Friday, January 31, 2014

እንደ እነዚህ ያሉ ሰዎች የክርስቶስን ሐዋርያት እንዲመስሉ ራሳቸውን እየለወጡ፥ ውሸተኞች ሐዋርያትና ተንኮለኞች ሠራተኞች ናቸውና! 2ኛ ቆሮ 11፤13-14

 

«የእግዚአብሔር መንፈስ እንዲያድርባችሁ ሳር ጋጡ የተባሉ ደቡብ አፍሪካውያን ሳር ሲግጡ ዋሉ!!» በሚል ርዕስ ከዚህ በፊት በጽሁፍ ያስነበብናችሁ መሆኑ አይዘነጋም። የሣር መጋጡን መርሐ ግብር ተንቀሳቃሽ ምስል እነሆ አቀረብናላችሁ። ፓስተር ሌሴጎ ዳንኤልና ተከታዮቹ በአዳራሽ ተቀምጠው የቀጥታ ስርጭቱን በማየት ይዝናናሉ። ፓስተሩ በመጀመሪያ ረጋገጣቸው፤ በጫማ ጠቀጠቃቸው ከዚያም ልቡናቸውን ሰውሮ እንደከብት ሳር እንዲግጡ አደረጋቸው።

«ነገር ግን ሐሰተኞች ነቢያት ደግሞ በሕዝቡ መካከል ነበሩ እንዲሁም በመካከላችሁ ደግሞ ሐሰተኞች አስተማሪዎች ይሆናሉ፤ እነርሱም የዋጃቸውን ጌታ እንኳ ክደው የሚፈጥንን ጥፋት በራሳቸው ላይ እየሳቡ የሚያጠፋ ኑፋቄን አሹልከው ያገባሉ፤ብዙዎችም በመዳራታቸው ይከተሉአቸዋል በእነርሱም ጠንቅ የእውነት መንገድ ይሰደባል» 2ኛ ጴጥ 2፤2


Wednesday, January 29, 2014

የሶርያ ክርስቲያኖች በአሸባሪዎች እየተገደሉ፤ እየተሰደዱ፤ ገዳማትና አድባራት እየወደሙ ናቸው!




በዴር አልዙር የሚገኘው የሶርያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ፍርስራሽ
ክርስትና በደም ተመስርታ፤ በፈተና ወጀብና ማዕበል እየተገፋች እነሆ ዛሬ ላይ ደርሳለች። ዓለም አንድ መንደር ሆናለች፤ ህግና ህግ ብቻ ዓለምን ይመራታል በተባለበት በ21ኛው ክ/ዘመን ላይም ክርስትና ሞትና የእሳት አደጋ አልተለያትም። 

የሚገርመው ደግሞ ክርስትና በእጇ የሚገኘውን መጽሐፍ ቅዱስ ይዛ ከመጓዝ ባሻገር ለእምነቷ መስፋፋት ጦርና ሰይፍ የማትመዝ ቢሆንም ባላጋራዎቿ እንዳትመጣባቸው ለመከላከል ሲሉ ወይም ከመጣች በኋላ ለማጥፋት ሲሹ በተቃራኒው ሰይፍና ጦር እየመዘዙባት ዘመናትን ማስቆጠሯ ነው።
 ይህንን መከራ ካሳለፉት ጥንታውያን አብያተ ክርስቲያናት መካከል የሶርያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን( የአንጾኪያ) ወይም ያዕቆባዊት ቤተ ክርስቲያን  ግንባር ቀደሟ ቤተ ክርስቲያን ናት።  በሐዋርያት ሥራ 11፤26 ላይ እንደተመለከተው «ሐዋርያት በመጀመሪያ ክርስቲያን ተባሉ» የሚለውን ቃል የክርስትናቸው መነሻ አድርገው የሚቆጥሩት ሶርያውያን ክርስቲያኖች፤ በሮማውያን፤ በፋርሶችና፤ በቱርኮች ወረራ ብዙ ግፍና መከራ ያሳለፉ ሲሆን ሶርያ ወደእስላማዊ ግዛት በእስላም ወረራ ከተለወጠችበት ጊዜ ጀምሮ ስቃይና ፈተናው ተጠናክሮ እንደቀጠለ ታሪክ ይነግረናል። ሀገሪቱ በአላዋይት የእስልምና ጎሳ በምትመራበት ዘመን የተሻለ ሰላም የነበራት የሶርያ ቤተ ክርስቲያን ዐረባዊ ዐመጽ በዐረብ ሀገራት ከተቀጣጠለ ጊዜ አንስቶ ግን ሰላም ርቋት፤ ገዳማቷ ፈርሰው፤ መነኮሳትና መነኮሳይያቷ ተገድለው፤ ክርስቲያኖቿ ተሰደው፤ አድባራቷ ተቃጥለው ዛሬ ላይ ወደመጥፋት ከተቃረቡት ጥናታዊ አብያተ ክርስቲያናት መካከል አንዷ ወደመሆን ደርሳለች።
በሰሜን ሶሪያ ወናውን የቀረው ገዳም

በቁስይር የሚገኘው የሶርያ ቤተ ክርስቲያን
 እስካሁን በዓለም አቀፍ አኀዛዊ መረጃ መሠረት 400, 000 ክርስቲያኖች የተወለዱበትንና ያደጉበትን ቀዬ ለቀው እግራቸው ወደመራቸው ተሰደዋል። 60 ትላልቅ ጥናታውያን አድባራትና ገዳማት ተቃጥለዋል። ከዚህ ውስጥ ለአብነት የሚጠቀሰው የጦርነቱ ቀውስ በክርስቲያኖቹ ላይ ያደረሰው በደል በታህሳስ ወር መጨረሻ ገደማ ላይ 13 መነኮሳይያት ጦርነቱን ሸሽተው ከተሸሸጉበት ገዳም ውስጥ እጃቸው በጽንፈኞቹ ተይዞ እንደመደራደሪያ መሣሪያ መቆጠራቸው አይዘነጋም። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የሱኒ/ወሀቢዝም ጽንፈኞች ባሉበት ቦታ ሁሉ ከሳዑዲ ጋር ከጀርባ የማትጠፋው ኳታር ከሊባኖስ መንግሥት ጋር ባደረገችው ሽምግልና አሸባሪዎቹ በመነኮሳይያቱ ላይ ምን ጉዳት እንዳያደርሱና እንደመያዣ መጠቀማቸውን አቁመው በነጻ እንዲለቋቸው በማግባባቷ መለቀቃቸውን የሊባኖሱ ዴይሊ ስታር መዘገቡ አይዘነጋም። ይህንኑ ዘገባ  የኳታሩ «አልጀዚራ ሙባሸር» ቴሌቪዥን መነኮሳይያቱን በምስል በማሳየትም ጭምር የኳታርን ትስስርና የማንነት አቅም መረዳት ችለናል።
በኳታሩ አልጀዚራ ሙባሸር ቲቪ ከቀረቡት የታፈኑ መነኮሳይያት በከፊል

    ይህ በዚህ እንዳለ ብዙ ሶርያውያን ክርስቲያኖች በዚያው ያሉ ሲሆን፤ የሚመጣውን ሞት ለመቀበል የተዘጋጁ መነኮሳይያትና መነኮሳት ከሶርያ ገዳማት እስካሁን አልወጡም። ከእነዚህ መካከል አንዱ የሆኑት ፋዘር ኢዮአቄም የተባሉት ካህን ለሚዲያ እንደገለጹት የሚመጣውን ሁሉ እዚሁ ሆኜ ከመቀበል በስተቀር የትም ለመሄድ አልተዘጋጀሁም። አያይዘው እንደተናገሩት «የሶርያ ክርስቲያኖች ስደትና እንግልት ግን ልቤን ያደማዋል፤ ይህ ሁሉ ለምን ሆነብን? እያልኩ አምላኬን እጠይቃለሁ» በማለት የተሰማቸውን መንፈሳዊ ስብራት ለጋዜጠኞች ገልጸዋል።

«ሞቴን እዚሁ እጠብቃለሁ» ፋዘር ኢዮአቄም ሶርያዊ መነኩሴ
የሶርያ ክርስቲያኖች እየደረሰባቸው ያለው እንግልትና መከራ ትኩረት አግኝቶ ዓለም አቀፍ ክርስቲያኖች ሁሉ ከጎናቸው በመቆም ለችግራቸው በአፋጣኝ እንዲደርሱ የሚያሳስብ ጉባዔ በአሜሪካ የተደረገ ሲሆን በተለይም ምሥራቃውያን ኦርቶዶክስ አብያተ ክርስቲያናት ፕሮግራሙን በጸሎትና እየጠፉ ላሉት ክርስቲያኖች እንድረስላቸው የሚል ጥሪ በማስተጋባት ማሰማታቸው ታውቋል። ይህንንም ተከትሎ የአሜሪካ መንግሥት በጎረቤት ሀገሮች ላይ ጫና በማሳደር የበኩላቸውን ሚና እንዲጫወቱ የሚያሳስብ መልዕክት እንድታስተላልፍ ጥሪ የቀረበላት ሲሆን ሳዑዲና ኳታርም የበሽር አልአሳድን መንግሥት በመጣሉ ዘመቻ ላይ ባላቸው ድርሻ ተዋጊዎቹ በክርስቲያኖች ላይ የሚያደርሱትን ጥቃት እንዲያቆሙ ጥሪ ቀርቧል።
ወሀቢያዊና ሰላፊያዊ  የዐረብ ዐመጽ ከተነሳ ወዲህ በዐረብ ሀገራት የሚገኙ ክርስቲያኖች መከራ፤ስደትና ሞት ከመቼውም ጊዜ የከፋ ቢሆንም እስካሁን የተደረገው ድጋፍ እዚህ ግባ የሚባል አይደለም።
አሸባሪዎች በሶርያ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ


  ከዚህ በፊት የሶርያ፤  አሌፖ ከተማ ሊቀጳጳስ ፖል ይዚጊ በአሸባሪዎቹ ታፍነው ከተወሰዱ በኋላ በብዙ ድርድር ሲለቀቁ በሶርያ የፍራንሲስካን ቄስ የነበሩት  ፍራንሶይስ ሙራድ የተባሉት ደግሞ አቡ ባናት በተባለው የአሸባሪዎቹ አለቃ ሌሎች ሦስት ሰዎችን ጨምሮ በሰይፍ« አላሁ አክባር» እያለ እንዳረዳቸው መረጃዎች ያሳያሉ። በኢራቅም ከነበሩት ክርስቲያኖች ውስጥ በመቶ ሺዎች ሀገራቸውን ለቀው ተሰደዋል። በግብጽ፤ በቱኒዚያ ያሉት ክርስቲያኖችም ለመኖር የሚያበቃ መንግስታዊ ጥበቃ ስለሌላቸው እየተሰደዱ ይገኛሉ። 
ከቀኝ ወደግራ በሁለተኛው ረድፍ የሚገኘውና አቡ ባናት (የእስላም ሴቶች አባት) የተባለው የአሸባሪዎቹ አለቃ ቄስ ፍራንሶይስ ሙራድንና ሁለት ዲያቆናትን በሰይፍ ያረደ

 የምሥራቅ ኦርየንታል ቤተ ክርስቲያን አባል የሆነችው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በዓለም ላይ መከራና ሞት ለሚደርስባቸው ክርስቲያኖች በዘወትር ጸሎቷ እንደምታስባቸው ቢታወቅም በኦፊሴል የጸሎትና የዓለም ክርስቲያኖች ኅብረት ለተጎጂዎች በፍጥነት እንዲደርስ ማሳሰብ ብትችል መልካም ነበር። በተለይም በአሁኑ ሰዓት ገዳማትና አድባራቷ እየወደሙ፤ክርስቲያኖቿ እየተሰደዱ፤ እየታረዱ፤ ለምትገኘው ለሶርያ ያዕቆባዊት ቤተ ክርስቲያን፤  የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን እንደአኀት ቤተ ክርስቲያንነቷ አጋርነቷን አለማሳየቷ ያሳዝናል። 
የክርስትና ምልክት መስቀል አንገታቸው ላይ በመገኘቱ ብቻ ክርስቲያኖች በገፍ እያተረዱ ነው

ለሶርያ ቤተ ክርስቲያን ሀዘንና ድምጽን ማሰማት የፖለቲካው ክፍል ፈቃድ የሚያስፈልገው ሳይሆን የክርስቶስን አገልግሎት መፈጸም መሆኑ መታወቅ ይገባዋል። በሶርያ ቤተ ክርስቲያን ላይ የእጅ አዙር መንግሥታት ሰይፍና ጦር ሲልኩ ያላፈሩ እኛ በጸሎትና በድምጽ ክርስቲያን ወንድሞቻችንን ለማጽናናት የሚያስፈራን ነገር ሊኖር ባልተገባ ነበር። እዚያ ያለው እሳት ኢትዮጵያ ውስጥ እንዳይመጣ ድምጻችን መሰማት ያለበት ዛሬ ነው።

Friday, January 24, 2014

አኩሪ አተር ወይስ አውሬ አተር?



 ከግደይ ገ/ኪዳን- ሉላዊ ሴራና የተሸሸጉ ታሪኮች (Anti Global Conspiracy) የተገኘ /

 በቅድሚያ አጠር ያለች ጉዳዩ ላይ የምታስረዳ ጽሑፍ ባቀርብ እንደ ማንቂያ ደወል ትሆንና ሌሎች የሚመለከታቸው ምሁራንና ተመራማሪዎች ይተጉበታል ብዬ ባቀርብ አጥብቀው የሚሞግቱኝ ሰዎች ገጠሙኝ፡፡ ጉዳዩን የሚቀጥልበት ሌላ ሰውም አልተገኘም፡፡ የቀጣዩ እርምጃ ሸክምም በኔው ላይ ወደቀ፡፡ ስለዚህም በጉዳዩ ላይ ጠለቅ ያለ ምርምር ያካሄዱ ሰዎች ስራዎችን ፈትሼ አጠር ያለች ቆንጆ ጽሑፍ ለማቅረብ በይነ መረብን ስሞግት ቆንጆ ያለቀለት ስራ አገኘሁ፡፡ የሳሊ ፋልኮን እና የሜሪ ጂ. ኢንግ (ፒኤች.ዲ.) የጥምር ስራ የሆነውን Newest Research On Why You Should Avoid Soy የተሰኘ ጽሑፍ፡፡ እነሆ ተርጉሜዋለሁኝ፡፡ አንብቡት፡፡
በሃገራችን ጓያ የተባለው ጥሬ በችግር ጊዜ ሰዎች ሲመገቡት እግራቸውን ሽባ እያደረጋቸው ሲመለከቱ “ጉልበት ሰባሪ” አሉት፡፡ የእግር ነርቭ የሚነካውን የጓያ አካል የሆነውን ንጥረ ነገር ጓያውን ውሃ ውስጥ በመዘፍዘፍ እና ገለባውን በማስወገድ ማጥፋት ይቻላል፡፡ ከክፍለ ሃገር የመጡ ሰዎችም መንግስትና መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋሞች በዚህ ዙርያ ህዝቡን የማንቃት ስራ በዘመቻ ይሰሩና ያስተምሩ እንደነበር ያስታውሳሉ፡፡ በጥፋት አይነቱ ከጓያ እጅግ በከፋው አኩሪ አተር ላይ ግን እንዲህ የሚያደርጉ አካላት ጠፍተዋል፡፡ መንግስታዊ ያልሆኑትስ ስለአኩሪ አተር የጤና ጠንቅ እናሳውቅ ቢሉ “በበጎ ምግባራቸው” ብዙ የሚያተርፉ አይሆኑም፡፡ ማን ሲደጉማቸው?
ችግሩ ያለው አኩሪ አተር እንደጓያ በግለሰብ ገበሬዎች ተመርቶ በትንሹ ጥቅም ላይ የሚውል ሳይሆን፣ በሰፊ ማሳ ታርሶ፣ በከፍተኛ ኢንዱስትሪ ተሳስሮ ከቅባት እስከ ስጋና ወተት እየተደረገ፣ ከከብት መኖነት እስከ ከሕጻናት ዱቄት ሆኖ ስለሚመጣ ይህን ግዙፍ ኢንዱስትሪ መጋፈጥ ከባድ እጅግ በጣም ከባድ ይሆናል፡፡ በዚህ ላይ ደግሞ ከሚያደርሳቸው ጥፋቶች አንጻር ሆን ተብሎ የሚሰራጭ መሆኑን ስናውቅ የሚቃወመው ሁሉ ከባድ ስልታዊ ትግል እንደሚገጥመው ይረዳል፡፡ በዚህ ላይ ደግሞ አውሬ አተሩ ከሰማይ እንደ ወረደ መና የሚቆጥሩት ቅጠል በሌ ግለሰቦች ስላሉ በፍቅሩ ተነድፈዋል፡፡ ሌሎችም ከጤና ጋር በተያያዘ ምርጫቸው ያደረጉት ይገኛሉ፡፡ ቅጠል በሎቹን ምንም ማድረግ አይቻልም ታውረዋልና ለማየት ካልፈቀዱ አይቻልም፡፡ በጤና ምክንያት የመረጡት ግን ሃኪማቸውን አማክረው ሌላ አማራጭ ቢፈልጉ ይሻላቸዋል፡፡ አተርፍ ባይ አጉዳይ እንዳይሆኑ፡፡
ከስር የተጠቀሱት ዘመን አቆጣጠሮች በግሪጎራውያኑ ነው፡፡ በመዓዝናዊ ቅንፍ ውስጥ ያሉት አስተያየቶች የኔው ናቸው፡፡ ይህ መነሻ ከነስእሉ ደግሞ እኔው የጨመርኩት መሆኑ እዳይዘነጋ፡፡ መልካም የማንቂያ ንባብ ይሁንልዎ፡፡


የሲንደሬላ መጥፎው ጎን


የአኩሪ አተር ሽያጭ በተአምራዊ መልኩ እንዲጨምር ያደረገው ፕሮፖጋንዳ እጅግ አስገራሚ የሚሆነው ከጥቂት ጊዚያት በፊት በኤስያም ሳይቀር አኩሪ አተር አይበሌ የነበረ መሆኑን ስንገነዘብ ነው፡፡ በቹ ስርወ መንግስት ዘመን (1134-246 ዓ.ዓ) አኩሪ አተር ከአራቱ ቅዱሳን እህሎች ማለትም ገብስ፣ ስንዴ፣ ዳጉሳ እና ሩዝ ጋር ተደምሮ ይቆጠር ነበር፡፡
ሆኖም ግን የወቅቱ የአኩሪ አተር ስእላዊ መግለጫ፣ ከቀደምት ዘመናት ጀምሮ የነበረው በምግብነት ይቆጠር እንዳልነበረ ያሳያል፡፡ የሌሎቹ አራቱ እህሎች ስእላዊ መግለጫ ፍሬያቸውንና ግንዳቸውን ሲያሳይ፣ የአኩቲ አተሩ ስእል የሚያሳየው ግን ስሩን ነበር፡፡ በዘመኑ የሰፈረው የእርሻ ጽሑፍ እንደሚያሳየው ከሆነ አኩሪ አተር ዘር ለማፈራረቅ ጥቅም ላይ ይውል እንደነበር ያስረዳል፡፡ እንደምንገነዘበው አኩሪ አተር የአፈሩን ናይትሮጅን ይዘት ለማስተካከል ነበር የሚተከለው፡፡ (13)
ማጠንሰስ (በውሃ መዘፍዘፍ) (ፈርመንቴሽን) ዘዴ እስኪደረስበት ድረስ አኩሪ አተር ለመብል አልዋለም ነበር፡፡ ይህ በቹ ስርወ መንግስት ዘመን የሆነ ነበር፡፡ መጀመርያ ላይ ተጠንስሶ ከአኩሪ አተር የተገኙት ምግቦች ቴምፔ፣ ናቶ፣ ሚሶ እና አኩሪ አተር ወጥ (ሶስ) ናቸው፡፡
በኋላ ላይ ምናልባት በ2ኛው ክ/ዘመን ዓ.ዓ ቶፉ (ወይም ወፍራም አተር ወጥ) በካልሺየም ሳልፌት ወይም በማግኒዠርየም ሳልፌት የነጠረ (ፕርሲፒቴትድ) የሚደረግ ምግብ አገኙ፡፡ ወድያው ወደ ጃፓንና ኢንዲነዥያ ተስፋፋ፡፡
ቻይናዎች ያልተጠነሰሰ አኩሪ አተር በሌሎች የጥራጥሬ ዝርያዎችን (ለጉምስ) ለምሳሌ እንደ ምስር ዓይነቶቹን እንደሚያደርጉት በልተው አያውቁም፡፡ ምክንያቱም አኩሪ አተር ከሌሎቹ የበለጠ ተፈጥሯዊ መርዝ ወይም “ፀረ-ንጥረ ምግብ” (“አንቲኒውትረንትስ”) አለውና፡፡ ከነዚህ የመጀመርያዎቹ ኢንዛይም አጋቾቹ ናቸው፡፡ ትራይፕሲን (trypsin) እና ሌሎች ፕሮቲንን ለመፍጨት የሚያስፈልጉ ኢንዛይሞችን ያግዳሉ፡፡
እነዚህ አጋቾች በመደበኛው የምግብ አዘገጃጀት ዘዴ ሊወገዱ የማይችሉ በጽኑ የተሳሰሩ ፕሮቲኖች ናቸው፡፡ ክፉኛ ጨጓራን የሚነኩ ሲሆኑ፣ የፕሮቲን መፈጨትን ይቀንሳሉ፣ የአሚኖ አሲድ ግብአታችንን በከፍተኛ መልኩ እንዲጠፋ ያደርጋሉ፡፡ በእንስሳት ላይ በተደረገ ሙከራ ትራይፕሲን አጋች የበዛበት ቀለብ የጣፊያ መተለቅ እና መታመም ሁኔታ ነቀርሳን ጨምሮ አስከትሏል፡፡(14)
አኩሪ አተር በተጨማሪ ሄማግሉቲኒን (haemagglutinin) አለው፣ ይህ የማርጋት ጠባይ ያለው ንጥረ ነገር ሲሆን ቀይ የደም ሴሎች እንዲጠባበቁ የሚያደርግ ነው፡፡
ትራይፕሲን አጋቾቹ እና ሄማግሉቲኒን እድገት ከልካይ ናቸው፡፡ እኚህ ፀረ-ንጥረ-ምግቦችን እንዲመገቡ የተደረጉ የአይጥ ጨቅላዎች በትክክል አላደጉም፡፡ በውሃ በሚዘፈዘፍበት ወይም በሚጠነሰስበት ወቅት እድገት የሚያውኩት ንጥረ ነገሮች ይመክናሉ፣ ቻይኖችም የመጠንሰስ ዘዴን መጠቀም ከጀመሩ በኋላ አኩሪ አተርን የመአዳቸው አካል አድርገውታል፡፡
ዝቃጭ የተደረጉ (ፐርሲፒቴትድ) ምርቶች ላይ ኢንዛይም ገዳቢዎቹ በሚነፋፋው አረፋ ላይ በመሰብሰብ እንደ እርጎ ከሚሆነው ይርቃሉ፡፡ እናም በቶፉ እና ቢን ከርድስ እድገት ከልካዮቹ በመጠን የሚቀነሱ ቢሆኑም ሙሉ ለሙሉ ግን አይወገዱም፡፡
አኩሪ አተር በተጨማሪም ጎይትሮጅንስ የተባለ ንጥረ ነገር ይገኝበታል፡፡ ጎይትሮጅን - የታይሮይድ እጢ ስራን የሚያደናቅፍ ንጥረ ነገር ነው፡፡
በተጨማሪም 99% የሚሆነው የአኩሪ አተር ምርት [ይህ በአሜሪካ መሆኑ ነው] ዘረ መሉ (ጀነቲክ) በሰው ሰራሽ መንገድ የተቀየረ ነው፡፡ ከምግቦችም ሁሉ በበለጠ በፀረ-ተባይ መድሃኒት የሚያድግ ነው፡፡
አኩሪ አተር ከፍተኛ ፋይቲክ አሲድ (phytic acid) አለበት፣ ይህ በሁሉም ጥራጥሬዎች ገለባ ወይም ቅርፊት ላይ የሚገኝ ነው፡፡ ይህ ንጥረ ነገር ወሳኝ የሆኑ ማዕድኖች በሰውነታችን እንዳይወሰዱ የሚገታ ነው፣ እንደ ካልሺየም፣ ማግኒዥየም፣ ኮፐር፣ ብረት እና በተለይም ዚንክ - በአንጀታችን እንዳይወሰዱ ያደርጋል፡፡
ፋይቲክ አሲድ በስፋት ጥናት የተደረገበት ንጥረ ነገር ነው፤ በአሁኑ በሳይንሳዊ ስነ ጽሑፍ ውስጥ ይህን የሚመለከቱ በመቶዎች የሚቆጠሩ ስራዎች ይገኛሉ፡፡ በፋይቴትስ ከፍተኛ መጠን ያላቸው ጥራጥሬ ወይም በተለይ የባቄላ ዘር ያላቸው እህሎችን ዋና ምግባቸው ያደረጉ በሶስተኛው ዓለም ያሉ ማሕበረሰቦች በስፋት ለሚፈጠርባቸው የማዕድን እጥረት ዋነኛው መንስኤ ፋይቴትስ መሆኑን ሳይንቲስቶች ይስማማሉ፡፡(15)
በነዚህ አካባቢዎች በተደረገው ጥናት በሚመገቧቸው አትክልት ምግቦች ውስጥ ካልሺየም፣ ማግኒዥየም፣ ብረት እና ዚንክ ይገኝበታል፣ ሆኖም ግን ከፍተኛ የፋይቴት ይዘት ያለው አኩሪ አተርና ጥራጥሬዎቹ እነዚህ ማዕድናት በሰውነታቸው እንዳይወሰዱ አድርጓቸዋል፡፡
አኩሪ አተር ከየትኛውም ጥራ ጥሬ ወይም የባቄላ ዘር (ለጉሜ) እጅግ በላቀ ሁኔታ የፋይቴት ይዘት አለው(16) በአኩሪ አተር ያለው ፋይቴት ደግሞ በተለመደው የፋይቴት መቀነሻ መንገድ ለምሳሌ እንደ ለረዥም ጊዜ በዝግታ ማብሰል ዓይነት ዘዴ አይቀነስም፡፡(17) በአኩሪ አተር ያለውን የፋይቴት ይዘት መቀነስ የሚቻለው ለረዥም ጊዜ በውሃ በመዘፍዘፍ (በመጠንሰስ) ብቻ ነው፡፡
እንዲዘቅጥ የተደረገ (ፕርስፕቴትድ) አኩሪ አተር ለምሳሌ እንደ ቶፉ ዓይነቱ ከስጋ ጋር ነው የሚበላው፣ በዚህም መዓድናትን የመከልከል የፋይቴት ባሕርይን መቀነስ ይቻላል፡፡(18) ጃፓኖቹም በባህላቸው እጅግ ትንሽ መጠን ያለው ቶፉ ወይም ሚሶ በማዕድናት ከበለጸገ የአሳ ሾርባ ጋር አድርገው ነው የሚመገቡት፣ ይህም ቀጥሎ የሚቀርብ ስጋ ወይም አሳ ይከተለዋል፡፡
በስጋ እና ወተት ተዋጽኦ ምትክ ቅጠል በሌ (ቨጀተርያን) የሆኑ ሰዎች ቶፉ እና የባቄላ “እርጎ” (በውሃ ተዘፍዝፎ ከታች እንደ አተላ የሚቀረው) ሲመገቡ ከፍተኛ የማዕድናት እጥረት አደጋ ይደቀንባቸዋል፡፡ የካልሺየም፣ ማግኒዥየም እና ብረት እጥረት ምን እንደሚፈጥሩ የታወቀ ነው፤ የዚንክ እጥረት ግን በብዛት አይታወቅም፡፡
ዚንክ የማስተዋል (ንቃተ ህሊና) መዓድን ይባላል፣ ምክንያቱም ለምርጥ የአእምሮ እና ነርቭ ስርዓት እድገትና ተግባር ስለሚያስፈልግ ነው፡፡ ዚንክ ለፕሮቲን መዋሃድ እና ኮላገን [አጥንት እና ጡንቻ መገጣጠምያ የሚገኝ] በመስራት ላይ ወሳኝ ሚና አለው፤ በደም-ስኳር ቁጥጥር ሂደት ሚና አለው፣ በዚህም ከስኳር በሽታ ይከላከላል፤ ለተዋልዶ ጤንነትም ያስፈልጋል፡፡
ዚንክ ብዛት ባላቸው ወሳኝ ኢንዛይሞች ውስጥ ቁልፍ አካላቸው ሲሆን በሽታ በመከላከል ስርአትም የራሱ ሚና አለው፡፡ በአኩሪ አተር የሚገኙ ፋይቴቶች ከሌሎቹ መዓድናት በይበልጥ ዚንክ መመጠጥን ይገድባሉ፡፡(19) የዚንክ እጥረት የቀንም ቅዠት ( “ምርቃና” ) ስሜት ውስጥ ይከታል፣ አንዳንድ ቅጠል በሌዎች [ቨጀተርያንስ ለማለት ነው ጫት ቃሚዎች ለማለት አይደለም፣ ወይ ምፀት/አይረኒ] ይህን ስሜት እንደ “ከፍ ከፍ” የሚያደርግ መንፈሳዊ ልምድ ወይም አብርሆት እንደገጠማቸው አድረገው እንዲያስቡ ያደርጋቸዋል፡፡ 
ወተት መጠጣታቸው አሜሪካ ያሉ የጃፓናውያን ሁለተኛ ትውልዶች ቁመት መርዘም እንደ ምክንያት ይቀመጣል፡፡ አንዳንድ ተመራማሪዎች እንደሚገምቱት ከሆነ ዝቅተኛ ፋይቴት ያለው የአሜሪካውያኑ መብል -ምንም እንኳ ሌላ ሰንኮች ቢኖሩበትም- ዋናው የቁመታቸው መጨመር ማብራርያ ነው ይላሉ፡፡ ፋይቴት የበዛበት ምግብ የሚወስዱና ተጽእኖውን ለመቀነስ በቂ ስጋ እና አሳ የማያገኙ የኤስያውያንም ሆነ የምእራባውያን ልጆች በብዛት ሪኬትስ፣ አጭር መሆን እና ሌሎች የእድገት እክሎች ይገጥሟቸዋል ሲሉ ይጠቁማሉ፡፡(20)


ፕሮቲንን ከአኩሪ አተር መነጠል፡ አደጋው


አኩሪ አተር ሰሪዎች እነዚህን ፀረ-ንጥረ ምግቦችን ካለቀለት የአኩሪ አተር ምርቶች ለማውጣት ብዙ ደክመዋል፣ በተለይ ከአኩሪ አተር የተነጠለው ፕሮቲን (soy protein isolate (SPI)) ውስጥ፣ ከአኩሪ አተር ከተነጠለ ፕሮቲን ስጋ እና ወተት ተዋጽኦን ለመምሰል የሚጥሩ ምርቶች ዋና አካል ነው፣ የሕጻናት የምግብ ቀመር (ፎርሙላ) እና አንዳንድ የወተት ስሪቶች፡፡
የፕሮቲን ንጣዩን እንዳሻህ በኩሽናህ መስራት የሚቻል ነገር አይደለም፡፡ ይህ የሚከወነው ኢንዱስትሪያዊ በሆኑ ፋብሪካዎች ውስጥ ሲሆን መጀመር የተለቆጠ (በውሃ የተለወሰ) አኩሪ አጠር ጥሬ ፋይበሩን ለማስወገድ ከአልካላይን ፈሳሽ ጋር ይቀላቀላል፣ ከዛ በአሲድ እጥበት እንዲዘቅጥ እና እንዲለያይ ከተደረገ በኋላ በመጨረሻ በአልካላይን ፈሳሽ ኒውትራል እንዲሆን ይደረጋል፡፡  
በአሉሚኒየም ገንዳ ውስጥ በአሲድ ማጠብ በመጨረሻ ምርቱ ላይ ከፍተኛ የአሉሚኒየም ይዘት እንዲቀላቀልበት ያደርጋል፡፡ ከዚህ የሚገኙት ዝቃጮች በከፍተኛ ሙቀት ርጭት እንዲደርቁ ይደረጋሉ፣ ይህም ከፍተኛ የፕሮቲን ምርቱን ይሰጠናል፡፡ አኩሪ አተሩን ለመጨረሻ ጊዜ ያራከሰው ቴክስቸርድ የአትክልት ፕሮቲን (ቲቪፒ) ከአኩሪ አተር ከተነጠለ ፕሮቲን ለመስራት በሚደረገው እጅግ ከፍተኛ ሙቀት፣ ከፍተኛ ግፊት (ፕሬዠር) ሂደት ነው፡፡
በከፍተኛ ሙቀት ሂደት አብዛኞቹ የትራይፕሲን አጋቾቹን ይዘቶች ማስወገድ ይቻላል፣ ሁሉም ግን አይወገዱም፡፡ በተለያዩ የአኩሪ አተር የፕሮቲን ንጥል ውስጥ የሚገኘው ትራይፕሲን አጋቾች እስከ አምስት እጥፍ ድረስ የተለያዩ ሊሆኑ ይችላሉ፡፡(21) (በአይጦች በተደረገ ሙከራ እጅግ ዝቅተኛ ትራይፕሲን አጋቾች ያሉዋቸው የአኩሪ አተር ፕሮቲን ንጥል የተመገቡት ካልተመገቡት (ማነጻጸርያዎች) ጋር ሲተያዩ ክብደታቸው የቀነሰ ሁነው ተገኝተዋል፡፡(22)) 
በተጨማሪ ከፍተኛ-ሙቀት ሂደት ሌላ ተጓዳኝ ጉዳት አለው፣ በአኩሪ አተር ያሉትን ሌሎች ፕሮቲኖችን ከተፈጥሮ ውጭ ስለሚያደርጋቸው በከፍተኛ ሁናቴ ከጥቅም ውጭ ያደርጋቸዋል፡፡(23) ለዚህም ነው መኗቸው አኩሪ አተር የሆኑ እንስሳት በትክክል እንዲያድጉ ላይዚን (lysine) በተጨማሪ ከቀለባቸው እንዲጨመር የሚደረገው፡፡
ከባድ ነቀርሳ አምጪ ንጥረ ነገር (ካርሲኖጂንስ) የሆኑት ናይትራይቶች የሚፈጠሩት በሙቀት ርጭት እንዲደርቅ ሲደረግ ነው፣ በአልካላይን ሲታጠብ ደግሞ ላይሲኖአላናይን (lysinoalanine) የተባለ መርዝ እንዲፈጠር ያደርጋል፡፡(24) ብዙ አርቲፊሻል ማጣፈጫዎች፣ በተለይም ኤምኤስጂ፣ ከአኩሪ አተር የሚነጠል ፕሮቲን ላይ እና ቴክስቸርድ አትክልት ፕሮቲን ላይ ይጨመራሉ፣ ይህ እንደ ባቄላ ያለ የጣእም ቃናቸውን ለመሸፈንና እንደ ሥጋ ሥጋ እንዲሉ የሚደረግ ነው፡፡(25)
በቀለብ ሙከራዎች ወቅት ከአኩሪ አተር የተነጠለ ፕሮቲን በተፈተሸ ጊዜ የቫይታሚን ኢ፣ ኬ፣ ዲ እና ቢ12 ላይ ያለው አስፈላጊነት እንዲጨምር አድርጓል፡፡ በተጨማሪም የካልሺየም፣ ማግኒዥየም፣ ማንጋኒዝ፣ ሞሊብዲነም፣ ኮፐር፣ ብረት እና ዚንክ እጥረት ምልክቶች እንዲፈጠር አድርጓል፡፡(26) በነዚህ አኩሪ አተር ውስጥ ቀሪ ሆኖ ያለው ፋይቲክ አሲድ በከፍተኛ ሁኔታ የዚንክ እና የብረት መወሰድ እንዲቀንስ አድርጓል፤ ከአኩሪ አተር የተነጠለ ፕሮቲን እንዲመገቡ የተደረጉ እንስሳት አንዳንድ ሕዋሳቶቻቸው በተለይም ጣፍያቸው እና ታይሮይድ እጢያቸው እንዲተልቅ አድርጓል፣ በተጨማሪም በጉበት ላይ ፋቲ አሲዶች ይበልጥ እንዲከማቹ አድርጓል፡፡(27)
እንዲህም ሆኖ የአኩሪ አተር ፕሮቲን ንጥል እና ቴክስቸርድ የአትክልት ፕሮቲን [በአሜሪካ] በትምህርት ቤቶች የምሳ የምግብ ፕሮግራሞች፣ ለሽያጭ በሚሰሩ የዳቦ ምርቶች፣ ተመጣጣኝ ምግብ ይዘት ላላቸው ለስላሳ መጠጦች እና የሽያጭ ምግቦች (ፋስት ፉድስ) ላይ ጥቅም ላይ ይውላሉ፡፡ በሶስተኛው ዓለም [ድሃ ሃገሮች] ውስጥ የእርዳታ ምግብ ሆኖ በስፋት ይሰጣል፡፡
በእንስሳት ላይ ተደርጎ የተገኘው ደካማ ውጤት እንዳለ ሆኖ የአኩሪ አተር ኢንዱስትሪው የተለመደው የሰው ልጆችን መብል በአኩሪ አተር መተካት የሚመክሩ የተለያዩ ጥናቶችን ስፖንሰር አድርጎ አሰርቷል፡፡
የዚህ አብነት የሚሆነው "Nutritional Quality of Soy Bean Protein Isolates: Studies in Children of Preschool Age" የተሰኘው ነው፣ በራልስቶን ፑሪና ኩባንያ ስፖንሰር አድራጊነት የተዘጋጀ ጥናት ነው፡፡(28) የተመጣጠነ ምግብ እጥረት ችግር ያለባቸው የማእከላዊ አሜሪካ ህጻናት ስብስብ ላይ የተደረገ ሙከራ ነው፡፡ መጀመርያ ላይ የተለመዱ ምግቦችን፣ ስጋንና ወተትን ጨምሮ፣ በመመገብ ወደ ጤናማ ሁኔታ ካመጧቸው በኋላ፣ ለሚቀጥሉት ሁለት ሳምንታት እነዚህ ልማዳዊ ምግቦች ከአኩሪ አተር በተነጠለ ፕሮቲን በተሰራ ፈሳሽ እና ስኳር እንዲተካ አድርገዋል፡፡
በኦርዌላዊ ዘዬ ወደ ሰውነታቸው የተወሰደ እና ከሰውነታቸው የተወገደ ናይትሮጅን እንዲለካ ተደርጓል፡ ልጆቹ ዘወትር ጠዋት እራቁታቸውን ክብደታቸው የሚመዘን ሲሆን፣ ዓይነ ምድራቸውና ትውከታቸው ተሰብስቦ ለምርመራ ይወሰድ ነበር፡፡ ተመራማሪዎቹ ልጆቹ ናይትሮጅ መያዝ (ማከማቸት) መቻላቸውን እና እድገታቸውም “በቂ” እንደነበር አገኙ፣ ምርምራቸውም (ሙከራቸውም) ስኬታማ ተብሎ ታውጇል፡፡   
በእርግጥ ልጆቹ በዚህ አመጋገብ ምጣኔ ጤነኛ ነበሩ ወይም በረዥም ጊዜ ልኬት በጤንነት ቆዩ ወይ የሚለው ሌላ ጉዳይ ነው፡፡ ተመራማሪዎቹ ልጆቹ “በተደጋጋሚ” ማስታወካቸውን፣ በተለይ ከማዕድ ሲነሱ፣ ከግማሽ በላይ የሚሆኑት ለተወሰነ ጊዜ በሚቆይ ተቅማጥ መያዛቸው፣ አንዳንዶች የላይኛው የትንፋሽ ስርአት መቁሰል (upper respiratory infections) ሲያጋጥማቸው፣ ሌሎቹ ደግሞ በሽፍታ እና በትኩሳት ይሰቃዩ እንደነበር ልብ ሊሉ እንደቻሉ ጠቅሰዋል፡፡
እዚህ ጋር ልብ ሊባል የሚገባው ነጥብ ተመራማሪዎቹ የሕጻናቱን የተመጣጣኝ ምግብ እጥረትን ለመቅረፍ የአኩሪ አተር ምርቶችን በመጠቀም ለመርዳት አለመሞከራቸውን እና የአኩሪ አተርና ስኳር ቅልቅል ከአኩሪ አተር ምርቶች የማይገኙትን በተለይ ቫይታሚን ኤ፣ ዲ እና ቢ12፣ ብረት፣ አዮዲን እና ዚንክ ንጥረ ምግቦችን ለመጨመር ተገደው ነበር፡፡  


እንከን የለሹን ምግብ መሸጥ


“እንከን የለሽ ምግብ ማሳደግ እችላለው ብለህ አስብ፡፡ ይህ ምግብ በቀላል ወጪ የሚገኝ የተመጣጠነ ምግብ ብቻ ሳይሆን፣ ጣፋጭና በተለያየ መልኩ ለማዘጋጀት ቀላል ይሆናል፡፡ ጤናማ ምግብና የታጨቀ ስብ (saturated fat) አይኖረውም፡፡ እንዲያውም በአርባዎቹ መጨረሻ ሁነህ የወጣትነት ፀጋ ይፈስብሃል፡፡”
ይህን ጥቅስ ዲን ሁግቶን የተባለው ለ ዘ ፉሮው በሚጽፍበት ወቅት ያሰፈረው ነው፡፡(2) ይህ በ12 ቋንቋዎች የሚታተመው በጆን ዴሪ መጽሔት ነው፡፡ “ይህ እንከን የለሹ ምግብ አንዳንድ የአለማችን አሰቃቂ በሽታችን መከላከልና የታመሙት እንዲያገግሙ ማድረግ ይቻለዋል፡፡ ይህን ተአምራዊ ሰብል በተለያዩ የአፈር ዓይነቶችና የአየር ሁኔታዎች ማብቀል ትችላለህ፡፡ ይህን ሰብል ማልማት መሬቱን የሚበላ ሳይሆን የሚያለማ ነው …፡፡ ይህ ተአምራዊ ምግብ በእውን አለ ….፡፡ አኩሪ አተር ይባላል፡፡”
አስበው፡፡ ገበሬዎች ሲያስቡት ነበር - በየአመቱም ተጨማሪ አኩሪ አተር ይዘራሉ፡፡ በአንድ ወቅታ አናሳ ሰብል የነበረው፣ በ1913 በአሜሪካ እርሻ ክፍል (ሚኒስቴር) ደብተር እንደ ምግብ ሳይሆን እንደ ኢንዱስትሪያዊ ምርት ተመዝግቦ የነበረው፣ ዛሬ ላይ በአሜሪካ እርሻ መሬት 72 ሚሊዮን ኤከር [291,384,000,000 ሜ. ካሬ] ሊሸፍን ችሏል፡፡ ከዚህ አርሻ አብዛኛው ዶሮዎችን፣ ተርኪዎችን (የአሜሪካ ዶሮዎችን)፣ አሳማዎችን፣ ላሞችን እና ሳልሞንኖችን (ትልልቅ አሶችን) ለመቀለብ የሚውል ነው፡፡ ሌላው ዋና ጥቅሙ የዳቦ ቅቤ (ማርጋሪን)፣ ለሚጋገሩ የሚሆን፣ እና ሰላጣ መቀቢያ የሚሆን ዘይት መሆን ነው፡፡  
በተገኘው የቴክኖሎጂ መሻሻል እንደ ቆሻሻ ተረፈ ምርት ይቆጠር ከነበረው ከአኩሪ አተር የተነጠለ ፕሮቲን ማስገኘት ተችሏል -ስብ የሌለው ከፍተኛ ፕሮቲን ያለው የአኩሪ አተር ምርት- ለማየት የሚያስጠላ እና አስቀያሚ ሽታ ያለውን ተረፈ ምርት ሰዎች ሊበሉት ወደሚችሉት ምርት መቀየር ተችሏል፡፡ ማጣፈጫዎች፣ ከመበላሸት ጠባቂዎች፣ ኢሙልሲፋየሮች እና ሲንተቲክ ንጥረ ምግቦች ከአኩሪ አተር የተነጠለ ፕሮቲን ምርትን የምግብ ሰሪዎቹን አስቀያሚ ዳክዬ ወደ አዲስ ዘመን ሲንደሬላ ቀይረውታል፡፡
አዲሱ ተረታዊ ምግብ ለውበቷ ሳትሆን ለምግባሯ ተብላ ነው ለገበያ የቀረበችው፡፡ ከመጀመርያውኑ ጀምሮ ከአኩሪ አተር የተነጠለ ፕሮቲን ጨማሪዎች (ኤክስተንደርስ) እና የስጋ ምትክ ተብሎ ነበር መሸጥ የተጀመረው - ይህ ስልት የተፈለገውን የደንበኛ ፍላጎት ሊያስገኝ አልቻለም፡፡ ኢንዱስትሪው አቀራረቡን ቀየረ፡፡
“ብዙም ያልተረፈው ማህበረሰብ ውስጥ ምርቱ ተቀባይነት እንዲያገኝ፣” ይላል የኢንዱስትሪው ቃል አቀባይ፣ “ምርቱ ለራሱ ፋይዳ ሲባል ብቻ በተረፈው ማህበረሰብ ውስጥ እንዲዘወተር ማድረግ ነው፡፡”(3) እናም አሁን ለከፍተኛው ማህበረሰብ ክፍል አኩሪ አተር ርካሽ የችግር ምግብ ሳይሆን ተአምራዊ ንጥረ ነገር፣ የልብ ህመንንና ነቀርሳን የሚከላከል፣ ፈጣን ትኩሳት (ሆት ፍላሽ፣ ያረጡ ሴቶችን የሚያጋጥማቸው) የሚከላከል፣ አጥንት የሚገነባና ዘላለም ወጣት አድርጎ የሚያኖር ተደርጎ እየተሸጠላቸው ነው፡፡
ተፎካካሪዎቹ -ሥጋ፣ ወተት፣ አይብ፣ ቅቤ እና እንቁላል- በሚመለከታቸው የመንግስት አካላት ተይጣናዊ ተደርገው ቀርበዋል፡፡ አኩሪ አተር ቅጠል በሊታ የሆኑ አዲስ መልካም ትውልዶች ሥጋ እና ወተት ሆኖ ያገለግላቸዋል፡፡


መሸጥ ገንዘብ ያስወጣል


ይህ ደግሞ በተለይ እውነት የሚሆነው ጉዳዩ በ “ምርምር” መግዘፍ የሚያስፈልግ ሲሆን ነው፣ ግን ደግሞ የገንዘብ ድጎማ ለዚህ ጉዳይ ሞልቷል፡፡ ሁሉም የአኩሪ አተር አምራቾች ከአኩሪ አተር የገበያ ዋጋ የአንድ ግማሽ እስከ አንድ መቶኛ ድረስ አስገዳጅ የመዋጮ ክፍያ ይጠበቅባቸዋል፡፡ በአጠቃላይ -ወደ 80 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር የሚጠጋ (4) የአኩሪ አተር ሕብረት እንቅስቃሴን ይደጉማል፣ “አኩሪ አተር በገበያ ያለውን ቦታ ማጠናከርና የአኩሪ አተር እና የአኩሪ አተር ምርት የሃገር ውስጥና የውጭ ሃገር ገበያን ለመጠበቅና ለማስፋፋት ይውላል፡፡”
የመንግስት የአኩሪ አተር መማክርት የሜሪላድ፣ ነብራስካ፣ ዴላዌር፣ አርካንሷ፣ ቨርጂንያ፣ ሰሜን ደኮታ እና መሺጋን ሌላ ተጨማሪ 2.5 ሚሊዮን ዶላር ለ “ምርምር” ያዋጣሉ፡፡(5) እንደ አርቸር ዳኒኤልስ ሚድላንድ [ኤዲኤም]  ያሉ የግል ኩባንያዎች ደግሞ የድርሻቸውን ያዋጣሉ፡፡ ኤዲኤምን ሚት ዘፕሬስ ላይ ለማስተዋወቅ 4.7 ሚሊዮን ዶላር ያወጣ ሲሆን፣ በተጨማሪም ፌስ ዘ ኔሽን ላይ ለማስተዋወቅ 4.3 ሚሊዮን ዶላር አውጥቷል፡፡(6)
የሕዝብ ግንኙነት ድርጅቶች የምርምር ፕሮጀክቶቹን ወደ ጋዜጣ መጣጥፎች ለመቀየር እና ማስታወቅያ ለማስደረግ ተከፍሏቸው ሲሰሩ፣ የህግ ድርጅቶች ደግሞ ተስማሚ የመንግስት ደንቦች እንዲወጡ ተከፍሏቸው ይወተውታሉ (ሎቢ ያደርጋሉ፡፡) በመላው አለም ደግሞ አኩሪ አተር የሚቀምሩ ፋብሪካዎች እንዲሰሩ አይኤምኤፍ ፈንድ ይሰጣል፣ በተጨማሪም አኩሪ አተር ነገፍ በዓለም ገበያ እንዲቀርብ ነጻ የንግድ ፖሊሲ እንዲኖር ያደርጋል፡፡
ተጨማሪ አኩሪ አተር እንዲኖር የሚደረገው ግፊት የማያባራ እና በተደራሽነቱም ሉላዊ ነው፡፡ አሁን የአኩሪ አተር ዳቦ [በአሜሪካ] ገበያዎች በአብዛኛዎቹ የደረሰ ነው፡፡ “በበቆሎ የሚሰራው የሜክሲኮን ቂጣ ቶርቲላንም በፕሮቲን የታጨቀ በማድረግ ወደ 20 ሚሊዮን የሚጠጉ የሜክሲኮ ድሆችን የተመጣጣኝ ምግባቸውን ከፍ ለማድረግ”(7) እየተጠቀሙበት ይገኛሉ፡፡ በብሪታንያ አላይድ ቤከርስ የተባሉ ዳቦ ሻጮች ደግሞ ያረጡ ሴቶች ላይ በማነጣጠር ፈጣን ትኩሳትን ይቀንሳል በሚል እያስተዋወቀ ይገኛል፡፡ በሳምንት ሩብ ሚሊዮን ዳቦ ይሸጣል፡፡(8) 
“በትምህርት ቤት የምሳ ማዕድ ላይ ተጨማሪ የአኩሪ አተር ምግቦች እንዲጨመሩ” የአኩሪ አተር ኢንዱስትሪው ኖርማን ሮበርት አሶሼትስ ተባለው የሕዝብ ግንኙነት ድርጅት ቀጥረዋል፡፡(9) የአሜሪካ መንግስት ግብርና ክፍል (ሚኒስቴር) በትምህርት ቤት ምሳ ላይ ሊቀርብ የሚችለው የአኩሪ አተር ከፍተኛ መጠን ገደብ፣ 30 መቶኛ የሚለውን ለመሰረዝ ተስማማ፡፡ የኑሜኑ (NuMenu) የተባለው የምሳ መርሐ ግብር በተማሪዎች ምሳ ሊቀርብ የሚችለው የአኩሪ አተር ድርሻን ያለ ገደብ ማድረግ ይፈቅዳል፡፡ ሃምበርገር፣ ታኮ እና ላዛኛ ላይ አኩሪ አተር ተጨምሮ አጠቃላይ ስቡ ከ30 መቶኛ ካሎሪ በታች አድርገው የመንግስት ቁጥጥር ጋር ተስማሚ ሁነው ይገኛሉ፡፡ “በአኩሪ አተር የበለጸጉ ምግቦች ተማሪዎች የተሻለ ተመጣጣኝ ምግብ እና ዝቅተኛ ኮሌስትሮል እና ስብ እያገኙ ነው፡፡” 
ከሁሉም ተጠቃሚ የሆነው የአኩሪ አተር ወተት ነው፣ በ1980 ከነበረው 2 ሚሊዮን ዶላር አምና [1999] ላይ ወደ 300 ሚሊዮን ዶላር ሊያድግ ችሏል፡፡(10)
የአሰራር ሂደት ተአምራቶች፣ ጥሩ አቀራረብ፣ እና ግዙፍ የማስታወቅያ ስራ እና ምርቱ ለመልካም ጤንነት ጥቅም ሊያስገኝ ይችላል በሚል የታጀበው የሽያጭ ስልት በሁሉም የእድሜ ክልል ለሚገኙ ሰዎች ተሸማችነቱ እንዲጨምር አድርጓል፡፡ ለምሳሌ አኩሪ አተር ፕሮስቴት ካንሰር ይከላከላል የሚሉት ዘገባዎች በመካከለኛ እድሜ (ጎልማሳ) ወንዶች አኩሪ አተር ወተት እንዲጠጡ አድርጓቸዋል፡፡ “ከ 55 እስከ 60 ዓመቱ የሆነውን ወንድ የአኩሪ አተር ወተት እንዲጠጣ እጁን መጠምዘዝ የለብህም፡፡” ይላል ማርክ መዚና፡፡ ማይክል ሚልከን የእርባና ቢስ አረቦን (ጃንክ ቦንድ) በመሸጥ የከበረው የቀድሞ የፋይናንስ ነጋዴ የአኩሪ አተር ኢንዱስትሪ የነበረውን የሂፒ ምስል (የወፈፌዎች ምግብነት) በጣም በተቀነባበረ የሕዝብ ግንኙነት ዘመቻው ለሁሉም በቀን 40 ግራም የአኩሪ አተር ፕሮቲን መውሰድ አስፈላጊ ነው በሚል አተያየት እንዲቀየር አድርጓል፡፡  
ዛሬ አሜሪካ፣ ነገ ዓለሙን፡፡ የአኩሪ አተር ወተት ሽያጭ በካናዳ እየጨመረ ነው፣ ምንም እንኳ በሃገሪቱ የአኩሪ አተር ወተት ከላም ወተት ሁለት እጥፍ በዋጋ የሚበልጥ ቢሆንም፡፡ በኬንያ እንኳ የአኩሪ አተር ማቀነባበርያ ፋብሪካዎች እየተቋቋሙ ነው፡፡(11) [ዛሬ በኢትዮጵያም ተቋቁሟል፡፡] በቻይና እንኳ ሳይቀር አኩሪ አተር የችግር ጊዜ ምግብ ተደርጎ የሚወሰደው እና ህዝቡ ተጨማሪ ሥጋ እንጂ ቶፉ የማይሹት፣ እንደ ምእራባውያን ያለ የአኩሪ አተር ኢንዱስትሪ ወደ መገንባት ገብተዋል፣ እንደ ምእራባውያኑ ለከብቶች ቀለብ የሚሆን የሳር መሬት ከማልማት ይልቅ፡፡(12)


አፍዲኤ የሰጠው የጤና እውቅና ጥያቄ ውስጥ


በኦክቶበር 25፣ 1999 የአሜሪካ መድሃኒትና ምግብ ባለስልጣን (ኤፍዲኤ) “በታጨቀ ስብ (ሳቹሬትድ ፋት) እና ኮሌስትሮል ዝቅተኛ የሆኑ” በአንድ ጊዜ ሲቀርቡ 6.25 ግራም የአኩሪ አተር ፕሮቲን የሚይዙ ምግቦችን ለጠየና ተስማሚ የሚል እውቅና ለመስጠት ይስማማል፡፡ የቁርስ ሲርያሎች፣ የተጋገሩ ምርቶች፣ የሚመቹ የሽያጭ ምግቦች፣ የሥጋ ቅያሪዎች ለልብ እና የደም ቧንቧ (ካርድዮ ቫስኩላር) ጤና ጠቃሚ ናቸው የሚል ማስታወቅያ ሊለጠፍባቸው ይችላል ማለት ነው፣ እነዚህ ምርቶች በመቶ ግራም ማዕድ ውስጥ አንድ ማንኪያ የአኩሪ አተር ፕሮቲን ብቻ እንዲኖራቸው ይጠበቃል፡፡
ለጤና ጠንቅ የሆነን ምግብ የምትሸጥበት ምርጡ መንገድ ለጤና ተስማሚ ነው ብለህ ነው፡፡
“ከኤፍዲኤ እውቅና ለማግኘት የተሄደበት መንገድ” ይላል አንድ የአኩሪ አተር አቀንቃኝ (አስተባባይ)፣ “ረዥም እና አድካሚ ነበር፣ ላለፉት 20 ዓመታት በሰው ላይ ምርምር የተደረገበት የክሊኒክ መረጃ ተይዞ በተደረገ ጥልቅ ትንተና ነበር፡፡ የአኩሪ አተር ፕሮቲን እጅግ ጥቂት ከሆኑት ለኤፍዲኤ የጤና እውቅና ለማግኘት በቂ ሳይንሳዊ መረጃ ያለው ብቻ ሳይሆን በመጨረሻም ከባድ የሆነውን የእውቅና ሂደት ለማለፍ የበቃ ነው፡፡”(29)
እንዲያውም ወደ ኤፍዲኤ እውቅና ማግኛ የወሰደው “ረዥም እና አድካሚ” መንገድ በመሃል ያልተጠበቁ ቅያሶችን ተጠማዟል፡፡ በፕሮቲን ቴክኖሎጂ ኢንተርናሽናል ድርጅት መጀመርያ ላይ የገባው ዋናው የእውቅና ይሰጠን ጥያቄ ወረቀት፣ አይዞፍሌቮኖች ለጤና ተስማሚ ናቸው የሚል ጥያቄ ነበር፡፡ አይዞፍሎቮን እንደ ኢስትሮጅን [የሴቶች ሆርሞን] አይነት ባሕርይ ያለው በአኩሪ አተር ውስጥ በስፋት የሚገኝ ንጥረ ነገር ነው፡፡ ጥያቄውም የቀረበው “አይዞፍሎቮኖቹ እንዳይጠፉ ተደርጎ የተነጠረ የአኩሪ አተር ፕሮቲን ብቻ ነው ኮሌስትሮል እንዲቀንስ የሚያደርግ፡፡” የሚል ነበር፡፡  
በ1998 ኤፍዲኤ የጠያቂው ድርጅት ወረቀትን ተሰምቶ በማይታወቅ ሁኔታ በማረም፣ ፋይቶ-ኢስትሮጅን የሚጠቅሱ መስመሮችን በመሰረዝ እና ጥያቄው ለአኩሪ አተር ፕሮቲንን የሚመለከት አደረጉት፡፡ ይህ ተግባር የባለስልጣኑ መመርያ ውጭ የተፈጸመ ነበር፡፡ ኤፍዲኤ በቀረበለት ወረቀት ላይ ፍርዱን ይሰጣል እንጂ የማረም ስልጣን የለውም፡፡
እንዲህ ሳይታሰብ እንዲቀይሩት ያስገደዳቸው በርከት ያሉ ተመራማሪዎች፣ የአሜሪካ መንግስት የቀጠራቸው ሳይንቲስቶች ሳይቀሩ፣ አይዞፍሌቮኖች መርዝ መሆናቸውን የሚያሳዩ ወረቀቶች ስላስገቡ ነው፡፡
ኤፍዲኤ ቀደም ብሎ በ1998 የእንግሊዝ መንግስት ፋይቶኢስትሮጅን ላይ የሰራውን የመጨረሻ ዘገባ ደርሶት ነበር፣ ዘገባውም ብዙም ጥቅም ያላገኘበት ሲሆን እንዲያውም ሌላ ከባድ ጉዳት እንደሚኖረው አስጠንቅቋል፡፡(30)
እውቅናው ወደ ከአኩሪ አተር የተነጠለ ፕሮቲን ቢቀየርም እንኳ “ከባድ የሆነውን የእውቅና ሂደት” ላይ የተሳተፉት የኤፍዲኤ ቢሮክራቶች ስለ መዓድናት አጋቾቹ፣ ኢንዛይም አጋቾቹ፣ ጎይትሮጅን፣ ኢንዶክራን ማወኩ፣ ስነ ተዋልዶ መዘዙ፣ እየናረ ያለው አለርጂ አስከታይነቱ የሰጠው ምልከታ እዚህ ግባ የሚባል አይደለም፡፡(31)
ከሁሉ ጠንከር ያለው የተቃውሞ ደብዳቤ የመጣው ከዶ/ር ዳን ሺሃን እና ከዶ/ር ዳንኤል ዶርጅ ነው፣ በመንግስት ስር የብሔራዊ የመርዛማነት ምርምር ማእከል (National Center for Toxicological Research) ውስጥ ተመራማሪዎች ናቸው፡፡(32) የማሳሰብያ ጽሑፎች በምርቶቹ ላይ እንዲለጠፉ መጠየቃቸው አላስፈላጊ ብለው ትተዋቸዋል፡፡
ኮሌስትሮል መጠን ይቀንሳል ለሚባለው “በቂ ሳይንሳዊ መረጃ” የመጣው በ1995 ዶ/ር ጄምስ አንደርሰን ካደረገው ሜታ-ትንታኔ ነው፡፡ ትንታኔውን የደጎመው ፕሮቲን ቴክኖሎጂስ ኢንተርናሽናል ሲሆን የታተመው ደግሞ በኒው ኢንግላንድ ጆርናል ኦፍ መዲስን ነው፡፡(33)
ሜታ-ትንተና ማለት በአንድ ርእስ ላይ የተደረጉ ብዛት ያላቸው ክሊኒካዊ ጥናቶች ዳሰሳ እና ማጠቃለያ ማቅረብ ማለት ነው፡፡ አጠቃላይ ድምዳሜ ላይ ለመድረስ ሜታ-ትንታኔን መጠቀም ከሳይንስ ማህበረሰቡ ከፍተኛ ትችት ይደርስበታል፡፡
“በጥብቅ ሙከራዎች ምትክ ሜታ-ትንተና የሚተኩ ተመራማሪዎች የተሳሳተ መላ ምት የመስጠት እና የፈጠራ ስሌት የማስቀመጥ ስህተት ውስጥ ሊገቡ ይችላሉ፡፡” ይላል የኒውዝላንድ ሮያል ሶሳይቲ ፕሬዚደንቱ ሰር ጆን ስኮት፡፡ “ተመሳሳዮች አይደሉም የሚጣበቁት፡፡ በመረጃ ስብስብ ትንሽም ትልቅም ያላቸው ምርምሮች በተለያዩ ቡድኖች አንድ ላይ እየተደባለቁ ነው፡፡”(34)
አሁን ደግሞ በአንዳንድ ተመራማሪዎች ዘንዳ በተለይ እንደ ፕሮቲን ቴክኖሊጂስ ኢንተርናሽናል ዓይነቱ ድርጅት የሚደጎሙት በትንተናቸው የሚፈለገው ድምዳሜ ላይ ከመድረስ የሚያግዱ ጥናቶችን የመተው አዝማምያ ይስተዋላል፡፡ ዶ/ር አንደርሰን ስምንት ጥናቶችን በተለያየ ምክንያት ወደ ጎን ብሏል፣ ሃያ ዘጠኝ ብቻ አካቷል፡፡
ያሳተመው ዘገባ የኮሌስትሮል መጠናቸው ከ 250 mg/dl በላይ የሆኑ ግለሰቦች “በወሳኝ ደረጃ” ከ7 እስከ 20 መቶኛ ድረስ የሴረም ኮሌስትተሮል መጠናቸው እንደሚቀንስላቸው ይናገራል፣ የእንስሳት ፕሮቲንን በአኩሪ አተር ፕሮቲን ከተኩት፡፡ የኮሌስትሮል መጠናቸው ከ 250 mg/dl በታች ለሆኑ ብዙም አልቀነሰላቸውም፡፡ 
በሌላ አነጋገር ለአብዛኞቻችን ሥጋ መተዋችን ያን ያህል የደም ኮሌስትሮላችንን አይቀንስልንም ማለት ነው፡፡ “በሰው ላይ ምርምር የተደረገበት የክሊኒክ መረጃ ተይዞ በተደረገ ጥልቅ ትንተና” በኋላ እውቅና የሰጠው የኤፍዲኤ ማረጋገጫ ሸማቾች ይህን ወሳኝ ነጥብ ማስታወሱን የዘነጋ ነው፡፡
የሞለኩዊላር ሕክምና ምርምር መርሃ ግብር እና የለውረንስ በርክለይ ብሔራዊ ላቦራቶሪ ሐላፊ የሆነው ሮናልድ ኤም. ክራውስ (ኤምዲ) አኩሪ አተርን ከኮሌስትሮል መጠን መቀነስ ጋር የሚያያይዙት ምርምሮች “እጅግ በጣም እንጭጭ” ደረጃ ያሉ ናቸው ይላል፡፡(35) በዚሁ ላይ እንደሚከተለው ማከል ይችል ነበር፡ በምግብ ወይም በመዳኒት ኮሌስትሮል መጠን ለመቀነስ በሚደረጉ ጥናቶች ለማነፃፀር ከሚቀመጡት መሞከርያዎች (ኮንትሮል ግሩፕ) ይልቅ ሙከራው የሚደረግባቸው ላይ ይበልጥ ሞት የሚደርስ መሆኑን - ሞቱም በድንገተኛ ጥቃት (ስትሮክ)፣ ነቀርሳ፣ የአንጀት መታመም፣ አደጋዎች፣ እና እራስን ማጥፋት ናቸው፡፡(36)
በሃገረ አሜሪካ ኮሌስትሮል ለመቀነስ በሚደረግ እንቅስቃሴ በአመት 60 ቢሊዮን ዶላር የሚፈስበት ኢንዱስትሪ እንዲነሳ አድርጓል፣ ሆኖም ግን ከዚህ ከሚመጣው የልብ ህመም ወረርሽኝ ህዝቡን አልታደገም፡፡


አኩሪ አተር እና ነቀርሳ (ካንሰር)


በአዲሱ የኤፍዲኤ መመርያ መሰረት በማንኛውም ምግብ ላይ ነቀርሳ ይከላከላል ብሎ መለጠፍ ይከለክላል፣ ሆኖም ግን ይህ መመርያ በአኩሪ አተር ኢንዱስትሪ ያሉት ሻጮች በማስተዋወቅያ ጽሑፎቻቸው ላይ እንዲሁ ከማለት አላገዳቸውም፡፡ 
“ልብን ከመጠበቁም በላይ፣” ይላል የቫይታሚን ኩባንያ በራሪ ወረቀት፣ “አኩሪ አተር ከፍተኛ የፀረ-ነቀርሳ ጥቅሞች አሉት …፡፡ ጃፓኖቹ ከሰሜን አሜሪካውያን 30 እጥፍ በላይ አኩሪ አተር የሚበሉት፣ ዝቅተኛ የጡት፣ የማሕፀን እና የፕሮስቴት ነቀርሳዎች ክስተት ይታይባቸዋል፡፡”(37)  
እርግጥ ነው ዝቅተኛ ነው፡፡ ሆኖም ግን ጃፓኖቹ እና ኤስያውያኑ ባጠቃላይ በሌላ የነቀርሳ ዓይነት በተለይ የኢሶፈገስ፣ የሆድ፣ የጣፊያ እና የጉበት ነቀርሳ በከፍተኛ መጠን ይጠቃሉ፡፡(38) ኤስያውያ በመላው ዓለም ደግሞ ከፍተኛ የታይሮይድ ነቀርሳ አለባቸው፡፡(39) በብልት አካባቢ (ፕሮስቴት) የሚነሳ ነቀርሳ ዝቅተኛ ደረጃ መሆኑ አኩሪ አተር በመብላት ነው ከተባለ ከፍተኛ የታይሮይድ እና የምግብ መፍጫ አካላት ይበልጥ በነቀርሳ መጠቃታቸው ተጠያቂነቱን ለአኩሪ አተር ማድረግ ውጤቱ ይሆናል፡፡ በተለይም ደግሞ ምርምር በተደረገባቸው የላቦራቶሪ አይጦች ላይ አኩሪ አተር እኚሁኑ ነቀርሳዎች አስከትሎባቸዋል፡፡
ኤስያውያኑ ግን ምን ያህል አኩሪ አተር ነው የሚመገቡት? በ1998 በተደረገ ጥናት በመሃከለኛው በጃፓን ውስጥ የሚወሰደው የአኩሪ አተር ፕሮቲን መጠን 8 ግራም ለወንዶች 7 ግራም ለሴቶች ከሁለት ማንኪያ በታች ሆኖ አግኝቶታል፡፡(40) ዝነኛው የኮርኔል የቻይና ጥናት የባቄላ ዘር (ለጉሜ) አወሳሰድ በቀን ከ 0 እስከ 58 ግራም እንደሆነና መሃከለኛው 12 መሆኑን አሳይቷል፡፡(41)
ከሚመገቡት የባቄላ ዝርያ ውስጥ ሁለት ሶስተኛው አኩሪ አተር ነው ብንል፣ በከፍተኛ መጠን ሊወስዱት የሚችሉት 40 ግራምና ከዛ በታች ነው፣ ወይም በቀን ከሥስት ማንኪያ በታች ማለት ነው፣ በመሃከለኛው ስሌት ደግሞ ስንቆጥር ወደ ዘጠኝ ግራም ይሆናል ወይም ከሁለት ማንኪያ በታች፡፡ በ1930ዎቹ በተደረገ ጥናት በቻይኖች ማዕድ አኩሪ አተር 1.5 መቶኛ የካሎሪ ምንጭ ድርሻ ነበረው፣ ከአሳማ የሚያገኙት ካሎሪ 65 መቶኛ ነበር፡፡(42) (ኤስያውያን በባሕላቸው ምግብ የሚያበስሉት በአትክልት ዘይት ሳይሆን በአሳማ ቅባት ነው!)
በባሕላዊ ልማድ በኤስያውያን ማዕድ የተዘፈዘፈ (የተጠነሰሰ / ፈርመንትድ የሆነ) የአኩሪ አተር ውጤት ጣፋጭ እና ለኤስያውያን ማዕድ የሚያስፈልጉ ንጥረ ምግቦችን ሊያስገኝላቸው ይችላል፡፡ ሆኖም ግን በድርቅ ጊዜ ካልሆነ በስተቀር ኤስያውያን እጅግ በጣም ትንሽ አኩሪ አተር ነው የሚመገቡት፣ እርሱም እንደማባያ ነው እንጂ እንደ እንስሳት ተዋጽኦ ምትክ አድርገው አይወስዱትም፣ ከአንድ ሁኔታ በስተቀር፡፡ ቅጠል በል ሁነው በገዳማት የሚኖሩት የመነኑ ባሕታውያን የአኩሪ አተር ምግብ ምርጫቸው ነው፣ ምክንያቱም የወሲብ ጉልበታቸውን (ሊቢዶአቸውን) ያደነዝዝላቸዋል፡፡  
በኑትሪሽንና ካንሰር ላይ የታተመው የ1994 የማርክ መሲና ሜታ-ትንታኔ ነበር አኩሪ አተር ፀረ-ካንሰር አነሳሽ (አንቲካርሲኖጂን) ጠባይ አለው የሚለውን ውዝግብ ያስነሳው፡፡(43) መሲና በ26 እንስሳት ላይ በተደረገው ጥናት እንደተመዘገበው 65 መቶኛዎቹ የመከላከል ውጤት አሳይተዋል፡፡ በዚህ ትንታኔው ላይ ከማካተት የዘነጋቸው ጥናቶች ነበሩ ቢያንስ በአንድ በ1985 በራኪስ በተደረገ ጥናት አኩሪ አተር መቀለብ የጣፍያ ነቀርሳ ምክንያት ሆኖ ተገኝቷል፡፡(44) ባሰፈራቸው በሰው ላይ በተደረጉ ጥናቶች ውጤቶቹ የተዘባረቁ ናቸው ብሏል፡፡ [በዚህ ሁኔታ ነው አኩሪ አተር መመገብ የሚመከረው?]
ጥቂቶቹ የመከላከል ውጤት ቢያሳዩም አብዛኞቹ በአኩሪ አተር መመገብና በነቀርሳ መካከል ትስስር የሌለው መሆኑን የሚሳዩ ነበሩ፡፡ በመደምደሚያው ላይ “በዚህ ክለሳ መረጃ መሰረት አድርጎ አኩሪ አተር የነቀርሳ ስጋትን ይቀንሳል ብሎ መናገር አያስችልም፡፡” ሆኖም ግን በቀጣይ “The Simple Soybean and Your Health” በሚለው መጽሐፉ ላይ እንዲሁኑ የከለከለውን ድምዳሜ ይሰብካል፣ አንድ ኩባያ ወይም 230 ግራም የአኩሪ አተር ተዋጽኦ በቀን መመገብ ነቀርሳ ይከላከላል ይላል፡፡
በአሁኑ ጊዜ በሺዎች የሚቆጠሩ ሴቶች አኩሪ አተር ከጡት ነቀርሳ ይከላከለናል በማለት እየተመገቡት ይገኛሉ፡፡ ሆኖም በ1996 ዓ.ም በተደረገ ጥናት ከአኩሪ አተር የተነጠለ ፕሮቲን የሚመገቡ ሴቶች የሰውነት ውስጥ አካላት ሽፋን ህመም በሆነው ኤፒተልያል ሃይፐርፕላዝያ (epithelial hyperplasia) ፣ ለማዳን የማይቻል ሁኔታ ከመድረሱ በፊት በሚታይ ህመም የመያዝ እድላቸው ጨምሮ ተገኝቷል፡፡(45) ገንስታይን [የፋይቶኢስትሮጅን አይነት] ለማዕድ ሲውል የጡት ሴሎችን ወደ ሴል ኡደት እንዲገቡ እንደሚያነሳሳቸው ተደርሶነታል - ይህም ግኝታቸው የጥናቱ አዘጋጆች ሴቶች ከጡት ካንሰር እራሳቸውን ለመታደግ አኩሪ አተር መመገብ የለባቸውም ከሚል ድምዳሜ እንዲደርሱ አድርጓቸዋል፡፡(46)   

 
ፋይቶኢስትሮጅንስ፡ ዕጸ ሕይወት ወይስ ዕጸ ሞት?


በሃሩሩ ቀጠና ያሉት አእዋፋት የወንድ ዝርያዎቹ ሲወለዱ ብዙ የማይስበው የእናታቸው ቀለም ያለውን ላባ ይይዙና ካደጉ በኋላ በተራቸው ወላጅ ሊሆኑ ሲሉ በዘጠኝ እና 24 ወር መሃከል ገደማ ቀለም ማውጣት ይጀምራሉ፡፡
በ1991 ሪቻርዳ ቫለሪ ጄምስ ዋንገራይ፣ ኒውዚላንድ የሚገኙ ወፍ አርቢዎች፣ ለአእዋፋቶቻቸው አዲስ የቀለብ ዓይነት ገዙላቸው - በአኩሪ አተር ፕሮቲን የተገነባ፡፡ (47) አኩሪ አተር መሰረት ያደረገ ቀለብ ሲሰጣቸው በጥቂት ወራት ውስጥ ቀለም አወጡ፡፡ እንዲያውም አንድ የቀለቡ ዓይነቱ አዘጋጅ እንዲህ ፈጥኖ መድረስ የቀለቡ ውጤት መሆኑን የሚገልፅ ፅሑፍ ምርቱ ላይ ለጥፏል፡፡ 
የ1992 የሩዲቡሽ (Roudybush) ቀለብ ማስታወቅያ የአውስትራሊያው በቀቀን የላባው ቀለም ከ 18 እስከ 24 ወር ጊዜ ውስጥ የሚያወጣው በ 11 ሳምንት እድሜው እንዲያወጣ ያደርገዋል ብሎ ቃሉን ይሰጣል፡፡
የሚያሳዝነው ግን ቀጥሎ ባሉት አመታት የአእዋፋቱ የመራባት አቅም ቀንሶ ተገኝቷል፣ ቀድሞ ለወላጅነት አቅም መድረስ፣ የአካል ቅርጽ መበላሸት፣ ደቃቅና ደንዛዛ ጫጩቶች መውለድ፣ ያለእድሜያቸው መሞት፣ በተለይ በሴቶቹ ላይ ታይቷ፣ ይህም አጠቃላይ የሚያረቧቸው የእእዋፋት ቁጥር እንዲቀንስ አድርጓል፡፡
ወፎቹ የመንቁርና የአጥንት መበላሸት፣ እንቅርት፣ በሽታ የመከላከያ ስርአታቸው መዛባት እና ከሕመም የደረሰ የአስቸጋሪነት ጠባይ ተከስቶባቸዋል፡፡ የእህል መፍጫ የሰውነታቸው ክፍሎች ክፉኛ እንደተጎዱ በአካላታቸው ላይ የተደረገው ምርመራ አሳይቷል፡፡ በአእዋፋቱ የታዩት ችግሮች የነጄምስ ቤተሰብ በሁለቱ ልጆቻቸው ላይ በተመሳሳይ መልኩ ተከስተዋል፣ ልጆች በጨቅላነታቸው በአኩሪ አተር የተሰራ የሕጻናት ምግብ በልተው ነው ያደጉት፡፡
የተደናገጡትና የተናደዱት እነ ጄምስ መርዛማነት አጥኚውን (ቶክሲኮሎጂስቱን) ማይክ ፊትዝፓትሪክን (ፒኤች.ዲ) በጉዳዩ እንዲመራመር ቀጠሩት፡፡ ዶ/ር ፊትዝፓትሪክ በመስኩ ያሉትን ጽሑፎች አገላብጦ አኩሪ አተር ብዛት ካላቸው ሕመሞች እንደ መሃንነት፣ የነቀርሳ መጨመር፣ የሕፃናት ሊኩሚያ፣ ጋር ትስስር እንዳለው ደርሶበታል፣ በተጨማሪም ቀደም ብሎ በ1950ዎቹ(48) በተደረጉ ጥናቶች በአኩሪ አተር ያለው ገንስታይን በእንስሳት የኢንዶክራይን መታወክ እንደሚያመጣ ያሳያል፡፡ 
ዶ/ር ፊትዝፓትክ ለአእዋፋቱ የቀረበውን ቀለብ በመመርመር ከፍተኛ የፍይቶኢስትሮጅን በተለይ ገንስታይን ይዘት እንዳለው ለማወቅ ችሏል፡፡ የጄምስ ቤተሰብ በአኩሪ አተር ላይ የተመሰረተ ቀለብ መጠቀም ካቋረጡ በኋላ፣ ከጊዜ በኋላ አእዋፋቱ ወደ ጤናማ የእርባታ ልማድና ጠባይ ተመልሰዋል፡፡
የጄምስ ቤተሰቦች በአኩሪ አተር ስላለው መርዝ ሕዝቡንና የመንግስት ባለስልጣናትን ለማስጠንቀቅ የራሳቸው ዘመቻ ጀመሩ፣ በተለይም ደግሞ ኢንዶክራይን በሚያውኩት አይዞፍሌቮኖች ገንስታይንና ዲያሰዜን ላይ፡፡ ፕሮቲን ቴክኖሎጂ ኢንተርናሽናል የነጄምስን ወረቀት በ1994 እንዲደርሰው ተደርጓል፡፡
በ1991 የጃፓን ተመራማሪዎች ባደረጉት ጥናት በቀን 30 ግራም ወይም ሁለት መመገቢያ ማንኪያ የሚያክል አኩሪ አተር ለአንድ ወር መመገብ ታይሮይድ የሚያነቃቃ ሆርሞንን እንዲጨምር እንደሚያረግ አሳይተዋል፡፡(49) የእንቅርት መነፋትና ሃይፖታይሮዲዝም በአንዳንድ ሙከራው በተደረገባቸው ላይ የታየ ሲሆን አብዛኞቹ የሆድ ድርቀት (constipation) ድካም፣ መልፈስፈስ (lethargy) ታይቶባቸዋል የሚወስዱት አዮዲን መጠን በቂ ሆኖ ሳለ፡፡
በ1997 ከኤፍዲኤ የመርዛማነት ምርምር ብሔራዊ ማእከል የመጡ ተመራማሪዎች ለተቋሙ በሚያሳፍር መልኩ የአኩሪ አተር ጎይትሮጅኖች አይዞፍሎቮኖች መሆናቸውን ደረሱበት፡፡(50)
ሃያ አምስት ግራም የሚሆን ከአኩሪ አተር የተነጠለ ፕሮቲን፣ ፕሮቲን ቴክኖሎጂ ኢንተርናሽናል ኮሌስትሮል ይቀንሳል ያለው መጠን መሆኑ ነው፣ 50 እስከ 70 ሚሊ ግራም አይዞፍሌቮን ይይዛል፡፡ ባላረጡ ሴቶች ላይ በተደረገው ጥናት 45 ሚሊ ግራም አይዞፍሌቮን ብቻ በሰውነታቸው ታይሮይድ ትክክለኛ ሥራ የሚያስፈልገው ሆርሞን እንዲቀንስባቸው አድርጓል፡፡ እኚህ ተፅእኖዎቹ አኩሪ አተር መውሰድ እንዲቆም ከተደረገ በኋላ ለሦስት ወራት ያክል ጊዜ ተጽእኖው ሰውነት ውስጥ ነበር፡፡(51)
መቶ ግራም የአኩሪ አተር ፕሮቲን - ኮሌስትሮልን ለመቀነስ ጥሩ ነው ተብሎ ከተነገረው ከፍተኛው መጠን፣ በፕሮቲን ቴክኖሊጂስ ኢንተርናሽናል የሚመከረው መጠን - 600 ሚሊ ግራም አይዞፍሌቮን ሊይዝ ይችላል፣ (52) ይህ ሊካድ በማይችል መልኩ መርዛማ ይዘት ነው፡፡ በ1992 የስዊዝ ጤና አገልግሎት 100 ግራም የአኩሪ አተር ፕሮቲን በኢስትሮጂን ከወሊድ መከላከያ ኪኒን ጋር ተነፃፃሪ መሆኑን ተናግሯል፡፡(53)
በቫይትሮ (ከሕይወታውያን ሰውነት ውጪ በሚደረግ) ጥናት አይዞፍሌቮኖች የኢስትራዶይል መዋሃድን ከልክሏል፣ የስቴሮይድ መዋሀድንም እንዲ ከልክሏል፡፡(54) [ኢስትራዶል የኢስትሮጅን እጥረትና የጡት ነቀርሳን ለመዋጋት የሚጠቅም ተፈጥሯዊ የሴት ሆርሞን ሲሆን ስቴሮይድ ደግሞ የወሲብ አካላት እድገት ላይ ተጽእኖ ያለው ሆርሞን ነው፡፡] የስርአተ እርባታ ችግር፣ መሃንነት፣ የታይሮይድ ህመም እና የጉበት ሕመም በአይዞፍሌቮን መውሰድ (መመገብ) ምክንያት እንደሚከተል በተለያዩ የእንስሳት ዝርያዎች፣ በአቦ ሸማኔ፣ በጅግራ፣ በአሳማ፣ በአይጥ፣ በትልቅ አሳ (sturgeon)፣ እና በበግ ላይ ታይተዋል፡፡(55)
አኩሪ አተር ባረጡ ሴቶች ላይ ጥሩ ጥቅም አለው ይባላል፣  ፈጣን ትኩሳት (ሆት ፍላሽ) እና የአጥንት መሳሳት (ኦስትዮፖሮሲስ) ይከላከልላቸዋል ይባላል፡፡ ከፈጣን ትኩሳት የሚመጣውን ምቾት መጓደል በቁጥር ለማስቀመጥ እጅግ ከባድ ነው፣ በግለሰቡ ስሜት ላይ ስለሚመረኮዝ፡፡ አብዛኞቹ ጥናቶችም በተሰጠው አኩሪ አተር ልክ የፈጣን ትኩሳት መቀነስ ተመዝግቧል ይላሉ፡፡(56) አኩሪ አተር ኦስትዮፕሮሲስ ይከላከላል የሚለው ጥቆማ እጅግ የሚያስገርም ነው፣ የአኩሪ አተር ምግቦች ካልሺየም የሚያግዱና የቫይታሚን ዲ እጥሬት የሚፈጥሩ መሆናቸው የሚታወቅ ነውና፡፡
ኤስያውያን ከምእራባውያን በላቀ መልኩ ዝቅተኛ የኦስትዮፖሮሲስ ችግር ካለባቸው፣ ምግቦቻቸው በቂ ቫይታሚን ዲ ከሽሪምፕ (አሳ)፣ ከአሳማ እና የባሕር ምግቦች ስለሚያገኙና፣ በቂ ካልሺየም ደግሞ ከአጥንት ቅቅል (bone broths) ስለሚያገኙት ነው፡፡ በምእራባውያኑ ከፍተኛ የኦስትዮፖሮሲስ ክስተት ያለው በቅቤ ምትክ የአኩሪ አተር ቅባት ስለተጠቀሙ ነው፣ ቅቤ ደግሞ የቫይታሚን ዲ እና ካልሺየምን በሰውነታችን ለመምጥ የሚያስፈልጉ በስብ ውስጥ የሚሟሙ ማነቃቅያዎች አሉት፡፡


የወሊድ መቆጣጠርያ ኪኒን ለሕጻናት


ሆኖም ግን እነ ጄምስን እጅግ ያወካቸው በሕጻናት ምግብ የሚገኙት አይዞፍሌቮኖች ነበሩ፡፡ በ1998 ተመራማሪዎች ይፋ ባደረጉት መሰረት አካል-ክብደት መጠን መሰረት በማድረግ ሲሰላ አዋቂዎች አኩሪ አተር ሲበሉ የሆርሞን ተጽእኖ ይፈጥርባቸዋል ከሚባለው ሕጻናት ከሚመገቡት ምግብ ላይ ያለው አይዞፍሎቮን ከ 6 እስከ 11 እጥፍ ይዘት እንዳለው አሳውቀዋል፡፡ ለሕጻናት በሚሰጡ በአኩሪ አተር የተሰሩ ምግቦች በላም ወተት ለሕጻናት ከሚዘጋጀው ምግብ በፕላዝማ ኢስትራዶይል ይዘት በ 13,000 እስከ 22,000 እጥፍ ድረስ ይበልጣል፡፡(57)
በጡጦ ከሚመገቡ ሕጻናት በአሜሪካ 25 መቶኛ የሚሆኑት በአኩሪ አተር የተሰራ ይመገባሉ - ከምእራቡ አለም እጅግ ከፍተኛው ነው፡፡ ፊትዝፓትሪክ ባስቀመጠው ግምት መሰረት በአኩሪ አተር የተሰራ ምግብ ብቻ የሚመገብ ሕጻን (አካል-ክብደት መሰረት በማድረግ) ሲሰላ አምስት የወሊድ መከላከያ ውስጥ የሚገኝ ያህል ኢስትሮጅን ይወስዳል ማለት ነው፡፡(58) በአንጻሩ ግን ከላም ወተት ወይም ከሰው ወተት እናትየዋ አኩሪ አተር ብትመገብ እንኳ ምንም ዓይነት ፋይቶኢስትሮጅን አልተገኘባቸው፡፡ 
ለረዥም ዘመናት ሳይንቲስቶች በአኩሪ አተር የተሰሩ የህጻናት ምግቦች የታይሮይድ ችግር እንደሚፈጥር የሚያውቁት ጉዳይ ነው፡፡ የአኩሪ አተር ምርቶች ግን በሁለቱም ወንድና ሴት ሕጻናት የሆርሞን እድገት ላይ ምን ዓይነት ተጽእኖ ነው ያላቸው?
ወንዶች ሕጻናት “የቴስተስተሮን መጨመር” በሕይወታቸው መጀመርያ ወራት ይገጥማቸዋል፣ የቴስተስተሮን መጠናቸው የአዋቂ ወንዶችን መጠን ሊያክል ይችላል፡፡ በዚህ ወቅት ለጉርምስና (ፑበሪቲ) በሚደርስበት ወቅት የወንዴ ባሕርያት እንዲያሳይ ይሞላል በወሲባዊ አካላቱና ሌላ ተክለ ሰውነቱ ብቻ ሳይሆን በአእምሮውም የወንዴ ባሕርያት ቅርጽ እንዲፈጠር ይሞላል፡፡
በጦጣዎች የወንዴ ሆርሞን እጥረት የቦታ ግንዛቤ (spatial perception) እድገት እንዲጎዳ ያደርጋል፡፡ (በሰዎች ላይ ይህ ከሴቶች ይልቅ በወንዶች ላይ ጉዳቱ ይልቃል) ፣ የመማር ችሎታን ይጎዳል፣ እና የእይታ መለየት የሚደረጉ ሥራዎች (ለምሳሌ ለማንበብ እንደሚያስፈልገን አይነት) ይቀንሳል፡፡(59) በዚህ አይነት ሆርሞናዊ ድባብ አድጎ የመጪው እድሜ ዘመን የወሲብ ዝንባሌ (ምርጫ) ቅጥ ላይም ተጽእኖ ሊያሳድር እንደሚችል መናገር አያስፈልገውም፡፡
በማሕፀን እያሉ ለዳይታይልስቲልብስትሮለ (ዲኢኤስ) የተጋለጡ ወንድ ፅንሶች፣ ለጉርምስና በሚደርሱበት ወቅት ከጤናማው ያነሰ ፍሬ ነብስ ይኖራቸዋል፣ ዲኢኤስ ማለት በእንስሳት ላይ በተደረገ ሙከራ ከፋይቶኢስትሮጅን ጋር ተመሳሳይ ባሕርይ ያለው ንጥረ ነገር ነው፡፡(60)
[በአሜሪካ] ወንዶች ልጆች ትምህርት መቀበል አለመቻል (መደደብ) መስፋፋት ከወረርሽኝ ደረጃ ደርሷል፡፡ በስፋት አኩሪ አተር ለሕጻናት ምግብ ሆኖ መሰጠት የጀመረው በ1970 መጀመርያዎቹ ነው - ይህም ክስተት ለወረርሽኙ ሁኔታ ማብራርያ አይሆንም ተብሎ ማለፍ አይቻልም፡፡
ሴቶቹ ደግሞ በአስደንጋጭ ቁጥር የሚሆኑት ወደ አቅመ ሔዋን ከጤናማው እድሜ ክልል በጣም ቀድመው እየደረሱ ነው፣ ፔድያትሪክስ የሚባለው ጥናታዊ ሕትመት እንደዘገበው፡፡(61) ተመራማሪዎች ከአጠቃላይ ሴት ልጆች አንድ መቶኛ ሚሆኑት ጡት ማውጣት እና የኮረዳ ፀጉር ማውጣት የመሳሰሉትን የኮረዳነት ምልክቶች ሦስት ዓመታቸው ሳይሞሉ ማሳየት እየጀመሩ ነው፤ በስምንት አመታቸው ከነጭ ሴቶች 14.7 መቶኛ የሚሆኑት እና ደግሞ ከጥቁር ሴቶች ወደ 50 መቶኛ የሚጠጉት ከተጠቀሱት ሁለት ምለክክቶች አንዱን ወይም ሁለቱን ያሳያሉ፡፡
በስነ ምህዳሩ የሚለቀቁ ከባብያዊ ኢስትሮጂንስ እንደ ፒሲቢ እና ዲዲኢ (ከዲዲቲ የሚገኝ) ዓይነቶቹ በሴቶች ላይ ቀድመው ኮረዳ እንዲሆኑ ያደርጓቸዋል፡፡(62) በ1986 በተደረገ የፖርተ ሪኮ ያለ እድሜ ጡት መውጣት (Premature Thelarche) ጥናት እንደተገኘው ከሆነ ያለእድሜ ቀድሞ ወሲባዊ እድገት ማሳየት የሚመጣው በብዛት በመገናኛ ብዙሃን እንደሚነገረው ዶሮ ሳይሆን የህጻናት ከአኩሪ አተር የተሰራ ምግብ እንደሆነ ደርሶበታል፡፡(63)
ሕጻንነትን እንዲሁ ያለጊዜው በመቀጨቱ የሚመጣው መዘዝ እጅግ አሳዛኝ ነው፡፡ ሕጻናት ሴቶች ለአቅመ ሔዋን ሲደርሱ አዋቂዎች እንኳ መጋፈጥ የሚከብዳቸው ስሜቶች ጋር ዝግጁ ሊሆኑ በማይችሉበት ሁኔታ ውስጥ ሁነው ለመጋፈጥ ይገደዳሉ፡፡ በሴቶች ልጆች ቀድሞ ለአቅመ ሔዋን መድረስ ኋላ ላይ በሕይወታቸው ከተዋልዶ ስርአታቸው ጋር በተያያዘ ለሚገጥማቸው ችግር አመላካች ነው፣ የወር አበባ መቋረጥ፣ መሃንነት እና የጡት ነቀርሳ ከችግሮቹ ይገኙበታል፡፡
እነ ጄምስ ቤተሰቦች ጋር የተገናኙ ሌሎች ልጆቻቸውን የአኩሪ አተር እያበሉ ያሳደጉ ወላጆች በልጆቻቸው የደረሰ የተለያዩ ችግሮችን አካፍለዋቸዋል፡፡ ፅንፍ የሚወጣ ስሜታዊ ባሕርያት፣ አስም፣ በሽታ የመከላከል አቅም መዳከም፣ የፒቱታሪ እጢ መዳከም (pituitary insufficiency) ፣ የታይሮይድ መታወክ፣ የሆድ እቃ መታወክ (irritable bowel syndrome) - ከነገሯቸው ችግሮች ይጠቀሳሉ፡፡ እኚህ ችግሮች እነ ጄምስ በሚያረቧቸው በቀቀኖች ላይም የታዘቧቸው ናቸው፡፡


የአውራዎቹ መከፋፈል


ሶስተኛው ዓለም አቀፍ የአኩሪ አተር አውደ ጥናት አዘጋጆች ጉባኤውን ሙሉ ለሙሉ ስኬታማ ነበር ለማለት አስቸጋሪ ይሆንባቸዋል፡፡ በአውደ ጥናቱ ሁለተኛ ቀን ተቀማጭነቱን ለንደን ያደረገው ፉድ ኮሚሽን እና የዋሽንግተን ዲሲው ዌስቶን ኤ. ፕራይስ ፋውንዴሽን ዓውደ ጥናቱ በሚካሄድበት ሆቴል የሕጻናት የአኩሪ አተር ምግብ ላይ ያላቸውን ስጋት ለማሳወቅ የራሳቸውን የጋራ ጋዜጣዊ መግለጫ ስብሰባ እያካሄዱ ነበር፡፡
የኢንዱስትሪው ተዋካዮች የተጨነቁ ሳይንቲስቶች እና ወላጆች በአኩሪ አተር የሚሰሩ የሕጻናት ምግቦችን ከገበያው እንዲወገዱ ሊያደርስ የሚችሉትን አደጋዎች ዝርዝር ሲቀርብ ደንዝዘው ሲከታተሉ ነበር፡፡ በእነ ጄምስ ቤተሰቦች ተጽእኖ ምክንያት የኒው ዚላንድ መንግስት በ1998 በአኩሪ አተር የሚሰራ የሕጻናት ምግብ ያለውን የጤና ጠንቅነት ማስጠንቀቅያ አውጥቷል፤ አሁን ደግሞ የአሜሪካ መንግስት እንዲሁ የሚያደርግበት ጊዜ ነው፡፡ [በሃገራችን የአኩሪ አተር ስጋት የሚነገርበት ጊዜው አሁን መሆን አለበት ኢንዱስትሪው ሳይፈረጥም፣ ሳይቃል በቅጠል፣ ማን ይሆን ህዝቡን ለማንቃት የሚንቀሳቀሰው፣ ሕዝቡ ከነቃ ባለስልጠናቱ ሊያወግዙት ይገደዱ ነበር፡፡]
በአውደ ጥናቱ የመጨረሻ ቀን ላይ የቀረበው ከመርዛማነት ጋር የተያያዘ መረጃ በምርቃና ውስጥ ለነበረው ጉባኤ መስበሪያ ነበር ሆነበት፡፡ ዶ/ር ሎን ዋይት በሃዋይ በሚኖሩ ጃፓን-አሜሪካውያን ላይ በተደረገ ጥናት በመጥቀስ ሁለት እና ከዛ በላይ በሳምንት የቶፉ ማዕድ መብላትና “የተፋጠነ የጭንቅላት ማርጀት” መሃከል ስታቲስቲካዊ ትስስር መኖሩ እንደተረጋገጠ ተናግሯል፡፡(64) 
በመሃከለኛ የእድሜ ዘመን ላይ ያሉ የምርምሩ ተሳታፊ ቶፉ ተመጋቢዎች በኋላ ሕይወታቸው ጊዜ የአእምሯቸው የመረዳት ችሎታ ዝቅተኛ መሆንና ከሌላው በላቀ መልኩ በአልዛይመር እና በአእምሮ መሳት (ዲመንሺያ) ሕመም ተይዘዋል፡፡ “በተጨማሪም” አለ ዶ/ር ዋይት “ቶፉ አብዝተው የተመገቡት በ75 ወይም 80 ዓመታቸው አምስት አመት ይበልጥ እድሜ ያላቸው መስለው ይታሉ፡፡”(65) [ይህ እየተባለ ያለው የአኩሪ አተር ኢንዱስትው ባዘጋጀው አውደ ጥናት መሃከል ነው፡፡] ዋይት እና አጋሮቹ ለአሉታዊ ጎኖቹ አይዞፍሌቮን ተጠያቂው እንደሆነ ተናግረዋል - ይህ አዲሱ ቃላቸውም ቀድሞ የተደረገው ያረጡ ሴቶች ከፍተኛ የኢስትሮጅን መዘዋወር በውስጣቸው ካለ የመረዳት ችሎታቸው ይቀንሳል የሚለውን የሚደግፍ ነው፡፡(66)
ዳንኤል ሺሃን እና ዳንኤል ዶርጅ የተባሉት ከብሔራዊ የመርዛማነት ምርምር ማእከል የመጡት ሳይንቲስቶች በአይጦች ላይ በተደረገ ጥናት መሰረት፣ በአኩሪ አተር ምግቦች የሚገኘው ገንስታይን ማዳን በማይቻል መልኩ የታሮይድ ሆርሞንን እንዲዋሃድ የሚያደርጉ ኢንዛይሞችን እንደሚጎዳ በመናገር የፕሮቲን ቴክኖሎጂስ ኢንተርናሽናልን ቀን አበላሹበት፡፡(67)
“በአኩሪ አተር መመገብና በእንቅርት መሃከል፣ በእንስሳትም በሰዎችም ዘንድ ረዥም ታሪክ አለው፣”  ይላሉ ዶ/ር ዶርጅ “በአሁኑ ጊዜ አኩሪ አተር ይሰጣቸዋል ለሚባሉ ጥቅሞች ማስረጃ ሲቀርብ ሊያደርስ ስለሚችለው አደጋ ሙሉ መረዳትም ያስፈልጋል፡፡”
ዶ/ር ክላውድ ሁገስ እንደዘገቡት ደግሞ ገንስታይን ከተቀለቡ አይጦች የተወለዱት ለንጽጽር ከተቀመጡት (ኮንትሮልስ) ያነሰ ክብደት አሳይተዋል፣ በወንዶቹ ደግሞ ለጉርምስና ቀድመው መድረስ ታይቷል፡፡(68) ምርምሩ እንዳሳወቀው ከሆነ በአይጦች ላይ የታየው “በትንሹ በሰው ልጆች ላይ ሊከሰት የሚችለውን አመላካች ነው፡፡” 
በጽንሱ ላይ አስደንጋጭ የቅርጽ መበላሸት ይደርሳል ማለት ላይሆን ይችላል ሆኖም ግን የነርቭ-ወ-ባሕርይ ቅጥ (neurobehavioral attributes) ፣ በሽታ የመከላከል ተግባራት፣ እና የፆታ ሆርሞኖች መጠን የመሳሰሉትን ሊያዛባ ይችላል፡፡ “ውጤቶቹ” ይላል ተመራማሪው “ምንም አለማለት ሊሆን ይችላል ወይም ደግሞ ትልቅ የስጋት ምንጭ ሊሆን ይችላል፣ እንደ ፆታ ሆርሞን የሚያደርግ ጠባይ ያለው ነገር እናት የምትበላ ከሆነ፣ የጨቅላው እድገት ላይ ለውጥ ያመጣ ይሆን ብሎ መጠየቁ መሠረተ እውነት የተከተለ ነው፡፡”(69)
እኚህ በጨቅላዎቹ ላይ ሊከሰቱ የሚችሉ ለውጦች ምን እንደሆኑ በጥር 2000 ዓ.ም የታተመው ቅጠል በል የሆኑ እናቶች የወለዷቸው ልጆች ላይ የተደረገው ምርምር አሳይቷል፡፡ ቅጠል በል የሆኑ እናቶች የሚወልዷቸው ልጆች በሃይፖስፓዲያስ፣ በውልደት ጊዜ የሚገኝ የወንድ ብልት እንከን፣ የመጠቃት እድላቸው አምስት እጥፍ ሆኖ ተገኝቷል፡፡(70) የጥናቱ ጸሐፊዎች በቅጠል በሌዎች ዘንድ ተወዳጅ የሆነው አኩሪ አተር ምግቦች ውስጥ የሚገኙት ፋይቶኢስትሮጅኖች በስፋት መጋለጥ እንደሆነ ገምተዋል፡፡
የቅጠል በል እናቶች ሴት ጨቅላዎች የሚገጥማቸው ችግር ወድያው ሳይሆን ይበልጡኑ ቆይቶ የመታየት እድል ያላቸው ናቸው፡፡ የአኩሪ አተር ኢስትሮጅናዊ ተጽእኖ ከዲያታይልስቲልቤስትሮል (ዲኢኤስ) ያነሰ ቢሆንም፣ በአጠቃላይ የሚወሰደው ይዘት ግን ሳይበልጥ አይቀርም ምክንያቱም በምግብነት ነውና የሚወሰደው፣ እንደ መድሃኒት አይደለም፡፡ በእርግዝና ወቅት ዲኢኤስ የወሰዱ እናቶች ልጆች በእድሜያቸው ሃያዎቹ ውስጥ ሲደርሱ ከመሃንነት እና ነቀርሳ ስቃይ ገጥሟቸዋል፡፡


ጥያቄ ምልክት በደህንነት መዓርጉ ላይ


ኢንዱስትው ለአኩሪ አተር ከፈጠረው ግዙፍ ምስል በስተጀርባ በምግብ ላይ ከአኩሪ አተር የተነጠለ ፕርቲን የመጨመር ተግባር በራሱ ህጋዊ ነው ወይ የሚል ወጥሮ የሚይዝ ጥቄ አለ፡፡ ከ1958 በፊት ጥቅም ላይ ያልዋሉ በምግብ ላይ የሚጨመሩ ኝጥረ ነገሮች ሁሉ የእውቅና መዓረግ ያስፈልጋቸዋል፣ ግራስ - GRAS (Generally Recognized As Safe) ይባላል፡፡ በ1972 የኒክሰን አስተዳደር የግራስ ማእረግ አላቸው ተብለው የሚታሰብ ንጥረ ነገሮችን ዳግም መረመረ፣ በወቅቱ ከነበረው ሳይንሳዊ መረጃ አንጻር፡፡
ይህን ዳግም ፍተሻ ካዚን (casein) ፕሮቲንን [ከወተት የሚገኝ ፕሮቲን] ያካተተ ነበር፣ በ1978 የግራስ ማእረግን አገኘ፡፡ በ1974 ኤፍዲኤ ስለ አኩሪ አተር ፕሮቲን ጽሑፍ ተሰጠው፣ ምክንያቱም እስከ 1959 ድረስ በምግብነት አልዋለም ነበርና፣ እስከ 1970ዎቹ ድረስ እንኳ በስፋት አይታወቅም ነበር፣ በምግብ፣ መድሃኒት እና መዋብያ አዋጅ የግራስ እውቅና ቀድሞውኑ እውቅና ለማግኘት እንኳ ብቁ አልነበረም፡፡(71)
እስከ 1974 ድረስ የነበረው በፋብሪካ በተሰራ አኩሪ አተር ፕሮቲን ላይ ብዙ ፀረ-ንጥ ምግቦችን መዝግቦ የያዘ ነበር፣ ትራይፕሲን አጋቾቹን፣ ፋይቲክ አሲድ እና ገንስታይን ጨምሮ፡፡ ሆኖም ግን ኤፍዲኤ ሰፊ አጥፊ ጎኑን የሚያነሳውን የጽሑፍ ክለሳ ላይ የሚደረግ ውይይትን “በቂ በሆነ ሁኔታ ከተሰናዳ” ያስወግዳቸዋል በማለት ችላ ብሏል፡፡ 
ገንስታይን በአልኮል ሲታጠብ ሊወገድ ይችላል፣ ሆኖም ግን ይህ ወጪ የሚያስወጣ ሂደት ስለሆነ ሰሪዎቹ አይተገብሩትም፡፡ በኋላ ላይ በተደረጉ ጥናቶች ትራይፕሲን አጋቾች ሊወገዱ የሚችሉት ረዘም ላለ ጊዜ ሙቀት እና ግፊት በመጠቀም ብቻ መሆኑን አስረዱ፣ ሆኖም ግን ኤፍዲኤ አምራቾች ይህን እንዲያደርጉ ምንም አይነት አስገዳጅ ደንብ አላወጣላቸውም፡፡
ኤፍዲኤ ይበልጥ የጨነቀው በሚቀነባበርበት ወቅት የሚፈጠሩት መርዞች ናቸው፣ በተለይም ናይትራይቶች እና ላይሲኖአላናይን፡፡(72) በጥም ዝቅተኛ በሚባል መልኩ እስከ አንድ ሶስተኛ ግራም በቀን መውሰድ፣ እዚህ ውስጥ የሚገኙት እነዚህ ነቀርሳ አነሳሽ ንጥረ ነገሮች (ካርሲኖጅንስ) ምክንያት ለሕብረተሰቡ ጤነማ ጠንቅ ናቸው ተብሎ የግራስ እውቅና ማግኘት ተከልክሎ ኑሯል፡፡
የአኩሪ አተር ፕሮቲን በካርቶን ለሚሰሩ ሳጥኖች መስሪያ እንዲሆን እውቅና ነበረው፣ ይህም ፈቃድ እንዲቀጥል ተደርጓል፣ ምክንያቱም ተመራማሪዎች ከሳጥኑ ወደ ምግቦች ሊሸጋገር የሚችለው ናይትሬት ነቀርሳ ያሲዛል የሚለው ስጋት ትንሽ ነው በሚል ነው፡፡ የኤፍዲኤ ባለስልጣናት ለምግን የግራስ ማእረግ ከመስጠታቸው በፊት የደህንነት ማረጋገጫ ትእዛዞችና የቁጥጥር አካሄዶች ያስቀምጡ ነበር፡፡
እኒህ ቅድመ ሁኔታዎች እንዲሟሉ አልተደረገም፡፡ እስከዛሬዋ እለት ድረስ የአኩሪ አተር ፕሮቲን የግራስ እውቅና ያለው ለዚህ ውሱን ኢንዱስትሪያዊ የሆነ የምግብ እቃዎች ማሸጊያ ካርቱን ለመስራት ብቻ ነው፡፡ ይህም ማለት አምራቾች እንደ ምግብ ሊጠቀሙበት ወይም ምግብ ላይ ሊጨምሩት ሲፈልጉ ለገበያ ከማውጣታቸው በፊት የፈቃድ ሂደቶችን የማለፍ ግዴታዎች ይኖርባቸዋል፡፡
የአኩሪ አተር ፕሮቲን የሕጻናት ምግብ ሁኖ የመጣው በ1960ዎቹ መጀመርያ ላይ ነበር፡፡ ይህም አዲስና በፊት ለምንም አይነት ጥቅም ሲውል ምንም ዓይነት ታሪክ ያልነበረው ምርት ያደርገዋል፡፡ የአኩሪ አተር ፕሮቲን የግራስ ማእረግ ያልነበረው ቅድመ ገበያ የምርት ምርመራ / እውቅና ፈቃድ ያስፈልገዋል፡፡ ይህ አልሆነም አሁንም አልተደረገም፡፡ ለሕጻናት የሚቀመረው ከአኩሪ አተር የሚሰራው ምግብ ግብአት ደህንነቱ አስጊ አይደለም የሚል እውቅና የለውም፡፡  


ቀጣዩ አስቤስቶስ?


[አስቤስቶስ ለግንባታ የሚውል ከሲሚንቶ ጋር የሚቀላቀል ምርጥ ግብአት ሲሆን ሥራው ካለቀ በኋላ ግን ለተገልጋዮቹ የሳምባ ነቀርሳ ያተርፍላቸዋል፣ እንደ አውሮፓ ሕብረት ያሉት ጥቅም ላይ እንዳይውል አግደውታል]
“ከወረደለት ሰፊ ውደሳ ጀርባ … -ምንም እንኳ የማያጠራጥር ጥቅም ያለው ቢሆንም- አኩሪ አተር አንዳንድ የጤና ጠንቆችን ሊያስከትል ይችላል፣” ስትል ትጽፋለች ማሪያን ቡሮስ፣ ለኒው ዮርክ ታይምስ የምግብ አምድ ጸሐፊ የሆነችው፡፡ ከማንኛውም ጸሐፊ በላይ ቡሮስ ስለ ዝቅተኛ ስብ፣ ቅጠል በሌ ማእዶችን የምትጽፋቸው በርካታ አሜሪካውያንን በአኩሪ አተር ላይ ተመሰረቱ ምግቦችን ከሱፐር ማርኬት መደርደርያዎች እንዲለቅሙ አድርጓቸዋል፡፡ 
በጥር 26፣ 2000 ዓ.ም የጻፈችው "Doubts Cloud Rosy News on Soy" የሚለው አምዷ ግን እንደሚከተለው የማስጠንቀቅያ መልእክት የያዘ ነበር፡ “እዚህ ከቀረቡት 18 ሳይንቲስቶች አይዞፍሌቮኖች ከስጋት ነጻ ናቸው ለማለት ፍቃደኛ የሆነ አልነበረም፡፡” ሙሮስ ስጋቶቹ ምን እንደሆኑ አልዘረዘረችም፣ እንዲወሰድ የተመከረው በቀን 25 ግራም አኩሪ አተርም ስስ ለሆኑ ግለሰቦች ስጋት ለመሆን በቂ አይዞፍሌቮኖች ይይዛል ወይ ስለሚለውም ያለችው ነገር አልነበረም፣ ሆኖም ግን ይህ የሚያመላክተን ኢንዱስትሪው ቀድሞ እራሱን መከላከል መጀመር እንዳለበት እንዳሰበ ያስረዳል፡፡
ኢንዱስትሪው በጣም ስለተጋለጠ … የወደፊት ሥጋት (የተጠንቀቅ) ጠበቆች ከሳሽ ሊሆኑ የሚችሉ ተጎጂዎች ቁጥር በሚሊዮኖች እንደሚቆጠርና ከፍተኛ ወጪ እንደሚያስወጣ የሚደርሱበት ጉዳይ ነው፡፡ ጥፋተኝነት ወሳኞች (ጁሪስ) እንደሚከተለው ያለ ነገር ይሰማሉ፡
“ኢንዱስትሪው አኩሪ አተር ብዙ መርዞችን እንደሚይዝ ለዓመታት ያውቅ ነበር፡፡
“መጀመርያ መርዞቹ በማጥራት ሂደት ተወግደዋል ብለው ለህዝብ ነገሩ፡፡ የማጥራት ሂደቱ የማያስወግዳቸው መሆኑ ሲታወቅ ጊዜ እኚህ ንጥረ ነገሮች ጥቅም አላቸው በሚል መከራከር ጀመሩ፡፡ መንግስታችሁ [የአሜሪካ] መርዛማ ለሆኑ ንጥረ ነገሮች ለጤና ተስማሚ የሚል ማረጋገጫ ሰጠ፣ ኢንዱስትሪው ደግሞ ተጨማሪ አኩሪ አተር ለመሸጥ ሕዝቡን ዋሸ፡፡”
“ኢንዱስትሪ” ሲባል ነጋዴው፣ አምራቾቹ፣ ሳይንቲስቶቹ፣ ሕዝብ ግንኙነት ሰራተኞቹ፣ ቢሮክራቶቹ፣ የቀድሞ የአረቡን ነጋዴዎች፣ ስነ ምግብ ጸሐፍት፣ የቫይታሚን ድርጅቶች እና ቸርቻሪዎቹን ሁሉ ያካተተ ነው፡፡ ገበሬዎች የማምለጥ እድል ይኖራቸው ይሆናል ምክንያቱም እነርሱም እንደኛው ተታለው ይሆን ይሆናል፡፡ ሆኖም ግን ነገሩ ከመገንፈሉ በፊት ሌላ የሚተክሉት ነገር በፍጥነት መፈለግ ይኖርባቸዋል፡ ሳር የሚበሉ ከብቶች፣ ጤናማ አትክልቶች … ወይም በእልፍ አእላፍ የሚቆጠር የክስ መዝገብ መጻፍያ የሚሆን ወረቀት መሥሪያ እንዲሆን ቃጫ ቢተክሉ ጥሩ ነው፡፡
ከኔክሰስ መጽሔት ተወሰደ፡
Nexus Magazine, Volume 7, Number 3 (April-May 2000)

ስለ ጸሐፊዎቹ፡


ሳሊ ፋሎን (Sally Fallon) Nourishing Traditions: The Cookbook that Challenges Politically Correct Nutrition and the Diet Dictocrats (1999, 2nd edition, New Trends Publishing, tel +1 877 707 1776 or +1 219 268 2601) የተባለው መጽሐፍ ደራሲና የዌስቶን ኤ. ፕራይስ ፋውንዴሽን (Weston A. Price Foundation, Washington, DC (www.WestonAPrice.org) ፕሬዚደንት ነች፡፡
ሜሪ ጂ. ኢንግ ፒኤች.ዲ. (Mary G. Enig, Ph.D.) በተለይ በስብ እና ቅባት ላይ በምታደርገው ምርምር የምትታወቅ የኑትሪሽኒስት ነች፣ አማካሪ፣ ክሊኒሺያን እና Nutritional Sciences Division of Enig Associates, Inc., Silver Spring, Maryland ዳይሬክተር ነች፡፡
የዶክትሬት ዲግሪዋን ያገኘችው በስነ ምግብ ሳይንሶች (Nutritional Sciences) ከሜሪላንድ ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ ፓር በ1984 ዓ.ም ነው፡፡ ለዩኒቨርሲቲው የስነ ምግብ ሳይንሶች ለመጀመርያ ተመራቂ ተማሪዎች ንጥረ ምግቦችና መድሃኒት ትስስር ያስተማረች ሲሆን፣ ከ1984 እስከ 1991 ድረስ የፋኩልቲ (ትምህርት ዘርፍ) ምርምር አጋርነት ቦታን ይዛለች፣ በኬሚስትሪና ባዮኬሚስትሪ ዲፓርትመንት (ትምህርት ክፍል) ውስጥ ከሊፒድስ ምርምር ቡድን ጋር፡፡  
የአሜሪካ የስነ ንጥረ ምግብ ኮሌጅ አጋር (ፌለው) ነች፣ የአሜሪካ የሥነ ምግብ ኢንስቲትዩት አባል ነች፡፡ በረዥም ዓመታት የምግብ ስብ እና ቅባት ምርመራ ዘመኗ እንደ “ተቀያሪ ኬሚስትነቷ” በፉደራልና ክልል መንግስታት የምግብ ደረጃና ይዘት ውሳኔ ላይ ሚና እንዲኖራት መሰረት ሁኗታል፡፡ 
ዶ/ር ኢንግ "Journal of the American College of Nutrition" የተባለው የምርምር ሕትመት አማካሪ አዘጋጅ (ኤዲተር) ስትሆን "Clinical Nutrition" ደግሞ ጽሑፏን የምታበረክት ኤዲተር ነች፡፡ የምግብ ስቦችና ቅባቶች በተመለከተ 14 ሳይንሳዊ ወረቀቶች ያሳተመች ሲሆን ለተለያዩ መጻሕፍት የሥነ ምግብ ምእራፎችን ጽፋለች፣ በተጨማሪም ስለ ምግብና ንረ ምግብና በተመለከተ ከ 35 በላይ ሳይንሳዊ ወረቀቶችን አበርክታለች፡፡
Maryland Nutritionists Association ፕሬዚደንት ስትሆን፣ Coalition of Nutritionists of Maryland የቀድሞ ፕሬዚደንት ነበረች፣ በተጨማሪም በ1986 በሜሪ ላን ገዢ የሜሪላንድ መንግስት የስነ ምግብ መማክርት አባል የተደረገች ሲሆን የጤና ንኡስ ኮሚቴም ሊቀ መንበር ሁና አገልግላለች፣ መማክርቱ በ1988 እስኪበተን ድረስ፡፡

ምስጋና ይድረስ ለእንስቱ ሊቃውንት፡
እጅግ አስፈላጊ የሆነውን ይን የአኩሪ አተር መረጃ ስላቀረባችሁ እናመሰግናለን፡፡ አንድ ሰው አኩሪ አተርን ከቤቱ ማእድ ማራቅ እንደሚገባው የሚስረዳ በቂ መረጃዎችን አሳይተውናል፡፡ ይህ በጣም ትልቅ ሥራ ነው የሚመለከተው ሁሉ አርአያቸውን በመከተል የሚገባውን ትኩረት እንዲያገኝ ይህን መረጃ ያሰራጭ፡፡ በግሌ የድርሻዬን አበርክቼ ጨርሻለው፡፡
[ተጨማሪ መረጃ]
http://www.westonaprice.org/soy-alert/studies-showing-adverse-effects-of-soy
http://www.westonaprice.org/soy-alert/studies-showing-adverse-effects-of-isoflavones
ማጣቀሻዎቹ፡
1. Program for the Third International Symposium on the Role of Soy in Preventing and Treating Chronic Disease, Sunday, October 31, through Wednesday, November 3, 1999, Omni Shoreham Hotel, Washington, DC.
2. Houghton, Dean, "Healthful Harvest", The Furrow, January 2000, pp. 10-13.
3. Coleman, Richard J., "Vegetable Protein - A Delayed Birth?" Journal of the American Oil Chemists' Society 52:238A, April 1975.
4. See www/unitedsoybean.org.
5. These are listed in www.soyonlineservice.co.nz.
6. Wall Street Journal, October 27, 1995.
7. Smith, James F., "Healthier tortillas could lead to healthier Mexico", Denver Post, August 22, 1999, p. 26A.
8. "Bakery says new loaf can help reduce hot flushes", Reuters, September 15, 1997.
9. "Beefing Up Burgers with Soy Products at School", Nutrition Week, Community Nutrition Institute, Washington, DC, June 5, 1998, p. 2.
10. Urquhart, John, "A Health Food Hits Big Time", Wall Street Journal, August 3, 1999, p. B1
11. "Soyabean Milk Plant in Kenya", Africa News Service, September 1998.
12. Simoons, Frederick J., Food in China: A Cultural and Historical Inquiry, CRC Press, Boca Raton, 1991, p. 64.
13. Katz, Solomon H., "Food and Biocultural Evolution: A Model for the Investigation of Modern Nutritional Problems", Nutritional Anthropology, Alan R. Liss Inc., 1987, p. 50.
14. Rackis, Joseph J. et al., "The USDA trypsin inhibitor study. I. Background, objectives and procedural details", Qualification of Plant Foods in Human Nutrition, vol. 35, 1985.
15. Van Rensburg et al., "Nutritional status of African populations predisposed to esophageal cancer", Nutrition and Cancer, vol. 4, 1983, pp. 206-216; Moser, P.B. et al., "Copper, iron, zinc and selenium dietary intake and status of Nepalese lactating women and their breastfed infants", American Journal of Clinical Nutrition 47:729-734, April 1988; Harland, B.F. et al., "Nutritional status and phytate: zinc and phytate X calcium: zinc dietary molar ratios of lacto-ovovegetarian Trappist monks: 10 years later", Journal of the American Dietetic Association 88:1562-1566, December 1988.
16. El Tiney, A.H., "Proximate Composition and Mineral and Phytate Contents of Legumes Grown in Sudan", Journal of Food Composition and Analysis (1989) 2:6778.
17. Ologhobo, A.D. et al., "Distribution of phosphorus and phytate in some Nigerian varieties of legumes and some effects of processing", Journal of Food Science 49(1):199-201, January/February 1984.
18. Sandstrom, B. et al., "Effect of protein level and protein source on zinc absorption in humans", Journal of Nutrition 119(1):48-53, January 1989; Tait, Susan et al., "The availability of minerals in food, with particular reference to iron", Journal of Research in Society and Health 103(2):74-77, April 1983.
19. Phytate reduction of zinc absorption has been demonstrated in numerous studies. These results are summarised in Leviton, Richard, Tofu, Tempeh, Miso and Other Soyfoods: The 'Food of the Future' - How to Enjoy Its Spectacular Health Benefits, Keats Publishing, Inc., New Canaan, CT, USA, 1982, p. 1415.
20. Mellanby, Edward, "Experimental rickets: The effect of cereals and their interaction with other factors of diet and environment in producing rickets", Journal of the Medical Research Council 93:265, March 1925; Wills, M.R. et al., "Phytic Acid and Nutritional Rickets in Immigrants", The Lancet, April 8,1972, pp. 771-773.


Saturday, January 18, 2014

የማኅበረ ቅዱሳን የግል ጋዜጦች ዘመቻና የሐራ ተዋሕዶ ጭቃ ሹምነት የትም አያደርስም!!





ደጀ ሰላም የተባለችው የማኅበረ ቅዱሳን ብሎግ ከተዘጋች በኋላ የጭቃ ሹምነቱን ሥልጣን የተረከበችው «ሐራ ዘተዋሕዶ» ብሎግ አንድም ቀን ተሳስታ ነገረ ወንጌል ሳታስተምር በነገረ ወሬ ጫሪነቷ እነሆ አንድ ዓመቷን አከበረች። የሐራ ዘተዋሕዶ ብሎግ አገልግሎት በወሬ ነጋሪነት ላይ ጊዜዋን የማጥፋቷ ምክንያት በማኅበሩና በዙሪያው ስላሉት የመርሃ ስብከት መልእክት በሙሉ «በማኅበረ ቅዱሳን» ዋናው ድረ ገጽ ስለሚተላለፍ «ሐራ» ስለወንጌልና ስለማኅበሩ አዳዲስ ዜና መዘገብ አይጠበቅባትም። ይህ የሚያሳየው የማኅበሩ  አመራር ቁጭ ብሎ እንዴት መተላለፍ እንዳለበትና ምን መተላለፍ እንደሚገባው በደንብ የመከረበት መሆኑን ያሳያል።
 ሰሞኑን ደግሞ በአዲስ አበባ ሀ/ስብከት ላይ ለመቸከል ያዘጋጁትን የአፈና እቅዳቸው መግቢያ መንገድ ይሆን ዘንድ የነደፉት የጥናትና ስትራቴጂ መርሃ ግብር በሐራ ዘተዋሕዶ ላይ  ብቻ እየለቀለቁ ዜና መስራት ስላቃታቸው የግል በተባሉ ጋዜጦች ላይ የጥናት ጩኸታቸውን ማስተጋባት ከጀመሩ ሳምንት አልፏቸዋል። ሐራ ደግሞ በማኅበሩ አባላት በጋዜጦች ላይ የወጡትን ዜና ወዲያው እንደ አዲስ ዜና ተከትላ ትለጥፋች።

ማኅበሩ የጳጳሳት አባላት ብቻ ሳይሆን በህክምና ሆስፒታሎች፤ በፌዴራል ፖሊሶች፤ በፍርድ ቤቶች፤ በትምህርት ሚኒስቴር፤ በመንገድ ትራንስፖርትና በመሳሰሉት መንግሥታዊ ተቋማት ውስጥ በግልጽና በስውር የሚሰሩ ምልምል አባላት እንዳሉት እርግጥ ነው።በግል ጋዜጦች ላይ የሚሰሩ አባላቱም በስም ጭምር የሚታወቁ እንዳሉም የአደባባይ ምስጢር ነው። ስለሆነም በፈለገው ጊዜ የፈለገውን መረጃና ዜና በፈለገው ጋዜጣ ላይ ለማውጣት የሚቸገር ባለመሆኑ የመረጃ መረቡን በቂ ሽፋን መስጠት ያቃታትን «ሐራ ዘተዋሕዶ» ብሎግን ለማስተንፈስ በስመ ነጻ ሚዲያዎች ላይ ያቀረበውን ጥናት ለመተግበር እንዲቻልና  ተፅዕኖ ለማሳረፍ ሲል በስመ አባ እስጢፋኖስ፤ በስመ ሰንበት ተማሪ አለያም ማን እንደዘገበው ስም ሳይገለጽ ጋዜጣ ላይ እንዲለቀለቅ ለማድረግ ውጣ ውረድ የለበትም።


በእርግጥ በስመ ነጻ ሚዲያ የሚታተሙት የኢትዮጵያ ጋዜጦች አብዛኞቹ ይህንን ያህል ትኩስና የአንባቢን ቀልብ በሚስብ መረጃ በቂ ልምድና ብቃት ያላቸው ስላልሆኑ ከጊዜ ማሳለፊያ ዜናነት ባለፈ ለማኅበረ ቅዱሳን ጥረት ውጤታማ ጎን ያስገኛሉ ተብሎ አይጠበቅም። ግማሾቹ የፕሬስ ህጉን ስለሚፈሩ እንደዱሮው በሬ ወለደ ብለው በመጻፍ ጉድ፤ ድንቅ የሚያሰኝ ፈጠራ ላለማቅረብ ራሳቸውን በራሳቸው ሳንሱር በማድረግ የተቸገሩ ናቸው። ገሚሶቹም «አቶ እንትና ተከሰሰ፤ ወ/ሮ ብሪቱ ቲማቲም ሸጠው ትርፋማ ሆኑ፤ ዓለማየሁ አዲስ ሆቴል ከፈተ » በሚል የተለመደ ዜና የሚውተረተሩ ስለሆነ የማኅበረ ቅዱሳንን የጥናት ወረቀት ተቀብለው ዜና ቢሰሩ ለጊዜ ማሳለፊያነት ማንበብ ከሚቻል ውጪ በዚያ ንባብ ስለጥናቱ የድጋፍ ይሁን የተቃውሞ ሰልፍ የሚወጣ እንደሌለ በእርግጠኝነት መናገር ይቻላል። ብዙዎቹም /tabloid /ወሬና ጭምጭምታ በመለቃቀም፤ የኮከብ ቆጠራና ታሮት በመተረክ፤ ስሜታዊ ፈጠራ ላይ የሚያተኩሩ ናቸው። society reporting/ ማኅበራዊ ዜና የሚሰሩ፤ ስለምግብ፤ ፋሽን፤ ስለቁንጅና የሚተርኩ ናቸው። comedic 
/ ዋዛና ፈዛዛ፤ ቀልድና ቧልት የሚዘግቡ ሲሆኑ በተወሰነ መልኩ gonzo journalism / የተሻለ ምልከታ አለው። ራሱ የመረጃው ምንጭ ሆኖ በመጀመሪያ ረድፍ የሚዘግብ ሲሆን በያዘው አሳማኝ ጭብጥ ለመረጃው ኃላፊነትን የሚወስድ ነው። አሉ፤ ሰማሁ፤ ሰዎች ነገሩኝ አይልም።  /Investigative journalism/ የምርመራ ጋዜጠኝነትን ባህል የተከተለ ጋዜጣ ኢትዮጵያ ውስጥ የለም ብቻ ሳይሆን አይታሰብም። ታዲያ ከዚህ አንጻር የማኅበሩ ስውር ጋዜጠኞች ጽሁፍ በደረጃ በየትኞቹ ጋዜጦች ላይ የሀ/ስብከቱን የጥናት አስፈላጊነት አከታትለው አወጡ ብለን ብንጠይቅ ግልጽ መልስ አናገኝም።  በቃ ዜና ሆኖ መውጣቱ ብቻ በቂያቸው ነበርና ለማውጣት ማውጣት በቻሉት ጋዜጣ ላይ ሁሉ ዜና ሆኖ እንዲወጣ ደክመዋል። ውጤቱ ድካም ሆኖ መቅረቱ ግን ያሳዝናል።

ምናልባት 50 ሚሊየን ተከታይ አለኝ የምትለዋን ቤተ ክርስቲያን የሚመሩት ሹመኞች «አንድ ለእናቱ» የሆነውና ያውም በየወሩ አንዴ ከሚታተመው «ከዜና ቤተ ክርስቲያን» ውጪ ለጋዜጦች ዜና ባይተዋር ስለሆኑ ዛሬ ምን ተባለ? አዲስ አድማስ ምን ይዞ ወጣ? በማለት እንደአዲስ የመረጃ ምንጭነት የጽሁፉ ስውር ባለቤት የሆነው  ማኅበሩ እንደአዲስ ግኝት ሲነግራቸው በመባነን ተደንቀው ከሚያነቡት በስተቀር ለማኅበሩ የዜና ስራ ድካም አንዳች ትርፍ ለማስገኘት የሚችል ተጨባጭ ነገር እንደሌለው እርግጥ ነው።
«ድከም ያለው ውሃ ይወቅጣል» እንዲሉ ማኅበሩ አንዴ በሐራ ተዋሕዶ፤ አንዳንዴ በግል ጋዜጦች፤ አንዴ በሰንበት ተማሪዎች፤ አንዴ በጥምቀት ተመላሾች፤ ሌላ ጊዜ በጳጳሳት በኩል የሚወጣ፤ የሚወርደው ለአዲስ አበባ ሀ/ስብከት ተጨንቆ ሳይሆን የራሱን መዋቅር በሀ/ስብከቱ ችግር አስታኮ ለመዘርጋት ከማለም የመነጨ ስለሆነ እንደታወቀበት ስንነግረው ፈጽሞ አይገባውም። 


አሁን ደግሞ የያዘው አዲስ ስልት ፓትርያርኩን በውዳሴ ከንቱ ጠልፎ በአንድ ጀንበር የጥናቱን ተአምር ለማሳየት ተዘጋጅተዋል የምትል ዜና ደጋግሞ ማሰማት ጀምሯል። ወደኋላ ያፈገፍጉብኛል ብሎ ስለሰጋ ብርታት ሰጪ የምስጋና መርፌ እየወጋ መሆኑ ነው። ቤተ ክህነትን በማኅበሩ ያስወረራት የሚያዥጎደጉደው ውዳሴ ከንቱ፤ ጥቅማ ጥቅምና በስለላ የሚሰበስበው የግለሰቦች የነውር ፋይል ናቸው። ስለዚህ ፓትርያርክ ማትያስ ቤተ ክርስቲያኒቷ ያለማንም ጣልቃ ገብነት በራሷ ልጆች፤ በራሷ ሊቃውንት፤ ለራሷ የሚሆን ሕግ ማውጣት ትችላለችና ማኅበሩ በግል ጋዜጦች፤ በወጣቶችና በጳጳሳት በኩል ጫና ለማሳደር የሚያደርገውን ዘመቻ እንዳይፈሩ እናሳስባለን። የማኅበረ ቅዱሳን የጋዜጦች ላይ ዘመቻና የሐራ ዘተዋሕዶ የጭቃ ሹምነት የትም አያደርስም!!

የአዲስ አበባ ሀ/ስብከት በ1994 እና በ1995 ዓ/ም በአንጻራዊነት የተሻለ የአስተዳደር ዘመን ነበረው!



ከመሪጌታ ይኄይስ ተአምኖ፤  ኩቤክ- ካናዳ

እንዲህ እንደዛሬው ሳይሆን የአዲስ አበባ ሀ/ስብከት ሥራ አስኪያጅ ማለት በሀ/ስብከቱ ውስጥ የፈለገውን ማድረግ የሚችል ሹመኛ ማለት ነው። ከ1992 ዓ/ም  ጥቂት ቀደም ብሎ በአዲስ አበባ ሀ/ስብከት የሊቀ ካህናት ብርሃኑ ገ/አማኑኤል ሥራ አስኪያጅነትና (ነፍሱን ይማረውና) የዮሐንስ ዋለ ዘመን እንዳበቃ፤ ከቤተ ክህነቱ ሙያ ውጪ የሌላ ሙያ ባለቤት ያልሆኑትና የተለየ ሥራ እንዳላቸው የማናውቅላቸው ነገር ግን በአድዋና በመቀሌ  ትልቅ ኢንቨስትመንት ያላቸው አለቃ መኮነን ገ/መድኅን የሥራ አስኪያጅነቱን ኃላፊነት ከተረከቡ በኋላ ሙስናው ያለማስታወቂያ መደበኛ የስራ መስክ ሆኖ እንደነበር የምናውቅ ሰዎች የምንዘነጋው አይመስለኝም።

  እንደዚያም ሆኖ አለቃ መኮነን ገ/መድኅን ጎበዝ የአስተዳደር ሰው ናቸው። በዚያ ላይም ባመኑበት ጉዳይ ደፋርና ወደኋላ የማያፈገፍጉ ጠንካራ ሰው ስለመሆናቸውም መጥቀሱ ተገቢ ይመስለኛል። በወቅቱ ፀሀፊ የነበረውና አሁን በአሜሪካ በታክሲ ሾፌርነት የሚሰራው ክነፈ ርግብ ሐጎስ ፈጣንና ከዓይን ላይ የሚነጥቅ ቀልጣፋ እንደመሆኑ መጠን የሚበቃውን ገንዘብ መሰብሰብ ችሎ እንደነበር የምናውቅ እናስታውሳለን። እንደዛሬው የጉቦው የጨረታ መነሻ ዋጋው ከፍ ሳይል በፊት ለጉቦው በተሰጠው የሀ/ስብከቱ ምሥጢራዊ መጠሪያ ሥም ማለትም «ሥላሴ ስንት ናቸው? ከተባለ መልሱ «አንድም ሦስትም ናቸው» ማለት ሲተረጎም ክፍያው ከአንድ ሺህ እስከሦስት ሺህ ይደርሳል ማለት ሲሆን «አምስቱ አዕማደ ምሥጢር» ከተባለ ደግሞ «እስከ አምስት ሺህ»፤ ሰባቱ ምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን ከተባለ ደግሞ « እስከ ሰባት ሺህ ብር» ጉቦ ይጠየቃል ወይም ይከፈላል ማለት ነበር። ዛሬን ወደኋላ መለስ ብዬ ሳየው በምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን ሽፋን የጉቦ መቀበያ ተመንን በቁጥር የማስቀመጥ መጥፎ ልምድ መነሻው እምነትን ለገንዘብ የማዋል ምሥጢራዊ ክህደትና ማላገጥ እየተስፋፋ የመምጣቱ ምልክት መሆኑን ያመላከተ እንደነበር ነው። እምነት ከሰዎች ውስጥ እየጠፋ በመጣ ቁጥር እምነቱ ለሥም መጠሪያ ይሆንና በተግባር ግን ወደሸቀጥነት ይለወጣል ማለት ነው። ጌታችንንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም በቤተ መቅደሱ ደጃፍ ሲሸጡና ሲለውጡ የነበሩትን በሃይማኖት ስም የመጡ ነገር ግን እምነቱን የመሸቀጫ መድረክ ያደረጉትን ሰዎች የገለጸበት መንገድ ተመሳሳይ ነበር። 

«የአይሁድ ፋሲካም ቀርቦ ነበር፥ ኢየሱስም ወደ ኢየሩሳሌም ወጣ።በመቅደስም በሬዎችንና በጎችን ርግቦችንም የሚሸጡትን ገንዘብ ለዋጮችንም ተቀምጠው አገኘ፤ የገመድም ጅራፍ አበጅቶ ሁሉን በጎችንም በሬዎችንም ከመቅደስ አወጣቸው፥ የለዋጮችንም ገንዘብ አፈሰሰ ገበታዎቻቸውንም ገለበጠ፥ ርግብ ሻጪዎችንም። ይህን ከዚህ ውሰዱ፤ የአባቴን ቤት የንግድ ቤት አታድርጉት አላቸው።ደቀ መዛሙርቱም። የቤትህ ቅናት ይበላኛል ተብሎ እንደ ተጻፈ አሰቡ» ዮሐ2፤13-17 

ዕለተ ፋሲካ ቀርቦ ሳለ የሃይማኖት ሰዎች ሸቀጥ በመቅደሱ ደጃፍ ከትንሿ እርግብ እስከ ትልቁ በሬ ድረስ ሲሸጥ እንደነበር ቅዱስ ወንጌል ይነግረናል። ዛሬም እንደ ቃሉ በአዲስ አበባ ሀ/ስብከት የነዋይ ፋሲካቸውን የሚያከብሩ ሞልተዋል። ከነጋዴውና ሸቃጩ ማኅበረ ቅዱሳን አንስቶ በሥራ አሥኪያጅነት ዘመናቸው ባርከውና ቀድሰው ጉቦውን ያስፋፉት አባ እስጢፋኖስ፤ ታሪክ ራሱን ይደግማል እንዲሉ ዛሬም ቤተ መቅደሱ ደጃፍ ላይ ተኮልኩለው አዋጭ ያሉትን የጥናትና ስትራቴጂ ገበያ ዘርግተው ለመሸጥ እያስማሙ መገኘታቸው ብዙም ላያስገርም ይችላል። በእምነት ሥም በዐደባባይ መሸጥ፤ መለወጥ ሲያያዝ የመጣ ነውና ብዙም ግር አያሰኝም።  ዛሬም ድረስ በአዲስ አበባ ሀ/ስብከት ውስጥ ሸቃጮቹ መልካቸውን እየለዋወጡ መነገዳቸውን አላቆሙም። «የቤትህ ቅናት በላኝ» ለማለት በመጀመሪያ የንግድ ሂሳቡን ዘግቶ ወደኋላ የሚጎትተውን ብዙ ሀብት ትቶ ሊመጣ ይገባል እንጂ ስሜትና አፍን አስተባብሮ ነፍስያን በማባበል ማንንም ማታለል እንደማቻል ግን እንነግራቸዋለን።

«እርሱም በመንገድ ሲወጣ አንድ ሰው ወደ እርሱ ሮጦ ተንበረከከለትና። ቸር መምህር ሆይ፥ የዘላለም ሕይወትን እወርስ ዘንድ ምን ላድርግ? ብሎ ጠየቀው። ኢየሱስም፦ ስለ ምን ቸር ትለኛለህ? ከአንዱ ከእግዚአብሔር በቀር ቸር ማንም የለም።ትእዛዛትን ታውቃለህ፤ አታመንዝር፥ አትግደል፥ አትስረቅ፥ በሐሰት አትመስክር፥ አታታልል፥ አባትህንና እናትህን አክብር አለው። እርሱም መልሶ፦ መምህር ሆይ፥ ይህን ሁሉ ከሕፃንነቴ ጀምሬ ጠብቄአለሁ አለው። ኢየሱስም ወደ እርሱ ተመልክቶ ወደደውና። አንድ ነገር ጐደለህ፤ ሂድ፥ ያለህን ሁሉ ሽጠህ ለድሆች ስጥ፥ በሰማይም መዝገብ ታገኛለህ፥ መስቀሉንም ተሸክመህ ና፥ ተከተለኝ አለው። ነገር ግን ስለዚህ ነገር ፊቱ ጠቈረ፥ ብዙ ንብረት ነበረውና እያዘነም ሄደ» ማር 10፤17-22

ሀብትና ንብረታቸውን እያከማቹ «የቤትህ ቅናት በላኝ» ቢሉ ሁሉን ዐዋቂ ፈጣሪን ቀርቶ በዓይን የምናያቸው እኛን ሊታልሉ ከቶ አይችሉም። የገነቡትን የመኖሪያ ቤት ለቤተ ክርስቲያናቸው ይስጡ፤ ከመቅደሱ ደጃፍ የተገተረውንም ህንጻ የተወደደ መስዋዕት እንዲሆንላቸው ለቤተ መቅደስ መባዕ ይስጡና ስለ ቤቱ ቅናቱ   ይንገሩን። ያኔም ምሳሌ የሚሆነውን ሥራቸውን ዐይተን እንደነዚህ ዓይነቶቹን ቤተ ክርስቲያን ትፈልጋቸዋለች ብለን ምስክርነታችንን እንሰጣቸዋለን።
   ከዚያ ባሻገር የወጣቱን ሀብታም ታህል  «አታመንዝር፤ አትስረቅ፤ አታታልል፤ በሀሰት አትመስክር» የሚለውን ትዕዛዛት ከህጻንነታቸው ጀምረው ማክበር ስለመቻላቸው አፋቸውን ሞልተው ለመናገር የማይችሉ «የቤተ መቅደሱ ቅናት በላኝ» ቢሉ ማን ያምናቸዋል? ሌላው ቀርቶ ማኅበረ ቅዱሳን  የቤተ መቅደሱን ደጃፍ ሰናዖር ህንጻውን መባዕ አድርጎ ሊሰጥ ይቅርና ቤተ ክርስቲያን ሂሳብህን ኦዲት ታድርግህ፤ በቤተክህነቱም ሰነድ ገቢህን ሰብስብ፤ ሲባል በሕጋዊ የውጭ ኦዲተር አስመርምሬአለሁና የምሰጣችሁ ወረቀት በቂያችሁ ነው በማለት አቅሙም፤ ሥልጣኑም የላችሁም በማለት ማናናቁ ብቻ የማንነቱ ምሥክር ነውና ወቅታዊውን ችግር ተመልክቶ የራስን አጀንዳ ማስፈጸም አግባብ አይደለም።
  ወደ ርዕሰ ጉዳያችን ስንመለስ በ1994 ዓ/ም  አለቃ መኮነን ገ/መድኅን የአዲስ አበባ ሀ/ስብከት ሥራ አስኪያጅነቱን ጨርሰው ለስድስት ወር ገደማ የወረቀት ራስጌና ግርጌ የማይለዩት፤ የማኅጸንቱ ልጅ ሥራ አስኪያጅነቱ እንደለቀቁ፤ በወቅቱ ከአሜሪካ የተመለሱት አባ ተከስተ ብርሃን ወ/ሳሙኤል / በኋላም አባ ሳሙኤል ሊቀ ጳጳስ/ መረከባቸው ይታወሳል።  ፀሀፊ የነበረው ክነፈ ርግብ ሐጎስም የዞረ ሂሳቡን በአባ ማኅጸንቱ በማስጨረስና የሚሸመጥጠውን ጨራርሶ በአጋጣሚ ያገኛትን ኢትዮጵያዊ አሜሪካዊትን አግብቶ ወደአሜሪካ ኮበለለ።
   አባ ተከስተ ብርሃን የወቅቱ ሥራ አስኪያጅ ሆነው በትኩስና ባልተበረዘ ስሜት በሀ/ስብከቱ ውስጥ ተንሰራፍቶ የነበረውን ሙስናና ቤተሰባዊ ተቋም ለመናድ ጊዜ አልፈጀባቸውም። የካህናት አስተዳደሩን መጋቤ ሃይማኖት ጸገየን፤ የትምህርትና ስብከተ ወንጌል ኃላፊውን ርዕሰ ደብር መሀሪን፤ የአስተዳደር መምሪያ ኃላፊውን (ነፍሱን ይማረውና) ኃይሉ ማርቆስን፤ ከወረዳ ቤተ ክህነት ወደ ፀሀፊነት የተዛወሩት አፈ መምህር ገ/ዮሐንስን፤ ከብዙ ድካምና ጥረት በኋላ ደ,ግሞ ወ/ሮ ሣራ ገ/ሥላሴን፤ ወ/ሮ ኢትዮጵያ ክፍሌን የመሳሰሉትን የማይገፉ ተራሮች አንድ በአንድ ለመናድ በመቻላቸው ትልቅ ስም ለመገንባትና በበታቾቻቸው ላይም የማይቻሉ ሰው የመሆናቸውን ተፅዕኖ ማሳደር ችለው ነበር።
 ከላይ የተዘረዘሩት ሰዎች በአንድም ሆነ፤ በሌላም ምክንያት ከበላይ ባለሥልጣናት በተለይም (ነፍሳቸውን ይማርና) ከወቅቱ ፓትርያርክ ከአቡነ ጳውሎስ ጋር ግንኙነት የነበራቸው ስለነበሩ እንደዚህ ዓይነቶቹን ሰዎች ከያዙበት ስኳር ከሆነ ሥልጣን ላይ ማስነሳት የሚታሰብ ባለመሆኑ የአባ ተከስተ ብርሃን ወ/ሳሙኤል ግንባር እድለኛ ስለነበር ይሆናል ወይም በበላይ አካል በኩል ተሰሚነት ያገኙ እንደነበሩ መገመት ይቻላል።  ይህም የስምና የኃይል ግንባታ ብቃት በበታቾቻቸው ላይ ፍርሃት በማንገሱ ትእዛዞቻቸው ሁሉ ተፈጻሚ እንዲሆኑ አስችሏቸዋል። 
በእርግጥም ቀደም ብሎ ከእነ አባ ኃ/ማርያም ዘመንና ከወዲህም በእነ ሊቀ ካህናት ብርሃኑና ዮሐንስ ዋለ በኋላም በአለቃ መኮንንና ክነፈ ርግብ ሐጎስ አስተዳደር ጊዜያት ውስጥ ሀ/ስብከቱ ተጨመላልቆ ስለነበር የአባ ተከስተ ብርሃን ወ/ሳሙኤል አዲስ የአወቃቀር መንፈስ ተስፋን መፈንጠቁ የሚጠበቅ ነው።  ደግሞም ከእነድክመቶቹ በወቅቱ የአዲሱ ሥራ አስኪያጅ ቀናና ትኩስ መንፈስ ብዙ ድጋፍ ከካህናቱ ወገን አግኝቶም ነበር።
  መረን የለሽ የግል ጋዜጦች የቤተ ክህነቱን ገመና ሳይዙ የሚወጡበት ቀን አለ ለማለት አይቻልም ነበር። ይህም በብዙ መልኩ ቀንሶ የተገኘው በአባ ተከስተ ብርሃን ሥራ አስኪያጅነት ወቅት ለመሆኑ የሚዘነጋ አይደለም። በተለይም በ1994 እና በ1995 ዓ/ም በይበልጥም አባ ተከስተ ብርሃን የሊቀ ጳጳስነቱን ሥልጣን ከማግኘታቸው በፊት የነበረው የሀ/ስብከቱ አስተዳደር በአንጻራዊነት ሲታይ በሀ/ስብከቱ ታሪክ ከመቼውም ጊዜ የተሻለ እንደነበር አይካድም። የዚህ ጽሁፍ አቅራቢም ይህንኑ ይመሰክራል።


 አባ ሳሙኤል ሊቀ ጳጳስ ከሆኑም በኋላ ጥቂት ለማስቀጠል ሞከረው ነበር። ነገር ግን ቀደም ሲል የነበራቸውን የመልካም ስራ መንፈሳቸውን ማን እንደቀማቸው ሳይታወቅ፤ በፓትርያርክ ጳውሎስ ፊት የነበራቸውንም ግርማ ሞገስ እየሸረሸረ የወሰደው ነገር ሳይገለጥ ሀ/ስብከቱን ማስተዳደር ትተዋል በሚባል ደረጃ ወደ መርሳት ደርሰው ነበር። ምናልባትም ሥራ የአስኪያጅነቱን ዘመን የተጠቀሙት ወደሥልጣን የመሸጋገሪያ ስልት አድርገውት ይሆን? የሚል ጥያቄ የሚያስነሳው ሥራ አስኪያጅ ሳሉ ከነበሩበት ዘመን የተሻለ ሥልጣን ሲይዙ የበለጠ መስራት እየቻሉ ለመስራት አለመፈለጋቸው ፍንጭ ሊሰጠን ይችላል። ከዚያም በላይ አብረውአቸው የሚውሉትንና የሚወርዱትን ሰዎች ማንነት ስንመለከት በወቅቱ በትክክለኛ የኅሊናቸው መስመር ላይ እንዳልነበሩ ያረጋገጠ ማረጋገጥ ችለናል።

  ከሀ/ስብከቱ ሽያጭ ክፍል ተነስቶ ወደሥራ አስኪያጅነት ያደገው መሪጌታ መኩሪያ ደሳለኝ ከያዘው በኋላ የሀ/ስብከቱ የአስተዳደር ዘመን ሳይሆን የሞት ዘመኑ ሆኖ ተተክቷል። የተገነባው መልካም አወቃቀርና አስተዳደር እምጥ ይግባ ስምጥ ሳይታወቅ በአፍ ጢሙ ተደፋቷል። በተመሳሳይ መልኩ ሊቀ ጳጳስ ሳሙኤል መተንፈሻ እስኪያጡ ድረስ ከረቫት ባሰሩ አሸርጋጅ ፀሐፊዎች፤ ራሳቸውን ባልሰበኩ ሰባኪዎች፤ በሙዳየ ምጽዋት ገልባጭ አስተዳዳሪዎች ተከበው በውዳሴ ከንቱ መከራቸውን ያዩ ነበር። ሃይማኖት የለሹ ዘሪሁን ሙላቱ (ዛሬም በየመድረኩ ሃይማኖት እንዳለው ሰው ያናፋል) ቀኝ እጃቸው ሆኖ አለሁልዎ ሲላቸው መጨረሻውን ለማየት እንመኝ ነበር። የዛሬው የቦሌ መድኃኔ ዓለም ፀሀፊ ሰሎሞን በቀለ የካዝናውን ቀበኛ አይጥ ይዘው ሲጓዙ ለተመለከተ አጀብ የሚያሰኝ ነበር። የባሌ ጎባው አጭበርባሪ ሰሎሞን ቶልቻ (ቄስ ነኝ ይላል)፤  የቅድስት ማርያሙ ሰንበት ተማሪ ሡራፌል ወንድሙ (እሱም አሁን አሜሪካ ገብቶ ቄስ ነኝ ይላል) የመሳሰሉት ሁሉ እንደበረዶ ናዳ የሚሟሙ ወዳጆችን አፍርተው አይተን የሚቀልጡበትን ቀን ስንጠባበቅ ነበር።

  ጉዳይ የሚፈጸመው በስልክ ወደመሆን ተቀይሯል። በጉድ ሙዳዩ አባ አብርሃም በኩል የሚቀርቡ ተቀጣሪዎች ውጤታማ መሆናቸውም የታየበት ወቅት ነበር። ባለ ጉዳይ፤ ጉዳይ የለሽ ሆኗል። የአድባራትና ገዳማት ምዝበራ ከመቼውም ጊዜ በላይ ገኗል። ከስራ የሚባረር፤ አላግባብ የሚዛወር፤ ከደረጃው የሚወርድ በርክቷል። ፍርድ ቤቶችን የቤተ ክህነት አቤቱታ አሰልችቶታል። ብዙ ችግሮችና የሥልጣን ሽኩቻዎች ተበራክተው የሀ/ስብከቱ አስተዳደር ግብዓተ መሬቱ ሊፈጸም ሲል ከአባ ጳውሎስ ጋር የጠለቀ ክርክር ሲነሳ ጎራው ይለይ ጀመረ። ዘመቻው ሁሉ ፈልቶ፤ ገንፍሎና ቀዝቅዞ የሆነው ሁሉ ሆነ።  በተለያየ ጊዜ ከሀ/ስብከቱ ያስቀየሯቸው ሰዎች አባ ሳሙኤልን መዋጋት ዛሬ ነው በማለት ጦር ሰበቁ። አየር ላይ የተንሳፈፉት እነአባ ዕዝራ በጀት መደቡ። እነኤልዛቤል እጅጋየሁም እንደጉዲት ተፋለሙ። አባ ሳሙኤልም ብቻቸውን ቀርተው፤ ብቻቸውን ተዋግተው ዘለቁ። ሁሉም ጥጉን ይዞ «ያመኑት ፈረስ በደንደስ» እንዲሉ ያመኗቸው ሁሉ ከዱ። አባ ሳሙኤል ሀ/ስብከታቸውን በአግባቡ የአስተዳደር ማዕከላዊነት ይዘውት ቢሆን ኖሮ አንድ ጊዜ ለዐራት፤ ሌላ ላንድ ሲጠቀለልና ሲፈታ ባልኖረም ነበር። እንደጀመሩት ለመጨረስ አልቻሉም።

  ዛሬስ? ዛሬ ያለፈውን ስህተት ሲደገም ማየት የባሰ ያሳምማል። አባ እስጢፋኖስ ያንን ስህተት እየደገሙት ነው። ማኅበረ ቅዱሳንና ተላላኪዎቹ ከኋላ ሆነው ሀ/ስብከቱን እያስተዳደሩት መገኘታቸው እርግጥ ነው። እኛ የምንለው ራሳችሁን ሁኑ ነው። ሌሎችን ተደግፋችሁ የራሳችሁን ገመና ለአጋልጦ ገላጭ አትስጡ ነው። እውነት መናገር ካስፈለገ ካህናቱ የማንንም አባቶች ገመና አደባባይ ማውጣት አይፈልጉም፤ አይወዱምም። ችግሩ ያለው ከራሳቸው ከባለገመናዎቹ ሲሆን ገመናቸውን እንደድመት ሽፍን አድርገው መያዝ ያቅታቸውና ያለቦታቸው ተገኝተው እንዲገለጥላቸው አርፎ የተኛውን ካህን በግድ ይነካኩታል።  አፄ ቴዎድሮስን እልክ ያጋባቸውና እስከሞት ያደረሳቸው የካህን አድማ ነው። አባ እስጢፋኖስም አዲስ አበባ ሀ/ስብከትን ያለማኅበረ ቅዱሳን ውሻል ማስተዳደር አልቻሉበትም። በእልኽ ቤት አይገነባምና በእልኸኝነት ሁሉን ከግብ አደርሳለሁ ማለቱን ትተው ሀ/ስብከትን ለቀው አንዱን፤ ጅማዎትን ለዚያውም ከቻሉ እስኪ እሱኑ በደንብ ያስተዳድሩ ምክሬ ነው!!

Wednesday, January 15, 2014

ትግርኛ ተናጋሪ ጎንደሬው ሊቀ ጳጳስ እስጢፋኖስ ከጎንደሬዎች ጋር እየመከሩ ነው!!


( ከብሶቴ ተሰማ አዲስ አበባ )
ዘር ለእህል ነው። የእህል ዘር ግንዱ አንድ አይደለም። ዘሩ በየመልኩ ልዩ ልዩ ነው። የሰው ልጅ ግን እንደዚያ አይደለም። መልኩ ቢለያይም ግንዱ አንድ አዳምና ሔዋን ናቸው። ከዚያም በላይ ሁላችንም በክርስቶስ ሞትና ትንሣዔ  አንድ ሆነናል። ይሁን እንጂ ክርስትናን ከስምና ከሹመት በስተቀር የማያውቁ አንዳንዶች ዛሬም  የሰውን ልጅ ከእህል የዘር ዓይነት ቆጠራ ራቅ ብለው ለማየት እንዳልቻሉ እርግጥ ነው።
ከእነዚህም አንዱ አባ እስጢፋኖስ በአዲስ አበባ ሀ/ስብከት የማኅበረ ቅዱሳን ሊቀጳጳስ ናቸው። ቤተ ክርስቲያን አንዲት ብትሆንም በአስተዳደር ይዞታዋ የተለያየ በመሆኑ ሊቀ ጳጳሱ በጅማ ሀ/ስብከት ሳሉ ገመናቸው ተሸፍኖ፤ በሰው መሳይ ሸንጎ ተከልለው በሰላም ይኖሩ ነበር።  ኅሊናቸውን አሳርፈው መኖር የሚችሉበትን ሀ/ስብከት ይዘው አርፈው እንደመቀመጥ ከወታደሮች ማኅበር ጋር አብረው በመቆም የእድሜ ልክ መጽሐፋቸው ይነበብ ዘንድ በየቦታው አለሁ ማለታቸው ያሳዝናል።  ደርሶ መንፈሳዊ መስሎ ለመታየት የአበው አጥንት ይወቅሰናል፤ የቤተ ክርስቲያን ታሪክ ይፋረደናል በሚል በአስመሳይ ተቆርቋሪነት የማኅበሩን ዓላማ ለማስፈጸም ደፋ ቀና ማለታቸው ለእርሳቸው የትጉህ ሰራተኛ ትግል ቢመስላቸውም እውነቱን ለሚያዩ ግን ያለቦታቸው በአጉል ሰዓት የተገኙ  ሰው ናቸው። ከአባ ገብርኤል ጋር ከአስመራ ጀምሮ በድሬዳዋ ዞረው፤ አዲስ አበባን አካለው ኮተቤ 02 እስካሳነጹት የመኖሪያ ህንጻ ድረስ ብዙ ጉድ መኖሩን የምናውቅ እናውቀዋለን።
በእርግጥ ሊቀጳጳሱ( ከተባሉ) ዓይናቸውን በጨው የታጠቡ ስለሆነ ስለበደልና ጥፋት ትንሽ ስሜት አይሰጣቸውም። የኅሊና ጸጸትም ፈጽሞ አይነካካቸውም። ከድፍረቱ ጋር የደነደነ ልብ ስለታጠቁ የተባለው ቢባል፤ የተወራው ቢወራ ደንታ የላቸውም። ለዚህም ነው ከበደል ጋር ዕረፍት በሌለው ወዳጅነት እስከ ህይወታቸው ህቅታ ድረስ ቃል በመግባት ዛሬም የአንድ ተራ ማኅበር ጉዳይ አስፈጻሚ ሆነው የመገኘታቸው ነገር  አረጋጋጭ ነው። በመሰረቱ የአዲስ አበባ ሀ/ስብከትን ለማስተዳደር ራሱ ከሙስናና ከአስነዋሪ ስነ ምግባር የጸዳ መሆን ይገባው ነበር። አፉን ሞልቶ ለመናገር፤ ሌባና ብልሹ አስተዳደር ለማስተካከል የሚችለው ከዚህ የጸዳ ቢሆንም አባ እስጢፋኖስ ግን ለአባ ማትያስ በዋሉላቸው ውለታ የተነሳ በስራ አስኪያጅነት ዘመናቸው በጉቦ የጋጡትን ሀ/ስብከት  በፓትርያርኩ ረዳት ሊቀ ጳጳስነት ስም ተመልሰው ባልያዙም ነበር። በዚህ ዘመን ከሰጪም፤ ከተቀባይም ኅሊና የሚባል ነገር ስለጠፋ እያየነው ያለው ሊሆን ግድ ሆነ።
በአዲስ አባ ሀስብከት ውስጥ መልካም አስተዳደር እንዲመጣ ካስፈለገ ያለው አማራጭ የአባ እስጢፋኖስ ከቦታው ማስነሳት ብቻ ነው። የተባለውም መዋቅር ጥናት እንደአዲስ ከሚታይ በስተቀር በእሳቸው አስፈጻሚነትና በማኅበሩ ገፊነት ችግሮችን ያባብሳል እንጂ ፈቺ ሊሆን አይችልም። /ሊሰመርበት የሚገባው ጉዳይ/ ችግሮችን ያባብሳል እንጂ ፈቺ ሊሆን አይችልም።
አባ እስጢፋኖስ የጎንደር ተወላጅ የቤተክርስቲያን አስተዳዳሪዎችንና የሰበካ ጉባዔ ምክትል ሊቃነ መናብርትን በደጋፊነት በማሰለፍ በማቅ የተዘጋጀውን የመዋቅራዊ ለውጥ በተግባር ላይ ለማዋልና ከጀርባቸው ያለውን አሳፋሪ ታሪክ ለመደበቅ ጥረታቸውን ቀጥለዋል፡፡
አቡነ እስጢፋኖስ የአዲስ አበባ ሥራ አስኪያጅ በነበሩበት በ1990ዎቹ መጀመሪያ ዓመታት በእሳቸው ድጋፍ የድራፍት ቡድን በማቋቋም አዲስ አበባን ሲያውኳት እንደነበር ቀደምት ታሪካቸው ያስረዳል፡፡ ያን ጊዜ ስያሜውን ያገኘው የድራፍት ቡድን አባ እስጢፋኖስን ቤተክርስቲያን ወንበር ላይ በስራ አስኪያጅነት አስቀምጦ በከተማዋ በሚገኙ ዝነኛ ሆቴሎች በመቀመጥ ቅጥር ዝውውርና እድገት በመስተት መላውን የቤተክርስቲያኒቱ ሰራተኞች ሲያበጣብጥ በወቅቱ በጉዳዩ መንግሥት እጁን አስገብቶ እሳቸውንም ከኃላፊነታቸው ድራፍት ቡድኑንም ከጣልቃ ገብነቱ በመግታት በወቅቱ ሰላም ተገኝቶ ቆይቷል፡፡ ታሪክ እራሱን ይደግማል እንደሚባለው ዛሬም ሳይገባቸው ያገኙትን አስኬማ ለዚሁ ሰላም አደፍራሽ ለሆነ ተልእኮ በመጠቀም በመላው አዲስ አበባ በመንግሥት ላይ ካኮረፈው የማቅ ቡድን ጋር በመሆን  ዛሬም ቤተክርስቲያኒቱን እያወኩ ይገኛሉ፡፡
በቅርቡ በማቅ ቡድን ራዕይ መሠረት ቤተክርስቲያኗን ለመቆጣጠር  በተዘረጋው ወጥመድ መዋቅራዊ ለውጥ በሚል የተዘረጋው ስውር እስትራቴጂ በግልጽ የቤተክርስቲያኗ ችግር መሆኑ ከተረጋገጠ በኋላ ቅዱስ ፓትርያርኩ በማቅ የተዘጋጀው የመዋቅራዊ ጥናት ውድቅ ሁኖ በቤተክርስቲያኗ ሊቃውንት ሁሉን ያማከለ ሕግ እና መመሪያ እንዲወጣ የማቅን የሽብር ሴራ ቀድመው ለተገነዘቡ አገልጋዮች ቃል ገብተው ነበር፡፡ አቡነ እስጢፋኖስ ከቤተክርስቲያኗ ሕግ ውጪ የወለዷቸውንና በየአብያተ ክርስቲያናቱ በቁጥጥር እና ሒሳብ ሹም የቀጠሯቸው ልጆቻቸው ጉዳይ እንዲጣራም ሐሳብ ቀርቦ ነበር፡፡ ታድያ ይህ አካሄድ ያሰጋቸው አቡነ እስጢፋኖስ በፖለቲካ ምክንያት የተገለሉና አካላቸው ኢትዮጵያ ሆኖ ልባቸው  የሰሜን አሜሪካው ሲኖዶስ  ጋር የሆኑ የጎንደር ተወላጅ አለቆችን በመሰብሰብ ይኸው የልጆቻቸው ጉዳይ ተዳፍኖ እንዲቆይና መዋቅራዊ ጥናቱ በተገባር ላይ እንዲውል የእሳቸው ሥላጣን ቆይታን የሚያረጋግጥ ውሳኔ በቅዱስ ሲኖዶስ እንዲያስወስኑ አደራ በማለት አሰማርተዋቸዋል፡፡ በየትኛውም ወገን አዲሱ መተዳደሪያ ሕግ ተግባራዊ ቢሆን  በሚፈጠረው አለመግባባት ሐገር ሲታመስ ከዚሁ ብጥብጥ ፖለቲካዊ ጥቅም ለማግኘትና የሰሜን አሜሪካው ሲኖዶስ ከብጥብጡ መልካም አጋጣሚ እንዲያገኝ ጥረታቸውን በመቀጠል ፓትርያርኩ ድረስ ዘልቀው የአደራ መልእክታቸውን አሰምተዋል፡፡
የአቡነ እስጢፋኖስ የሀገር ልጅና የጥቅም ተሳታፊ የሆነው የአፍሪካ ኅብረቱ ዋና ጸሐፊ አቶ አብርሃም አቧሀይ የእነዚህ የጎንደር ኃይሎች ዋና አደራጅና መሪ ሲሆን እራሳቸውንም የአርበኞች ግንባር ብለው ሰይመው ፓትርያርኩ ዘንድ በመቅረብ የተሰጣቸውን ተልእኮ ለመፈጸም ሞክረዋል፡፡ የጳሳሳት ልብስ ሰፊው ወርቁ አየለ ፤ የየረር ዑራኤል አለቃ ዘማርያም ሙጬ፤ የጃቲ ኪዳነምሕረት አስተዳዳሪ፤ የደብረሲና እግዚአብሔር አብ ምክትል ሊቀ መንበር፤   እና የሰሚት መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን አስተዳዳሪ አባ ገብረ ስላሴ ከጎንደር ተወላጅ ሊቃነ መናብርቶቻቸው ጋር በመሆን ብዙ ባሉበት ስብሰባ  የአቡነ እስጢፋኖስ ሥልጣን እንዲራዘም ልመናቸውን ለፓትርያርኩ አቅርበዋል፡፡
ከአቡነ እስጢፋኖስ ተቃዋሚዎች ይቅርታ ጠይቀዋል በማለት  አዲስ ፕሮፓጋንዳ በማናፈስ ሌሎች ተቃዋሚዎችን ለማስበርገግ ጥረታቸውን ቀጥለዋል፡፡ እንደ ሌሊት ወፍ ከዚህኛውም ከዚያኛውም ቡድን አለሁ በማለት በመሀል ሰፋሪነት አንዴ ተቃዋሚ ሌላ ጊዜ ደጋፊ አሁን ደግሞ አስታራቂ የሆነውና የቦሌ መድኃኔዓለምን ጸሐፊነት ላለመነጠቅ በሚባዝነው በቀሲስ ሰሎሞን በቀለ አስታራቂነት ይቅርታ የጠየቁት የሲኤምሲ ሚካኤል አለቃ መ/ር ዘካርያስ ሲሆኑ እሳቸውም ይቅርታ የጠየቁት አዲስ በሚሰራው  ካቴድራል ስም የሚገባ ሲሚንቶ  ከንብረት ክፍል ኃላፊዋ ወ/ሮ ሰርክ አዲስ እና ከምክትል ጸሐፊው ፋንታሁን ከሙጨ ወንድም ጋር በመሆን መሸጣቸውን የሚያረጋግጥ መረጃ በአቡነ እስጢፋኖስ ሰዎች በመያዙ ይህንን እንደመደራደሪያ በመጠቀም አንተም ተው እኔም እተዋለሁ በሚል በአቡነ እስጢፋኖስ የተደረሰ ድራማ መሆኑን ታውቋል፡፡
ለቤተክርስቲያን ለውጥ የሚያስፈልጋት ቢሆንም ለውጡ ሁሉን አቀፍ የሆነና ከቤተክርስቲያኒቱ ሌሎች ሕጎች ጋር የማይጣረስ አዘገጃጀቱም ሁሉን ያሳተፈ እንዲሆን የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት አስተዳዳሪዎችና ሌሎች ሰራተኞች በግልጽ መጠየቃቸው አይዘነጋም፡፡
ጥያቄው መቼም አይቆምም!!

Monday, January 13, 2014

ጦርነቱ በማጣጣር ላይ ባለው የማኅበረ ቅዱሳን አልሞት ባይነትና እጁን ለመስጠት በተዘጋጀው የቤተ ክህነት ባለሥልጣናት መካከል ነው!!!



እንደወትሮው ስለማኅበረ ቅዱሳን የምናትተው ሰፊ ጽሁፍ የለንም። ማኅበሩ እያጣጣረ ነው። ለጊዜው ትንሽ መቆየቱ የእድገት መጨረሻውን አያስቀጥለውም።  ይሁን እንጂ ይህ የብላቴ ትራፊ «አንዲት ጥይት ወይም ሞት» በማለት የጥንት ቃል ኪዳኑን ለማደስ እየተንፈራገጠ ነው።
ለዚህም በመሞትና በመዳን መካከል እየተንፈራገጠ ያለው ማኅበረ ቅዱሳን ራሱን ለማዳን እየታገለ ይገኛል። ለመዳን የሚያደርጋቸውን ትግሎች በአጭር በአጭሩ በነጥብ ሲቀመጡ ይህንን ይመስላሉ።


1/ በሙስናና በአስተዳደር ብልሹነት ሊጠየቁ የሚገባቸው አስተዳዳሪዎችና ፀሐፊዎች አዲሱን ስልቴን እየተቃወሙት ነው በማለት ራሱን ደብቆ ለቤተ ክህነት የለውጥ ማሻሻያ ህግ አያስፈልጋትም የተባለ አስመስሎ ማሳየት ይፈልጋል።

2/ ህጉ ከየትምና ከማንም ይመንጭ ለቤተ ክህነት ስለማስፈለጉ ብቻ እንተማመን በማለት የሕጉን ምንጭ ማንነት እንዳይገለጥ በአስፈላጊነቱ ስር ሸሽጎ ለማስቀጠል ይፈልጋል።

3/ ከአባ አማቴዎስ፤ ከአባ ሉቃስ፤ ከአባ እስጢፋኖስ እና ለጊዜው ስማቸው መጥቀስ ከማንፈልጋቸው ሌሎች ጳጳሳት ጀርባ ተጭኖ የህጉን አስፈላጊነትን በማጦዝ ሲኖዶሳዊ ለማስመሰል በትጋት ይሰራል።

4/ ስለህጉ እጹብ ድንቅነትና ትንግርታዊነት በመረጃ መረብና በስመ ነጻ ሚዲያ ጋዜጦች ላይ በመለፈፍ የምርጫ ዓይነት ቅስቀሳውን በህዝብ ውስጥ በማስረጽና በጳጳሳቱ መካከል የወደፊት በል  ዘመቻውን ለማስቀጠል  ድፍረት የሚሆናቸውን ኃይል በማስታጠቅ ላይ ተጠምዷል።

5/  በካህናት ሽፋን፤  የጥምቀት ተመላሾችንና የተወሰኑ አባላት ምእመናኑን በማሰለፍ በፓትርያርኩ ላይ ጫና በማሳደር የሰማይ ተሰበረ ሽብሩን በመንዛት ላይ ላይ ይገኛል።
እነዚህ ከብዙ በጥቂቱ የተዘረዘሩት እስትንፋሱን የማስቀጠል ዘመቻው ጊዜ ከሚገዛለት በስተቀር በፍጹም ሊታደጉት አይችሉም። ምክንያቶቹ፤
ሀ/ በቤተ ክህነት አጠቃላይ መዋቅራዊ ማሻሻያና የለውጥ እስትራቴጂ ጥናት አስፈላጊነትን የተቃወመና የሚቃወም ማንም የለም። ሊቃወምም አይችልም።

ለ/ የለውጥ ጥናቱ መምጣት ያለበት  ከሲኖዶስ ውስጥ የሚመነጭ ሆኖ በሊቃውንቱ፤ በምሁራኑ፤ በካህናቱ፤ በአዋቂዎቹና በህግ ባለሙያዎች የሚዘጋጅ እንጂ ከማኅበረ ቅዱሳን ጡንቻ ነጻ የመሆን አቅምና ጠባይ በሌላቸው አባ እስጢፋኖስ በአዲስ አበባ ሀ/ስብከት ላይ የማዘዝ ስልጣንን ያገኙትን አጋጣሚ በመጠቀም  ዓላማን የማስፈጸም ግብ ሊሆን አይችልም።

ሐ/ በመሰረቱ ማኅበረ ቅዱሳን ለቤተ ክርስቲያኒቷ ምኗም አይደለም። ቤተ ክርስቲያን ነጋዴ አይደለችም። እሱ ግን የሚታይ የሚጨበጥ የንግድ ተቋም ያለው ግልጽ ነጋዴና አትራፊ ድርጅት ነው። በዐውደ ምሕረቷ ላይ የሚነግድ ይህ ድርጅት የንግድ ጠረጴዛው መገልበጥ አለበት። በጅራፍም ሊባረር የተገባው ነው። ስለዚህ በምንም ዓይነት መልኩ ወርቅና አልማዝ አቅርቤአለሁ ቢል ተቀባይነት ሊኖረው አይችልም።

መ/ ማኅበረ ቅዱሳንን የሚደግፉ ሊቃነ ጳጳሳት በግልጽ ቋንቋ ስንናገር፤

ሀ/ በቤተ ክርስቲያኗ ሕግና ደንብ መሰረት ለጵጵስና የሚያበቃ ሥነ ምግባር በጭራሽ የሌላቸው ናቸው።

ለ/ በዘር ፖለቲካ የተለከፉና ኢህአዴግ እንደጉም ተኖ፤ እንደጢስ በኖ  ይጠፋ ዘንድና  የራሳቸውን ሥርወ ቤተ ክህነት ለመትከል የሚናፍቁ ናቸው።  ከዚህ የወጣ  ደጋፊ የለውም።
በተለይ አባ እስጢፋኖስ ለማኅበሩ ጥብቅና የመቆማቸው ነገር በፍቅሩ ስለተቃጠሉ አይደለም።  ጵጵስና ስሙና ታሪኩ ክብር ያጣው ጸሊማን አርጋብ በምግባር /ጥቋቁር እርግቦች/ የሆኑ ቦታውን ከወረሩት በኋላ ነው። አባ እስጢፋኖስ ኮተቤ ያሰሩት የሚሊዮን ብሮች ግምት ቤታቸው የተሰራው በደመወዛቸው ነው?  መነኩሴ እናቱም አባቱም ቤተ ክርስቲያን ናት ስለሚባል እስኪ ለቤተ ክርስቲያን የውርስ ኑዛዜ ይስጡ!!
ስለዚህ እስትራቴጂ፤ ጥናት፤ ስብሰባ፤ ተቃውሞ፤ ስነ ምግባር፤ ሙሰኛ ወዘተ በሚሉ የቃላት ማደናገሪያ ቤተ ክህነቱ እጁ ሲጠመዘዝ አሜን ማለት የለበትም። አካፋን አካፋ ማለት የሚገባው ወቅት ቢኖር አሁን ነው። ቤተ ክህነት ችግሮቿን ታውቃለች። ለችግሮቿም መፍትሄ ማመንጨት አይሳናትም። የወላድ መካንም አይደለችም። ስለዚህ በፓትርያርኩ አመራር ከራሷ ልጆች በወጣ ህግ ለችግሮቿ መፍትሄ መስጠት አለባት እንጂ በማመልከቻና በደጋፊ ብዛት መጠምዘዝ አይቻልም። 
የማኅበረ ቅዱሳን ስፍራው መናገር ካስፈለገ ሼር ካምፓኒ/ የአክሲዮን ማኅበር መሆን ብቻ ነው። አዲዮስ ማኅበረ ቅዱሳን ከማለት ውጪ በዚህ ማኅበር ስንታመስ መቆየት ያብቃ!!  በዚህ ማኅበር ዙሪያ ከቤተ መንግሥቱ የተሰማውን መረጃ በሌላ ጽሁፍ ይዘን እንመለሳለን።

Saturday, January 11, 2014

የእግዚአብሔር መንፈስ እንዲያድርባችሁ ሳር ጋጡ የተባሉ ደቡብ አፍሪካውያን ሳር ሲግጡ ዋሉ!!

የፍጻሜው ዘመን የተቃረበ ይመስላል። ጤናማ አእምሮና በማኅበራዊ ኑሮው ሰላማዊ የነበረ ሕዝብ እንደጋማ ከብት ሳር እንዲግጥ ሲታዘዝ  ሲበላ ዋለ ማለት እጅግ ያስገርማል። ነገሩ በእርግጥ ሆኗል። በደቡብ አፍሪካ ፤ ጋራኑካ በተባለች ከተማ ውስጥ  የተቋቋመችውና ከ1000 በላይ ተከታዮች ያሏት ማኅበር መሪ የሆነው ፓስተር ሌሴጎ ዳንኤል የስብከት መርሐ ግብሩን እንደፈጸመ መገለጥ መጥቶልኛልና ከአዳራሽ ወጥታችሁ የሜዳውን ሳር ጋጡና በመንፈሰ እግዚአብሔር ትሞላላችሁ ባላቸው መሰረት ትእዛዙን ተቀብለው ሳር ለመጋጥ መሰማራታቸውን «ክርስቲያን ፖስት» ጋዜጣና «ቺካጎ ዲፌንደር» ዘግበዋል።


   ግማሹ ሳሩን አጎንብሶ እንደከብት እየጋጠ፤ ገሚሱ ደግሞ እንደጭላዳ ዝንጀሮ እየነጨ ሳሩን ሲበላ የዋለ ሲሆን የሰው ጭላዳ ከሆኑት መካከል አንዷ የሆነችው የ21 ዓመቷ የህግ ተማሪ ሮዝመሪ ፔታ ለጋዜጠኞች እንደተናገረችው «ሳሩን በመጋጤ ለአንድ ዓመት ያህል ሲያሰቃየኝ ከነበረው ከጉሮሮ ቁስለት በሽታ ተፈውሻለሁ» በማለት ያገኘችውን አስደናቂ ተአምርና የሳር መጋጡን ጠቃሚነት የገለጸች ሲሆን የ27 ዓመቷ ዶሪን ጋትል የተባለችው ደግሞ እንዲህ ስትል ስለተደረገላት ተአምር ያገኘችውን ጥቅም ገልጻለች። «በነበረኝ የስትሮክ በሽታ እግሮቼን ላለፉት ሁለት ዓመታት ማንቀሳቀስ ተስኖኝ ነበር። ሳር ብትበሉ በመንፈስ ትሞላላችሁ፤ በማለት ስለሳር መብላት አስፈላጊነት ፓስተሬ ባዘዘኝ ጊዜ በመብላቴ ከበሽታዬ በፍጹም ድኜ እነሆ በሁለት እግሬ ለመሄድ በቅቻለሁ» በማለት ስለተደረገላት ተአምር ለሚዲያ ተናግራለች።

  ይሁን እንጂ የሁለቱንም ሴቶች አባባል የሰሙ ታዛቢዎች በአባባላቸው ስቀዋል። ጤንነታቸውንም ተጠራጥረዋል።  ይህ የማይታመን ቀልድና በእግዚአብሔር ስም ማላገጥ ነው። መንፈስ ቅዱስ እንዲያድርብን ሳር አጎንብሳችሁ ጋጡ ተብለናል የሚሉት ጉዳይ የግድ መቆም ያለበትና ለህብረተሰቡ በመጥፎ አርአያነቱ ካልሆነ በመልካምነቱ የሚታይ አይደለም በማለት የተመለከቱ ታዛቢዎች ተቃውሟቸውን ገልጸዋል ። የሰው ልጅ ሲፈጠር እንደእንስሳ ሳር ለመጋጥና ለመፍጨት የተዘጋጀ የሰውነት አወቃቀር ስለሌለው የተደረገው ነገር ሁሉ ከክርስትና ሃይማኖት ጋር የማይገኛኝና መጽሐፍ ቅዱሳዊ መሰረት የሌለው በመሆኑ ድርጊቱን እንቃወማለን ሲሉ ስለሳር ጋጮቹ ተናግረዋል።

 ከዚሁ ጋር ተያይዞ ስለሳር መጋጡ ውሎ እንደተዘገበው፤ በመስኩ ላይ ተሰማርተው ሳር ሲግጡ ከዋሉት የሰው ጭላዳዎች መካከል አብዛኛዎቹ ሲያስመልሳቸውና ሲሰቃዩ የዋሉ ሲሆን ገሚሶቹ መብላት አቅቷቸው ሲያለቅሱ ታይተዋል። አንዳንዶቹም ሆዳቸውን ታመው ህክምና እስኪደርስላቸው ድረስ መታመማቸውም ታውቋል። ከዚህ በፊትም ፓስተር ሌሴጎ ዳንኤል በአዳራሹ ውስጥ የተገኙ ተከታዮቹን በጥፊ እንዲጠፋጠፉ ባዘዛቸው ጊዜ ትእዛዙን ተቀብለው፤  ጉንጫቸው ድልህ እስኪመስል በጥፊ መጠዛጠዛቸውም ተዘግቧል።

እንደሚታወቀው ሳር በመጋጥ እንደእንስሳ ይሆን ዘንድ ከእግዚአብሔር ትእዛዝ የወጣበትና ልቡ የተሰወረበት ናቡከደነጾር እንደነበረ መጽሐፍ ቅዱስ ይነግረናል።  ናቡከደነፆርም ለዚህ የበቃው በትምክህቱና በትዕቢቱ እንጂ ለበጎ ተግባሩ የተሰጠው ልዩ ጸጋ አልነበረም። እና ታዲያ የዘመኑ ሰዎች እንደናቡከደነፆር ወደእንስሳነት ወርደው ሳር በመጋጣቸው የናቡከደነፆር ቤተሰቦች የማይሆኑበት ምክንያት ይኖር ይሆን?
«ልዑሉም በሰዎች መንግሥት ላይ እንዲሠለጥን፥ ለሚወድደውም እንዲሰጠው እስክታውቅ ድረስ ከሰዎች ተለይተህ ትሰደዳለህ፥ መኖሪያህም ከምድር አራዊት ጋር ይሆናል እንደ በሬም ሣር ትበላ ዘንድ ትገደዳለህ፥ ሰባት ዘመናትም ያልፉብሃል አለው» ዳን 4፤32

Wednesday, January 8, 2014

በሰዓሊተ ምሕረት ካቴድራል የተንሰራፋው የክህደት፤ የዘረፋ፤ የሕገ ወጥ መሬት ንግድና ኪራይ ሰብሳቢነት እውን መንግሥትና ሕግ ባለበት ሀገር የተፈጸመ ነው?


የደ/ም ሰዓሊተ ምሕረት ቅ/ማርያም ካቴድራል
እኩይ ዓላማውን ይዞ ገለልተኛ ቤተክርስቲያን መፍጠር የሚለውን የመናፍቃን ሐሳብና መንግሥትን በሽምቅ ለመዋጋት የሰአሊተ ምህረት ቅድስት ማርያም ካቴድራል የመቃብር ሥፍራ የተሸሸገገው ቡድን 2 ፓትርያርኮች ፣ 3 ጳጳሳትንና ፣ 3 ሥራ አስኪያጆች ደክመውበት መፍትሔ ሳይሰጡት  በአክሲዮንነት ቤተክርስቲያኗን በመዋጋት  አሁንም ቤተክርስቲያኗን እየበጠበጠ ነው፡፡
ሰንበቴዎቹ በ 70 ሺህ ብር ለኢ አማንየን ፤በ50 ሺ ብር ከውጭ ለሚመጣ አስክሬን፤ በ 35 ሺህ ብር ለሀገር ውስጥ የሚሸጡትን ፉካ ንግድ አላቆሙም።




በመንፈሳዊ ቅብብሎሽ ሲያያዝ የመጣ የቤተክርስቲያን የታሪክ መዝገብ የሚያውቀው ትውፊት ስለሆነ በሀገራችን ተጠብቆና ተከብሮ እስከ አሁን መቆየቱ የሚያስመሰግን ነው፡፡ የሚያኮራም ነው፡፡
ነገር ግን በዚህ መንፈሳዊ ትውፊት ውስጥ የግል ፍላጐትን ለማሳካት ነቀፋን የሚያስከትሉ ጠብ፣ ክርክር ወይም ሌላ ሥጋዊ ፍላጎት ወይም የቤተክርስቲያኗን ዶግማ ቀኖናና ትውፊት ያልጠበቁ ድርጊቶች ሰርገው ገብተው ዛሬ ሰንበቴ ማኅበራት መንግሥት ግብር የማይቀበልበት በአቋራጭ መክበሪያ እና የመናፍቃን መሰብሰቢያ ሆኗል፡፡ በምስራቃዊ አዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የምትገኘው ደብረ ምጥማቅ ሰአሊተ ምህረት ቅድስት ማርያም ካቴድራል በ1969 ዓ.ም ስትመሰረት በወቅቱ ገጠር ልትባል የምትችል ደብር ነበረች፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ መስፋፋት ጋር ተያይዞ እንዲሁም በ1997 ዓ.ም ተመርቆ አገልግሎት በመስጠት ላይ በሚገኘው ካቴድራል ግንባታ ቦታው በአዲስ አበባ ከተማ ከሚገኙ አብያተ ክርስቲያናት አይን ማረፊያ ለመሆን በቃ፡፡ ከዚህም በላይ በማንኛውም አብያተክርስቲያናት የሌለ 200.000.00 (ሁለት መቶ ሺህ) ካሬ ሜትር ይዞታ ባለቤት መሆነኗ ግን ብዙ ሺህ ጠላቶች በቦው ላይ እንዲነሱ አደረጋቸው በቅድሚያ በቁጥር 11 የሚሆኑ አገልጋዮቿ ከካቴድራሉ ይዞታ 18.000.00 (አሥራ ሰስምንት ሺህ ካሬ ሜትር ) ቦታ በመውሰድ ለግል ጥቅማቸው በማዋላቸው ከ 8 ዓመት በላይ በቆየ የፍርድ ቤት ክርክር ከፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት እስከ ሰበር ሰሚ ይዞታው ለቤተክርስቲያኗ ተፈረደ ይህን ተከትሎ አዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ባለ አደራ  ካቢኔ ከይዞታዋ ላይ በአውደ ምህረቱ ትክክል 7000 ካሬ ሜትር ለግዮን ጋዝ ኃ.የተ.የግ ማኅበር በሊዝ ሸጠው ይህንን ሁሉ ችግር እያለ በሰንበቴ ሽፋን የገቡ 7 ሰንበቴዎች እያንዳንዳቸው ከ1000 ካሬ ሜትር በላይ ቦታ በመያዝ ከዚያው ከቤተክርስቲያኑ በወጣ የድንጋይ ማእድን ትልልቅ አዳራሾችና የቀብር ፉካ በመገንባት የይዞታ ተቀናቃኝ ሆኑ፡፡ (ይህ ቦታ አሁን ባለው የሊዝ ዋጋ ከ850 ሚሊዮን ብር በላይ ይገመታል ) ለእነዚሁ ሰንበቴዎች ቦታውን ከፋፍሎ በመስጠት ጉልህ ስፍራ የነበረው ወልዴ የሺጥላ የተባለው የህንጻ ኮሚቴ ሊቀ መንበር ሲሆን ኤርትራዊው ፎርማን አቶ ጸሐዬ እራሱን ኢንጂነር ብሎ በመጥራት ልኬቱን አከናውኗል፡፡ አቶ ወልዴ የህንጻ ሊቀ መንበር ሆኖ ቤተክርስቲያኗ ላይ ሲያዝና ሲናዝዝ ኖረ ቀድሞ የቴሌ ጉርድ ሾላ ቅርንጫፍ ሥራ አስኪያጅ ሲሆን በአሁኑ ወቅት በቂ የትምህርት ዝግጅት ስለሌለው አለኝ ብሎ ባቀረበው ሰርተፍኬት በሽያጭ ሰራተኝነት ተመድቦ ኮተቤ ቅርንጫፍ የሚሰራ ግለሰብ ነው ይህ ግለሰብ  ለሰንበቴ ቦታ አከፋፍሎ ሲጨርስ ለእሱና ለሚስቱ ማረፊያ የሚሆን ዘመናዊ ሰርቪስ ቤት እና 26 የቀብር ፉካ ለቤተክርስቲያኑ ሕንጻ ማሰሪያ ከመጣው ሲሚንቶና አሸዋ  በመገንባት የፉካ ንግዱን ተቀላቀለ፡፡ 


ዛሬ ወልዴ ቅዳሴ የሚያስቀድሰው በቤተክርስቲያኒቱ  ቤተልሔም ጎን በሰራው ሰርቪስ ሳሎን ሶፋ ላይ ጋደም ብሎ ሲሆን መሸት ሲል ደግሞ አየር ለመቀበል ወደ መኝታ ቤት ይገባል፡፡ ለቤተክርስቲያን መላ ዘመናቸውን የደከሙ የቀድሞ ነገስታት እንኳ ያላደረጉትን ድፍረት በመድፈር በቅድስት ቤተክርስቲያን ውስጥ ለራሱ መኖሪያ የሰራ በ 21 ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ከእሱ ሌላ መገኘቱን እጠራጠራለሁ፡፡ ሕንጻው ከተመረቀ ከ 6  ዓመታት በላይ አንዳች የልማት ተግባር ሳያከናውን በሊቀ መንበርነት ሕንጻ ኮሚቴ ብሎ የሰየመውን የቤተክርስቲያኗን ሐብት የሚዘርፍበት ኮሚቴ   ከመሰሎቹ ጋር ቤተክርስቲያኗን በአጽሟ አስክትቀር ድረስ ከዘረፋት በኋላ በዚያ ገንዘብ አያት ግቢ ውስጥ ዘመናዊ ባለ ሁለት ፎቅ መኖሪያውን ገዝቶ የቀድሞ ቤቱን አከራይቶ ሲኖር ንቡረ እድ ኤልያስ አብርሃ በነባሩ ሰበካ ጉባዔ አባላት በቀረበላቸው ጥቆማ ቀደም ሲል ጀምሮ ሲፈርምበት ለነበረው ባንክ እግድ በመጻፍ ቋሚ የዘረፋ ገቢውን እንዲቆም አደረጉ፡፡ በወቅቱ የነበረው ሰበካ ጉባዔም ያላለቀውን ቤተክርስቲያን ለማስፈጸም ጥረት ያደረገ ሲሆን ቀድሞ ኮሚሽን የተቀበለባቸውን የሥዕል ሥራ ለሌላ ባለሙያ በመስጠት እንዲጠናቀቅ ከማድረጉም በላይ አጥር የሌላትን ቤተክርስቲያን በአጥር እንድትከበር፤ ዶሙ ዝናብ ያስገባ የነበረውን ሕንጻ 4 ዶሞች አሉሚኒየም በማልበስ ዘመናዊ መጠለያ በመስራት ለካቴድራሉ አቋቋምና ዜማ ትምህርት ቤት የተማሪዎች መኖሪያ የአረንጓዴ አጸዶች ሥራ የመጠለያ ግንባታ እና ወደ ካቴድራሉ በ 3 አቅጣጫ የሚያስገቡ ዘመናዊ ኮብል ስቶን መንገዶችና ሌሎችም  ሥራ ሰርቷል፡፡ የቤተክርስትያኑ አስተዳዳሪ እና የሥራ ባልደረቦቻቸው ለረጅም ዘመን በጭቅጭቅ የቆየውን ይህንን ቦታ በካርታ ለማስከበር ከፍተኛ መስዋእትነት ከፍለው 200.000.00 ካሬ ሜትሩን የሚያረጋግጥ ካርታ ተቀብለውበታል፡፡ በቀጣይ ሰንበቴዎቹ ያለ ከልካይ የሚያደርጉትን ሕገ ወጥ ተግባር ሥርዓት ለማስያዝ በወቅቱ ፓትርያርክ አቡነ ጳውሎስን በመውሰድ የሰንበቴዎቹን ይዞታና ሕገ ወጥ ድርጊት አሳይቷቸዋል፡፡ ቅዱስነታቸውም እንባ እየተናነቃቸው በንዴት ከግቢው እንደወጡ ይዞታውን የወሰዱና ተከራክረው በፍርድ ቤት የተረቱ 13 ሰራተኞች ከቦታው እንዲነሱ በማድረግ ሰንበቴዎቹ ላይ ሕግ እንዲወጣ መመሪያ ሰጡ፡፡
-    ሰንበቴ ማኅበራቱ በካቴድራሉ ግቢ ሚገኘውን የድንጋይ ማእድን እንደፈለጉ   አስፈልጠው በመሸጥ ከፍተኛ ገንዘብ በመሰብሰባቸው፡፡
-    ያለ ፈቃድ በገነቧቸው ሰፋፊ አዳራሾች ውስጥ በኪራይ ኗሪዎችን በማፈራቸው
-    ያለ ቁጥጥር በሚሸጡት ፉካ ከፍተኛ ገቢ በማግኘታቸው
-    በአዳራሾቹ ያልተፈቀዱ ፖለቲካ ስብሰባ በማካሄዳቸው
-    ቤተክርስቲያኗን ሥርዓት በመጣስ በቅዳሴ ሰዓት ግቢን በ40 እና 80 ቀን መታሰቢያ ድግሶች ከድርገት በፊት ምግብ እንዲበላ በማድረጋቸው፡፡
-    ባልተፈቀደ የንግድ ተግባር በመሰማራታቸው
-    በሕገ ወጥ መልኩ ቦታ በመውረር ለብዙኃኑ ጥቅም መስጠት የሚገባውን ቦታ ለግል ጥቅም በማዋላቸው
-    ከቀብር የሚያገኙትን ገንዘብ በሕይወት መድን ዋስትና ዓይነት ለአባላት በጥሬ ገንዘብ የሚከፍሉ በመሆናቸው፡
-    ሁሉን እምነት ያቀፍን ነን ለማለት ወደ በጎ አድራጎት ማኅበርነት ለመቀየር በመንቀሳቀሳቸው፡፡
-    ዛሬም ማንነታቸው በውል የማይታወቅ በወንጀል ጭምር የተገደሉ ሰዎች ከተለመደው የጥቁር አንበሳ መዝገበ ሙታን ውጪ ሳይመዘግቡ የሚቀብሩ መሆናቸው፡
-    በጥበቃ ስም ባስገቡዋቸው ግልሰቦች ምክንያት ቤተክርስቲያን ውስጥ ከፍተኛ ወንጀል እንዲፈጸም የሚያደርጉ በመሆናቸው፡፡
ነበር ሕግ ያስፈለጋቸው፡፡
ነገር ግን ይህን ቤተክርስቲያን ዓመታት ብቻ 10 አለቆች ተደብድበው የተባረሩ ሲሆን ሊቀ ጉባዔ ኤርሚያስ ወልደኢየሱስ፣ መላከ ሰላም ዘለዓለም እሰይ እና መልአከ ሣህል አወቀ ተጠቃሽ አስተዳዳሪዎች ናቸው፡፡
እነዚህ ሰንበቴ ማኅበራት መካከል ዋነኛው የመድኃኔዓለም ሰንበቴ ማኅበር ሊቀ መንበር የደርግ የፖለቲካ ትምህርት ቤት መምህር የመቶ አለቃ አባቡ መሰል የደርግ ዘመን ጓደኞቹን በመጥራት ጥቅማቸውን ለማስቀጠል በቡድን ተደራጁ እዚህ ቡድን ውስጥ የሴት ሰባኪ ሆነችውና ሕጋዊ ባሏንና ሥራዋን ጥላ ከእድሜ አባቶቿ ጋር  በካቴድራሉ ግቢ የቀን ቀን ኑሮዋን የመሰረትችው ቅድስት አሳልፍ ስትገኝበት የቀድሞ የደርግ የምስራቅ ጎጃም አስተዳዳሪውና በቅርቡ ከእስር ተፈታው ስመ ገናናው አንሙት ክንዴ የቀድሞ የደርግ የቀጠና  2 አስተዳዳሪና የአንሙት ክንዴ ዘመድ አስማረ ዋሴ በ1997 ምርጫ የቅንጅት ፓርቲ የወረዳ ኃላፊ ሙሉ በለጠ በቀድሞ መንግሥት ካድሬ አብቡ ታከለው በመሪነት የተሳተፉበት እና ሌሎችም በመንግሥት ላይ ያኮረፉ አብዮታዊ ጡረተኞች ያሉበት ሲሆን በቤተክርስቲያኗ የተዘጋጀውንና ካለ ቤተክርስቲያኗ ፈቃድ ቀብር እንዳይፈጸም፣ በሰንበቴ አዳራሾቹ በካቴድራሉ ግቢ በጥበቃና በጽዳት ስም የሚያኖሩዋቸውን ተዋልደው በካቴድራሉ ውስጥ መንደር የመሠረቱ ግለሰቦችን  በማስወጣት በቤተክርስቲያኗ ሃይማኖታዊ ተቋም ባቻ ሆና እንድትቀጥል፡፡ መናፍቃንን በ70 ሺ ብር መቅበር እንዲቀር፣ የቤተክርስቲያኗን የድንጋይ ማእድን መሸጥ እንዲቆም የሚያዘውን ሕግ እንደማይቀበሉ አስታወቁ፡፡ ጉዳዩ ወደ ፍርድ ቤት ሲያመራ እነዚሁ ቀድሞ መንግሥት መኮንኖችና መናፍቃን ይዦታው የቤተክርስቲያኗ አይደለም በማለት መቃወሚያ አቀረቡ፡፡ ዳኛው እነዚህን ቡድኖች አንድ ጥያቄ ጠየቁ ለመሆኑ ቀብር ትፈጽማላችሁ ሲሉ “አዎ ” አሉ የሰንበቴ ቡድኖች ታድያ ቤ/ክ ግቢ አይደለንም ካላችሁ ቀብር የምትፈጽሙት መንገድ ላይ ነው መልስ አልነበራቸውም ፍርድ ቤቱ ቤተክርስቲያኗ በራሷ ሕግና ሥርዓት አደብ ታስገባቸው ሲል ሥልጣኑን ለቤተክርስቲያኗ ሰጠ፡፡ እስከ ሰበር በደረሰው የፍርድ ሂደት ይኸው ውሳኔ ጸና፡፡ እነ አቶ ወልዴ በዚህ ወቅት አማራጭ ያደረጉት ሟቹን ፓትርያርክ በሚያውቋቸው ሰዎች ማግባባት ነበር፡፡ እናም ፓትርያርኩን የሚያውቁ ግለሰቦችና ባለሥልጣናትን ይዘው ገብተው ፉካ መነገዳቸው ቤተክርስቲያኗን እንደማይጎዳ እና ለማስፋፊያ ቦታ እንዲጨምሩላቸው አነጋገሯቸው ፓትርያርኩም ‹‹የሥራ ተነሳሽነታችሁ መልካም ነው ነገር ግን ይህንን የቢዝነስ ሐሳባችሁን ወደ መንግሥት ውሰዱት በጠቃቅንና አነስተኛ ተደራጅታችሁ ብትሞክሩት ይሻላል እኔ የምላችሁ ይህንን ነው›› በማለት መለሱላቸው ሕጉ ይጎዳናል በማለት ቅሬታቸውን ለወቅቱ ጳጳስ ለአቡነ ቀውስጦስ አቀረቡ አቡኑም እኔ የቤተክርስቲያን ይዞታ ልጠብቅ እንጂ ልሸጥ አልመጣሁም አሏቸው፡፡ ጉዳዩ እልባት ሳያገኝ ፓትርያርኩን አረፍተ ዘመን ገታቸው አቡነ ዳንኤልም የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ሆኑ ሥራ አስኪያጃቸው ሊቀ ኅሩያን ሰርጸ ጋር በመሆን ጉዳዩ ለሀገረ ስብከቱ አስተዳደር ጉባዔ ቀረበ ጉባዔውም በሰንበቴ ስም ተደራጅቶ መነገድ አግባብ አይደለም ቤተክርስቲያኗም በይዞታዋ ተጠቃሚ መሆን አለባት ቀብር መፈጸምም የሰንበቴ ድርሻ ተግባር አይደለም በማለት አስተዳደራዊ ውሳኔ ሰጥቶ ለሰንበቴዎቹ መተዳደሪያ ሕግና መመሪያ አውጥቶ ላከ፡፡ በካቴድራሉ ከሚገኙ 11 ሰንበቴ ማኅበራት 5 የሚሆኑት ሕጉን ተቀብለናል ሲሉ ለሀገረ ስብከቱ አስታወቁ 7 የቀድሞ መንግሥት ወታደሮች የሚመሯቸው  ሰንበቴዎች ግን የሥራ ጊዜውን በጨረሰው የሰበካ ጉባዔ ምትክ ምርጫ እንዲደረግና እነሱ በምርጫው ሊቃነ መናብርቶቻቸውን በማስመረጥ ሕጉ ተግባራዊ እንዳይሆን ለማድረግ ምርጫ ይደረግ ሲሊ ለአዲስ የአቡነ እስጢፋኖስ አስተዳደር አቤት አሉ ፡፡ አቡነ እስጢፋኖስና ሥራ አስኪያጃቸው መጋቤ ሐዲስ ይልማ ቸርነት እንዲሁም የእሳቸው አስተዳደር ጉባዔ ከመከረ በኋላ ቀደም ሲል በአቡነ ዳንኤል የሚመራው ጉባዔ ያሳለፈውን ውሳኔ መልሶ በማጽደቅ ሰንበቴዎቹ በ 70 ሺህ ብር ለኢ አማንየን በ50 ሺ ብር ከውጭ ለሚመጣ አስክሬን በ 35 ሺህ ብር ለሀገር ውስጥ የሚሸጡትን ፉካ ንግድ እንዲያቆሙ ለተለያዩ የፖለቲካ ስብሰባዎች፣ ለሰርጋና ለቅሶ አዳራሽ በማከራየት መነገዳቸው እንዲያቆሙ አዘዘ፡፡
አዲሱ ፓትርያርክ ብፁዕ አቡነ ማትያስ በቦታው ተገኝተው የሰንበቴ ማኅበራቱ (አክሲዮን ማኅበራቱ) ሕንጻ እና ሕገ ወጥ የቀብር ሥፍራ ከተመለከቱ ባኋላ ባስተላለፉት መመሪያ ይህ ቦታ የቤተክርስቲያን ብቻ ነው ማንም አለአግባብ ሊጠቀምበት አይገባም ሲሉ መልእክት አስተላልፈዋል፡፡
ጠቅላይ ቤተክህነት በዋና ስራ አስኪያጁ በብፁዕ አቡነ ማቴዎስ በቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ አቡነ ሉቃስ አማካኝነት በሰንበቴ ማኅበራቱ የካቴድራሉን ይዞታ ለመንጠቅ ክስ የመሰረተ ግለሰቦች በተመራጭነት እንዳይሳተፉ መመሪያ አስተላለፉ ፡፡ በዚህ ሁኔታ የአጥቢያው ሰንበት ትምህርት ቤት በሰራው ከፍተኛ ቅስቀሳ ብዙ መራጭ የእነዚህን ነጋዴ ሽማግሌዎች ሐሳብ በመረዳት በተጻራሪነት በምርጫው ስፍራ ተገኘ፡፡ ከሰንበቴዎቹ ጋር በመሆን በእብነበረድ ሽያጭ የተሰማራ እና የደህንነት አባል ነኝ በማለት ጳጳሳቱን ጭምር የሚያስፈራራቸው አለማየሁ ከልል የተባለ ግለሰብም ከደህንነት ተወክያለሁ በማለት ምርጫው ውስጥ የሚሳተፉ ግለሰቦችን ስም ዝርዝር አዘጋጅቶ በስፍራው ተገኘ፡፡ ምርጫው በቤተክህነቱ ቀላል ግምት ስላልተሰጠው መስከረም 8 ቀን ብፁዕ አቡነ ሉቃስ ብፁዕ አቡነ ማቴዎስ ብፁዕ አቡነ እስጢፋኖስ በስፍራው ተገኙ የሀገረ ስብከቱ ሁሉም የመምሪያ ኃለፊዎችም በእለቱ በአውደ ምህረቱ ተሰየሙ በፉካ ንግድ የተሰማሩት ግለሰቦች አመጽና አድማ በመፍራት የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አባላት ስፍራው ላይ በተጠንቀቅ ቆሙ፡፡ ነጋዴዎቹ አበል ከፍለው ያመጡት ሕዝብ በቁጥር አንሶ ለቤተክርስቲያን የቆመው ወጣት ቁጥሩ በልጦ ሲያዩ ምርጫውን መበጥበጣቸው አልቀረም ነገር ግን ጳጳሳቱ እምነታቸው ዘብ ቆመው ዋሉ፡፡ በዚህ ሁናቴ ምርጫው በሰላም መካሄዱን ሲመለከቱ ብዙዎቹ የተቃዋሚ ሰንበቴ አመራሮች ምርጫውን ረግጠው ወጡ፡፡ መናፍቋ ቅድስት አሳልፍ ብፁዕ አቡነ እስጢፋኖስን ‹‹ገዝቼዎታለሁ ›› በማለት ኦፈ ግዝት እርግማን አወረደች፡፡ እሳቸውም ገዘተው አወገዟት፡፡ ምርጫውም በሰላም ተጠናቆ አዲስ አመራር ቤተክርስቲያኗና የእነዚህን ነውጠኛ ቡድኖች መካል ተመረጠ፡፡ ማንኛውም የቤተክርስቲያን አካል እነዚህን ቡድኖች በመፍራት ወደ ሰአሊተ ምህረት ቅ/ማርያም ካቴድራል ለመዛወር ፈቃደኛ አይደለም፡፡ ከመንግሥት የጸጥታ አካላት በላይ የሚፈሩ ቤተክህነቱን እንደ እንስራ ውሃ ባሻቸው ጊዜ እያንቦጫቦጩት 2 ፓትርያርኮች 3 ሊቃነ ጳጳሳትና 3 ሥራ አስኪያጆችን ሲሻቸው እጠሳደቡና እያስፈራሩ ዛሬ ላይ ደርሰዋል፡፡
አሁንም እነዚህ ቤተክርስቲያን ብር ከልዩ ልዩ የቢራ አምራች አክስዮን ማኅበራት ከፍተኛ አክስዮን በሚገዙ በቤተክርስቲያን ብር ለኃጢአት ተግባር  ገንዘብ ከሚመድቡ እድሜ ያላስተማራቸው ግለሰቦች ቤተክርስቲያኗን እየበጠበጡዋት ይገኛሉ፡፡ ቤተክርስቲያኑንም የሚመራው አካል አንድ ዘላቂ እርምጃ ካልወሰደ በተደጋጋሚ እንደሚዝቱትና በተግባርም እንደሚሞክሩት ገለልተኛ ቤተክርስቲያን በሚል ሕዝበ ክርስቲያኑን መክፈላቸውና ቋመጡለትንና ለዘመናት ያልተሳካላቸውን  የፖለቲካ ሥራ በድብቅ ለማካሄድ በሚፈጥሩት ችግር ቤተክርስቲያኗ የሰላም ስፍራነቷን ማጣት የለባትም፡፡ እነሱም ካለፈው የስህተት ዘመናቸው በመነሳት ይህ ወቅት የንስሀ ሊሆንላቸው ይገባ ነበር፡፡ ዛሬም ቤተክርስቲያን ውስጥ ባሉት አንዳንድ ደላሎች አማካኝነት ወልዴ የምሸጠው 5 ፉካ አለና ሰዎች በሕይወት እያሉ ይጫረቱ በማለት የግለሰቦችን ገንዘብ እየሰበሰበ ይገኛል፡፡ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የጥቅምቱ ሲኖዶሰ በወሰነው መሠረት የነጋዴ ሰንበቴ ማኅበራት ጉዳይ እልባት ይሰጠው፡፡ መንግሥትም እነዚህን ድብቅ የፖለቲካ ኃይሎች ሕጋዊ እርምጃ በመውሰድ ምነው በእንቁላሉ የሚሉበትን ጊዜ ሊያቀርብ ይገባል፡፡

Sunday, January 5, 2014

የምስካየ ኅዙናን መድኃኔዓለም ገዳም ሰራተኞች አስተዳደሩን አማረሩ


 (የጽሁፍ ምንጭ፤ አዲስ አድማስ )
በገዳሙ እንክብካቤ እንጂ ጭቆናና እንግልት የለም /የገዳሙ አስተዳደር/
የምስካየ ህዙናን መድሀኒያለም ገዳም ሰራተኞች በቤተ - ክርስቲያኑ አስተዳደር ከፍተኛ ጭቆናና በደል እንደሚደርስባቸው ተናገሩ፡፡ የቤተክርስቲያኑ አስተዳዳሪ መላዕከ ገነት አባተክልማርያም አምኜ የገዳሙን ሰራተኛየ ሚያስተዳድሩት እንደመፈንሳዊ አባት ሳይሆን እንደ አምባገነን መሪ ነው ሲሉ ሰራተኞቹ አማረዋል የቤተክርስቲያኑ አስተዳዳሪ አባ ተ/ማርያም አምኜ በበኩላቸው በቤተክርስቲያኒቱ ሁሉም ስርዓትና ደንብን ተከትሎ እንጂ ያለ አግባብ የሚንገላታም የሚጨቆንም የለም ሲሉ መልሰዋል፡፡ “ቤተክርስቲያኑ የሚመራው በፓትሪያርኩ ነው” ያሉት ቅሬታ አቅራቢዎቹ የደሞዝ ማነስን ተከትሎ እንዲያነጋግሩን አባ ተክለ ማርያምን ለስብሰባ ጠርተን እግረ መንገዳችንን የገዳሙን የመልካም አስተዳደር ችግር፣ እርሳቸው ያለ አግባብ የሚሰሯቸውን ስራዎች፣ እና አጠቃላይ ያለውን ችግር አስረዳናቸው ይላሉ ቅሬታ አቅራቢዎቹ፡፡
ይሁን እንጂ ለምን አካሄደን ተቃወማችሁ በሚል በግል እየጠሩ ማስፈራሪያና ዛቻ ያቀርቡብናል ለአንዳንዶቻችን ያለ አግባብ የማስጠንቀቂያ ደብዳቤ ተፅፎብናል ብዙዎችም ከስራ ተባረዋል ብለዋል የገዳሙ ሰራተኞች፡፡ አስተዳዳሪው ወደ ገዳሙ ተሹመው ከመጠ አንድ አመት ከስድስት ወር ቢሆናቸውም እስከዛሬ በቤተክርስቲያኑ አንድም ልማት እንዳላካሄዱ የገለፁት ቅሬታ አቅቢዎቹ ችግር አለ ይስተካከል በማለት ቅሬታ የሚያርበውን ሁሉ እንደጠላት በማየት ሊመደብ ወደማይገባው ቦታ ይመድባሉ፣ ከደረጃ ዝቅ ያደርጋሉም ብለዋል፡፡ ቤተክርስቲያኒቷ ያለ አግባብ እየተመራች ነው ሰራተኞቹ እየተንገላቱ ነው በሚል ቅሬታ ያቀረበውና የቤ/ክርስቲያኑ ጉዳይ አስፈፃሚ የነበረውን መምህር ሰለሞን ተስፋዬን ከስራው አንስተው ሙያው ወደማይፈቅደው የገዳሙ ክሊኒክ እንደመደቡትና በዚህም ለገዳሙ የቦርድ ሊቀመንበር አመልክቶ ጉዳዩ እየታየ ባለበት ከስራ እንዳባረሩት ቅሬታ አቅራቢዎቹ ተናግረዋል፡፡
የቤተክርስቲያኑ አስተዳዳሪ አባ ተክለማሪያም በጉዳዩ ዙሪያ ተጠይቀው ሲመልሱም ሰራተኞቹ የደሞዝ ጥያቄ ባነሱ ጊዜ ባለፈው ሀምሌ ጨምረናልም ምግብ መጠለያና ሁሉን አሟልተን ይዘናችሁ እንዴት አሁን የጭማሪ ጥያቄ ታነሳላችሁ ብለናቸዋል ይላሉ፡፡ የመምህር ሰለሞንንን ከስራ መባረር በተመለከተም “ወደ ክሊኒኩ ያዛወርነው በእድገትና በሁለት እርከን የደሞዝ ጭማሪ ነው” ያሉት አስተዳዳሪው ጉዳዩን አምኖበት ስራውን ከተረከበ በኋላ ማንም ሳያውቅ ዘግቶ በመጥፋቱ ሊሰናበት ችሏል ብለዋል፡፡ ማስጠንቀቂያውን በተመለከተ ለአንድ ሰራተኛ መስጠቱን አምነው “ቤተክርስቲያኗ ሲኦል ናት” በሚል ለተናገረው ንግግር ማስጠንቀቂያ መስጠታቸውን ተናግረዋል፡፡ የገዳሙ ክሊኒክ መካከለኛ ሆኖ ሳለ አልትራ ሳውንድ ይጠቀማሉ፡፡ ይህ ክልክል ነው በሚል ቅሬታ አቅራቢዎቹ የተናገሩ ሲሆን “በፊት እንጠቀም ነበር አሁን ተከልክለን አቁመናል” ብለዋል አባ ተክለማሪያም አምኜ፡፡ “የቤተክርስቲያኗን ስም ለማጥፋት የሚንቀሳቀሱ ሀይሎች እንዳሉ እናውቃለን” ያሉት አስተዳዳሪው በገዳሙ ያሉ እስረኞች በእንክብካቤ ተያዙ እንጂ በአንዳቸውም ላይ ጭቆናና እንግልት አላደረስንም ብለዋል፡፡