Saturday, March 30, 2013

ንስሐ ለአብያተ ክርስቲያናት




የዲያቆን አሸናፊ መኰንን ገጽ ዓርብ መጋቢት 20/2005 ዓ.ም.

ከዛሬ ሠላሣ ሁለት ዓመት በፊት በጎጃም ይኖሩ የነበሩ 40 ዓመት የዘጉ አንድ ባሕታዊ ከዘጉበት በኣት/ቤተ ጸሎት/ ወጥተው ለሕዝቡ ታዩ፡፡ ታይተው የማያውቁ እኚህ አባት ዛሬ መውጣታቸው ሕዝቡን አስደንግጦታል፡፡ ለሰንበት ቅዳሴ ለተሰበሰበው  ሕዝብ እንዲህ በማለት ተናገሩ፡- “በሕልሜ ቤበ- መኩ- እፍ- ጸጉ የሚሉ ቃላትን ያሳየኛል፡፡ ተጨንቄአለሁና እባካችሁ ፍቱልኝ” አሉ፡፡ ሕዝቡም፡- “አባታችን እኛ ምኑን እናውቀዋለን? ለእርስዎ እንዳሳየ ይፍታልዎ እንጂ” አሏቸው፡፡ እርሳቸውም ሕልሙን ሲተረጕሙ፡-
ቤበ  - ማለት ቤተ ክርስቲያን በረት ሆነች ማለት ነው፡፡
መኩ - መሥዋዕት ኩበት ሆነ ማለት ነው
እፍ -  ዕጣን ፍግ ሆነ ማለት ነው፡፡
ጸጉ - ጸሎት ጉባዔ/ ታይታ/ ሆነ ማለት ነው በማለት ተረጎሙ፡፡
ሕልምም ሆነ ትንቢት በፍጻሜው ይታወቃል፡፡ እኝህ አባት ያሳያቸው እውነት እንደሆነ ዛሬ እያየነው ነው፡፡ በረት ቆሻሻ የበዛበት፣ ንጽሕና የጎደለው፣ ሥነ ሥርዓት የሌለበት፣ የሕያው ነፍስ ሳይሆን የደመ ነፍስ /የእንስሳት/ መከማቻ፣ ነጻነት የማይሰጥ፣ በውስጡ የሚኖሩት የሕሊና፣ የሰብአዊና የመንፈሳዊ ሕግ የማያዛቸው፣ ዙሪያው የሚበርድ ክፍት የሆነ ስፍራ ነው፡፡ እኝህ አባት ቤተ ክርስቲያን በረት ሆነች ይለኛል አሉ፡፡ ንስሐን የመሰለ የሕይወት ውኃ የሚነገርባት ቤተ ክርስቲያን አገልጋዮቿ  ያልታጠቡባት፣ ንስሐን ተሸክመው ንስሐ የሚቀበሉባት፣ በዓለም የሌለ ነውር በእርስዋ የሚሰማባት፣ ቅድስና የራቃት፣ ሁሉም በፊቱ ደስ ያለውን የሚያደርግባት፣ የደፈረ የሚኖርባት፣ እንኳን መንፈሳዊነት ሰብአዊነት የማይሰማቸው አገልጋዮች የተሰበሰቡባት፣ ትሩፋት የሚሠራ አይደለም የታዘዘውን የሚፈጽም የታጣባት፣ ለሚያያቸው ዕረፍት የማይሰጡ ያልተገሩ ሠራተኞች የሞሉባት፣ ለእግዚአብሔርና ለአገር ሕግ የማይገዙ የተከማቹባት፣ ሲያስቧቸው ብርድ ብርድ የሚሉ ሥርዓት አልበኞች የነገሡባት ስፍራ ሆናለች፡፡


ከደብረ መድኃኒት መድኃኔ ዓለም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ካቴድራል ኮለምቦስ ኦሃዮ የተሰጠ መግለጫ



ከሁሉም በላይ በሆነች ሐዋርያት በሰበሰቧት በአንዲት ቅድስት ቤተክርስቲያን እናምናለን

በስመ አብ፣ ወወልድ፣ ወመንፈስ ቅዱስ አሀዱ አምላክ፤ አሜን። ላለፉት ሃያ አንድ ዓመታት በሥልጣን ላይ ያለው የኢ ሕ አ ዴ ግ  መንግሥት በኃይማኖት ጉዳዮች ውስጥ ጣልቃ በመግባት በመንፈሳውያን አባቶች፤ በካህናትና በምዕመናን መካከል ልዩነት በመፍጠር ፤ ይህንኑ ልዩነት በማስፋትና በማራገብ ለዘመናት የኦርቶዶክሳዊት ተዋህዶ እምነት አገልግሎት ያለአንዳች እንከን እየተካሄደ ባለበት ዘመን  በተቀደሰና በተከበረ ዓውደምህረት፤ ላይ ስር የሰደደ ጥላቻ እንዲሰፍንና በኦርቶዶክሳውያን መካከል ሰላም እንዲደፈርስ፤ ብሎም የቡድንና የጐጥ ስሜት እንዲስፋፋ ያላቋረጠ ሴራ ሲሸርብ መቆየቱ ይታውሳል። ይህንን ኃላፊነት የጐደለውን እኩይ ተግባር መላው ሕዝበ ክርስቲያን ተረድቶ በተገቢው ጊዜና ሰዓት አፋጣኝና ሥርነቀል የሆነ ምላሽ ካልሰጠበት፤ የሁለት ሺሕ ዓመታት እድሜ ባለፀጋ የሆነችውን ቤተክርስቲያናችን ሕልውናዋን በፅኑ መሠረት ላይ እንደተጠበቀ ለመጭው ትውልድ ለማስረከብ  ውስብስብ መሰናክሎች እንደሚገጥሙት ከወዲሁ መገመት ይቻላል።
በመሆኑም ጥቂት የችግሩን አስከፊነት በጥልቀት የተረዱት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን የሰላምና የአንድነት ጉባኤ አባላት በቅን ልቦና ተነሳስተው፤ ተግባብተውና ተቀራርበው በመወያየት በተለይም አሁን በአገራችን የታየው የቀኖና ቤተክርስቲያን ጥሰት፤ የኦርቶዶክስ አማኞች አሳፋሪ የመለያየት ፈተና፤ የእምነት ክፍፍል፤ በተለይም የአራተኛው ፓትርያርክ የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳስት ዘኢትዮጵያ በመንግሥት ጫናና ግፊት ያለ በቂ ምክንያት ከመንበረ ከፕትርክናቸው በግፍ እንዲነሱ የተደረገበትን ሁኒታ ለአንዴና ለመጨረሻ  ጊዜ እልባት እንዲያገኝ ሰፊ ጥረት እያደረጉ በነበሩበት ወቅት፤ አባ ጳውሎስ ከዚህ ዓለም በሞት ስለተለዩ ይህም ወደ አንድነት የማምጣቱን ሂደት  መልካም አጋጣሚ በመፈጠሩ፤  የሰላሙ ኮሚቴ የጀመረውን ጥረት አጠናክሮ በመቀጠል ለሦስተኛ ጊዜ በሀገር ቤትና በውጭ ሀገር ያሉትን የቤተክርስቲያን አባቶች ፊት ለፊት አገናኝቶ እንዲነጋገሩና  ለተፈጠረው ችግሮች መፍትሔ እንዲያፈላልጉ የሚይስችል ዕድል አመቻችቶ ነበር።


Friday, March 29, 2013

የአርማጌዶን ዘመን ቀርቧል?


ምልክት እያደረጉ የአጋንንት መናፍስት ናቸውና፥ በታላቁም ሁሉን በሚገዛ በእግዚአብሔር ቀን ወደ ሚሆነው ጦር እንዲያስከትቱአቸው ወደ ዓለም ሁሉ ነገሥታት ይወጣሉ።
እነሆ፥ እንደ ሌባ ሆኜ እመጣለሁ፤ ራቁቱን እንዳይሄድ እፍረቱንም እንዳያዩ ነቅቶ ልብሱን የሚጠብቅ ብፁዕ ነው።
በዕብራይስጥም አርማጌዶን ወደሚባል ስፍራ እስከተቱአቸው።



Thursday, March 28, 2013

የጅማ ቅዱስ ሚካኤል አስተዳዳሪ አባ ማቴዎስ ታምሩ የገቡበት አልታወቀም !

          
                  source: http://dejeselaam-dejeselaam.blogspot.com
 "ማኅበረ ቅዱሳን" አፍኖ እንደወሰዳቸው ይጠረጠራል"

የጅማ ቅዱስ ሚካኤል አስተዳዳሪ አባ ማቴዎስ ታምሩ የገበቡበት አለመታወቁን ከስፍራው የደረሰን መረጃ ያመለክታል፡፡ አባ ማቴዎስ ታምሩ በተለይ ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ ከ"ማኅበረ ቅዱሳን" ተከታታይ የሆነ ጥቃት እንደደረሰባቸው ሲታወቅ፣ እርሳቸውም "ማቅ" የአጥቢያ ቤተክርስቲያኑን መዋቅር በመቆናጠጥ ፈላጭ ቆራጭ ለመሆን የሚያደርገውን ሕገ ወጥ አካሄድ በመቃወም ረገድ ብርቱ እንደነበሩ ተመስክሮላቸዋል፡፡
ይሁን እንጂ "ማቅ" አንድ ጊዜ ያተኮረበትን ቦታና ሰው እስኪቆጣጠር ዕረፍት የሌለው በመሆኑ አባ ማቴዎስን ሌት ተቀን መነዝነዝና ስቃይ ማብላትን ሥራዬ ብሎ መያያዙን ታዛቢዎች ገልጸዋል፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ አባ ማቴዎስ በራሳቸው ጊዜና ፍላጎት ዕረፍት ለማድረግና ዘመዶቻቸውን ጠይቀው ለመምጣት ወደ ሲዳማ ዞን አርቤጎና  ወረዳ መሄዳቸው ታውቋል፡፡


እስልምና በኢትዮጵያ ታሪክ

                                        
                       (የጽሁፉ ባለቤቶች ለእስልምና መልስ አዘጋጅዎች ነው)
( ክፍል ሦስት )

መሰረታዊና ታሪካዊ ጥያቄ፡

የሼክ አብደላ ርዕዮተ ዓለም በሌላው ዓለም ውስጥ ተቀባይነት ሲያገኝና ዓለም አቀፍ ሲሆን በኢትዮጵያ ሙስሊሞች ዘንድ  ተቀባይነት ስለምን ሊያገኝ አልቻለም? ይህ ጥያቄ በኢትዮጵያውያን መካከል መነሳትና መብላላት ያስፈልገዋል፡፡ ይህ ጥያቄ የኢትዮጵያ ሙስሊሞች ሁሉ ሊጠየቁበት የሚገባው ጥያቄ ነው፡፡ ይሁን እንጂ ጥያቄው በምንም መልኩ ቢላመጥና ቢገላበጥ የሚሰጠው መልስ ከሚከተሉት ከሁለቱ መልሶች መካከል ከአንዱ በፍፁም ሊዘል አይችልም፡
አንደኛ፡ በኢትዮጵያ ውስጥ ያለው የእስልምና እምነት በጣም ጥንታዊ ወይንም የተለምዶ ብቻ ስለሆነ ነው፡ አል-አሕበሽን አይቀበልም፤ ወይንም፤
ሁለተኛ፡ በኢትዮጵያ ውስጥ ስር የሰደደውና ብዙዎች የሚከተሉት የእስልምና እምነት ርዕዮተ ዓለም የዋሃቢው አክራሪ እስልምና ስለሆነ የአል-አሕበሽን ትምህርት አይቀበልም የሚሉት ብቻ ናቸው፡፡
እንግዲህ በአሁኑ ጊዜ የተነሳው የተቃውሞ እንቅስቃሴ በማነው የተነሳው፣ ማን መራው፣ ዓላማው እና የወደፊት ግቡ ምንድነው የሚሉት ሁሉ መልሳቸውን የሚያገኙት ከዚህ መሰረታዊና ታሪካዊ ጥያቄ ጋር ተያይዘው ሲታዩ ብቻ ነው፡፡ ይህ ነጥብ ነው ለምናደርገው ነገርና ለምንሰጠው ድጋፍ ጥንቃቄ እንድናደርግ የሚጠራን፤ ይህ ነጥብ ነው ዛሬ ተቀምጠን የሰቀልነው ነገ ቆመን የማናወርደው እንዳይሆን የሚመክረን፣ ይህ ነጥብ ነው የጠላቴ ጠላት ወዳጄ ነው የሚለውን አባባል አቁመን አሁን አርቀን ለማሰብ መነሳት አለብን የሚለን፡፡

የአል-አሕበሽ መሰረታዊ እምነቶች

የአል-አሕበሽ መሪ ሼክ አብደላ ለተከታዮቹ ካደረጋቸው ንግግሮች ውስጥ በአንዱ እንቅስቃሴው የሚከተለውን መሰረታዊ ርዕዮተ ዓለም ለማስቀመጥ እንደሞከረና በዚያም ውስጥ ከዋነኛው ተቃዋሚ እራሱን ለይቶ እንዳስቀመጠ ፕሮፌሰሮቹ አመልክተዋል ንግግሩም፡-
 “እኛ እስላማዊ ማህበር ነን፣ (ማህበራችን) የሚወክለውም ምንም ዓይነት የፈጠራ ልዩነት የሌለበትን ነው፣ ማለትም እንደነዚያ ከሃምሳ፣ ሁለት መቶ ወይንም ስድስት መቶ ዓመታት በፊት እንደተጨመሩት ዓይነት አይደለንም፡፡ የመጀመሪያዎቹ የሳይድ ካታብ ሐሳቦች ናቸው ... ሁለተኛዎቹ ደግሞ የመሐመድ ኢብን አብድ አል-ዋሃብ ናቸው፣ ሦስተኛዎቹ ደግሞ  የኢብን ታይሚያ ናቸው ከእነዚህ ነው አብድ አል-ዋሃብ ሐሰቦቹን ያመጣቸው፡፡ (የወሰዳቸው)፡፡ እኛ ግን አሻሪስ እና ሻፊዎች ነን፡፡ የእምነታችንም መሰረት አሻሪያ ሲሆን ሻፊያ ደግሞ የየዕለቱ መለያችን ነው፡፡” የሚል ነበር፡፡
በንግግሩ ውስጥ የጠቀሳቸውን ሰዎች እንደ ዋነኛ ጠላቶች አድርጎ ለምን እንደመረጣቸው እና ምክንያቱንም ሊቃውቱ ሲያስረዱ የሚከተሉትን ከታሪክ አቅርበዋል፡ ሳይድ ኩታብ የግብፅ እንቅስቃሴ መሪና ሊቅ ሲሆን፣ በእስልምና የፖለቲካል ሐሳቦች ላይ ሥራን በመስራት በሙስሊም ወንድማማችነትና በዋሃቢዝምን መሰረታዊ ነጥቦች መካከል ድልድይ የሰራውን መጥቀሱ እንደሆነ፡፡ ሼኩ አል-ዋሃብን እና ኢብን ታይሚያምን ሲጠቅስ ደግሞ የዋሃቢዝም መስራችና የትምህርቱ ታሪካዊ አነሳሽንና ምንጭን ማለትም ግልፅ የሆነውን ነገር ማንሳቱ ነበር ይላሉ፡፡ ኢብን ታይሚያ የ14ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ሊቅ ነበር፡፡ ዘመናዊው የፓኪስታን ፈላስፋ አቡ አል-አላ አል-ማውዱዲ የተነሳሳው በኢብን ታይሚያ እና በሳይድ ኩታብ በተሰጠው በዋሃቢያ ትምህርት ነው፣ እርሱም የሙስሊም ወንድማማቾችን የሃይማኖታዊ ሕጋዊነት በመስጠት ከ1960 ጀምሮ ወደ አክራሪ እንቅስቃሴነት የመቀየር ህጋዊነት አምጥቷል ይህም እስላማዊ ያልሆኑትን እና መሰረታዊ ያልሆኑትን ትምህርቶችና ነገሮች በማስወገድ እስልምናን ለማጥራት ተብሎ ነበር፡፡ የአል-አሕበሽ መሪ እነዚህን አስተማሪዎችና መሪዎች ከታሪካዊ አስተምህሮአቸው በመነሳት የጠቀሰበት ዋናው ምክንያት እዚህ ላይ ግልፅ ነው፣ እርሱም እነርሱ በሙሉ ያራምዱት የነበረው እስልምና ከሌሎች ጋር በሰላም ለመኖር የሚፈልግም የሚችልም እንዳይደለ ነው፡፡

Tuesday, March 26, 2013

የሚኒሶታውን የደብረሠላም መድሃኔዓለምን ከይሁዳዎች መጠበቅ የሁላችን ኃላፊነትም ግዴታም ነው


 (የጽሁፍ ምንጭ፤ ዘሐበሻ)
ደብረሰላም መድሃኔዓለም ከተመሠረተ ጊዜ ጀምሮ በብዙ ውስብስብ ችግሮች ያለፈ ሲሆን ከዓመታት በፊት በማን ሥር መሆን አለበት ተብሎ 3 ምርጫ ቀርቦ ነበር። ይኸውም ሃገር ቤት በወያኔ ሥር በሚገኘው ሲኖዶስ፣ ኒውዮርክ በነበሩት አቡነ ይስሃቅ እና 3ኛው ገለልተኛ እንዲሆን ሲሆን በጊዜው በስብሰባው ቦታ በነበርነው አባላት በውጭ የሚገኘው ሲኖዶስም በደንብ ባለመጠናክሩ ገለልተኛ ሆኖ እንዲቆይ ተስማምተን ቤተክርስቲያኑ ለተወሰኑ ዓመታት ገለልተኛ ሆኖ ቆይቷል። ሆኖም ለቤተከርስቲያኑ ምስረታና ዕድገት በጊዜው ትልቅ አስተዋጽኦ ያደረጉት አባ ፍቅረማርያም የአሁኑ (አቡነ ዳንኤል) ወደ ሃገር ቤት ተመልሰው ጳጳስ ከሆኑ በኋላ የደብረ ሠላም መድሃኔዓለም ገለልተኛ ሆኖ መቀጠል አጠያያቂ ሆኗል።

Monday, March 25, 2013

በቆብ ላይ ሚዶ ትምህርትና ተማሪ ቤት


ፕሮፌሰር መሥፍን ወ/ማርያም
(ክፍል ሁለት)

የዛሬዎቹ ባለሥልጣኖች በደርግ ጊዜ አልነበሩም፤ የደርግን ስሕተት በማየት አልተማሩም፤ ትምህርታን አቋርጠው ወደጫካ የገቡት ከትምህርት የሚበልጥባቸው ምኞት አጋጥሟቸው ነው፤ የትምህርት ገዜያቸውን በጫካ ባለሥልጣን በመሆን፣ እነሱው ሕግ አውጪና ዳኛ፣ እነሱው የጫካ አስፈጻሚ ሆነው ቀዩ፤ ደርግ በጠራራ ጸሐይ የሚሠራውን እነሱ በጫካ ጭለማ ሲሠሩ ቆዩ፤ በሥልጣን ላይ ከወጡ በኋላም በጣም ቆይተው ትምህርት አስፈላጊ መሆኑን በትንሹ ተገነዘቡ፤ በጣም የተማሩ ሰዎች ጋር ሲገናኙ ማፈር አስጨነቃቸው፤ ስለዚህም ቀላሉ ነገር የተማሩ ሰዎችን አለማቅረብ፣ ትምህርታቸውን በጠባያቸው ካላጠቡ የተማሩ ሰዎች ጋር በቀር አለመገናኘት፣ እንዲያውም የትምህርትን ዋጋና ጥራት በማዋረድ አዲስ የሚመረቁት ሁሉ ለባለሥልጣኖች አንገታቸውን የሚደፉ ዓይነት እንዲሆኑ ማድረግ ዓላማ ሆነ።
የተማሩና የሠለጠኑ የጦር መኮንኖችም ተሸናፊዎች በመሆናቸው ትምህርታቸው ዋጋ እንደሌለው ማረጋጋጫ እያደረጉ የወያኔ መሪዎች በአደባባይ ተናገሩ፤ ትንሽዋ ቢምቢ ሰውን መግደል እንደምትችል ያልተገነዘቡት ከጫካ የመጡ ሰዎች በመግደል ማሸነፍን የትምህርትን ዋጋ-ቢስነት ማረጋጋጫ አደረጉት፤ የተማሩ ሰላማዊም የጦር መኮንኖችም ዋጋ-ቢስነታቸው ኑሮአቸውን በማናጋቱ በችግር ወደሌላ ሥራ ተሰማሩ፤ ወይም አገር ጥለው ተሰደዱ፤ በሰላማዊውም ሆነ በፖሊስና በጦር ሠራዊቱ የተማረ ሰው እጥረት መፈጠሩ ለወያኔ መግቢያና መደላደያ ምቹ ሁኔታን ፈጠረ።

በቆብ ላይ ሚዶ ትምህርትና ተማሪ ቤት

መስፍን ወልደማርያም

ጥር 2005

ክፍል አንድ

በአለፉት አርባ ዓመታት ውስጥ አንድ ልብ ያላልነው መሠረታዊ ለውጥ አለ፤ እንዲያውም የመከራችን ሁሉ ምንጭ ነው ለማለት ይቻላል፤ የመሪዎቻችን አለመማር ብቻ ሳይሆን ትምህርትን መናቅ ወይም ጭራሹኑ መጥላት ዋና ባሕርያቸው ሆነ፤ እስከደርግ ዘመን የነበሩት የአገር መሪዎች ቢያንስ የአንደኛ ደረጃውን (ዳዊት መድገም) የአገሩን ባህላዊ ትምህርት ያከናወኑ ነበሩ፤ ከዚያ በኋላ ለጨዋ ቤተሰብ ልጆች ትምህርት ማለት በቤተ መንግሥት በመዋል የሚገኝ ልምድ ነበር፤ ተፈሪ መኮንን በአሥራ ሦስት ዓመቱ ደጃዝማች የሆነውና ሥልጣን ላይ የወጣው በመወለድ ያገኘውን ዕድል በልምድ እንዲያዳብረው ነበር፤ ተክለ ሐዋርያት ከአሥር ዓመታት በላይ ሩስያ ተምሮ ሲመለስ ተፈሪ ያገኘውን አላገኘም።

በአጼ ኃይለ ሥላሴ ዘመን ትውልድ ለሥልጣን መነሻ አይሆንም ነበር ባይባልም፣ ለእድገት ትምህርት አስፈላጊ መሆኑ በመታመኑ የዓየር ኃይል እጩ መኮንኖችም ሆኑ መኮንኖቹ ከደብረ ዘይት እየተመላለሱ ይማሩ ነበር፤ በማታው ትምህርት ብዙ የፖሊስና የጦር ሠራዊት መኮንኖች (ኮሎኔል ሚካኤል አንዶም ጭምር) ይማሩ ነበር፤ ማታ ከተማሩት የፖሊስ መኮንኖች ውስጥ ሁለቱ አምባሳደሮችም ሚኒስትሮችም ሆነው ነበር፤ ከሐረር አካደሚ የወጣ መኮንንም አምባሳደር ሆኖ ነበር፤ በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ አገዛዝ የደሀ ልጆች ወደሥልጣን ወንበሩ አልተጠጉም የሚሉ ካሉ የማያውቁ ናቸው፤ ትምህርታቸውን በታማኝነት ከፍነው ቀብረው ሚኒስትርና ሌላም ሹመት ያገኙ የደሀ ልጆች ብዙዎች ናቸው።

የዳላሱ ቅዱስ ሚካኤል ካቴድራል በአቡነ መርቆሪዎስ ወደሚመራው ሲኖዶስ ተቀላቀለ

 (የጽሁፍ ምንጭ፤ ዘሐበሻ)
የዳላሱ ርዕሰ አድባራት ደብረ ምህረት ቅዱስ ሚካኤል ካቴድራል ዛሬ ባካሄደው ምርጫ መሰረት በአቡኑ መርቆሪዎስ ወደ ሚመራው ስደተኛው ሲኖዶስ ተቀላቀለ።
ላለፉት 21 ዓመታት በገለልተኝነት የቆየው የዳላሱ ቅዱስ ሚካኤል ካቴድራል ምዕመናኑ አባት ይኑረን፣ በገለልተኛነት መቆየት ይቅርብን በሚል ባቀረበው ጥያቄ መሠረት ዛሬ ምርጫው ተጠናቆ በተደረገው ቆጠራ;
- 140 ሰዎች በ4ኛው ፓትርያርክ አቡነ መርቆሪዎስ ወደ ሚመራው ስደተኛው ቅዱስ ሲኖዶስ እንዲጠቃለል
- 2 ሰዎች በሃገር ቤቱ ሲኖዶስ እንዲጠቃለል;
- 85 ምዕመናን በገለልተኝነት እንዲቀጥል ድምጽ የሰጡ መሆናቸውን የዘ-ሐበሻ ምንጮች ገልጸዋል። በዚህም መሠረት በአሜሪካ ከቀደምት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤ/ክ አብያተ ክርስቲያናት በትልቅነቱ ትልቅ የሆነውና በቀዳሚነቱም የሚጠቀሰው የቅዱስ ሚካኤል ካቴድራል ስደተኛው ሲኖዶስን ተጠቃሏል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ በሰሜን አሜሪካ በገለልተኝነት የቆዩ የተለያዩ አብያተ ክርስቲያናት በቅርብ ቀናት በ4ኛው ፓትርያርክ ወደሚመራው ስደተኛው ሲኖዶስ ይጠቃለላሉ ተብሎ እየተጠበቀ ነው

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ዘኢትዮጵያ ከቪኦኤ ጋር ያደረጉት ቃለ ምልልስ


( for IE9 & 10 Users )


___________________________________

( for Firefox10 & above Users )


Sunday, March 24, 2013

ዓለም ለእኔ ብቻ በሚሉ ስግብግቦች የተሞላች ነች!


በአንድም ይሁን በሌላ ምክንያት ሁላችንም የዚህ ስግብግብነት ሰለባዎች ነን። ምናልባት ላይታወቀን  ቢችል ወይም በሌላው ላይ ያደረስነው የስግብግበት መገለጫ ጠባይዓት በግልጽ ባለመታየቱ ብቻ ራሳችን ነጻ እንደሆንን እናስብ ይሆናል። ነገር ግን የሰው ልጅ ከሥጋ ድካምና ከፈተናው ጽናት የተነሳ ስግብግብ ነው። ስግብግብነት ማለት ሁሉን ለእኔ በሚል ፍላጎት ዙሪያ ብቻ የሚሽከከረከር  ሳይሆን ስሱዕ /ስስታምነትን/ ፤መጠን የለሽ ጉጉነትን ይጨምራል።  ስስታምነት ለራስ ማድላትና ራስን ማዕከል ባደረገ ስሜት ስር መታጠር በመሆኑ የስግብግብነት አንድ አካል ነው። ጉጉነት ደግሞ እዚያ ጠርዝ ላይ ለመድረስ የሚጠይቀውን መስዋዕት ሁሉ ለመክፈል መሮጥ ነው። ስግብግብነት ከመጠን በላይ መብላት፤ በብዙ ወጪ ለመርካት መሞከር፤ የፍላጎት ጣሪያ መናር እና የአኗኗር ቅንጡነትንም ይጨምራል። «ሁሉ አማረሽን ገበያ አታውጧት» የሚባለው የፍላጎት ስግብግብነት ልክ ማጣት ማሳያ ነው።
ስግብግብነትን ካምብሪጅ ዲክሽነሪ በምሳሌ እንዲህ ይለዋል።
(industrialized countries should reduce their gluttonous (= greater than is needed) consumption of lifesyle)
የበለጸጉ ሀገሮች የስግብግብ ፍጆታ አኗኗራቸውን መቀነስ አለባቸው እንደማለት ነው።  ምክንያቱም የአኗኗራቸው ቅንጡነት ስግብግቦች እንዲሆኑ አድርጓቸዋል።ለልቅ ኑሮ ጉጉ ናቸው። ጉጉነት /AVID / ያላዩትን ነገር እንዲያዩ ይገፋቸዋል። ጉጉነት ምንጊዜም አንድን እርከን ከመሻገር በኋላ የሚመጣ ፍላጎት ነው።  ምንም የሌለውና በጣም የተራበ ሰው በቅድሚያ የሚታየው ወይም ከፊቱ ድቅን ብሎ የሚመጣበት ጉጉት ምንም ይሁን ምንም ረሃቡን የሚያስታግስበትን የእህል ዘር እንጂ ከትልቅ አዳራሽ ውስጥ ተሰይሞ የበግ አሮስቶ በውስኪ እያወራረደ መርካት አይደለም።  ያ ማለት ግን አይፈልግም ማለት አይደለም። ይህ የቅንጦት እሳቤ ምንም ከማጣት ችጋር ጋር ስለማይቀራረብ ብቻ ነው። የበለጸጉ ሀገሮች ግን በብዙ መልኩ ከችጋር ስለወጡ አመጋገባቸው ሁሉ ጊዜ ሰርግና መልስ ነው። እንደ ችጋር ሀገሮች የበሉት የምግብ ተረፍ ለበኋላ ተብሎ ይቀመጥ ዘንድ በፍጹም አይታሰብም። አዲስ ሞዴል መኪና፤ አዲስ የቤት እቃ፤ አዲስ ሁሉ አዲስ እንዲሆንላቸው ፍላጎታቸው ጣሪያ ነው። ለሌላው አዲስ ለእነሱ አሮጌ ነው። መሪዎቻቸው የእነዚህን ቅንጡ ሰዎች ኑሮ ላለማጓደል ከሌላው ዘርፈው ወይም ቀምተው ያመጡላቸዋል። ዘረፋው በቀጥታ ላይሆን ይችላል። ሚዛናዊ ባልሆነ ንግድ ወይም የምርት ልውውጥ፤ ሽያጭና ጥቅሞቻቸውን በሚያስከብሩ ስምምነቶች ሊሆን ይችላል። በአንዱ ቦታ የመሳሪያ ቅነሳ ወይም ማስተላለፍ እገዳ ፊርማ ቢያኖሩ  በሌላ ቦታ ደግሞ በመርከብ ጭነው ሊሸጡ ይችላሉ። ይህንን ካላደረጉ ሰማይ የደረሰውን ስግብግብ ፍላጎታቸውን መሙላት አይችሉም።

Friday, March 22, 2013

«እስልምና በኢትዮጵያ ታሪክ» ክፍል ሁለት


ሁለቱ እስላማዊ ርዕዮተ ዓለሞችና ትግላቸው (ጽሁፍ በእስልምና መልስ አዘጋጅዎች)

በወቅቱ በአገሪቱ ውስጥ ያለው የሙስሊሞችን እንቅስቃሴ፣ ለመደገፍ፣ ወይንም ዝም ብሎ ለማየት ወይንም ለመቃወም የሚቻለው እስልምና በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ ምን ይመስል እንደበረ በትክክል በመገንዘብ ነው፡፡ የአሁኑ የተቃውሞ እንቅስቃሴ በእርግጥ የሃይማኖት ነፃነት ጥያቄ ነውን? ብዙዎችን መስሏቸዋል፡፡ በጣም የቅርቡ በኢትዮ ሚዲያ የድረ-ገፅ ጽሑፎች ላይ የቀረበው የኦክላንድ መግለጫ እንዲሁም  www.ethiomedia.com/2012_report/4059.html የቀረበው የነጃሺ ካውንስል መግለጫ፣ አሜሪካ ውስጥ ባለው በኢትዮጵያ ክርስትያንና እስላም ካውንስል በJuly 26 2012 በኢትዮ ሚዲያ ላይ የወጣው www.ethiomedia.com/2012_report/4097.html ጋዜጣዊ መግለጫ እንዲሁም በሌሎች ድረገፆች ላይ በተደጋጋሚ የተሰጡት መግለጫዎች በሙሉ ሁኔታውን ያቀረቡት የእምነት ነፃነት ተደፈረ ከሚል አመለካከት የተነሳ ነው፡፡
ይህንን በተመለከተ የሚጻፉትም የተለያዩ ጽሑፎች አስገራሚዎች ሆነው አግኝተናቸዋል፤ በተለይም በዚያው በኢትዮ ሚዲያ ላይ Standing up with our Moslem citizens በሚል ርዕስ በይልማ በቀለ የቀረበው ጽሑፍ ለምሳሌነት የሚጠቀስ ነው፡፡ ሙሉ ጽሑፉን www.ethiomedia.com/2012_report/4554.html ማንበብ ይቻላል፡፡ አቶ ይልማ በቀለ የሙስሊሞችን እንቅስቃሴ እንደ እውነተኛ የሃይማኖት ነፃነት ጥያቄ አቅርቦ የገዚው ፓርቲ እነርሱን ለማፈን አንዳንድ የፈጠራ ፕሮፓጋንዳዎችን እንደተጠቀመ በማድረግ አስቀምጦታል፡፡ በእርግጥ ይልማ በቀለ እንዳለው ኢትዮጵያን የምንመኛት የሁሉም እምነት ተከታዮች በነፃነት የሚኖሩባት አገር እንድትሆን ነው፡፡ የሙስሊሞች ጥያቄና የዘመናት ዕቅድ ግን በእርሱና በመሰሎቹ ዘንድ የታየው ላይ ላዩን ከሚሆነው ነገርና  ከሞኝነትም ጭምር የተነሳ ነው ምክንያቱም ነገሩ ሁሉ እነሱ እንደሚሉት አይደለም፡፡
ሙስሊሞች በተለይም በአሁኑ ተቃውሞ ውስጥ የተሳተፉት መሰረታዊ ፍላጎታቸው በእርግጥ የሃይማኖት ነፃነት ጥያቄ ነውን? የአንድ አገር መንግስትስ  በሃይማኖት ውስጥ ጣልቃ ለመግባታ ስለምን ይገደዳል? በስልጣን ላይ ያለ አንድ መንግስት በሃይማኖት ስም የተቀነባበረና አገሪቱን ችግር ውስጥ የሚጥል አደጋ ሲመጣ እያየና መረጃዎችና ማስረጃዎች እያለውና እያወቀ ዝም ሊልስ ይገባዋል ወይ? ለዚህ ነው የተሰጡት መግለጫዎች እና ይልማ በቀለን በመሳሰሉ ሰዎች የቀረቡት ጽሑፎች ሚዛን የጎደላቸውና ታሪካዊ ምንጮችን ያላገናዘቡ የሆኑት፡፡
የዚህ ድረገፅ አዘጋጆች ካለው ውዥንብርና መወናበድ ባሻገር ያሉትን ታሪካዊ ምርምሮችን እና አቅጣጫ ጠቋሚ እውነታዎችን ማሳየት የተገደዱት ለዚህ ነው፡፡ ከገዢው ፓርቲ መርሆ የተነሳ በአገሪቱ ውስጥ ሃሳብን በነፃነት የመግለፅ የመናገርና የመጻፍ ነፃነት በእርግጥ አለ ማለት አይቻልም፡፡ ለዚህም ነው ብዙ ጋዜጠኞች በእስር ላይ የሚገኙት፡፡ ሰዎች የፈለጉትን እምነት የመከተልም ነፃነት በመጠኑ የለም ማለት ይቻላል፣ ይሁን እንጂ የአሁኑ የኢትዮጵያ ሙስሊሞች የተቃውሞ እንቅስቃሴ መሰረታዊው ጥያቄ የሃይማኖት ነፃነት ጥያቄ ሊሆን አይችልም፣ ምክንያቱም የሃይማኖት ነፃነት አልተነፈጋቸውምና፡፡ እንዲያውም በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ ሙስሊሞች ነፃነት ያገኙት በመለስ ዜናዊ አገዛዝ ስር መሆኑ ለማንም ግልፅ ነው፡፡ ታዲያ ለሙስሊሞች እንቅስቃሴ መሠረታዊው ምክንያት ምንድነው?


Monday, March 18, 2013

«ቦኪሜ ነህ ኢየሱስ» ዘማሪት ምርትነሽ

«የእግዚአብሔርም መልአክ ከጌልገላ ወደ ቦኪም ወጥቶ እንዲህ አለ፦ እኔ ከግብፅ አውጥቻችኋለሁ፥ ለአባቶቻችሁም ወደ ማልሁላቸው ምድር አግብቻችኋለሁ እኔም። ከእናንተ ጋር ያደረግሁትን ቃል ኪዳን ለዘላለም አላፈርስም፤ እናንተም መሠዊያቸውን አፍርሱ እንጂ በዚህች ምድር ከሚኖሩ ሰዎች ጋር ቃል ኪዳን አታድርጉ አልሁ። እናንተ ግን ቃሌን አልሰማችሁም፤ ይህንስ ለምን አደረጋችሁ? ስለዚህም። ከፊታችሁ አላወጣቸውም፥ ነገር ግን ያስጨንቋችኋል፥ አማልክቶቻቸውም ወጥመድ ይሆኑባችኋል አልሁ። የእግዚአብሔርም መልአክ ይህን ቃል ለእስራኤል ልጆች ሁሉ በተናገረ ጊዜ ሕዝቡ ድምፃቸውን አንሥተው አለቀሱ። የዚያንም ስፍራ ስም ቦኪም ብለው ጠሩት በዚያም ለእግዚአብሔር ሠዉ»መሣ 2፤1-5



Sunday, March 17, 2013

ክርስቶስ በአምላክነቱ ቃል ማዳን ሲችል ለምን ሥጋ መልበስ አስፈለገው?


የብዙ ሃይማኖቶች መምህራን «ኢየሱስ ክርስቶስ ፍጹም አምላክ፤ ፍጹም ሰው ነው» በማለት ይመሰክራሉ። ይህም እውነት ነው። ነገር ግን ከሦስቱ አካላት አንዱ አካል የሆነው እግዚአብሔር ወልድ በመለኮታዊ ሥልጣኑ ማዳን ሲችል ለምን ሥጋ በመልበስ በሞቱ አዳምንና ልጆቹን ማዳን አስፈለገው? ለሚለው ጥያቄ የጠራ መልስ የላቸውም። ሥጋ መልበስ ማለት አምላካዊ ስልጣኑን በመተው ራሱን ባዶ ማድረግ እንደሆነ ለመቀበል ሲቸገሩ ይስተዋላሉ። ይሁን እንጂ ሐዋርያው ጳውሎስ እንዲህ ሲል በትክክል ገልጾታል።

«እርሱ በእግዚአብሔር መልክ ሲኖር ሳለ ከእግዚአብሔር ጋር መተካከልን መቀማት እንደሚገባ ነገር አልቈጠረውም፥ ነገር ግን የባሪያን መልክ ይዞ በሰውም ምሳሌ ሆኖ ራሱን ባዶ አደረገ» ፊልጵ ፪፤፮-፯ 

ፍጹም ሰው ሆነ ስንልም መለኮታዊ ማንነቱን ተወ ማለት ሳይሆን አምላካዊ ሥልጣኑን ሸሸገ ማለታችን ነው። ከኃጢአት ብቻ በቀር እንደእኛ የተፈተነውም ለዚህ ነው። መለኮታዊ ስልጣኑን የመሸሸጉ ምክንያትም ፍጹም ሰው በመሆን ከአብ ጋር ያለውን መለኮታዊ ዕሪናውን  እንደተወ ሳይቆጥር እንደልጅ ለመታዘዝ ነው።  ብዙዎች ኦርቶዶክሳውያን የሆንን ሰዎች ልጅ ሆኖ መታዘዙን ልክ፤ ከአብ  ያነሰ አድርጎ እንደመቁጠር ስለምናስብ እንደነግጣለን። አማለደ፤ አስታረቀ፤ ታዘዘ የሚሉ ቃላትን መስማማት የወልድን ባሕርይ ህጹጽ አድርጎ  የሚያወርድ ነው በማለት ለመቀበል የማይፈልጉ አስተሳሰቦች ሞልተዋል። አምላካዊ ባህርይውን ለመጠበቅ ሲባል ፍጹም ሰው የሆነበትን ምስጢር በመሸርሸር ከማማለድ፤ ማስታረቅና መካከለኛ የመሆን ማንነቱ ለመሸሽ መሞከር  ምስጢረ ሥጋዌን በሽፍንፍኑ እንደመሻር ይቆጠራል። 

 ማማለድ፤ ማስታረቅና መካከለኛ መሆኑን አምኖ መቀበል ከሌለ ፍጹም ሰው እንደሆነ ማመን በፍጹም ሊመጣ አይችልም። በመለኮታዊ ሥልጣኑ ማዳን እየቻለ ሥጋ መልበስ ያስፈለገው በሰውና በእግዚአብሔር መካከል የነበረውን የጥል ግድግዳ ማፍረስ የሚችል ከኃጢአት ሁሉ ንጹህ የሆነ የእግዚአብሔር ልጅ በመካከል እንዲገባ በማስፈለጉ እንደሆነ አምኖ መቀበል የግድ ነው። ያለበለዚያ ነገረ ድኅነት የሚባል አስተምህሮ አይመጣም።
ቀድሞ ሰውና እግዚአብሔርን ሲያገናኝ የቆየው ሕግ ነበር። ሕጉ የሚያዘውን ሁሉ የሚያስፈጽሙ መካከለኞች ደግሞ ካህናቱ ናቸው። በሕግ ተቀባዮች በሕዝቡና በሕግ ሰጪው በእግዚአብሔር መካከል ያሉት መካከለኛ የሕግ አስፈጻሚዎቹ ራሳቸው ንጹህ መሆን ይጠበቅባቸው ነበር።  ይህንንም የስርየት መስዋዕት በማቅረብ መንጻት ግዴታቸው ነው። ከዚያም የሕዝቡን ሥርየት ሕጉን በመተግባር ያስፈጽማሉ። እንግዲህ ይህ መስዋዕት ዕለት ዕለት የሚደረግ ነው። እንደዚያም ተደርጎ ለሕጉ ፈጻሚዎች  ዘላለማዊ የሆነ ስርየትን ማስገኘት አይችሉም። ይህ መስዋዕት ምድራዊ ነው። ምክንያቱም በሰውና በእግዚአብሔር መካከል ትዕዛዝን የማፍረስ የጥል ግድግዳ በቀዳማዊው ሰው ጥፋት የተነሳ ተተክሎ ነበርና። 

ይህ የጥል ግድግዳ ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ መፍረስ ነበረበት። በሕዝቡና በእግዚአብሔር መካከል የነበረውን የጥል ግድግዳ በብቃት ለማፍረስ ደግሞ ኃጢአት የማያውቀው ሰው ያስፈልጋል። ክህነቱም ፍጹም ሊሆን ይገባል። ይህንንም ለማሟላት አምላክ ሰው በመሆን ያንን ደካማ ሥጋችን በመልበስ ከውድቀት ማዳን ነበረበት። በዚህም የተነሳ ከሦስቱ አካላት አንዱ አካል ወልድ በፈቃዱ የአብ የባህርይ ልጅ ሆኖ ሥጋችንን ለመልበስ በግብረ መንፈስ ቅዱስ በመካከላችን አደረ። እንደሰውነቱ ኃጢአት አያውቀውም። እንደካህንነቱ ዘላለማዊ ካህን ነው። እንደአዳኝነቱ ሞት አያሸንፈውም። እንደልጅነቱ የአባቱን ፈቃድ የሚፈጽም ነው። እንደስርየት መስዋዕትነቱ አንዴ፤ ግን ለሁል ጊዜ  የሚሆን ነው። ይህም የነበረውን ጥል አፍርሶ በአብ የተወደደ መካከለኛና ለሕዝቡ ኃጢአት ዘላለማዊ ሥርየትን ማስገኘት የሚችል ሊቀ ካህን ሆኗል።

Saturday, March 16, 2013

የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ ተማሪዎች ለመብት ጥያቄ እየጮሁ ናቸው፤ሰሚ አላገኙም!

  •  
  •  ቤተ ክህነትም አካባቢውን በፌዴራል ፖሊስ እያስጠበቀች ነው።
  •  
  • የምግብ አቅርቦት ከተቋረጠባቸው ሦስተኛ ቀኑ መሆኑ ተሰምቷል።

በቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ የአስተዳደር ጉድለት፤  የትምህርት ጥራትና የመምህራን ብቃት ጉዳይ ተማሪዎቹን ለዓመታት እያስጨነቀ የቆየና አቤቱታ ቢያቀርቡበትም መፍትሄ የራቀው ሆኖ መዝለቁ ይታወቃል። ሙስና የተስፋፋበት ሆኖ ቆይቷል። ለተማሪዎች ጥያቄ የሚሰጠው ምላሽ  ኃይል፤ ዛቻና ከትምህርት ገበታ ላይ ማባረር ሆኗል። ብዙ ጊዜ የተነገረለትን የአስተዳደርና የመብት ጥያቄ ጉዳይ ቤተ ክህነት ጆሮ ዳባ ልበስ ከማለትዋም በላይ መፍትሄ ብላ የያዘችው ጉዳይ ጣቷን ወደሌላ አካል መቀሰርና በሙስና ለበሰበሱ ሹመኞቿ ጋሻ በመሆን መከላከል ነው። አባ ጢሞቴዎስ የበላይ ጠባቂነቱን ወንበር እንደግል ርስት ከተረከቡበት ጊዜ አንስቶ ተማሪዎቹ የተለያዩ ጥያቄዎችን ቢያቀርቡም ለተማሪዎቹ አንድም ነገር ጠብ ካለማለቱም በላይ ችግሩ እንተንከባለለ ቀጥሏል።

Friday, March 15, 2013

እስልምና በኢትዮጵያ ታሪክ



ፎቶ ከ /britainfirst.org/


ኢህአዴግ ችግሮችን ለመፍታት የሚሞክርባቸው ጥሩ ያልሆኑ መንገዶቹና ሌላውን ለማሳመን የሚጓዝባቸው የህጻናት ጫወታ ዓይነት ስልቶቹ፤  እንከን ሲለቅም ለሚኖር ለሌላ ወገን ቀርቶ ዳር ቆሞ በአንክሮ ለሚታዘበውም ሰው ሳይቀር የሚያሳፍር ሆኖ ይገኛል። ሕዝቡ በፍርሃት ቆፈን ውስጥ ወድቆ፤ «ዝምታ ቤቴ» ቢል የወደደው መስሎት ከሆነ የውድቀቱ መጀመሪያ መሆኑ ማወቅ ይገባዋል። ለሀገርም፤ ለወገንም የማይበጅ ፍጻሜ ይኖረዋል።  የአሜሪካ ብሔራዊ የደኅንነት ምክር ቤት ባደረገው ጥናትና የመረጃ ትንተና ውጤት መሠረት 2030 በዓለም ላይ በውስጣቸው በሚነሳ ሽኩቻና በአካባቢ ጥበቃ ጉዳዮች ምክንያት ሊፈራርሱ ከሚችሉ ሀገሮች አንዷ ኢትዮጵያ  ናት ሲል ያወጣውን መረጃ ሟርት ነው ብሎ የሚያልፍ ከሆነ ውስጡን ማየት አቅቶታል ማለት ነው። መልኳን በመስታወት ውስጥ ያገኘችው ዝንጀሮ «አቤት የፊቷ ማስቀየም፤ በዚያ ላይ የመቀመጫዋ መመለጥ» ብላ አክፋፍታ መናገሯ የሚያመለክተው ራሷ ምን እንደምትመስል ምንም ግንዛቤ የሌላት በመሆኑ ነው። የኢህአዴግም የቁጣ ፊት እያስቀየመ፤ መቀመጫው ሁሉ እየተመላለጠ መጥቶ ሳለ የሌላውን በማየት ሲሳለቅ ሀገሪቷን ይዞ እንዳይወድቅ እንሰጋለን። በተለይም በሃይማኖት ጉዳይ ላይ ለፖለቲካው የሚመች ሥራ ለመሥራት ብቅ ጥልቅ ማለቱ ከእሳት ጋር መጫወት ይሆናል። ኦርቶዶክሱ ውስጥ ውስጡን ቆስሏል። የእስልምናውንም አያያዝ «ቀድሞ ነበር እንጂ መጥኖ መደቆስ፤ አሁን ምን ያደርጋል፤ ድስት ጥዶ ማልቀስ» በማለት እየተናገርንበት ነው። ጀሃድ በለው፤ ግፋ በለው፤ እሰር በለው የትም አድርሶ አያውቅም። መንግሥት ሰከን ብሎ በማስተዋልና በጥበብ መጓዝ ካልቻለ ስለወደድነው አይቆምም፤ ስለጠላነው አይሞትም። ተግባር ራሱ ወደመጨረሻው ምዕራፍ ይገፋዋልና ያንን ስንመለከት የሚያሳስበን ብዙ ነገር አለ።   
ምንም እንኳን በመንፈሳዊ ጉዳዮች ላይ ብታተኩርም ሀገራችን ለእግዚአብሔር መንግሥት የምትታዘዝ፤ ሰላምና ፍቅር የሰፈነባት፤ ሕዝቦች በነጻነት የሚኖሩባት ሀገር እንድትሆን ካለን ዓላማ አንጻር ማኅበራዊው፤ ፖለቲካዊውና ኢኮኖሚያው ሁኔታ ያሳስበናልና እንደዜጋ በዚህ ላይም ከወገንተኝነት በጸዳ ያለውን እውነታ ብሎጋችን ትናገራለች። ኢህአዴግ እንደፖለቲካ ሽንፈት ሳይሆን ለሀገር ሰላምና መረጋጋት ሲል በየምክንያቱ ያሰራቸውን ፖለቲካዊና ሃይማኖታዊ ሰዎች በመፍታት ትኩሳቱን ያብርድ እንላለን። አሁን ባለው ሁሉን ነገር የመቆጣጠር ግትርነትና ሥነ ልቡና ሰልቦ አደብ የማስገዛት ስልት ወንጀለኛ ቢሆን እንኳን እንደትክክል ቆጥሮ የሚያምነው ወገን ማግኘት ከማይችልበት ደረጃ ደርሷል። «ሆድ ለባሰው ማጭድ አታውሰው» እንዲሉ ከኑሮው ውድነት ጋር ተስፋ አድርጎ «ሌላ ቀንም አለ» እያለ በተስፋ የሚኖርበትን ሃይማኖት በሆነ ባልሆነው እየነካኩ ዝም ብሎ የተኛውን መቆስቆስ  ወደበጎ አያደርስም።  ለማንኛውም መንግሥት ወደክንዱ ሳይሆን ወደልቡ ይመለስ።  «እመ እግዚአብሔር ኢሐነጸ ቤተ፤ ከንቶ ይጻምዉ እለ የሐንጹ። እመ እግዚአብሔር ኢዐቀበ ሀገረ ከንቶ ይተግሁ እለ ይኄልዉ»   «እግዚአብሔር ቤትን ካልሠራ፥ ሠራተኞች በከንቱ ይደክማሉ እግዚአብሔር ከተማን ካልጠበቀ፥ ጠባቂ በከንቱ ይተጋል» መዝ ፻፳፯፤፩ ጉልበት ብቻውን ልብ ለሌለው ደርግም አልጠቀመም።
ይህ በእንዲህ እንዳለ ከታች ለማንሳት ወደፈለግነው ጉዳይ እናመራለን። ኢህአዴግ ከሚታማበት ችግሮች አንዱ እስከአሁን ድረስ በየሚዲያው የምንሰማቸውና የምናነባቸው ነገሮች የእስልምና ሃይማኖት መብት ኢትዮጵያ ውስጥ እንደተረገጠ እያስተጋቡ ሆነው መገኘታቸው ነው። ከዚህ በፊት በዚህ ጉዳይ ላይ በሁለት ክፍል ብሎጋችን ጽፋለች። እውነት ኢትዮጵያ ውስጥ ከሌሎች ሃይማኖት በተለየ የእስልምና ሃይማኖት ጭቆና አለ? ብለን ጠይቀናል። ከዚያም በተለየ መልኩ በአፍሪካው ክፍለ አህጉር የእስልምና አክራሪነት እየሰፋ አልመጣም? ኢትዮጵያስ ከእስልምናው የአክራሪነት መንፈስ እንቅስቃሴ ውጪ የሆነች ሀገር ናት? ብለንም ጠይቀናል። ኢህአዴግን በመጥላት ወይም የሚጓዝባቸውን መጥፎ ስልቶች በመመልከት ብቻ ያፈጠጠውን ሀቅ መካድ ይቻላል? ብለናልም። የኢህአዴግን ድርቅናና ግትርነት ለመነቅነቅ አሁን ካለው የትኛውም አኩራፊ ኃይል ጋር አንድ መሆን ነው የሚል መርህ እውነቱን በመጨፍለቅ ወደእርስ በእርስ ፍጅት ሊያስገባን ይችላል። ስለዚህም በኢትዮጵያችን ውስጥ ስላለው የእስልምና እንቅስቃሴ አህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ ጠባዩን የተመለከተ የጥናት ጽሁፎችን የዳሰሱ መረጃዎችን ለአስተዋዮች ለማቅረብ ወደናል። እውነታውን ማሳየት ችግሩን አውቆ በጋራ የምንኖርበትን ሀገር ለመገንባት ይረዳናል። ምድሪቱን እንድንጠብቃትና እንድንንከባከባትም ከእግዚአብሔር አደራ አለብን። ዘፍ ፪፤፲፭
እስልምና በኢትዮጵያ ታሪክ በሚል ርዕስ ከሚቀርበው ሦስት ሰፋፊ ተከታታይ ጽሁፎች ውስጥ የመጀመሪያውን እነሆ ብለናል።

ክፍል  
             የጽሑፉ ባለቤቶችለእስልምና መልስ» አዘጋጆች ነው)