተመለሱ... እነዚህ ሁሉ ከሴቶችና ከኢየሱስ እናት ከማርያም ከወንድሞቹም ጋር በአንድ ሆነው ለጸሎት ይተጉ ነበር" የሐዋ 1፥12፡14 ይጸልዩበት ስለነበረው ሥፍራ ሲናገርም "በገቡም ጊዜ ወደሚኖሩበት ሰገነት ወጡ" ይላል ቁ 13። ይህ ሰገነት ጽርሐ ጽዮን የተባለው የማርቆስ እናት ቤት ነው። የጸለየችውም ከሐዋርያት ጋር ነበር በዚያ ቤት ሳሉም መንፈስ ቅዱስ እንደወረደላቸውና ምሥጢር ሁሉ እንደተገለጠላቸው እንጂ ሌላ ታሪክ አናነብም። እስከ ዓለም ፍጻሜ እኔ ከናንተ ጋር ነኝ ስላለ ጌታ ከእመቤታችንም ተለይቶ አያውቅም። እናም እመቤታችን ካረገ በኋላ አብሯት እንደሌለና የማታገኘው ይመስል መቃብር ላይ ቆማ የምታለቅስበት ምክንያት የለም። ብዙ ጊዜ መቃብር ላይ እየቆሙ ሲያለቅሱ መኖር የሥጋውያን ሰዎች ሥርዓት ነው።  ሥጋውያን የሞቱ ዘመዶቻቸውን ከተሰናበቱ በኋላ በዓይን ለማየት፤ በመንፈስ ቅዱስ ኃይል ለመመልከት ስለማይችሉ በተስፋ መቁረጥ ተሞልተው በሚወዷቸው ሟቾቻቸው መቃብር ላይ ሄደው ሲያለቅሱ እናያለን። መንፈሳውያን ግን እደዚህ አያደርጉም። ባህሉም የኢትዮጵያውያን እንጂ የእሥራኤላውያን አይደለም። አልቅሰው ከቀበሩ በኋላ ተስፋ እንደሌለው ሰው ዕለት ዕለት መቃብር ላይ ሄደው ያለቅሱ ነበር የሚል ታሪክ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ተጽፎ አናገኝም።
እንደ ዘርዓ ያዕቆብ አባባል እመቤታችን የጌታን ምሥጢር በሚገባ እያወቀች መቃብር የምትጎበኝበት ምክንያት ምንድር ነው? ጌታ በመንፈስ ቅዱስ ሙላት ከርሷ ጋር እያለ፤ ከመቃብር ደጃፍ ተቀምጠው የታዩት መላዕክት «ሕያውን ከሙታን መካከል  ስለምን ትፈልጋላችሁ?» መባሉን ያወቀችና የተረዳች እናት መቃብሩ ላይ ዕለት ዕለት እየሄደች  ለአንድ ዓመት አለቀሰች ማለት ስም ማጥፋት ነው። የጌታን እናት ማርያምን ሳይሆን ሌላ የኦርቶዶክሶች ማርያም መሆን አለባት። በእውነቱ ይህ ጠላት የጠነሰሰው ሐሰት እንጂ የጌታየ እናት ቅድስት ድንግል ማርያም ይህን ታሪክ አታውቀውም። ከሁሉም በላይ ጸጋ የበዛላት በእምነት እና በመለኮታዊ ምሥጢር የተሞላች ናት።
መቃብሩ ላይ ቆማ ጸለየችው የተባለው ጸሎት ደግሞ ኢየሱስ ለምን እንደሞተ የማታውቅ እስኪያስመስሏት ድረስ ዋሽተውባታል።
"በእንተ ዘይገብር ተዝካርየ ወዘየሐንጽ ቤተ ክርስቲያን በስምየ ወዘያለብስ እሩቀ በስምየ ወዘይሄውጽ ድውየ ወዘያበልዕ ርኍበ፣ ወዘያሰቲ ጽሙአ፣ አው ዘይናዝዝ፣ ኅዙነ፣ ወዘያስተፌስሕ ትኩዘ አው ዘጸሐፈ ውዳሴየ፣ ወሰመየ ወልዶ ወወለቶ በስምየ ወዘሐለየ ማኅሌተ በስምየ፣ ወበበዓልየ፣ እሥዮ እግዚኦ ዕሴተ ሠናየ ዘዓይን ኢርእየ፣ ወእዝን ኢሰምዓ ውስተ ልበ ሰብእ ዘኢተሃለየ"
ትርጉም "ተዝካሬን የሚያደረግ፣ ቤ/ክርስቲያኔንንም በስሜ የሚያሠራ፣ በስሜ የታረዘ የሚያለብስ፣ የታመመ የሚጎበኝ፣ የተራበ የሚያበላ፣ የተጠማ የሚያጠጣ፣ ወይም ያዘነ የሚያረጋጋ፣ ቢሆን፣ የተከዘ ደስ የሚያሰኝ፣ ወይም ምሥጋናዬን የጻፈ፣ ሴት ልጁን እና ወንድ ልጁን በስሜ የሰየመ፣ እኔም በምከብርበት ቀን፣ ምስጋና ያመሰገነውን፣ አቤቱ ዓይን ያላየውን፣ ጆሮ ያልሰማውን፣ በሰው ልብ ያልታሰበውን፣ በጎ ዋጋ ስጠው" ታምር 12 ቁ 39-42።
እያንዳዱን ልመና በዝርዝር እንመልከተው
"ተዝካሬን የሚያደርግ"
ተዝካር ማለት መታሰቢያ ማለት ነው፣ ድንግል ማርያም ጌታን ከጸነሰች ጀምሮ መንፈስ ቅዱስ እስከ ወረደበት እስከ በዓለ ሃምሳ ድረስ መጽሐፍ ቅዱስ ያስባታል።
ጌታን የሚያውቅ ሁሉ እናቱንም ያውቃል፣ ስለጌታ መወለድ ስንናገር ማን እንደወለደው መናገር የግድ ነው። ጌታ ሲሰደድ ማን ይዞት እንደተሰደደ መናገር አያጠያይቅም። የድንግል ማርያም መታሰቢያ መልዓኩ ካበሠራት ጀምሮ ጌታን መውለዷ፣ መሰደዷ፣ በሞቱ ጊዜ እስከ መስቀል ድረስ መገኘቷ፣ በሰርጉ ቤት ለባለሠርጉ ያሳየችው ርኅራሄ፣ ወዘተ ነው። ይህም የተጻፈው ታሪኬን ተናገሩልኝ ውዳሴየን  ጻፉልኝ ብላ ስለለመነች ሳይሆን በመንፈስ ቅዱስ ምሪት የተደረገ ነው። እመቤታችን "ተዝካሬን ያደረገ" ብላ ስትጠይቅ እንደ ዘርዓ ያዕቆብ አባባል ድግስ ደግሶ፣ ጠላ ጠምቆ፣ ንፍሮ ቀቅሎ፣ በየወሩም ሆነ በያመቱ የመገበ ሰው ምሕረት እንዲያገኝ ጌታን ለመነችው ማለት ነው።
ጌታ ብራብ አብልታችሁኛል ብጠማ አጠጥታችሁኛል ወዘተ ብሎ የተራበን ማብላት የተጠማን ማጠጣት እንደሚገባን አስተምሮናል። ይህን የልጇን የወዳጇን ቃል ወደራሷ ወስዳ «በስሜ ያበላውን ያጠጣውን» በማለት እመቤታችን አትዋሽም።  «ብራብ አብልታችሁኛል፤ ብጠማ አጠጥታችሁኛል» በማለት ልጇ ያስተማረውን ቃል ከማንም በላይ እሷ ታውቃለችና።
የፍቅር እናት በመጽሐፍ ታሪኳ እንዲጻፍ ማንንም አልጠየቀችም። ለመጽደቅ ከፈለጋችሁ የምስጋናዬንም ድርሳን ጻፉልኝ ብላ ለማንም አልተናገረችም። «ሁሉን ነገር በልቧ ትጠብቅ» የነበረች የፍቅርና የትህትና እናት  ድንግል ማርያም እንደምድራውያን የነገሥታት ቤተሰቦች ሃሳብ ታሪኬን ጻፉልኝ፤ ድርሳኔንም አባዙልኝ፤ ያኔ አጸድቃችኋለሁ ብላለች ማለት ፈጽሞ ሀሰት ነው። መጽሐፍና ድርሳን የኋላ ሠዎች ታሪክን ሰንደው፤ ገድልን ጠርዘው ለማስታወስ እንዲቻል ያዘጋጁት እንጂ «ትውልድ ሁሉ ብጽእት» እንደሚላት የምታውቅ የጌታ እናት ስሟ እንዲታወስና ሰዎች እንዲጸድቁ ሽታ እኔ ስሞት ጻፉልኝ አላለችም።
ታዲያ በየወሩ በምንሰጠው እንጀራ ለዚያዉም በርሷ ስም እንደምንጸድቅ እንዴት አሰበች? በርግጥ ይህ የድንግል ማርያም ልመና ነው? ወይስ መብላት የለመደ ደሞዙን ለማስተካከል ያለ ሥራ በሰው ትከሻ ለመኖር ያሰበ ደብተራ የፈጠረው ፈጠራ?
ደሞዝን ለቤተ ክርስቲያን በአግባቡ በአሥራት በስጦታ ከመጣው ማግኘት ሲቻል ወሩን እና ዓመቱን ቀኑን ሁሉ የመታሰቢያ ቀን በማድረግ ሕዝብን ለመዝረፍ ለምን ታቀደ?
የምናደረግውን ሁሉ በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም እንድናድረገው መጽሐፍ ቅዱስ ያዝዛል "እግዚአብሔርን አብን በእርሱ እያመሰገናችሁ በቃል ቢሆን ወይም በሥራ የምታደርጉትን ሁሉ በጌታ በኢየሱስ ስም አድርጉት" ቆላ 3፥17
እንግዲህ እመቤታችን በመንፈስ ቅዱስ የተሞላች ናትና እራሷን ከጌታ ጋር በማወዳደር "በስሜ መታሰቢያየን ያደረገ" የሚለውን ልመና አላቀረበችም ብለን እንደመድማለን፤ እመቤታችን ትሑትና ዝምተኛ ሁሉንም በልቧ ይዛ እግዚአብሔርን የምትጠብቅ እጅግ የተቀደሰች እናት ናት። ስሜ ይጠራልኝ በሚል ስሜት ልመና አቀረበች ብሎ በማርያም ላይ መናገር ስድብና ድፍረት ነው።

Friday, January 31, 2014

እንደ እነዚህ ያሉ ሰዎች የክርስቶስን ሐዋርያት እንዲመስሉ ራሳቸውን እየለወጡ፥ ውሸተኞች ሐዋርያትና ተንኮለኞች ሠራተኞች ናቸውና! 2ኛ ቆሮ 11፤13-14

 

«የእግዚአብሔር መንፈስ እንዲያድርባችሁ ሳር ጋጡ የተባሉ ደቡብ አፍሪካውያን ሳር ሲግጡ ዋሉ!!» በሚል ርዕስ ከዚህ በፊት በጽሁፍ ያስነበብናችሁ መሆኑ አይዘነጋም። የሣር መጋጡን መርሐ ግብር ተንቀሳቃሽ ምስል እነሆ አቀረብናላችሁ። ፓስተር ሌሴጎ ዳንኤልና ተከታዮቹ በአዳራሽ ተቀምጠው የቀጥታ ስርጭቱን በማየት ይዝናናሉ። ፓስተሩ በመጀመሪያ ረጋገጣቸው፤ በጫማ ጠቀጠቃቸው ከዚያም ልቡናቸውን ሰውሮ እንደከብት ሳር እንዲግጡ አደረጋቸው።

«ነገር ግን ሐሰተኞች ነቢያት ደግሞ በሕዝቡ መካከል ነበሩ እንዲሁም በመካከላችሁ ደግሞ ሐሰተኞች አስተማሪዎች ይሆናሉ፤ እነርሱም የዋጃቸውን ጌታ እንኳ ክደው የሚፈጥንን ጥፋት በራሳቸው ላይ እየሳቡ የሚያጠፋ ኑፋቄን አሹልከው ያገባሉ፤ብዙዎችም በመዳራታቸው ይከተሉአቸዋል በእነርሱም ጠንቅ የእውነት መንገድ ይሰደባል» 2ኛ ጴጥ 2፤2