Tuesday, April 30, 2013

አባ አብርሃም በአሜሪካ ያለውን የሀገረ ስብከት ጽ/ቤት እንዲያስረክቡ ቋሚ ሲኖዶሱ ወሰነ


http://awdemihreet.blogspot.com/) በማኅበረ ቅዱሳን አይዞህ ባይነት የአሜሪካውን ሃገረ ስብከት /ቤት ለብጹዕ አቡነ ፋኑኤል አላስረክብም ብለው የነበሩት አባ አብርሃም የሀገረ ስብከቱን /ቤት እንዲያስረክቡ ቋሚ ሲኖዶሱ ወሰነ፡፡ ይህ በቅዱስ ፓትርያርክ አቡነ ማትያስ ፊርማ የወጣው እና አድራሻውን ለአባ አብርሃም ያደረገው ደብዳቤ እንዳስታወቀው አባ አብርሃም ሀገረ ስብከቱን በዝውውር ለቀው ከወጡ በኃላ የሀገረ ስብከቱን /ቤት አላስረክብም ማለታቸው ህገ ወጥ ድርጊት ነው፡፡
አባ አብርሃም ቤተክርሰቲያን አንዲት መሆንዋን መረዳት ከብዷቸው እና እሳቸውን ለማዘዝ ሙሉ ስልጣን ያለውን ቅዱስ ሲኖዶስ ተጋፍተው ላለፉት ሁለት አመታት የሀገረ ስብከቱን /ቤት አላስረክብም በማለት በሀገረ ስብከቱ ውስጥ የሽፍታ ሠራዊት ማስፈራቸው አስገራሚ ሆኖ ሰንብቷል፡፡ እኚህ ጉድ አያልቅበት የሆኑት ጳጳስ መንፈሳዊ አገልግሎት የሚሳካው እሺ ብሎ በመታዘዝ መሆኑ ከዲቁና እስከ ጵጵስና ድረስ አለመረዳታቸው በብዙዎች ዘንድ የሚያስተዛዝብ ሆኗል፡፡

Monday, April 29, 2013

ወድቆም ያፈራል


Wedkom Yaferal Read in pdf

የዲያቆን አሸናፊ መኰንን ገጽ ዓርብ ሚያዝያ 18/2005 ዓ.ም.
ከጸሎት ክፍሎች አንዱ ስእለት ነው፡፡ ስእለት ለእግዚአብሔር የምንገባው ቃል ነው፣ እግዚአብሔርም የሚጠብቀው ብርቱ ነገር ነው /መክ. 5፡4-5/፡፡ በተሳልንበት ግለት እንድንፈጽመው ይጠበቅብናል፡፡ ስእለት ለእግዚአብሔር አመጣለሁ የምንለው የምስጋና መግለጫ ነው፡፡ አንዳንዶች ገንዘባቸውን፣ ሌሎች ሕይወታቸውን፣ የቀሩት ልጆቻቸውን፣ ውስኖች የሰጣቸውን ለእርሱ ለመስጠት ስእለት ይገባሉ፡፡ ስእለት መሳል ፈቃድ ነው፣ አለመፈጸም ግን ትልቅ ኃጢአት ነው፡፡ ሰው እግዚአብሔርን እንዴት ይዋሸዋል?
ስእለት እግዚአብሔር ስላደረገልን ነገር የምስጋና መግለጫ ይዘን የምንመጣበት ነው፡፡ ስእለት የውለታው ምላሽ ሳይሆን የውለታው መታሰቢያ ነው ብንል ይገልጸዋል፡፡ በብዙ ጭንቀቶች ባለፍኩባቸው ዘመናት ሁሉ ስእለትን ለእግዚአብሔር እሳላለሁ፡፡ እነዚያን የከበዱኝን ወራቶች ሳስብ መከራው ከባድ ሆኖ ነው ወይስ እኔ ደካማ ሆኜ ነው? የሚለውን እስካሁን ልመልሰው አልቻልኩም፡፡ ብዙ የሀዘንና የስብራት ዘመኖችን እግዚአብሔር አሻግሮኛል፡፡ እንደ ፈቃዱም መልስ ሰጥቶኛል፡፡ እንደ ፈቃዱ ከልክሎኛል፣ እንደ ፈቃዱ ባርኮኛል፡፡

Sunday, April 28, 2013

የአሜሪካው ሲኖዶስ ስለተፈናቀሉ ዜጎች መግለጫ አወጣ



ቅዱስ ሲኖዶስ
The Holy Synod
4127 Redwood
Oakland, CA 94610
በአገራችን በኢትዮጵያ በአማርኛ ተናጋሪ ወገኖቻችን ላይ እየተካሄደ ያለውን የዘር ማጽዳትና ማጥፋት ዘመቻ አስመልክቶ ከሕጋዊው ቅዱስ ሲኖዶስ የቀረበ ጥሪ
ሚያዚያ ፲፬ ቀን ፪ ሺ ፭ ዓ.ም"
እግዚአብሔር እንዲህ ይላል።የዋይታና የመራራ ልቅሶድምፅ በራማ ተሰማ፤ራሔል ስለ ልጆችዋ  አለቀሰች፤የሉምና ስለ ልጆችዋ መጽናናትን እንቢ አለች። " ኤር 31 ፡16
የተወደዳችሁ በአገራችን በኢትዮጵያ እና በመላው ዓለም ተበትናችሁ የምትገኙ ኢትዮጵያውያን ወገኖቻችን፤

ሙሉውን ጽሁፍ ለማንበብ እዚህ ይጫኑ  ( Click here )

Saturday, April 27, 2013

በአካፋ የሚዛቀውን ሳይጨምር የ71 ሺህ ብር የወር ደመወዝተኛ ሐዋርያ/ፓስተር/ በኢትዮጵያ? ይቺ ናት ጫወታ!!


በእንግሊዝኛ የአማርኛው ስም «ቸርች» ተብለው ከሚጠሩት ባንዱ የተፈጸመ ድርጊትና እሮሮ ነው።  ምሬት የበዛበት ይህ ሰው «ሐዋርያዬ» በሚለው የዘመኑ ሰው የደረሰበትን ሰቆቃ ሲያሰማ አገኘነውና ራሳቸውን የክርስቶስ ባለሟል አድርገው እውቀት የጎደለውን ሰብስበው እንዴት እንደሚያጃጅሉ ከማሳየቱም በላይ በግራም በቀኝም በክርስቶስ ስም የሚፈጸመውን ዐመጻ ልናካፍላችሁ ወደድን። በወዲህ ሰባኬ ወንጌልና ማኅበር፤ በወዲያ ደግሞ ሐዋርያና ፓስተር ገንዘብ አምላካቸውን ይነግዳሉ።  ከረጅሙ ትርክት ውስጥ ቆንጥረን አቀረብን።
የጽሁፉ ባለቤት ኢዮብ ደምሴ ነው።
ይሄን ጽሑፍ ለምታነቡ ወገኖች ልጠይቅ የምፈልገው ነገር፣
1ኛ. “መልሱኝ” ብዬ ያልጠየቅሁና በብዙ ውትወታና ንግግር ቤተ ክርስቲያን ጥሪ ያደረገችልኝ ሆኖ ሳለ፣
2ኛ. በቤተ ክርስቲያኒቱን ባገለገልኩበት ጊዜ ሁሉ በትጋት በማገልገሌ ውጤታማና ፍሬያማ መሆኔ በራሱ በሐዋርያው እጅ በምስጋና የተጻፈ ያማረ የመሸኛ ደብዳቤ ተሰጥቶኝ እያለ፣
3ኛ. የእረኞች አለቃ የሆነው ጌታ “ጠብቁልኝ” ያለውን መንጋ “ምስጢሩን አያውቅም” በሚል እሳቤ ብቻ፣ በሐሰት ንግግር በማሳሳት ለተሳሳተ ዓላማ እንዲሰለፉ እንዳደረገው ሳይሆን፣ መንጋው እንዳያዝንና እንዳይበተን፣ በመጠንቀቅ ከቤተ ክርስቲያኒቱ አገልግሎት ካቆምኩበት ጊዜ ጀምሮ ራሱን በአደባባይ እስከገለጠበት ጊዜ ድረስ የማውቀውን የሐዋርያውን ችግር በአመራር ክፍሉ ብቻ እንዲያልቅ በምስጢር ይዤ የቆየሁ መሆኔ እየታወቀ፣
4ኛ. እግዚአብሔር ሰፊ የአገልግሎት በር ከፍቶልኝ ከጌታ ምሕረት የተነሳ ተቀባይነትም ባገኘሁበት ጊዜ የተበላሸውንና የፈረሰውን ነገር መልሶ ለመገንባቱ ሥራ ራሴን መስጠቴ ስሕተቱ ምንድን ነው?

Friday, April 26, 2013

ማኅበረ ቅዱሳን እና የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ተሐድሶ ያስፈልጋታል የሚሉ ተሐድሶዎች!


ጽሁፍ፤ በተስፋ አዲስ (ይህ ጽሁፍ ከዚህ በፊት የቀረበ ነው)1
ክፍል አንድ
ተሐድሶዎች እነማን ናቸው?

ብዙ ጊዜ ቤተ ክርስቲያን ስሄድ የስብከት ካሴት ሳዳምጥ፤ የተለያዩ ሥነ ጽሑፎችን ሳነብ ፡ተሃድሶዎች ተሐድሶዎች፡ የሚል ጩኸት እሰማለሁ። በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ሥር የተቋቋመው ማህበረ ቅዱሳን የሚባለው ድርጅት አባላቱም ሆኑ አመራሮቹ ስለተሃድሶዎች በስብከታቸው እና በጽሑፋቸው ሁሉ በቀጥታም ሆነ በተዛዋዋሪ ሳያነሱ አያልፉም።
እኔም ተሐድሶዎችን ለማወቅ ብዙ ጥረት አድርጌአለሁ። ምን ዓይነት አቋም እንዳልቸውና የት እንደሚገኙ፤ አላማቸው ምን እንደሆነ ለኢትዮጵያ ሕዝብ ማሳወቅ ፈለግሁ። እነርሱ ግን ተሃድሶ የሚለውን  ስም አይቀበሉትም።  እኔ ተሃድሶዎች ስል አንባቢ በሚገባው ቋንቋ ለመጠቀም እንዳሰብሁ ይረዳልኝ። ማህበረ ቅዱሳን የሚባለው ማህበርም ከተሐድሶዎች ጋር ያለውን ቅራኔ ለማቅረብ እሞክራለሁ። አንባቢ የራሱን ተቃውሞም ሆነ ድጋፍ እንዲሠጥ አንዳችም ሳልቀንስ እና ሳልጨምር ትክክለኛውን መረጃ ለማቅረብ እሞክራለሁ። መነሻየ ግን ከማህበረ ቅዱሳን እና ከተሐድሶዎች ሥነ ጽሑፎች ነው። የሁለቱንም ቡድን እንቅሥቃሴ በተከታታይ አቀርባለሁ መልካም ንባብ።
ተሀድሶ ማለት ይላሉ ቤተ ክርስቲያን መታደስ አለባት የሚሉ ወገኖች ማደስ፣ መጠገን፣ ማጽዳት፣ ማለት ነው ይላሉ።ለምሳሌ ቤት ከተሠራ በኋላ ሳይታደስ ብዙ ከቆየ ከጥቂት ጊዜ በኋላ ሊፈርስ ይችላል ስለዚህ ከመፍረሱ በፊት የሚደርግለት እንክብካቤ ቤቱን ያጸናዋል። እንደሸረሪት ድር፤ የጢስ ጠቀርሻ ያሉ ነገሮችም ከቤቱ ላይ ሊጠረጉ ይገባል። ማደስ ማለት ማፍረስ አይደለም በቤቱ ውስጥ ያለውን ቆሻሻ፤ ማስወገድ እና በፈረሰው በኩል መጠገን ነው በሌላ አነጋገር መሠረቱን ሳይነኩ እና ሳያናውጡ ጥንታዊነቱን እንደያዘ ቤቱን ማሳመር ማለት ነው።የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያንም ብዙ ዘመን ከመኖሯ የተነሣ ብዙ ስሕተቶች ይገኙባታልና መጽዳት አላባት፤ ባህሉን ከሃይማኖቱ፤ ውሸቱን ከእውነቱ፤ ክፉውን ከደጉ መለየት አለባት የሚል ራእይ ያላቸውና ለዚህ ሌት ተቀን ያለ እረፍት የሚሠሩ ናቸው።
የሚገኙት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ነው ጳጳሳት፤ ቀሳውስት፤ ዲያቆናት፤ መምህራን፤ የድጓ፤ የቅኔ የቅዳሴ መምህራን የሰንበት ተማሪዎች፤ እንዲሁም ምእመናን ሁሉ ያሉበት የአስተሳሰብ ኃይል ነው። የታወቀ ማህበር ግን የላቸውም። አንዳንዶች ማህበር መሥርተዋል ። ኑራቸው እና ሥራቸው በዚያው በቤተ ክርስቲያኒቱ ውስጥ ሲሆን በተለያየ ቦታ ጽ/ቤት እና በርካታ ማሰልጠኛዎች አሏቸው። በርካታ መነኮሳት እና ሰባኪዎች በነዚህ ቦታዎች ይሰለጥናሉ። ይህን ሁሉ እንቅሥቃሴ የሚያደርጉት ግን ቤተ ክህነቱ ሳይውቅ ነው። ቀሳውስቱ ስልጠናውን ከወሰዱ በኋላ በየቤተክርስቲያናቸው ሌሎች ቀሳውስት በመመልመል ያሰልጥናሉ። ከጳጳሳትም ውስጥ ለዚሁ ሥራ የሚውል በግላቸው ከፍተኛ እርዳታ ያደርጋሉ። ተሐድሶዎች ቤተ ክርስቲያኒቱ ውስጥ ቁልፍ ቦታና ስልጣን አላቸው። በተለይ በአሁኑ ሰዓት በየአብያተ ክርስቲያናቱ  ሚሊዮኖች በብዛት ይገኛሉ። በገጠር አጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት እና በገዳማት ሁሉ አሉ። ደሞዛቸውን የሚያገኙት ከዚያው ከቤተ ክርስቲያኒቱ ነው። ግን ከሌሎች የእምነት ድርጅቶችም እርዳታ ያገኛሉ ተብለው ይታማሉ። ተሐድሶዎች  እንደቀደምት ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ አማኞች እንጂ እራሳቸውን ተሃድሶ ብለው አይጠሩም።  ስማቸው በሥራቸው ምክንያት ከሚጠሏቸው ወገኖች የተሰጣቸው ነው። በቤተ ክርስቲያን ባሕላዊ ትምህርት ጥልቅ የሆነ ዕውቀት ያላቸው ስለሆኑ የቤተ ክርስቲያኒቱን ሁለንተና ደካማ ጎንም ሆነ ጠንካራ ጎን ለይተው የሚያውቁ ሊቃውንት ናቸው። የተሃድሶዎች እንቅሥቃሴ ከባድ እንቅሥቃሴ ነው ምክንያቱም እስከሞት ድረስ የቆረጡ ሲሆኑ ታላቅ ራዕይ ያላቸው ናቸው። በማኅበር መደራጀት ሳይሆን  በግል እያንዳንዱ አውቆ መስራት አለበት ስለሚሉ እዚህ ጋ ወይም እዚያ ጋር ናቸው ያሉት አይባልም። በአጭሩ የሌሉበት ቦታ የለም።
የማኅበረ ቅዱሳን ደጋፊ ነን የሚሉ ጳጳሳት ሳይቀሩ የዚህ ተሐድሶ የሚባለውን እንቅስቃሴ በስውር ይደግፋሉ። አሁን ባለው ሁኔታ ተሐድሶ የሚባሉት ክፍሎችን ከቤተክርስቲያኒቱ ማስወገድ በፍጹም አይቻልም። ከላይ እስከታች በተያያዘ ሰንሰለት የሚሰሩ ናቸው።

Wednesday, April 24, 2013

ንስሐ ለማን፤ ለምንና እንዴት?


 (ከዚህ በፊት የቀረበ ጽሁፍ ነው)

«ነስሑ እስመ ቀርበት መንግሥተ ሰማያት» (መንግሥተ ሰማያት ቀርባለችና ንስሐ ግቡ ማቴ ፫፤፩-፪)

«ነስሐ»  ስርወ ቃሉ እብራይስጥ ሲሆን ትርጉሙም አዘነ፤ ተጸጸተ፤ ተመለሰ፤ ክፉ ዐመሉን ተወ፤ መጥፎ ጠባዩን ለወጠ ማለት ነው። የግእዙም ግስ ይህንኑ ቃል እንዳለ ወርሶ ይጠቀምበታል።
«ነስሑ እምፍኖቶሙ እኩይ፤ ወእግዚአብሔርኒ ነስሐ እምዘነበበ» ይላል በዮናስ ፫፤፲ ላይ። ከክፉ መንገዳቸው ተመለሱ፤ እግዚአብሔርም በተናገረው ተጸጸተ»  እንደማለት ነው። ሰብአ ነነዌ ከኃጢአታቸው በንስሐ በተመለሱ ጊዜ እግዚአብሔርም ሊቀጣቸው በነበረው ፍርድ አዘነና ምህረትን ሰጣቸው። የእግዚአብሔር ሀዘን ከምህረቱ ሲሆን የሕዝቡ ሀዘን ደግሞ ከበደሉ ነው።       «ነስሐ» የሚለው ቃል በሁሉም ሥፍራ ማዘንን፤ መመለስን፤ መፀፀትን፤ መተውን ያመለክታል። «እግዚአብሔር ተፀፀተ» ስንል አምላካዊ ምሕረቱን ለመቀበል በማይፈልግ የሰው እልክኛ ልብ ወይም በሌላ መልኩ ምሕረቱን በሚጠይቅ ተነሳሒ ላይ ባለው አባታዊ ፍቅር እንጂ የሚጎድለው ወይም የሚጨመርለት ስላለ ያንን ከማጣትና ከማግኘት ጋር በተያያዘ አይደለም። ሰብአ ነነዌ ከተዘጋጀው ጥፋት ለመመለስ ንስሐ ሲገቡ እግዚአብሔርም በአምላካዊ ምህረቱ አዝኖላቸው ጥፋቱን መልሶላቸዋል። በሌላ ቦታም እንዲህ የሚል አለ።
በዘመነ ኖኅ የሰው ልጅ ዐመጻ በዝቶ የጥፋት ውሃ በታዘዘ ጊዜ «እግዚአብሔርም ሰውን በምድር ላይ በመፍጠሩ ተጸጸተ፥ በልቡም አዘነ» ዘፍ ፮፤፮ ይላል።
«ተጸጸተ» የሚለው ቃል «ነስሐ» የሚለው ቃል ትርጉም ነው። «እግዚአብሔር ተጸጸተ፤ አዘነ» ሲል ቀድሞ ያላወቀው ነገር በመድረሱ ወይም የማያውቀው ነገር እንደተከሰተ በማየቱ የተሰማው ስሜት ሳይሆን የሰው ልጅ ቀድሞ ከገነት ሕጉን አፍርሶ በመውደቁና ዳግመኛም በዚህ ምድር ላይ ኃጢአቱን እያበዛ በመሄዱ የተነሳ ሰው በራሱ በደል የሚመጣበት የፍርድ ቁጣ ስለሚያሳዝነው ብቻ ነው። ፻፳ የንስሐ ዘመንን ለመጠቀም ያልፈለገ ሕዝብ በውሃ ሰጥሞ ሲጠፋ ቢመለከት እግዚአብሔር መጸጸቱ አምላካዊ ባሕሪው ነው። እግዚአብሔር አባት በመሆኑ ሰዎች ይጠፉ ዘንድ ሳይፈልግ ዐመጻቸው ከሚያመጣባቸው ፍርድ የተነሳ ግን ያዝናል፤ ይጸጸታል።

Tuesday, April 23, 2013

እስልምና በኢትዮጵያ ታሪክ ( ክፍል ስድስት )

 ክፍል ስድስት (የጽሁፉ ባለቤቶች ለእስልምና መልስ አዘጋጅዎች ነው)
(www.answering-islam.org)

ሙሶሊኒና የሳውዲው የግመሎች ግዢ
 
በግንቦቱ ስምምነት መሰረት የሳውዲና የጣሊያኖች ግንኙነት በጣም እየተቀጣጠለ ሄደ፤ በዚያው ወር የጣሊያን ወኪል የሆነውና በጣሊያን የወታደራዊ ስለላ ውስጥ የሌተናንት ኮሎኔልነት ማዕረግ ያለውሴልሶ ዖዴሎባለቤቱና ሴት ልጃቸው ጅዳ ደረሱ፡፡ እርሱም እራሱን የተለያዩ የጣሊያን የንግድ ድርጅቶች ወኪል እንደሆነ አድርጎ አቀረበ፡፡ እርሱም ወዲያውኑ የጅዳ ሕይወት ማዕከል ሆነና ከምሁራን እንዲሁም ከያሲን ጋር ጥብቅ ወዳጅነትን መሰረተ፡፡ በሐምሌም ወር ዖዴሎና ያሲን በኤርትራ ውስጥ እየተከማቸ ላለው የጣሊያን ሰራዊት አስፈላጊ ስለሆኑት 12,000 ግመሎች ለጣሊያን የመግዛት ጉዳይ ላይ ውይይት አደረጉ፡፡ሴልሶ ዖዴሎምከመደበኛ ዋጋቸው ሦስት እጥፍ እንደሚከፍል ሐሳብን አቀረበ፡፡ ዓለም አቀፉ ውጥረት እየተፋፋመ ነበርና ሳውዲ አረቢያ ከመቼውም በላይ ከሙሶሊኒ ጋር ባደረገችው ድርድር ብሪቴንን የሚያስቆጣና በመካከላቸው ማለትም በብሪቴንና በጣሊያን ጦርነት ያስከትላል በማለት በጣም ተጨንቃለች፡፡ በዚህም ምክንያት ከሳውዲ የጦር ወታደር እንዳይመለመል አግዳለች፣ ይሁን እንጂ ሌሎች ነገሮች የምግብ ግዢዎችና ግመሎች ግዢዎች ላይ ምንም ችግር አልነበረም፡፡
በዖዴሎም አማካኝነት ለጣሊያኖች አትክልቶች ይሸጡላቸው ነበር፣ ምፅዋ ላይ በሚደርሱበት ጊዜ ከጥቅም ውጭ ይሆኑ የነበረ ቢሆንም፡፡ አሁን የጣሊያን ጦር መሳሪያዎች የሚፈልጉት ግመሎችን ነበር፤ ለጦርነት የሚደረገው ዝግጅት እንደቀጠለ ከባድ የሆኑ የጦር መሳሪያዎችን ማጓጓዝ በጣም ችግር እንደነበረ በጣም ግልፅ እየሆነ መጥቷል፡፡ በኢትዮጵያ ተራራዎች አካባቢዎች መሳሪያዎችን ለማጓጓዝና አስፈላጊ ነገሮችን ለማግኘት የጣሊያን ሰራዊት በግመሎች ላይ መደገፍ ነበረበት፡፡ በእርግጥ ጦርነቱ ከተጀመረ በኋላም እንኳን የተረጋገጠው ነገር የግመሎች አስፈላጊነት ነበር፡፡

Monday, April 22, 2013

«ኩሉ ዐረየ ወኅቡረ ዐለወ፤ አልቦ ዘይገብራ ለሠናይት፤ አልቦ ወኢአሐዱ»

ሰነፍ በልቡ። አምላክ የለም ይላል። ረከሱ በበደላቸውም ጐሰቈሉ በጎ ነገርን የሚያደርጋት የለም።
የሚያስተውል እግዚአብሔርንም የሚፈልግ እንዳለ ያይ ዘንድ እግዚአብሔር ከሰማይ የሰው ልጆችን ተመለከተ።
ሁሉ በደሉ፥ አብረውም ረከሱ አንድ ስንኳ በጎን ነገር የሚያደርጋት የለም።
ሕዝቤን እንጀራ እንደሚበላ የሚበሉ ግፍ አድራጊዎች ሁሉ አያውቁምን? እግዚአብሔርንም አይጠሩትም። መዝ ፶፫፤፩-፬

ማንም በማንም ኃጢአት አይጠየቅም። ማንም ራሱን ጻድቅ አድርጎ በሌላ ሰው ድካም መፍረድ አይገባውም። ይህ የእግዚአብሔር ቃል ለእውነተኛ ክርስቲያኖች የተሰጠ መመሪያ ነው። በትክክልም እንገነዘባለን። ይህን ማለት ግን መንጋውን ለመምራት ሥልጣንና አደራ ተረክበው፤ በሌላ መልኩም ከእግዚአብሔር ጋር ቃለ መሐላ በመፈጸም በጎችህን እንጠብቃለን ብለው አዋጅ ተናግረው ሲያበቁ በማጭበርበርና ወደ ሥርየት ከማቅረብ ይልቅ በጎቹን ኃጢአት በማስተማር የተካኑ፤ ቤቱን በማፍረስ የተሠማሩ የዐመጻና የየበደል ማኅደሮችን በተቀመጡበት ቦታ ተሸክመናቸው እንዞራለን ማለት ባለመሆኑ አንድም አልታወቀብኝም ከሚሉት ዐመጻ ወጥተው በንስሐ እንዲመለሱ፤ አለያም ያንን የጣፈጣቸውን ዐመጻ ቤቴ ብለው እንዲኖሩበት ለማድረግ ሲባል እውነቱ ሊነገራቸው ይገባል ብለን እናምናለን። የክርስቶስ ቤተሰቦች በተናጠል ብዙ ኃጢአት ይኖረናል። የግላችንን ኃጢአት ግን ወስደን ለቤተክርስቲያን የኃላፊነት መድረክ ማዋል ግን የበደል በደል ነው። ከተራራ ላይ የተቀመጠችን መብራት መሸሸግ አይቻልምና ለተቀመጥንበት የከፍታ ስፍራ ጥንቃቄ ማድረግ የግድ ነው።

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ጳጳስ እንደሆኑ የሚነገርላቸው አባ ኤዎስጣቴዎስን የተመለከተ መረጃ ከዚህ ቀደም ማውጣታችን ይታወሳል። የዚያ የመልካም ነገር ሁሉ እንቅፋት የሆነው ማኅበር የ/ማቅ/ ፓትርያርክ ሆነው ከሲኖዶስ በማፈንገጥና እንደአሜባ ቤተክርስቲያንን እየሰነጣጠቁ ባርኬ ሰጥቼሃለሁ በማለት ችግር ሲፈጥሩ እንደነበር ዘግበንበታል። በዳላስ ቅ/ሚካኤልን በሰባኬ ወንጌሉ በኩል ሁለት ቦታ በመሰንጠቅ በሥላሴ ስም የማቅ አዳራሽ የተባረከው በኚሁ የማቅ ፓትርያርክ ነበር። ያም ሆኖ አባ ኤዎስጣቴዎስን የነካቸው ማንም አልነበረም። ይሁን እንጂ የመሰነጣጠቅ ልምዳቸው፤ እየተከተለ እነሆ ብፁዕ ነኝ የሚሉበትን የእረኝነት ቀሚሳቸውን የሚሰነጥቅ ነውር ተከትሎ ለጥፋት ዳረጋቸው።

መሸከም ያልቻሉትን ድስት አስቀምጠው የሚችሉትንና የፈለጉትን የማድረግ መብት እንዳላቸው እናምናለን። ኃጢአቱ ያልተሰጣቸውን ጸጋ ለማግኘት መፈለግ እንጂ «ጋብቻ ክቡር ነው መኝታውም ንጹህ ነው» ያለው የእግዚአብሔርን ቃል መፈጸም አይደለም። ክፋቱ ያንን የእግዚአብሔር ቃል አልፈልግም ብሎ ሊጠብቃቸው የተሰጡትን በጎች እያጋደሙ በዝሙት ሰይፍ ማረድ አይደለም። ለዚህም እግዚአብሔር ይቅር ባይ ነውና ንስሐ ይግቡበት። ሚስት ማግባትም በደል አይደለምና የማይችሉትን ሰው ሰራሽ ድስት በመሸከም ከመንገዳገድ የሚችሉትን አግብተው የሥጋን ሸክም እያቀለሉ መኖር ይሻላልና ይህንኑ ይተግብሩ ምክራችን ይህ ነው።
ለነገሩ የኃጢአት ዋጋው ሳይታሰብ እንደዚህ ዓይነት ዋጋ የሚያስከፍል በመሆኑ እንጂ  የብፁዕነት ስያሜን ያለአቅማቸው ተሸክመው የሚንገዳገዱ ስንኩላን  ሹማምንት ብዙዎች ናቸው። የመገለጡ ዕጣ ቀድሞ ለአባ ኤዎስጣቴዎስ ከመውጣቱ በስተቀር ይህ ድርጊት የእሳቸው ብቻ አይደለም። ሌሎቹንም በዚህ አጋጣሚ የምንመክራቸው እግዚአብሔር ኃጢአትን እንጂ ኃጢአተኛን አይጠላምና በስመ ብፁዕ የሸፈናችሁትን ኃጢአት ተሸክማችሁ፤ ለራሳችሁ ሞትን፤ ለቤተ ክርስቲያን ውርደትን፤ ለእግዚአብሔር መንጋውን መጠበቅ ያለመቻል ቅጥረኝነት ለመላቀቅ ንስሐ ግቡ፤ ጋብቻችሁን መስርቱ፤ ንግድና ገንዘብ የመሰብሰብ ክፋታችሁን አራግፉ እንላለን። ኃጢአታችሁ ከራሳችሁ አልፎ ሀገር ሁሉ አውቆታል። ሰምቶታል። ኢትዮጵያዊ ይሉኝታ ስለሚያጠቃው ገመናችሁን ሸፈነው እንጂ ፈረንጅ ቢሆን ኖሮ በጋዜጣ ላይ አውጥቶ ንስሐ የመግባት እድላችሁን በማፋጠን ይተባበራችሁ ነበር። ያ ጊዜ ከመድረስ በፊት ለራሳችሁም፤ ብፁዕ አለመሆናችሁን እያወቃችሁ ብፁዕ መባላችሁ እንደማይገባችሁ አምናችሁ እንደዚያ እንደቀራጭ ራሳችሁን ዝቅ አድርጋችሁ ለንስሐ አዘጋጁ።
ለአባ ኤዎስጣቴዎስ የተጻፈው ሴት አዳኝና አደገኛ የወሲብ ቀበኛ የተባሉበትን ደብዳቤ አስፍተው/zoom/አድርገው እንዲያነቡ አቅርበነዋል።

እዚህ ላይ ይጫኑና አስፍተው ይመልከቱ

Friday, April 19, 2013

«እኛ ኢትዮጵያውያን ያለነው የት ነው? ተስፋችንስ ምንድነው?»

የሰው ልጅ ሁሉ የአዳምና የሔዋን ዘር ነው። ከዚህ የወጣ የለም።  ሰው ክቡርና በእግዚአብሔር አምሣል የተፈጠረ ስለሆነ እንስሳ አይደለም። ሰው በተፈጥሮው እንስሳ ነው የሚሉ ሰዎች ቢኖሩም እንኳን ሰው ግን እንስሳ አይደለም። በእርግጥ በተፈጥሮው ሰው ቢሆንም በአስተሳሰቡ ከእንስሳ ያልተሻለ ሰው ይኖራል። እንደባለጤና አእምሮ ሰው፤ ሰውኛ ማንነቱን ገላጭ አስተሳሰብ ሊኖረው የግድ ነው። እንስሳ አስተሳሰብ ማለት በሰው አምሣል ተፈጥሮ እንስሶች የሚሰሩትን የሚሠራ ወይም እንደእንስሳ የሚያስብ ማለት ነው። ዳዊትም በመዝሙሩ ይህን ኃይለ ቃል ሲገልጸው እንዲህ አለ። «ሰው ግን ክቡር ሆኖ ሳለ አያውቅም እንደሚጠፉ እንስሶች መሰለ»               (መዝ ፵፱፤፲፪)

አዎ ሰው ክቡርነቱን ትቶ በሃሳቡና በግብሩ፤ ነፍስያቸው ምናምንቴ እንደሆኑት እንስሶች መሰለ። ሁሉም ሰው የአንድ ዘር ምንጭ ቢሆንም ቅሉ ለሰይጣን ፈቃድ አድሮ በልዩነትና በክፍፍል መኖርን መርጧል። በክፍፍሉም እርስ በእርሱ ይባላል። ምክንያቱም አእምሮው ወደእንስሳነት አስተሳሰብ በወረደ ማንነት ተመርዟልና ነው። እንስሳት እርስ በእርሳቸው ይጠላላሉ። ነገን የሚጠብቁት አድነው ስለሚበሉት እንስሳ እንጂ በተስፋ ስለሚገነቡት ሕይወት አይደክሙም። ከዚያ ባለፈ እንስሳት ተስፋ የሚያደርጉት ዘላለማዊ ነገር ምንም የላቸውም። የማይሞት ተስፋ የተሰጠው የሰው ልጅ ግን በሚሞት ምድራዊ ተስፋ ላይ ራሱን አጣብቆ ይኖራል።ዳዊትም በመዝሙሩ ላይ ቃሉን በማስረገጥ  ድኩማነ አእምሮው ሰዎችን በእንስሳ ይመስላቸዋል። «አእምሮ የሌለው ክቡር ሰው እንደሚጠፋ እንስሶች መሰለ» (መዝ ፵፱፤፳)

ጠቢቡስ «ከፀሐይ በታች አዲስ ነገር የለም» ማለቱ ምን ማለቱ ነበር?  አዎ! ያን ማለቱ በአንጻራዊ ትርጉም አዲስ ነገር ያለው ከፀሐይ በላይ ነው ማለቱ ነበር። ከፀሐይ በላይ አዲስ ነገር እንዳለ እየተናገረን እንደሆነ እንረዳለን።  ስለዚህም ነው ተስፋችን በማይጠፋና ዘላለማዊ በሆነው ከፀሐይ በላይ ባለው ነገር ላይ እንዲሆን አበክሮ በመናገር ከፀሐይ በታች አዲስ ነገር የለም የሚለን። እንዲያውም ከፀሐይ በታች ባለው ነገር ላይ ተስፋ ማድረግ ነፋስን እንደመከተል ነው ይላል። «ከፀሐይ በታች የተሠራውን ሥራ ሁሉ አየሁ እነሆም፥ ሁሉ ከንቱ ነው፥ ነፋስንም እንደ መከተል ነው» (መክ ፩፤፲፬) ነፋስን ማን ሊከተል ይችላል? ነፋስስ መሄጃው ወደየት ነው? መኖሩን እናውቃለን እንጂ ወደየት እንደሚሄድ አንረዳም፤ መቆሚያውም የት እንደሆነ አናውቅም፤ ልንከተለውም ማሰብ ከንቱ ድካም ነው። ከፀሐይ በታች ያለውን ነገር ሁሉ መከተል እንደዚሁ ይለናል። የቀደመው  ነገር አልፏል፤ ያኔ ግን እንደአዲስ ይቆጠር ነበር። ዛሬ ደግሞ ነገ ቀድሞ ይሆናል። ቀድሞም ሆነ ዛሬ የምንላቸው ነገሮች ደግሞ ነገ የሉም። ሁለቱን የሚከተል ተስፋ የለውም።  ቀድሞና፤ ዛሬ የሚባልለት ሁኔታ በሌለው ከፀሐይ በላይ ባለው አዲስ ነገር ላይ ተስፋ ማድረግ ይሻላል። ሐዋርያው እንዲህ ሲል ያስተምረናል። «እርሱም የሰጠን ተስፋ ይህ የዘላለም ሕይወት ነው» (፩ኛ ዮሐ ፪፤፳፭)

የማይጠፋውን የዘላለም አዲስ ተስፋ በእምነቱ የሚጠባበቅ እንደምናምንቴ ሰው ተስፋ በሌለው በዚህ ዓለም ከንቱ ነገር ላይ ራሱን አያጣብቅም። ሰማያዊ ተስፋ የሌላቸው ሰዎች በዚህ ምድር ላይ መኖራቸውን እንደመጨረሻ ምዕራፍ ቢቆጥሩት አያስገርምም። መዝሙረኛው እንደተናገረው በአሳባቸው የሚጠፉ እንስሳትን መስለዋልና።

በእምነት ተስፋ ውስጥ ያሉ ሰዎች ከፀሐይ በላይ ያለውን አዲስ ነገር ይጠባበቃሉ። ስለሆነም በዚህ ምድር ላይ እስካሉ ሁላቸውም በእምነት አንድ ናቸው። ልዩነትን አይሰብኩም። ጳውሎስም እንዲህ አለ። «በእምነት በኩል ሁላችሁ በክርስቶስ ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጆች ናችሁና፤ ከክርስቶስ ጋር አንድ ትሆኑ ዘንድ የተጠመቃችሁ ሁሉ ክርስቶስን ለብሳችኋልና።አይሁዳዊ ወይም የግሪክ ሰው የለም፥ ባሪያ ወይም ጨዋ ሰው የለም፥ ወንድም ሴትም የለም፤ ሁላችሁ በክርስቶስ ኢየሱስ አንድ ሰው ናችሁና። እናንተም የክርስቶስ ከሆናችሁ እንኪያስ የአብርሃም ዘር እንደ ተስፋውም ቃል ወራሾች ናችሁ» (ገላ ፫፤፳፮-፳፱)

Wednesday, April 17, 2013

'ማሪያም ነኝ` ባዩዋ ተፈረደባት


በአሸናፊ ደምሴ
ሰንደቅ ጋዜጣ ረቡዕ 9/8/2005 ዓ/ም
የፌዴራሉ አቃቤ ህግ የማይገባትን ጥቅም ለማግኘት በማሰብ በተለያዩ ጊዜያትና ቦታዎች በመንቀሳቀስ ሰዎችን በማታለልእኔ ማርያም ነኝ፤ እንደኢየሱስም በጅራፍ ተገርፌያለሁ፤ ከሞትም ተነስቻለሁ፤ የወለድኳቸውንም ልጆች ያገኘሁት በመንፈስ ነውስትልና የዓለም ፍፃሜ ደርሷል በሚል የሰዎችን የግል ሀብት ለራሷ ስታደርግ ደርሼባታለሁ ሲል ክስ የመሰርተባት 34 ዓመቷ ትዕግስት ብርሃኑ /ጊዮርጊስ፤ በፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 6 ወንጀል ችሎት ፊት ቀርባ ጥፋተኛ ሆና በመገኘቷ 2 ዓመት 4 ወራት ፅኑ እስራትና በአንድ ብር የገንዘብ መቀጮ እንድትቀጣ ሲል ባሳለፍነው ሳምንት ወሰነ።
እንደአቃቤ ህግ የክስ ዝርዝር ከሆነ ግለሰቧ በአራት የተለያዩ ክሶች የተወነጀለች ሲሆን፤ የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤትለሰው ህይወት ማለፍ ሳቢያ ነችሲል አቃቤ ህግ ያቀረበውን ክስ ያልተሟላ ነው ሲል ውድቅ ሲያደርገው በተቀሩት ሶስት ክሶች ግን ጥፋተኛ ነች ብሎ እንድትከላከል ብይን ሰጥቶ ነበር።
ተከሳሿ ጥፋተኛ የተባለችበት አንደኛ ክስ በየካቲትና በመጋቢት ወራት ውስጥ 1999 . የማይገባትን ጥቅም ለማግኘት አስባ በጉለሌ ክፍለ ከተማ ቀበሌ 21 ልዩ ቦታው ኪዳነምህረት ተብሎ በሚጠራው አካባቢ 300 በላይ ሰዎችን በመሰብሰብእኔ ማርያም ነኝ፤ እንደኢየሱስም በጅራፍ ተገርፌ፤ ከሞትም ተነስቼያለሁየሚል የሀሰት ወሬ በመንዛትና የዓለም ፍፃሜ ደርሷል ንብረት አያስፈልግም በሚል ያላችሁን ንብረት አምጡ ስትል ከተለያዩ የግል ተበዳዮች ጥሬ ገንዘብና ወርቅ የተቀበለች ሲሆን፤ በአጠቃላይም 40 ብር ለግል ጥቅሟ አውላለች ሲል በክስ መዝገቡ ያስረዳል።