Sunday, September 30, 2012

ክርስቲያን በፖለቲካ ውስጥ በንቃት መሳተፍ ይኖርበታልን?

                                             ከተስፋዬ ሮበሌ
                                                              ወርኀ ጥር 2004 .
                                                                                                         እንደ ኢትዮጵያውያን የዘመን አቈጣጠር
                                                                                                         ግራንድ ራፒድስ ፣ ሚሽገን

በአንድ መስቀለኛ መንገድ ላይ በየቀኑ አሠቃቂ አደጋ ይከሠታል፤ ከአደጋው የተነሣም በርካታ ሰዎች ይሞታሉ፤ ከፍተኛ ንብረትም ይወድማል፡፡ ሁኔታው ያሳሰባት፣ በዚህ አካባቢ የምትገኝ አንዲት ቤተ ክርስቲያን፣ የአደጋው ሰለባ የሆኑትን ሰዎች የሚረዱ ሐኪሞችንና ነርሶችን በማሠማራት የአካባቢውን ማኅበረሰብ በንቃት ማገልገሉን ሥራዬ ብላ ተያያዘችው፡፡ የሕዝብና የመኪና ቊጥር ዕለት በዕለት እየጨመረ በመሄዱ ምክንያት ግን፣ ችግሩ በዛው መጠን ተባብሶ ቀጠለ፡፡ ይህች ቤተ ክርስቲያን እርዳታዋን በመጠንና በዐይነት ማሳደግ ብቻ ሳይሆን፣ አንድ መለስተኛ ሆስፒታል አደጋው በሚከሠትበት አካባቢ አቋቋመች፡፡ ይህ ሠናይ ምግባር የሰለባዎቹን ጤንነትና ሕይወት ከመታደግ አንጻር ብዙ ጠቀሜታ ቢኖረውም፣ ችግሩን ግን ከምንጩ ማድረቅ አልቻለም፡፡ ምክንያቱም የችግሩ ምንጭ የተሳሳተ የመንገድ ዲዛይን ነውና፡፡ በመስኩ የሠለጠኑ መሐንዲሶች መንገዱ በአዲስ መልክ ዲዛይን ቢደረግ ችግሩ ሊፈታ እንደሚችል የትራፊክ ፖሊስ ጽሕፈት ቤቱን በቃልም ሆነ በጽሑፍ ቢያሳስቡም፣ ባልታወቀ ምክንያት ጽሕፈት ቤቱ ጆሮ ዳባ ልበስ አለ፡፡ በየዘመናቱ ቤተ ክርስቲያን ክርስቶስ ሰጠኝ የምትለውን ዐደራ ከዳር ለማድረስ፣ በሚያስፈልገው ሁሉ በመውተርተር ላይ ትገኛለች፡፡ ቤተ ክርስቲያን ነዳያንን በማብላት፣ የታመሙትን በማስታመም፣ ለመበለቶች ዳኛ በመሆን ጥልቅ ስም አላት፡፡ በርግጥም ቤተ ክርስቲያን የምስካየ ኅዙናን መንበር ናት፡፡ ወደ ፊትም ይህንኑ ግብረ ሠናይ ምግባሯን አጠናክራ መቀጠል እንዳለባት አያጠያይቅም፡፡ ነገር ግን ችግሩን በዘላቂነት መፍታት የምትችለው የተሳሳተ ፖሊሲ ያስከተለውን ፍሬ በመልቀም ብቻ ሳይሆን፣ መንግሥት ትክክለኛ ፖሊሲ እንዲነድፍ ስታስተምር፣ መንግሥት ሲሳሳትም ስሕተቱን ስሕተት ነው ማለት ድፍረትና ክህሎት ሲኖራት ብቻ ነው፡፡
ፖለቲካ፣ የሕዝብ አስተዳደር መዘውር ነው፡፡ ቤተ ክርስቲያን የመዘውሩ ነገር ምን ተዳዬ የምትል ከሆነ ግን፣ በመዘውሩ እክል ምክንያት በሚከሠቱ ችግሮች ላይ ብቻ መጠመዷ አይቀሬ ነው፡፡ ይህ አስተሳሰብ በክርስቲያኑ ማኅበረሰብ ውስጥ ሠርጾ በመዝለቁ ምክንያት፣ ወደ ፖለቲካው ዓለም የሚገቡ ወይም የፖለቲካ ሳይንስ የሚያጠኑ የቤተ ክርስቲያን ልጆች፣ ከመንፈሳዊነት እንደ ጐደሉ ምናልባትም ክርስቶስን ከመከተል እንዳፈገፈጉ ይታሰባል፡፡ ክርስቲያን የዓለም ብርሃንነው፣ የዓለም ጨውነው የሚለው የቃለ እግዚአብሔር ትምህርት፣ በፖለቲካ ሕይወት ውስጥ ጨለማና አልጫ ነው ያለው ማነው? እንዲያውም ክርስቲያኖች በንቃት ሊሳተፉበት የሚገባ፣ ጨውነታቸውንና ብርሃንነታቸውን ሊገልጡበት የሚገባው የሕይወት ክፍል ፖለቲካ ነው፡፡ እንደ ንጉሥ ዳዊት፣ እንደ ንጉሥ ሰሎሞን ያሉ የእምነት አበው ፖለቲከኞች ነበሩ፡፡ እንደ ነቢዩ ናታን፣ ነቢዩ ኢሳይያስ፣ ነቢዩ ዳንኤል፣ ነቢዩ አሞጽ ወዘተ ያሉ ነቢያት ደግሞ መንግሥትን በማማከር አገልግለው እንዳለፉ ገድላቸው የናገራል፡፡ መንግሥት ሲስት ይገሥጹና ከስሕተቱ እንዲመለስ መንገድ የመላክቱ እንደ ነበር ቅዱስ ቃሉ ያስተምረናል፡፡ እንዲያውም ባልንጀራህን/ጐረቤትህን እንደ ራስህ ውደድ የሚለው የክርስቶስ ቃል ከየትኛውም የትምህርት ዘርፍ ይልቅ ፖለቲካን የሚያመላክት ነው (ማቴዎስ 22÷39)፡፡ ለተጠቃው ከመጮኽ፣ የታረዘውን ከማልበስ፣ ፍትሕ ያጣውን ለፍትሑ ከመሟገት በላይ ምን ጐረቤትን መውደድ አለ? እግዚአብሔር አምላክ ለንጉሥ ሰሎሞን የሰጠው ስጦታ የፖለቲካ ስጦታ ነው፡፡ ይህ ደግሞ ፖለቲካ የጸጋ ስጦታ መሆኑን የሚያጸና ነው፡፡
ወገኖቼ ክርስትና የማይዳስሰው የሕይወት ክፍል የለም፡፡ ክርስቲያኖች በፖለቲካው ውስጥ በመግባት ብርሃንና ጨው መሆን ካልቻሉ፣ ክርስቲያን ያልሆኑና እኵይ ሥነ ምግባር ያለቸው ሰዎች የፖለቲካውን መድረክ መቈጣጠራቸው አይቀሬ ነው፡፡ እየሆነም ያለ ይመስላል፡፡ ወገኖቼ፣ ኀጥኣን ከፍ ከፍ ሲሉ ሕዝብ ይጨነቃልየሚለው የጠቢቡ ሰሎሞን አነጋገር ፖለቲካን ታሳቢ ያደረገ ነው፡፡ ወዲህም ወዲያም ብታገላብጡት ሐቁ ይኸው ነው፡፡ ክርስትናና ፖለቲካ ዐይንና ናጫ ናቸው ወዘተረፈ የሚለው ወልጋዳ አስተሳሰብ የብዙዎችን ጐዳና አሰናክሏል፡፡ ከዚህም የተነሣ ብዙ የቤተ ክርስቲያን ልጆች፣ ስለ ፖለቲካ ያለን ዕውቀት በየጋዜጣው ላይ ከሚጻፉ መጣጥፎች አንዲሁም በየዜና አውታሮች ከሚተላለፉ ፕሮግራሞች የዘለለ አይደለም፡፡ ይህ ዐይነቱ ዕውቀት ደግሞ፣ ለፕሮፖጋንዳ ውዥንብር በቀላሉ ይዳረጋል፡፡ ቃላትን ቀምሮና እውነትን አስታኮ የመጣ ብልጣብልጥ ፖለቲካኛ ሁሉ ወዳሻው ቦታ ይዞት ይሄዳል፡፡ ወደድንም ጠላንም የአገሬ ጕዳይ ግድ ይለኛልየምንል ሰዎች ሁሉ፣ ቢያንስ መሠረታውያን የሚባሉትን የፖለቲካ መርሖች በቅጡ ልናውቃቸው ግድ ነው፡፡ ለምሳሌ ፖለቲካ በአገር ግንባታ ውስጥ ያለው ቦታ እስከምን ድረስ ነው? ሰብአዊ መብት ማለት ምን ማለት ነው? ኢሕአዴግ፣ አብዮታዊ ዴሞክራሲብሎ የሚጠራው የፖለቲካ አካሄድ፣ ከምዕራባውያኑ ለዘብተኛ (ሊብራል) ዴሞክራሲ በምን ይለያል?
ይህ የፖለቲካ ፍልስፍና በአገሪቱ ፖለቲካና ምጣኔ ሀብት የሚያስከትለው አሉታዊ መዘዝም ሆነ አዎንታዊ እንድምታ እንዴት ይተነተናል? ክርስቲያኖች በፖለቲካ ውስጥ ተሳትፎ ማድረግ አለባቸው ወይስ የዳር ታዛቢ መሆናቸው ብቻ ጥሩ ዜጋ ያሰኛቸዋል? ሕዝባዊና ማኅበራዊ ተቋማት ማለትም የመገናኛ ብዙኃን፣ ፖሊስ፣ ፍርድ ቤቶችና የምርጫ ቦርድ ከመንግሥት ጣልቃ ገብነት ፍጹም ነጻ መሆን አለባቸውየሚባለው ለምንድን ነው? ነጻናቸው የሚባል ከሆነስ ደግሞ ነጻነታቸው በምን መስፈርት ይለካል? ፖለቲካ ለምጣኔ ሀብት ሕግጋት ይገዛል ወይስ ምጣኔ ሀብት ለፖለቲካ ሎሌ ያድራል? ወይስ ሁለቱም ለየቅል ናቸው? አንድ አገር ፖለቲካ ሰብአዊ መብትን እንዳሻው እየጨፈለቀ የምጣኔ ሀብት በረከት ሊያመጣ ይችላል? የማይቻል ከሆነ የቻይና ጕዳይ እንዴት ይታያል? የመናገር መብት፣ የመጻፍ መብት፣ የመደራጀት መብት ወዘተ የሚባሉት ጕዳዮች፣ በሰብአውያን ሕይወትና ዕድገት ውስጥ ያለቸው ስፍራ ምንድን ነው? መጽሐፍ ቅዱስ ስለ ፖለቲካ የሚያስተምረው ትምህርት ምንድን ነው

Saturday, September 29, 2012

በሀገራችን ተጨባጭ ሁኔታ የሃይማኖት ብሔርተኝነት አደገኛ ነው!

«መጪውን ጊዜ በሃይማኖት ብሔርተኝነት መዋጀት» ይገባል። (ማኅበረ ቅዱሳን )

ምንጭ፡- ስምዐ ጽድቅ ጋዜጣ 20ኛ ዓመት ቁጥር 1 2005 ዓ.ም.
ሃይማኖታዊ ብሔርተኝነት ማለት ምን ማለት ነው?
በሳንዲያጎ ግሮስሞንት ኰሌጅ ፕሮፌሰር የሆኑት ዶ/ር ጆን ኦክስ የሃይማኖት ብሔርተኝነትን በተነተኑበት ጽሁፋቸው እንዲህ ሲሉ ያስቀምጣሉ። የሃይማኖት ብሔርተኝነት /Religious Nationalism/ የሚከተሉትን አራት ባህርያት ያሟላ ወይም ለማሟላት የሚሰራ ሲሆን በአንድ ሀገር ውስጥ ህልውናው ይረጋግጣል ይላሉ።
1/ የሀገሪቱ መንግሥት ለአንድ የተለየ  የሃይማኖት ተቋም ብቻ የእለት ከእለት እንቅስቃሴ የገንዘብ ድጋፍ የሚሰጥ ከሆነ፣
2/ የሃይማኖቱ ተቋም፦ ሞራልን፤ ግብረ ገብንና ሥነ ምግባርን በተመለከቱ በመንግሥታዊው ጉዳዮች ላይ ጫና ማሳረፍ ከቻለ፤
3/  በሀገሪቱ ውስጥ ያሉ ሌሎች ሃይማኖቶች በመንግሥት የሚደገፈውን ሃይማኖት መብት መጠበቅ ከተገደዱ፤
4/ መንግሥታዊ ድጋፍ ያለው ይህ ልዩ ሃይማኖት በፖለቲካው መስክ የመንግሥቱ ደጋፊ ሲሆን  በአንድ ሀገር ውስጥ የሃይማኖት ብሔርተኝነት አለ ማለት ይቻላል በማለት ያብራራሉ።
ለምሳሌ ኢራን፤
በኢራን ውስጥ ክርስቲያኖች፤ ቡድሂስቶችና አይሁዳውያን ያሉ ቢሆንም መንግሥታዊው ሃይማኖት ግን እስልምና ነው። እስልምናው በመንግስት በጀት ይደገፋል፤ ሃይማኖታዊውን ተቋም የሚጻረር አንድም ሕግ አይወጣም፤ ሌሎች ሃይማኖቶች የእስልምናን ብሔራዊነት የበላይነት የመጠበቅ ግዴታ አለባቸው ( ከእስልምና ሰው ሰብከው ቢወስዱ ይቀጣሉ፤ እስልምና ግን ከእነሱ ሰብኮ ቢወስድ አይጠየቅም)፤ መንግሥታዊው ሥልጣን  ከእስላም ሰዎች እጅ እንዳይወጣ ሃይማኖቱ ድጋፍ ይሰጣል።
ግሪክና፤ ራሺያም በተወሰነ መልኩ ተመሳሳይ ሃይማኖታዊ ብሔርተኝነት ይታይባቸዋል። በሀገሪቱ ውስጥ ብዙ ሃይማኖታዊ ሰዎች ቢኖሩም የመንግሥቱን ስልጣን የሚረከበው ሰው ቃለ መሃላ የሚፈጽመው በመንግሥቱ ተቀባይነት ባለውና በሚደገፈው የኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ውስጥ በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ እጁን ጭኖ እንጂ በፌዴራሉ ዳኛና በዱማው ፊት ብቻ አይደለም።
የሃይማኖት ብሔርተኝነት /Religious Nationalism/ በራሱ ሃይማኖታዊ ተቋም ውስጥ የተለየ ሃሳብና ጥያቄን ለማስተናገድ በፍጹም ቦታ አይሰጥም ብቻ ሳይሆን ባለው የኃይል ተደማጭነት የተነሳ ልዩ ሃሳብና ጥያቄ ወይም ተቃውሞ አቅራቢዎችን የመጨፍለቅና የማስጨፍለቅ አቅም አለው።
ለምሳሌ ኢትዮጵያ ውስጥ ወደ ሃይማኖት ብሔርተኝነት ጎዳና እያዘገመ ያለው ማኅበረ ቅዱሳን የተለየ ሃሳብና አቋምን የማይቀበልና እንደነዚህ ዓይነት ልዩነቶች ለማስተናገድ ስለማይችል የሚወስደው እርምጃ  ማስደብደብ፤ ማሳሰር ብሎም ከተመቸው ማስገደል ነው። በመምህር ጽጌ ስጦታውና በዲ/ን ሙሉጌታ ወ/ገብርኤል ላይ የደረሰውን ድብደባ ማስታወስ ይሏል።
ብሔር ማለት በቁሙ ወሰን፤ ክልል፤ድንበር፤ ጠረፍ ያለው  ሀገር ማለት ነው። የሃይማኖት ብሔርተኝነት ማለትም የራሱ ድንበር፤ አጥር፤ክልል ወሰን ያለው የሃይማኖት ተቋም  ማለት ነው። የኮርኔል ዩኒቨርሲቲ የስነ ሃይማኖት ሌክቸረር ማይክል ኤሪክ ዳይሰን ስለሃይማኖት ብሔርተኝነት እንደዚህ ይላሉ። "No religion has a particular right on the nation»  በሀገሪቱ ውስጥ የተለየ መብት ያለው ሃይማኖት የለም»
ታዲያ የሃይማኖት ብሔርተኝነትን ማኅበረ ቅዱሳን የሚያቀነቅነው ለምንድነው? ምናልባት ከአባ ጳውሎስ በኋላ የፓትርያርክነቱ  ተራ የወሎዬዎች ነው እየተባለ የሚዘፈነውን በመስማቱ ሃይማኖታዊ ብሔር እንጂ ጎጣዊ ብሔር በቤተክርስቲያን የለም ለማለት ፈልጎ ይሆን?  የብሔር ድጋፍና ጥላቻ እንግዳ ነገር አልነበረምና ሹመቶቹን ሁሉ በእግዚአብሔር ፈቃድ ላይ ማላከክ ተገቢ አይደለም። የእግዚአብሔርን ፈቃድና እውቅና ማቀላቀል አይገባም። ሰዎች የእግዚአብሔርን ፈቃድ ሲከተሉ፤ ፈቃዱ ይፈጸምላቸዋል። የልባቸውን አሳብ ሲከተሉ ደግሞ  የልባቸውን መንገድ እንዲሄዱ እግዚአብሔር እውቅና ይሰጣቸዋል እንጂ በሁሉም ሹመቶች ላይ የእግዚአብሔር ፈቃድ የለም።
እንደ ልባቸው ሥራ ተውኋቸው፥ በልባቸውም አሳብ ሄዱ» መዝ 81፤12
እስራኤላውያን ሳኦል ይነግስ ዘንድ የእግዚአብሔር ፈቃዱ ባይሆንም የልባቸውን አሳብ አይቶ ሳሙኤል ቀብቶ እንዲያነግስላቸው እግዚአብሔር እውቅናውን ሰጥቷል።
« እግዚአብሔርም ሳሙኤልን አለው። በእነርሱ ላይ እንዳልነግሥ እኔን እንጂ አንተን አልናቁምና በሚሉህ ነገር ሁሉ የሕዝቡን ቃል ስማ» 1ኛ ሳሙ 8፤7
ስለዚህ ሰዎች በቡድንና በጎጥ እየተደራጁ የሚያደርጓቸውን ሹመቶች ሁሉ በእግዚአብሔር ፈቃድ እንደተፈጸመ ለማድረግ ቢሞክሩ ከእግዚአብሔር ቃል አንጻር ሚዛን አይደፋም።  እንደማኅበረ ቅዱሳን ዜና ዘገባ ከዚህ በፊት በቡድንና በፖለቲካ ድጋፍ የተደረገ የፓትርያርክ ሹመት እንዳልነበረ  በመቁጠርና ዛሬ እንደዚህ ዓይነት አስተሳሰብ መከሰቱን በሚያሳብቅ መልኩ የሃይማኖት ብሔርተኝነትን ወደማራገብ መሸጋገሩ ጉንጭ አልፋ ስነ ሞገት ከመሆን አያልፍም። ምክንያቱም በሁላችንም ዘንድ ያለው እውቀት ያንን አያሳይምና ነው። ያለን መረዳት ከዚህ በፊት የቡድን ወይም የፖለቲካ ድጋፍ እንደነበረ ሲሆን የከዚህ በፊቱ የቡድንና የፖለቲካ ድጋፍ ምርጫ መቀጠል የለበትም ነው ሊባል የሚችለው። ይህ እውን ሊሆን የሚችለው ደግሞ በእግዚአብሔር ላይ በመታመን እንደ ሐዋርያው ማትያስ ምርጫ በመንፈስ ቅዱስ እጣ ሰጪነት  ላይ በመጽናት ብቻ ነው። (ሐዋርያም ማትያስ አልኩኝ እንጁ አባ ማትያስ ዘካናዳ ወይም አባ ማትያስ ዘአሜሪካው አላልኩም)። ምርጫ ምንም ዓይነት «የሃይማኖት ብሔርተኝነት» ሳይጨመርበት መሆን ይገባዋል። ሃይማኖታዊ ብሄርተኝነት የሚታመነው በሃይማኖታዊ ወግና ባህል ላይ እንጂ በእግዚአብሔር አሠራር ላይ ስላይደለ የከዚህ በፊቶቹ  ስህተቶች እንዳይደገሙ ለማድረግ ዋስትና አይሰጥም።
ከዚህ አንጻር ማኅበረ ቅዱሳን በሃይማኖት ብሔርተኝነት እንቁም በማለት ጥሪ ሲያቀርብ ምን ማለቱ ነው?
ሁሉም ሃይማኖት የየራሱን እምነት አጥብቆ መያዝና መከተል ባህርያዊ ነው። ነገር ግን ችግሩ የሚመጣው «የኔ ብቻ» የሚል ጽንፍ ሲከተለው ነው። እግዚአብሔር አሜሪካና ሕዝቧን ይባርክ ማለት ለራስ የማሰብ አንድ አካል ነው። ነገር ግን እግዚአብሔር አሜሪካና ሕዝቧን ባርኳል ማለት ሌላ ነገር ሲሆን ይህም «እኔ ብቻ» የሚለው ጽንፍ «ኢራንን አልባረከም» እንደማለት በመሆኑ ራስን በሁሉን ዓቀፍነት ዓይነት ማየት አደገኛ ነው በማለት የኮርኔሉ ሌክቸረር ዳይሰን ያሰምሩበታል።
« Religious nationalism can also give a sense of exclusivity»

Wednesday, September 26, 2012


ውድ የደጀ ብርሃን ብሎግ ተከታታዮች፤

በፅሑፍ፤በሃሳብ፤ በገንቢ አስተያየት፤ ትችትና ነቀፋ አብራችሁን ለዘለቃችሁ ሁሉ በእግዚአብሔር ስም እጅግ በጣም እናመሰግናለን።

"....ለኢትዮጵያ እና ለኢትዮጵያውያንስ ምን ተናግረው ይሆን?

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ እና ጠቅላይ ሚ/ር መለስ ዜናዊ በእስትንፋሳቸው መጨረሻ ስለ ራሳቸው፣ ለኢትዮጵያ እና ለኢትዮጵያውያንስ ምን ተናግረው ይሆን…?

ይህ መጣጥፍ በሪፖርተር ጋዜጣ የእሁድ እትም በፍቅር ለይኩን የተባሉ ጸሐፊ ካስነበቡት ጹሑፍ ለጦማራችን በሚመስማማ መልኩ መጠነኛ ማሰተካከያ ተደርጎበት የተወሰደ ነው፡፡

 ‹‹እግዚአብሔር ሆይ ሁሉንም ነገር ለአንተ እተዋለሁ. . . አሜን!›› (በቅርቡ የሞቱት የጋናው ፕሬዝዳንት ፕሮፌሰር ሚልስ ከመሞታቸው በፊት ከተናገሩት የተወሰደ፡፡)
ሞት የሰው ልጆች ሁሉ አይቀሬ የሆነ የሕይወት ዕጣ ፈንታ ነው፡፡ ትልቁ ቁም ነገር በምድር ላይ በኖርንበት ወይም እንድንኖርበት በተሰጠን ዘመን የሠራነው ደግ/መልካምም ሆነ ክፉ ሥራችን ግን ሁሌም ከመቃብር በላይ ቋሚ ሀውልታችን ወይም ቅርሳችን ሆኖ እንድንታወስ ሊያደርገን እንደሚችል በቅጡ ማሰብ ይመስለኛል፡፡
ሰዎች ስለ ሞት የተለያየ አመለካከት አላቸው፡፡ ለአንዶንዶች ሞት ትርጉም የለሽ ጸጥታ ነው፡፡ ለሌሎች ደግሞ ሞት ዘላለማዊ እረፍት ነው፡፡ ለአንዳንዶች ሞት ምስጢራዊ እና ረቂቅ ነገር ነው፡፡ በክርስትናው ዓለም ውስጥ ላለን በርካቶች ደግሞ ሞት ወደ ዘላለማዊው፣ ፍፁም ሰላም እና እረፍትን ወደ ተሞላው ሰማያዊ ዓለም እንደ መሸጋገሪያ ድልድይ የሚቆጠር ነው፡፡
ስለ ሞት ያለን ግንዛቤ፣ ትንታኔ እና ፍልስፍና እንዳለንበት እና እዳደግንበት ማኅበረሰብ የኑሮ ልማድ፣ ባሕል እና እምነት/ሃይማኖት የተለያየ ፍቺ ይሰጠዋል፡፡ ሞት የቅርባችን እና የዕለት ተዕለት ክስተት የመሆኑን ያህል በአንፃሩ ደግሞ መቼም የማይለመድ እንግዳ ክስተት ሆኖ መቀጠሉ ለብዙዎቻችን እንቆቅልሽ ነው፡፡ ምነው በአዲሱ ዘመን፣ በወርኻ አደይ፣ ምድር፣ ተራሮች እና ሜዳዎች፣ ጋራ እና ሸንተረሩ በአበቦች አምረውና ተውበው በሚያጌጡበት፣ ሰዎች ሁሉ በአዲስ ራእይ ሕይወትን ውብ እና ፍቅርን የተሞላች ለማድረግ ብሩህ ተስፋን ሰንቀው ‹‹ጉልበቴ በርታ በርታ!›› በሚሉበት ውብ እና ተወዳጅ በሆነችው በወርኻ መስከረም ምን ነክቶህ ነው እንዲህ ሞት ሞት የሚሸት ጹሑፍ ምነው!? እረ…! ደግም አይደል የሚሉኝ ሰዎች አይጠፉም ብዬ እገምታለሁ፡፡
ግና ወደድንም ጠላንም መራሩ እውነታ ሞት ለሁላችንም የማይቀር ዕዳ መሆኑ ነው፡፡ ሞት የሁላችንም ዕጣ ፈንታ መሆኑ ማንኛችንም ብንሆን ለአፍታም ያህል ቢሆን እንዘነገዋለን ብዬ ለመናገር አልደፍርም፡፡ ስለዚህም ሞት ሲመጣ አማክሮ፣ ጊዜ እና ወቅትን ተከትሎ አይደለምና ስለ ሞት ለማውራት ምቹ ጊዜ፣ የተመረጠ ሰዓት ሊኖር ይችላል ብዬ አላስብም፡፡ ሞት አዲስ ዘመን፣ ወርኻ ክረምት፣ በጋ ወይም ጸደይ፣ ትንሽ፣ ትልቅ፣ መሪ ተመሪ፣ ንጉሥ፣ አገልጋይ፣ ሕጻን፣ አዛውንት… ወዘተ አይልምና፤ ለዚህም ነው በለመለመ ብሩህ ተስፋ እና ራእይ ሕይወትን ውብ እና ጣፋጭ ለማድረግ መልካም ምኞታችንን በምንገልጽበት በአዲሱ ዘመን መባቻ ስለ ሞት ለማውራት መጨከኔ፡፡
    የዕብራውያን ጸሐፊ የሆነው ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ፡- ‹‹ለሰዎችም አንድ ጊዜ መሞት ከእርሱም በኋላ ፍርድ ተመደቦባቸዋል፡፡›› (ዕብ ፱፣፳፯) በማለት የሞትን አይቀሬነት ያስገነዝበናል፡፡ ሐዋርያው ጳውሎስ እንደገናም በሮሜ መልእክቱ፡- ‹‹በአዳም ኃጢአት ምክንያት ሞት በሰው ልጆች ሁሉ ላይ መንገሱን እና የዚህ የሞት ኃይል በክርስቶስ ኢየሱስ ሞት ድል መነሳቱን እና በክርስቶስ ሞት ምእመናን የዘላለም ሕይወትን እንደታደሉ›› እንዲህ ይተርካል፡- ‹‹በአንዱም (በአዳም) በደል ሞት በአንዱ በኩል ከነገሠ፣ ይልቁን የጸጋን ብዛት እና የጽድቅን ስጦታ ብዛት የሚቀበሉ በአንዱ በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል በሕይወት ይነግሣሉ፡፡›› (ሮሜ ፭፣፲፯) ይለናል፡፡

   ጌታችን እና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም በወንድሟ በአልዓዛር ሞት እጅጉን ልቧ ተሰብሮ እና ሁለንተናዋ በሀዘን ደቆ በእግሩ ሥር ተደፍታ እያነባች፡- ‹‹ጌታ ሆይ አንተ በዚህ ኖረህ ቢሆን ኖሮ ወንድሜ ባለሞተ ነበር!›› ላለችው ለማርታ፡- ኢየሱስም፡- ‹‹ትንሣኤ እና ሕይወት እኔ ነኝ፤ የሚያምንብኝ ቢሞት እንኳን ሕያው ይሆናል፡፡›› በማለት በእርሱ (በሕያው እግዚአብሔር ልጅ) የሚያምኑ ሁሉ የዘላለም ሕይወት እንዳላቸው በቃሉ አረጋገጦላታል፡፡ ቅዱስ ዮሐንስ በቅዳሴው ‹‹ሞትን ይሽረው ዘንድ ሞተ!›› በማለት የሞት ኃይል በክርስቶስ ኢየሱስ በጌታችን ሞት ለዘላለም መሻሩን ይመሰክራል፡፡
ሞት በክርስቶስ ላመኑ በፍፁም የሚያስፈራ እና የሚያስጨንቅ ነገር አይደለም፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ፡- ‹‹ለእኔስ ወደ ጌታዬ መሄድ ይሻለኛል ይህንንም እናፍቃለሁ፡፡›› ሲል ሞቱን ወደ ጌታው እና አምላኩ የሚሻገርበት ድልድይ እንደሆነ ለፊሊጵስዩስ ክርስቶሳውያን የወንጌል ልጆቹ በላከላቸው መልእክቱ በግልፅ ነግሯቸዋል፡፡ እናም ሞት በክርስቲያኖች ዘንድ አስፈሪ እና አሳፋሪ አይደለም፣ ሊሆንም አይችልም፣ ሆኖም አያውቅም፡፡ የቀደሙት አባቶቻችን የወንጌል አርበኞች፣ ጻድቃን እና ሰማዕታት ሞታቸውን እግዚአብሔር አምላካቸውን በዝማሬ እያመሰገኑ፣ እያመለኩ፣ በታላቅ ደስታ እና በጸጋ ነው የተቀበሉት፡፡
ወደ ተነሳሁበት ወደ ርዕሰ ጉዳይ ስመለስ 2004 ዓ.ም በሀገራችን በሃይማኖት፣ በሥነ ጥበብ እና በፖለቲካው መስክ አንቱ የተባሉ ሰዎችን ያጣንበት ዘመን ነው፡፡ በተለይም ደግሞ ወርኻ ነሀሴ ከሕይወት ጋር ግብ ግብ የገጠመ በሚመስል አስገራሚ ጥድፊያ፣ ዓመቱ ከማለቁ በፊት ሳልቀደም ልቅደም ያለ ይመስል በዓመቱ መጨረሻ በወርኻ ነሀሴ ሁለት ታላላቅ መሪዎችን በሳምንት ልዩነት ውስጥ ያጣንበት እንደ አየሩ ጠባይ ሁሉ ጨፍጋጋ እና አስደንጋጭ ወር ሆኖ አልፏል፡፡    
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤ/ን አባት እና መሪ የሆኑት ፓትርያርክ አቡነ ጳውሎስ እና የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚ/ር አቶ መለስ ዜናዊ የተከታተሉበት የሞት መርዶ ኢትዮጵያን እና ኢትዮጵያውያንን ከዳር እስከ ዳር ያነጋገረ እና የሀዘን ከል ያለበሰ ክስተት ሆኖ አልፏል፡፡
በዚህ የሞት ክፉ ዜና የተነሳ በሀገራችን ያረበበው የሀዘኑ ድባብ እንደ ሰማዩ ደመና ገና ሙሉ በሙሉ የተገፈፈ አይመስልም፡፡ አሁንም ድረስ የእነዚህ የቤተ መንግሥቱ እና የቤተ ክህነቱ መራኅያን ያልተጠበቀ የሞት ጥሪ ለብዙዎቻችን ባሰብነው ቁጥር እንቆቅልሽ እንደሆነብን ዘልቋል፡፡ ለአንዳንዶች በተመሳሳይ ወቅት በቤተ መንግሥቱ እና በቤተ ክህነቱ የተከሰተው ይህ ያልተጠበቅ የሞት ጥሪ ‹‹የእግዚአብሔር ቁጣ ነው›› እኛም ንስሀ እንግባ ዘንድ ያስፈልገናል በማለት የእግዚአብሔርን ታላቅነት እና ኃያልነት ዳግም እንዲያስቡ እና እንዲያስተውሉ እንዳደረጋቸው ሲናገሩ በአደባባይ ተደምጠዋል፡፡
ለሌሎች ወገኖቻችን ደግሞ የቤተ መንግሥቱ እና የቤተ ክህነቱ የሞት መርዶ ያው እንደተለመደው ተራ የፖለቲካ ጉንጭ አልፋ ወሬ ከመሆን አላለፈም፡፡ እናም አንዳንዶች ለሰሞኑ የቤተ መንግሥቱ እና የቤተ ክህነቱ ያልተጠበቀ የሞት ጥሪ ያልተገባ የስንፍ እና የፍርድ አስተያየት ከመሰጠት ባለፈ ሌላ አንድምታ እንዳልሰጡት በሰሞኑ ከሚነገሩ ወሬዎች፣ በማኅበረሰብ ድረ ገጾች እና በየብሎጉ ከሚጻፉ በርካታ ፍርድ አዘል ጹሑፎች እና አስተያየቶች ታዝበናል፡፡ እንዲያም ሲል ደግሞ እሰይ ስለቴ ሰመረ በሚል የሚያዜሙ እና ፍፁም ኢትዮጵያዊ ጨዋነት እና ባሕል በጎደለው ሁኔታ በእነዚህ መሪዎች ሞት ጮቤ እየረገጡ ያሉ ወገኖችንም እረ ምን ጉድ ነው እያልን ለመታዘብም በቅተናል፡፡ 
እንዲሁ እንደ ዋዛ ለህክምና በሚል ሰበብ እንደ ወጡ እስከ ወዲያኛው የተለዩንና ከአሁን ከአሁን ጤንነታቸው ተመልሶ ይመጣሉ በሚል ተስፋ የጠበቅናቸው ጠቅላይ ሚ/ር መለስ ዜናዊ በስተመጨረሻ ለብዙዎቻችን ጆሮ የማይታመን የሆነውን የሞታቸውን መርዶ ዜና ለማመን እየቸገረንም ቢሆን ለመስማት ነበር የተገደድነው፡፡ ደህና ናቸው፣ ከህመማቸው እያገገሙ ነው፣ በአዲሱ ዓመት ሥራቸውን ይጀምራሉ የተባለላቸው ጠቅላይ ሚ/ር በድንገት በተከሰተ ኢንፌክሽን ምክንያት በድንገት ሞቱ መባላቸው አሁንም ድረስ ለብዙዎቻችን ኢትዮጵያውያን የጠቅላይ ሚ/ሩ ህመማቸው እና አሟሟታቸው ምስጢር ነው፡፡
በዚህ ጽሑፌ ለመዳሰስ የፈለግኩት የቤተ ክህነቱ እና የቤ መንግሥቱ መሪዎች በሕይወታቸው እስትንፋስ መጨረሻ ምን እንደተናገሩ በመጠየቅ የተነሳው የመጣጥፌ ርዕሰ ጉዳይ እንደ አለመታደል ሆኖ አትኩሮቱን ያደረገው በውጩ ዓለም ባሉ መሪዎች እና ታላላቅ ሰዎች ላይ ነው፡፡ የዚህ ዐቢይ ምክንያት ደግሞ በቅርብ በሞት የተለዩን ፓትርያርክ አቡነ ጳውሎስም ሆነ ጠቅላይ ሚ/ር መለስ ዜናዊ በመጨረሻ የሕይወታቸው እስትንፋስ ምን እንዳሉ፣ ምን እንደተናገሩ እና ለሕዝባቸው ምን ዓይነት የመጨረሻ መልእክት እንዳስተላለፉ የነገረን ሰው ወይም እኔ ምስክር አለሁ የሚለን ሰው እሰካሁን አለመገኘቱ ነው፡፡
ፍቅርን፣ ይቅር ባይነትን/እርቅን፣ ግልፅነትን፣ ታማኝነትን… ወዘተ በቃላቸውም ሆነ በተግባራቸው የሚሰብኩ መሪዎች ድርቅ ክፉኛ የመታት እናት ኢትዮጵያ መሪዎቿ እና ሕዝቦቿ በቅጡ ሳይተዋወቁ እና በፍቅር ሳይቀራረቡ ማዶ ለማዶ እንደተያዩ በሞት እስከ ወዲያኛው የሚሸኙባት ምድር የመሆኗ ምስጢር ማብቂያው መቼ እንደሆነ ግራ የሚያጋባ ነው፡፡
በምስኪኗ ኢትዮጵያ መሪዎቻችን ብዙ ነገራቸው ለሕዝባቸው ምስጢር ነውና እነዚህ ለሁለት አሥርት ዓመታት በቤተ መንግሥቱ እና በቤተ ክህነቱ መሪዎች ሆነው ያስተዳደሩ ፓትርያርክ አባ ጳውሎስ እና ጠቅላይ ሚ/ር መለስ በእስትንፋሳቸው መጨረሻ ምን እንዳሉ ምን መልእክት እንዳስተላለፉ ለማወቅ አልታደልንምና ሳንወድ በግድ ቁጭት እና እልህ እየተፈታተነንም ቢሆን በጀመርኩት ርዕስ ስለ ባሕር ማዶዎቹ መሪዎችና ታላላቅ ሰዎች የመጨረሻ የሕይወታቸው እስትንፋስ መልእታቸው ላምራ፡፡
ከጠቅላይ ሚ/ር መለስ ከጥቂት ሣምንታት በፊት በሞት የተለዩት የጋናው ፕሬዝዳንት ፕሮፌሰር ሚልስ በጉሮሮ ካንሰር በሽታ ምክንያት በአሜሪካ አገር ህክምና ያደረጉ ቢሆንም በቅርቡ ህመማቸው አገርሽቶ ወደ ሀገራቸው የጦር ኃይሎች ሆስፒታል ገብተው ሕክምና በመከታተል ላይ እያሉ ነበር ያረፉት፡፡ Web Ghana የተባለው ድረ-ገጽ ‹‹Mills’ Last Words Before He Died/የፕሬዝዳንት ሚልስ እልፈት እና ከመሞታቸው በፊት የተናገሩት የመጨረሻ ቃላቸው›› በሚል ርዕስ ባስነበበው ጹሑፍ ፕ/ር ሚልስ ከሞታቸው በፊት ካጠገባቸው የነበሩትን ወንድማቸውን ዶ/ር ካድማን ሚልስን በመጥቀስ የሚከተለውን ዘገባ አስነብቦ ነበር፡-
"Before my brother (Mills) died, the last words that he said that I clearly remember is that, he raised his hands in the air and he said ‘God, I leave it all to you, Amen’. I’ve no doubt that God heard his call. I’ve no doubt that he is now in the bosom of the Lord. I’ve no doubt that he’ll find eternal peace. Pray for him, and May God be with you, Fiifi," Dr Cadman Mills said.

Saturday, September 22, 2012

መንፈሳዊ ሃሳብ ላለው ሰው ሁሉ ከፓትርያርክ ምርጫ በፊት እርቅ ይቀድማል!

ስለእርቅ ብዙ ብዙ ተብሏል።  ሰዎች እርቅን ከሁኔታዎችና ከአዋጭነቱ አንጻር መዝነው ይፈጽማሉ። በእርቁ የሚያገኙትን ሂሳብ ቅድሚያ ያሰላሉ። አንድ የተጨበጠ ነገር ካላገኙ እርቅን ሰማያዊ ዋጋ ከማግኘት ጋር አያይዘው  ለመወሰን ይቸገራሉ። ብዙ እርቆች በዚህ መንገድ የሚከናወኑ ናቸው። ፖለቲከኞቹ እንኳን /Give & Take/ ሰጥቶ መቀበል ይሉታል። ይህ የሥጋዊ እሳቤ ውጤት በመሆኑ በዚህ እርቅ ምድራዊ ስምምነት ካልሆነ በስተቀር ከላይ ከአምላክ ዋጋ ያስገኛል በሚል ስላልሆነ ውጤቱ ጊዜያዊና ምድራዊ ነው። ሰማያዊ አስተሳሰብ ምን ጊዜም የእርቁን ጥቅም ከአዋጭነቱ ወይም ከሚያስገኘው የሚታይ ዋጋ በላይ በመሆኑ ለዚህ እርቅ ራስን የመስጠት ዋጋ እስኪከፈልበት ድረስ ግዴታን ያስከትላልና ከባድ ነው። እንኳን የበደሉትን፤ የበደለንን ይቅር እስከማለት የሚያደርስ ህግጋት ስለሆነ ሚዛናዊነቱ በመንፈስ ዓይን ብቻ የሚታይ ነው። በዘወትር ጸሎት «ከመ ንሕነኒ ንሕድግ ለዘአበሰ ለነ» እኛም የበደሉንን ይቅር እንደምንል…» እያልን በደላችንን ሁሉ በደሙ እንዳጠበው ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እኛም የበደሉንን ይቅር እንላለን እያልን የምናውጀው የጸሎት አዋጅ ዋጋ የሚኖረው በእውነትም ለእርቅ የተዘጋጀ ልቡና ሲኖረን ነው። ያለበለዚያ እየዋሸንና ጌታችንንም ለዚህ ዋሾ አንደበታችን ተባባሪ እንዲሆነን እየጠራነው ካልሆነ በስተቀር  በተግባር ይቅርታ በሌለበት ልባችን ውስጥ መንፈስ ቅዱስ በምንም መልኩ ሊያድር አይችልም። ይቅርታ የሌለው ልቦና መንፈሳዊ አይደለም።


«እናንተ ግን ይቅር ባትሉ በሰማያት ያለው አባታችሁም ኃጢአታችሁን ይቅር አይላችሁም» ማር 11፤26

ይቅርታን የማያውቅ ሲኖዶስ ወይም ማኅበር እንዴት ለሀገርና ለህዝብ ይጸልይ ዘንድ ይችላል? ከማን ዘንድ ይቅርታን ለማግኘት? አንዳንዶች በስም ብጹእና ቅዱስ ተብለው በተግባር ግን ከቅድስና ማንነት የሚመነጨው መንፈሳዊ ብቃት ሲታይ፤ ፍሬ አልባዎች ናቸው። የክብርና ዝና፤ የገንዘብና ሥልጣን ምኞቶች ይቅር ማለት በሚገባው ልባቸው ላይ ተቀምጠው ይገኛሉ። ከዚህም የተነሳ ለሌሎች ይቅርታን ለማድረግ ጊዜን ይፈጃሉ፤ እነርሱ ግን ለኃጢአታቸው ወዲያውኑ ከእግዚአብሔር ዘንድ ይቅርታ እንዲወርድላቸው ሲጸልዩ ይታያሉ።  በእርግጥም ለጸሎታቸው ምላሽ ያልመጣላቸው ከዚህ እልከኛ ልባቸው የተነሳ ይሆናል። «አድን ሕዝበከ ወባርክ ርስተከ» ብለው ይጸልያሉ። ህዝቡም አልዳነም፤ በበረከትም ተሞልቶ በስደት ከመሞት አልዳነም። በእልከኝነት መንፈስና ይቅር ባለማለት  የእግዚአብሔርን የይቅርታ ፈቃድ በእጃቸው ያሰሩ ሰዎች እንዴት፤ የይቅርታ እጅ ለእነሱ ከሰማይ እንዲወርድ ይለምናሉ? እግዚአብሔር ልብና ኩላሊት ያመላለሰውን እልከኛ ልብ አይመረምርም ማለት ነው? ለይቅርታ ባልተዘጋጀ ማንነት ያሉ ጨካኞችና ክፉዎች ይቅርታን አያውቁም፤ ልበ ርኅሩኆችና ቸሮች እንጂ!!

«እርስ በርሳችሁም ቸሮችና ርኅሩኆች ሁኑ፥ እግዚአብሔርም ደግሞ በክርስቶስ ይቅር እንዳላችሁ ይቅር ተባባሉ» ኤፌ 4፤32

እንግዲህ እውነት እውነቱን እንነጋገር ከተባባልን ይቅርታን ገንዘብ ማድረግ የማይችሉት ክፉዎችና ጨካኝ መሪዎች ሁሉ ናቸው። በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የተባራሪና አባራሪ፤ የውስጥና የውጪ፤ የሕገ ወጥና ሕጋዊ፤ ሲኖዶስ ስያሜ ሕልውና ኖሮት በየራሱ ክፍል ተለያይቶ መኖር ከጀመረ እነሆ ሃያ አንድ ዓመት አስቆጠረ። እንዴትና ምክንያቱን ለመዘርዘር የዚህ ጽሁፍ ዓላማ ባለመሆኑ ወደዚያ የቆሸሸ ታሪክ መግባት አያስፈልግም።   በተወጋገዘ የጳጳሳት ቡድንና ደጋፊ የቤተክርስቲያኒቱ አንድ ማኅበር ልዩነቱ ዛሬም መኖሩን በማመን መፍትሄ በመፈለግ ላይ ለማተኮር ይሻል። 21 ዓመት በልዩነትና በክፍፍል የቆየነው ለምንድነው? አሁን ያህ ክፍፍል እንዳይቀጥል ምን የሚታይ ነገር አለ? ወደፊትስ ምን ማድረጉ ይበጃል? በሚሉት ላይ ጥቂት ለማለት እንወዳለን።

1/ ለይቅርታ የተዘጋጀ ወገን የለም!

በሁለቱም ሲኖዶሶች በኩል በክርስቲያን ይቅርባይ የእምነት ማንነት ላይ ሆኖ ይቅር ለመባባል የፈለገ ማንም  ወገን የለም። የክርስቶስ አማኝ ይቅርታን በሁኔታ፤ በአዋጭነቱና በሚያስገኘው የሚታይ ዋጋ ላይ ተመስርቶ ለይቅርታ ድርድር አይቀመጥም። ይሁን እንጂ ሁለቱም ሲኖዶሶች ለይቅርታ የሚነጋገሩት የሚያዋጣቸውን ስልት ነድፈው ጥቅሞቻቸውን በማስጠበቅ ውጤታማ ለመሆን የሚታገሉለት ምድራዊ አስተሳሰብ የነገሰበት ሆኖ በመቆየቱ አንዳችም ውጤት ማምጣት አልተቻለውም። የቤተክርስቲያን አንድነት ሰዎች ስለፈለጉት  ወይም ስላልፈለጉት ሳይሆን የተመሰረተው በክርስቶስ ደም ስለሆነ አንዳችም ቅድመ ሁኔታ የሌለበት ነገር ነው።
«ቤትም እርስ በርሱ ከተለያየ ያ ቤት ሊቆም አይችልም » ማር 3፤25
«በገዛ ደሙ የዋጃትን የእግዚአብሔርን ቤተ ክርስቲያን ትጠብቁአት ዘንድ መንፈስ ቅዱስ እናንተን ጳጳሳት አድርጎ ለሾመባት ለመንጋው ሁሉና ለራሳችሁ ተጠንቀቁ» የሐዋ 20፤28
የክርስቶስን መንጋ ለሁለቱ የከፈሉ ሲኖዶሶች የክርስቶስን ቤት በአንድነት ለማቆም ያለመቻላቸው ዋናው ምክንያት ቤተክርስቲያንን ለመጠበቅ መንፈስ ቅዱስ የሰጣቸውን ሹመት ወደ ሥጋዊ አስተሳሰብና የድርድር ሂሳብ ስላወረዱት ብቻ ነው። እንዲያ ካልሆነማ 21 ዓመት ለእርቅ ያንሳል? ከእንግዲህስ ስንት 21 ዓመት ያስፈልጋል? በሁለቱም ወገን ለቤተክርስቲያን አንድነት የተዘጋጀ ማንነት ባለመኖሩ ውጤቱ ከህልም ዓለም አልፎ እውን መሆን አልቻለም። አሁንም ይህን አስተሳሰብ አስቀምጠው የክርስቶስን ማኅበር መሰብሰብና የቤተክርስቲያንን አንድነት ማስቀደም እስካልቻሉ ድረስ ከመንፈሳዊ ውጤት ላይ መድረስ አይቻላቸውም።

2/ የሀገር ውስጡ ሲኖዶስ የበለጠ ችግር አለበት።

አንዳንዶች ማለትም ማኅበረ ቅዱሳንን ጨምሮ የፓትርያርክ መርቆሬዎስን ሀገር ለቆ መሄድ ሲኮንኑ ይታያሉ።  የመንፈሳዊ አባቶችን የጥንት የስደት ሁኔታ ከታሪክ አምጥተን እዚህ ላይ ብዙ መከራከሪያ ጭብጥ በማቅረብ መሞገት ይቻላል። ይሁን እንጂ ጉልጭ አልፋ እንዳይሆን እንለፈውና የፓትርያርክ መርቆሬዎስን ስደት ተገቢ እንዳልነበረ ብንቆጥረው እንኳን ስህተታቸውን አጉልቶ የማያሳይ ነገር አለ። ይኼውም  ፓትርያርክ መርቆሬዎስ መንፈሳዊ ሥልጣናቸውን የሚጠሉት ኢህአዴግ ሲገባ ሊሆን አይችልም። ታመዋልም ቢባልም እንኳን  በሞት ከዚህ ዓለም ተለይተዋል ማለት አይደለም። በሞት እስካልተለዩ ድረስ በህመም ይሁን በሌላ ምክንያት ከመንበሩ ላይ ካልተገኙ በምትካቸው ሌላ ፓትርያርክ ይመረጣል የሚል ሕግ አለ ወይ?    ምንም እንኳን ፓትርያርክ መርቆሬዎስ እስከመጨረሻው ድረስ ባሉበት መቆየት እንደነበረባቸው ባያጠያይቅም እውነታው ግን የፓትርያርክ መርቆሬዎስን መባረርና ከስልጣን በህመም ይሁን በሞት መሰናበት የሚፈልጉ የሲኖዶስ አባላት መኖራቸውን ልንክድ አይገባም። ምክንያቱም ፓትርያርኩ በሕይወት እያሉ ሌላ ፓትርያርክ አንሾምም ያለ አንድም የሲኖዶስ አባል አልነበረም። ይልቁንም ከባለጊዜው ንፋስ ጋር ሲነፍሱ ታይተዋል። አንዳንዶቹም ለመሾም ሲሯሯጡ ነበር።  በህመም ወይም በሌላ ምክንያት መሥራት ባይችሉ እንደራሴ የማይመራበት ምክንያቱ ምን ይሆን? ሕጉን በሕግ ባለማሻሻል ለመጣስ ያደረሰው ምን ይሆን?  ተወደደም ተጠላ፤ ፓትርያርኩን በመጥላትና በማስወገድ ሥልጣኑን ለመጨበጥ የፈለጉ ቡድኖች ለቤተክርስቲያን መከፋፈል ትልቁን ሚና ተጫውተዋል። ብዙዎቹን ባለድርሻዎች እናውቃቸዋለን። ገሚሶቹም ሞተዋል፤ በህይወት ያሉትም አሉ። ይህ ከሆነ እነሆ 20 ዓመታት አለፉ።  ስህተቶችን በማመን ለማስተካከል መሞከር ግን አሁንም ቁርጠኝነቱ ካለ አልረፈደም። በመሬት ላይ ያለው እውነታ ግን ለመተራረም ያለውን ነገር ብዙም አያሳይም።
 የሀገር ቤቱ ሲኖዶስ ከውጪው ሲኖዶስ ጋር ለሚደረገው እርቅ እንቅፋት ናቸው ብሎ የክስ መዝገቡን በአቡነ ጳውሎስ ላይ ሲለጥፍ የነበረ ቢሆንም  ከሞታቸውም በኋላ ይህ እርቅ በየምክንያቱ እንዲጨናገፍ የሚፈልግ አካል እንጂ ከአቡነ ጳውሎስ በተሻለ መልኩ ለእርቁ ቀናዒ  ስለመሆኑ የምንሰማውና የምናየው ነገር የለም። ይልቁንም ከወዲያ ወዲህ የሚናፈሰው ስለ 6ኛው ፓትርያርክ ምርጫ ነው። ምናልባትም አቡነ ጳውሎስን ከመጥላት የተነሳ  ውንጀላን የሚቆልሉባቸው ከሳሾቻቸው እሳቸው በሞት ዘወር ሲሉ  የከሳሾች የሀሰት ክስ ጊዜውን ጠብቆ እየተገለጸ እያየን ነው። ስለ6ኛው ፓትርያርክ በተዘዋዋሪና በቀጥታ መነገሩ እርቁ አልተፈለገም ማለት ነው። ድሮውንም ፓትርያርክ ጳውሎስን የሚወነጅሉት ለስም ማጥፋት እንጂ እርቁን ፈልገውት አልነበረም። ምክንያቱም እርቁ እውን ሆኖ የውጪዎቹ ጳጳሳት ወደ ሀገር ውስጥ ለመግባት ቢችሉ፤ አሁን ባለው የሀገር ውስጡ ሲኖዶስን ጉባዔ በሚፈልጉት መንገድ የሚጠመዝዙ ቡድኖች ከልዩ ልዩ አስተሳሰብና ከእውቀት ብልጫ አሰላለፍ አንጻር የመዋጥና የያዙትን የወሳኝነት  ወንበር በመልቀቅ ወደጥጉ እንገፋለን የሚል የስነ ልቦና ፍርሃት አላቸው። ያን ጊዜ የማኅበረ ቅዱሳን ነደ እሳት የሚባል ጳጳስ አይኖርም፤ እገሌ ጧፍ ነው፤ እገሌ ደግሞ ሻማ እያሰኘ የሚያሞካሸውን ጀግና ደጋፊ አያገኝም።  ስለዚህ ሁሉም ቡድኖች እርቁ በፍጥነትና በሁኔታዎች አጋጣሚ እንዲፈጸም አይፈልጉም። ከእነዚህም አንዱ የሀገር ውስጡ ሲኖዶስ አጫፋሪ የሆነው ማኅበረ ቅዱሳን ከነተባባሪ አባቶቹ እርቁን አይፈልጉትም።

3/ የውጪውም ሲኖዶስ ችግር አለበት።

 ፓትርያርክ መርቆሬዎስ እድሜአቸው መግፋቱ እውነት ነው። በዚህ እድሜያቸው አሁን ያለውን የቤተክርስቲያን ተግዳሮቶች ፈጥነው በመረዳትና በመንቀሳቀስ ተፈላጊውን መፍትሄ በመስጠት ላይ ተገቢውን አመራር መጠበቅ እንደሚቸግር መረዳት አይከብድም። በዚህ ላይም ሕመም እንዳለባቸውም እንሰማለን።  ብዙ ጊዜም የሲኖዶሱ ዋና ጸሐፊ ድምጽ በውክልና ከሚሰማ በቀር የፓትርያርኩ ድምጽ ርቋል። ይህም እንደ አንድ ችግር ቢነሳ አግባብነት ይኖረዋል። ከዚህ በተጨማሪም እርቅን የሚያክል ትልቅ ኃላፊነትና ተልእኮ የሚጠብቀው የውጪው ሲኖዶስ አባላት ለእርቅ እንቅፋት የሚሆኑ ፖለቲካዊና ሃይማኖታዊ መሰል መግለጫዎችና አሰላለፎችን ሲያሳዩ ይታያሉ። ከሀገር ውስጥ ሲኖዶስ ጋር በመስማማት ብቻ ያለ ኢትዮጵያ መንግሥት ድጋፍ እርቁ ከግብ ሊደርስ እንደማይችል ይታወቃል።  የውጪው ሲኖዶስ አባላት የፖለቲካ ሰልፎችን በማስተባበር የኢትዮጵያን መንግሥት ማስኮረፍ በራሱ ችግር አለው። መቃወም መብት ቢሆንም የፖለቲካ «ሀሁ» ብዙም በሀገሩ ውስጥ ባላስፋፋ መንግሥት ጉዳይ እየገቡ ወደእርቅ እንደርሳለን ለማለት እንዴት ይቻላል? እርቁ ቢቀርም፤ ይቅር ካልተባለ በስተቀር  እስከ ኤርትራ የደረሰ የሲኖዶስ አባል ያለው የውጪው ሲኖዶስ አቋሙ ጥርት ያለና ለእርቅ ዝግጁነት ያለው ነው ለማለት ይቸግራል።  እስካሁንም እነዚህ ጉዳዮች ለእርቅ ያላቸውን ጉዳት ገምግሞ ዝግጁነቱ እስከየት ድረስ እንደሆነ በግልጽ የሚታወቅለት ነገር የለም። ፖለቲካዊ ጥያቄዎችንም እንደሚያነሳ ይሰማል። ቤተክርስቲያንን አንድ ለማድረግ ካልሆነ በስተቀር ሲኖዶስ ለፖለቲካዊ ጥያቄ መፍትሄ የቅድሚያ ስራው እንዴት ሊሆን ይችላል? የሚቀድመውን ማስቀደምና በሂደት ደግሞ የሚከተለውን ከመስራት ይልቅ አቀላቅሎ ሁሉንም ፍላጎቶች በአንዴ ለማሳካት መፈለግ ሁሉም እንዳይሆን ለማድረግ ከመጣር የተለየ አይደለምና ሊታሰብበት ይገባል።

Thursday, September 20, 2012

የማኅበረ ቅዱሳን ሰዎች በአቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ ሹመት ደስተኛ አለመሆናቸውን ቤተክህነት አካባቢ በሚያናፍሱት ወሬ እየገለጹ ነው

ዐቃቤ መንበሩ «መናፍቃኑ ኃይለ ማርያምን ጠቅላይ ሚኒስትር ሊያደርጉት እየጸለዩ ነው አሉ፤ እርሱ ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነ ማለት ለእኛ እጅግ ክፉ ነገር ነውና የምንችለውን ሁሉ ማድረግ አለብን» ብለዋል

ምንጭ፦ አባ ሰላማ ድረ ገጽ


 ዐቃቤ መንበሩ «መናፍቃኑ ኃይለ ማርያምን ጠቅላይ ሚኒስትር ሊያደርጉት እየጸለዩ ነው አሉ፤ እርሱ ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነ ማለት ለእኛ እጅግ ክፉ ነገር ነውና የምንችለውን ሁሉ ማድረግ አለብን» ብለዋል.
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የነበሩት አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ የኢህአዴግ ሊቀመንብር ሆነው መመረጣቸውንና በቀጣይም ለጠቅላይ ሚኒስትርነት ቃለ መሐላ የሚፈጽሙ መሆናቸው ከተገለጸ ጊዜ ጀምሮ፣ የፕሮቴስታንት እምነት ተከታይ በመሆናቸው ምክንያት በማኅበረ ቅዱሳን መንደርና በቤተክህነቱ አካባቢ ከማኅበረ ቅዱሳን ጋር ግንኙነት ባላቸው አካላት ዘንድ «ጴንጤ አይገዛንም» የሚል ቅስቀሳ ውስጥ ውስጡን እየተደረገ መሆኑ እየተነገረ ነው፡፡
በዘመን መለወጫ በዓል ላይ በጠቅላይ ቤተክህነት አዳራሽ በተዘጋጀው መርሀግብር ላይ የተገኙትና ንግግር ያደረጉት አቃቤ መንበር አባ ናትናኤል ትዝብት ላይ የጣላቸውን ንግግር ማድረጋቸውን በስፍራው የነበሩ ምስክሮች እየገለጹ ነው። አቡነ ናትናኤል በአቃቤ መንበርነት ከተሾሙ ጀምሮ ጊዜውን እየተሻሙና ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስን ለመምሰል ጥረት እያደረጉ መሆናቸውን እያደረጉ ካለው እንቅስቃሴ መታዘብ ተችሏል፡፡ «እርሳቸው ወንበር ላይ አስቀምጡኝ» ከማለት «እርሳቸው የሚበሉትን ስጡኝ» እስከማለት መድረሳቸውን ምንጮቻችን ገልጸዋል፡፡
ከዚሁ ጋር ተያይዞ በየዓመቱ በዘመን መለወጫ በዓል ለሚደረገውና ቅዱስ ፓትርያርኩን እንኳን አደረስዎ ለሚባልበት መርሐግብር ከአዲስ አበባ ገዳማትና አድባራት ለተገኙ የደብር አለቆች፣ ካህናትና ዲያቆናት ባደረጉት ንግግር ውስጥ «መናፍቃኑ ኃይለ ማርያምን ጠቅላይ ሚኒስትር ሊያደርጉት እየጸለዩ ነው አሉ፤ እርሱ ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነ ማለት ለእኛ እጅግ ክፉ ነገር ነውና የምንችለውን ሁሉ ማድረግ አለብን» ያሉ ሲሆን፣ ከበዓሉ ጋር የተገናኙ ሐሳቦችን ካቀረቡ በኋላም መጨረሻ ላይ «ቅድም ያነሣሁላችሁ የመናፍቃኑ ጉዳይ ምሥጢር ነውና በምሥጢር ያዙት» ብለዋል፡፡ ይህም የተናገሩት ተገቢ ያልሆነ ቃል እንደወቀሳቸውና ሀሳቡ መጀመሪያም ቢሆን ከራሳቸው ያመነጩት እንዳልሆነ ግምት እንዲወሰድ አድርጓል፡፡ አባ ናትናኤል ከእርጅናም ዲፕሎማሲያዊ አቀራረቡንም በሚገባ ባለማወቃቸው የተነሳ በብዙዎች ፊት የሰነዘሩትን ይህን ሀሳብ እነማንያዘዋል ሹክ እንዳሏቸው ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ሰዎች ገልጸዋል፡፡
አቶ ማንያዘዋል የጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ቀብር እለት ወደቤተመንግስት እገባለሁ አትገባም በሚል ቤተመንግስት በር ላይ ከአስተናጋጆች ጋር ሲወዛገብ በቴሌቪዥን መስኮት ያዩትና የሚያውቁት ሁሉ መነጋገሪያ አድርገውት የሰነበቱ ሲሆን፣ «አባ ናትናኤልን ደግፌ የምይዝ ነኝ» በሚል በትግል መግባቱ ታውቋል፡፡ ይህም ማኅበሩ ቀድሞም ያደርግ እንደነበረ የሚፈልገውን በእርሱ በኩል ወደአባ ናትናኤል እያቀረበ ለመሆኑ በቂ ምስክር ነው ይላሉ ታዛቢዎች፡፡ የአቶ ኃይለማርያም ደሳለኝን ሹመት በመቃወም በዋናነት እያቀነቀነ የሚገኘው ማኅበረ ቅዱሳን መሆኑን ምንጮቻችን እየተናገሩ ነው፡፡ ቤተክህነት አካባቢ «ጴንጤ ሊገዛን አይገባም» የሚል ወሬ እያናፈሰ ሲሆን፣ አንዳንድ ወዳጆቹ ጳጳሳት ግን «ከዚህ በኋላ አንዳች ስሕተት ከተገኘባችሁ የምትከፍሉት ዋጋ ቀላል አይሆንምና ሁሉን ነገር በጥንቃቄ ነው ማድረግ ያለባችሁ» የሚል ምክር እንደለገሷቸው ለማወቅ ተችሏል፡፡


Wednesday, September 19, 2012

‹‹ባለራእዮች ይሞታሉ ራእያቸው ግን አይሞትም›

ዲያቆን ፈታሂ በጽድቅ ከተባለ የብሎጋችን ተከታታይ የተላከ ጽሁፍ

የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስቴር የመለስ ዜናዊን ዜና ዕረፍት ከሰማን በኋላ ብዙዎቻችን አዝነናል፡፡ በሰውኛ አቅሙ ሁሉም ምንም ማድረግ ስላልቻለ ነው እንጂ አንዳንዶች እሳቸው ከሞት ተርፈው እኔ በተተካሁ ሲሉ ሌሎች ደግሞ ምንም እንኳ ራሳቸውን አሳልፈው ለመስጠት ባያስቡም በሆነ መንገድ ከሞት አስነስተው የማቱሳላን እድሜ ቢቸሯቸው ደስተኛ እንደሚሆኑ በየመጓጓዣው፣ በየስራ ስፍራውና በየመዝናኛ አካባቢዎች የነበሩት ጭውውቶች ይናገሩ ነበር፡፡

ከሞት ማስነሳት ባንችልም ግን ሁላችንም ሐዘናችንን በተለያየ መንገድ ስንገልጽ ቆይተናል፡፡ ምንም እንኳ ሐዘኑ አሁን እየቀነሰ ያለ ቢሆንም የሐዘኑ ስሜትና የሐዘን መግለጫ መልእክቱ አሁንም በቴያ መልኩ እንዳለ ነው፡፡ ከብዙዎቹ የሐዘን መግለጫዎቻችን መካከል ከላይ በርዕስነት ያነሳነው አንዱ ነው፡፡ ይህን መልእክት ጎላ ጎላ ባለ ፊደል ከአቶ መለስ ፎቶግራፍ ጋር በተደጋጋሚ በተለያየ ይዘትና ስፍራ ላይ ተስቅሎ አይተነዋል፡፡

ይህን መልእክት የሰቀሉ ሰዎች ሊሉ የፈለጉት ምንም እንኳን አቶ መለስ ዜናዊ የዚህ ዓለም ቆይታቸውን ጨርሰው በሞት ቢለዩንም ራእያቸውን ግን ቀደም ሲል ጀምረውት ወይም አካፍለውን ስለሆነ የሄዱት ራእያቸው አይሞትም፡፡ ይልቁንስ እኛ እንጨርሰዋለን የሚል ነው፡፡ እነዚህ ሰዎች በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ ቃል እየገቡ እንዳሉት ለማድረግ ከቻሉ የአቶ መለስ ራእይ አይሞትም ማለት ነው፡፡ አለበለዚያ ግን. . .

በዚህ መልእክቴ ለማሳየት የፈለኩት የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስቴር የአቶ መለስ ዜናዊን ራእይ እንዴት እንፈጽም? እንዴትስ እንዳይሞት ለማድረግ እንችላለን? የሚለውን ማሳየት አይደለም፡፡ እርሱን ለማድረግ ያለሁበት ስፈራ፣ ዕውቀትና ሁኔታ አይፈቅድልኝምና ወደዚያ አልገባም፡፡ ነገር ግን ብዙዎች ሊገድሉት ተማምለው ስለወጡበት አንድ ራእይ ነው ለማሳየት የምፈለገው፡፡

ቤተ ክርስቲያናችን ወደቀደመ ትምህርቷና ወደሐዋርያት እምነት እንድትመለስ እስጢፋኖሳውያን ሕይወታቸውን ሰውተዋል፡፡ በወቅቱ የነበረው ጨካኝና ከሃዲ መሪ ሰዎቹ እንዲደበደቡ፣ እንዲታሰሩ፣ እንዲሰደዱ እንዲሁም እንዲሞቱ ሲያደርግና ሲያስደርግ በእሱ እምነት ራእያቸውም አብሮ ይሞታል ብሎ ተስፋ አድርጎ ነበር፡፡ ነገር ግን ታሪካቸው እንደሚለው መሰደዱም፣ መገደሉም፣ መታሰሩም ሰዎቹ እንዲጠፉ ከማደረግ ይልቅ ‹‹እግዚአብሔር የተጋዙበትን ሀገር እየከፈተላቸው ብዙዎችን በስብከታቸው እያሳመኑ ክርስቲያኖች እንዲያውም መነኮሳት አድርገዋቸዋል›› (ደቂቀ እስጢፋኖስ በህግ አምላክ ገጽ 35)፡፡ ጨካኙ መሪ እንደጠበቀው ሳይሆን ካሰበው ውጪ ሲሆንበት ጭካኝና ፀረ ወንጌል በመሆኑ የሚከተሉትን የማሳቀያና የመግደያ መንገዶች ወደመጠቀም ዞረ፡-

1.         በድንጋይ ደበደቧቸው፡፡
2.         ቆመውም ሆነ ተንበርክከው መጓዝ እንዳይችሉ የእግሮቻቸውን ጅማቶች አወጡባቸው በዚህ ምክንያት ደብረ ብርሃን ከተማ ወድቀው ቀሩ፡፡
3.         በጅራፍ ገረፏቸው፡፡
4.         በመሬት ላይ አስተኝተው እንደሚለፋ ቆዳ በመርገጥ ጤማይ የተባለ የንጉሡ ወንጀለኞች መግረፊያ ሁሉም የሠራዊቱ አባል እጃቸው እስኪደክማቸው ገረፏቸው፡፡
5.         አንዲትን ሴት ሁለት እግሮችዋን ግራና ቀኝ ወጥረው በማሰር ራቁትዋን አስተኝተው እሳት ካነደዱ በኋላ በፍሙ ቀኑን ሙሉ ጭኗን እና ብልቷን በእሳቱ እየጠበሷት ሲያቃጥሏት በስቃይ ሞተች፡፡
6.         እጃቸውንና እግራቸውን በመቁረጥ በድንጋይ በመደብደብ የተገደሉም ነበሩ፡፡
7.         አንገታቸውን የተቆረጡም ነበሩ፡፡
8.         በጣም በሚያሰቅቅ ብርድና ቅዝቃዜ ውስጥ ራቁታቸውን እንዲሆኑ በማድረግ በቅዝቃዜውና በእርጥበቱ ምክንያት ከመጣው ተላላፊ በሽታ የተነሳ 98 ሰዎች ሞቱ፡፡
9.         ጆሮአቸው ውስጥ ጉንዳን የተጨመረባቸው ነበሩ፡፡

የማኅበረ ቅዱሳን የጥናት እና ምርምር ማእከል ባዘጋጀው በ፬ኛው የኢትዮጵያ ቤተ- ክርስቲያን ጥናት ጉባኤ ላይ የተደረገ አጭር ደሰሳ፡፡



   ፍቅር ለይኩን ለደጀ ብርሃን የላከው ጽሁፍ
[fikirbefikir@gmail.com/befikir12@yahoo.com

‹‹ሁሉን መርምሩ የተሻለውን ያዙ!›› የሚለው የመጽሐፍ ቅዱስ ሕያው ቃል ባለ አእምሮ የሆነ ሰው ሁሉ በማስተዋልና በጥበብ መንፈስ ሆኖ መልካሙን ከክፉ ለመለየት ጥናት እና ምርምር በእጅጉ አሰፈላጊ መሆኑን የሚያሳስበን ኃይለ ቃል/ምክር ይመስለኛል፡፡ የሐዋርያት ሥራ መጽሐፍም ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ በአይሁድ ምኩራብ ተገኝቶ በተደጋጋሚ ስለ ጌታችን፣ አምላካችን እና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አምላክነት፣ ጌትነት እና አዳኝነት የሰበከላቸው ልበ ሰፊዎቹ የቤሪያ ሰዎች፡- ‹‹ነገሩ እንዲህ ይሆንን በማለት መጻሕፍትን በመመርመር ቃሉን በሙሉ ልብ ተቀበሉ ይለናል፡፡›› (ሐዋ  ፲፯፣፲፩)   
የሥልጣኔ ምንጭ፣ የሺህ ዘመናት ባለ ታሪክ እና የበርካታ ቅርሶች ባለቤት ለሆነችው ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን የጥናት እና ምርምር ሥራ ታላቅ ፋይዳ ያለው መኾኑ አያጠራጥርም፡፡ በኢትዮጵያ ባሕልና ቱሪዝም ሚ/ር በቅርስ ጥናት እና ጥበቃ ባለሥልጣን አዳራሽ ጳጉሜን ፫ እና ፬ ለሁለት ቀናት በተካሄደው ‹‹ኛው የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ጥናት ጉባኤ›› አንገብጋቢ እና ወቅታዊ በሆኑ ሀገራዊና ሃይማኖታዊ ጉዳዮች ላይ በቤተ ክርስቲያኒቱ ምሁራን፣ በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት በመጡ፣ ከተለያዩ መንግሥታዊ እና መንግሥታዊ ካልሆኑ መሥሪያ ቤቶች በተጋበዙ እንግዶች በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ ሰባት የጥናት ወረቀቶች የቀረቡበት ጉባኤ ነበር፡፡
ጥናት እና ምርምር በሳይንሳዊ ዘዴ ለችግር መፍትሔ ለማፈላለግ፣ አዳዲስ ግኝቶችን ለመፍጠር፣ ተጨማሪ እውቀትን ለማግኘት፣ አስፈላጊውን መረጃ ተገቢውንሳኔ ለመስጠት የሚያስችል ዐቢይ ተግባር ነው፡፡ ዛሬ አንቱ የተባሉ፣ ዓለምን ያስደመሙ ጥበባት ኹሉ የጥናትና ምርምር ውጤቶች ናቸው፡፡ በዘመናችን በዓለም ላይ የተጋረጡ በርካታ ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ አካባቢያዊ፣ ፖለቲካዊ እና መሰል ችግሮችን ለመፍታት ዋነኛው መንገድ ጥናት እና ምርምር መሆኑ ግልፅ ነው፡፡
ስለሆነም በሀገራችን ይህን የሚያስፈጽሙ አያሌ የጥናት እና ምርምር ተቋማት ተመሥርተዋል፡፡ ይሁን እንጂ በሀገራችን የረጅም ዘመን የሥነ መንግሥት/ፖለቲካ፣ ኢኮኖሚ፣ ማኅበራዊ ኑሮ፣ ታሪክ፣ ባሕል እና ሥልጣኔ እንዲሁም ፍልስፍና፣ ሕግ፣ ሥነ ጹሑፍ፣ ኪነ ጥበብ እና ሥነ ሕንጻ/አርክቴክቸር ሰፊ እና ጉልህ አሻራ ያላት የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ዙሪያ ሰፊ የሆነ ምርምር እና ጥናት በማድረግ ረገድ ቤተ ክርስቲያኒቱ በሀገራችን ለትምህርት መጀመር ከተጫወተችው ግንባር ቀደም ሚና እንዲሁም ጥንታዊት፣ ሐዋርያዊት እና ወንጌላዊት እና በበርካታ ሚሊዮን የሚቆጠሩ ምእመናን ያሏት ተቋም የመሆኗን ያህል በበቂ ሁኔታ የተደራጀ የጥናት እና የምርምር ማእከል የላትም፡፡
ለቤተ ክርስቲያኒቱ አንድ ለእናቱ ሊባል የሚችለው በዩኒቨርስቲ ኮሌጅ ደረጃ አለ የሚባለው የቅድስት ሥላሴ ኮሌጅም በብዙ አካዳሚያዊ እና አስተዳደራዊ ችግሮች የተተበተበ በመሆኑ እንደ አንድ አካዳሚያዊ ተቋም በበቂ ሁናቴ የተደራጀ እንኳን ቤተ መጻሕፍት የለውም፡፡ በየጊዜው በአኀተ አብያተ ክርስቲያናትም ሆነ በክርሰቲያኑ ዓለም የሚወጡ አዳዲስ መጻሕፍቶች፣ የጥናት እና የምርምር ጆርናሎች እና ፐሮሲዲንጎች በዚህ ተቋም ውስጥ እጅጉን ብርቅ ናቸው፡፡ እናም ይህ ለቤተ ክርስቲያኒቱ ብቸኛ እና አንድ የሆነ የሥነ መለኮት ተቋም የሚጠበቅበትን ያህል ለቤተ ክርስቲያኒቱም ሆነ ለሀገር መፍትሔ አመላካች የሚሆኑ ብቁ እና ወዳዳሪ የሆኑ ምሁራንን በብዛት እና በጥራት ለማፍራት ቀርቶ ተቋም እራሱ በበርካታ ችግሮች ተተብትቦ የሌሎችን ብርቱ እገዛ ወደሚፈልግበት ደረጃ የደረሰ ይመስላል፡፡
እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ ማለት ይቻላል የኢትዮጵያን ቤተ ክርስቲያን በማጥናት በኩል ከእኛ ይልቅ ምዕራባውያኑ እና አሜሪካውያን ምሁራን ሰፊውን ድርሻ ይወስዳሉ፡፡ ይህ ደግሞ በቤተ ክርስቲያናችን ብቻ ሳይሆን በሀገራችን ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ማኅበራዊ ጉዳዮች ላይ ስለ ችግሮቻችን አጥንተው መፍትሔ አሳብ የሚያቀርቡልን ፈረንጆቹ መሆናቸው ነገሩን እንቆቅልሽ ያደርገዋል፡፡ ለዚህም ደግሞ በተለይም በቤተ ክርስቲያናችን ጥናት እና ምርምርን የሚያበረታቱ አመቺ ሁኔታዎች እና ተቋማት አለመኖራቸውና ለረጅም ዘመናት የቆየው የቤተ ክርስቲያኒቱ ባሕላዊ የሆነ የትምህርት ሥርዓትም ያለውን ከማስጠበቅ አልፎ አዲስ እውቀት ለማምረት (Knowledge Production) የሚያስችል የጥናት እና ምርምር በር ለመክፈት አለመቻሉ እንደ አንድ ምክንያት ሊወሰድ የሚችል ይመስለኛል፡፡
ፊደል ቀርፃ፣ ቀለም በጥብጣ፣ ብራና ዳምጣ የድንቁርና እና የአለማወቅን ጨለማ ለመግፈፍ ገና ከጥንት ከጠዋቱ ታጥቃ የተነሳች ቤተ ክርስቲያናችን በጀመረችው ፍጥነት መጓዝ ተስኗት እና ይባስም ሲል በምርምር እና በጥናት እጅጉን የተራቀቁ እና የመጠቁ የሥነ መለኮት እና የፍልስፍና ሊቃውንቶችን ያፈራች ቤተ-ክርስቲያን በዘመናችን በብዙ ችግሮች ተተብትባ መንገዷ ሁሉ ባለህበት እርገጥ መሆኑ ሁላችንንም ሊያስቆጨን የሚገባ ጉዳይ መሆኑን መዘንጋት አይኖርብንም፡፡
ይህን ቤተ ክርስቲያኒቱ እና የትምህርት ተቋማቶቿ ኅብረተሰቡ ከእነዚህ ተቋማት የሚጠብቀውን ያህል አለመንቀሳቀሳቸው፣ ያሉባቸውን እና የተጋረጡባቸውን ሁለተናዊ እንቅፋቶች እና ቤተ-ክርስቲያኒቱ በዚህ ረገድ እጅግ ወደ ኋላ መንደርደሯን የታዘቡ አንድ ምሁር እና ፖለቲከኛ በአንድ ወቅት ‹‹ነፃነትን የማያውቅ ነፃ አውጭ›› በሚል በመጽሐፋቸው ላይ፡-
በአንድ ወቅት በምድረ አውሮፓ እና በአረቢያ ከነበሩ ተመሳሳይ የመንፈሳዊ እውቀት ተቋማት ጋር መወዳደር የሚችል የትምህርት ዓይነቶች ያስተምር የነበረ ቤተ ክህነት፣ አውሮፓውያኑ እነዚህን ተቋማት ወደ ትላልቅ እና ዝነኛ የጥናት እና የምርምር ማእከላት እና ዩኒቨርስቲዎች መቀየር ሲችሉ የእኛው ቤተ ክህነት ተቋማት እንዴት ከነ ከፍተኛ ሕዝባዊ ተቀባይነታቸው እና ክብራቸው ጋር የእርግማን ሰባኪ ተቋም ብቻ ሆኖ እንደቀረ እኔም ሆነ ትውልዴ ለማወቅ አልጣርንም፣ አልፈለግንም በማለት ቁጭታቸውን ገልጸው ነበር፡፡
ዛሬ በዓለማችን ያሉ ትላልቅ የሃይማኖትም ሆኑ ዓለማዊ ተቋማት ከፍተኛ የሆነ ወጪ የሚመድቡት ሰፊ እና ጥልቅ በሆነ ጥናት ለታገዙ የምርምር ስራዎች እና አማካሪዎች/መማክርት ነው፡፡ በሀገራችንም ሆነ በቤተ ክርስቲያናችን ለተጋረጡብን ሁልቆ መሣፍርት ለሌላቸው ችግሮቻችን በዚህ ዘመን ጥልቅ የሆኑ በእግዚአብሔር ጥበብ እና ማስተዋል መንፈስ የተቃኙ ጥልቅ የሆኑ አሳቢዎች/ተመራማሪዎች (Great Thinkers) በእጅጉ ያሰፍልጉናል፡፡
በቀደመው ታሪካችን ዘመን በሀገራዊ እና በቤተ ክርስቲያን አጀንዳዎች ላይ ሰፊ ጊዜ በመውሰድ የሚያሰላስሉ፣ የሚጸልዩ፣ በጽሞና መንፈስ ሆነው በእግዚአብሔር ፊት በጽናት እና በትዕግስት የሚቆዩ አባቶች እንደነበሩን የታሪክ ድርሳናቶቻችን ይመሰክራሉ፡፡ እንዲህ ዓይነቱ ተጋድሎ እና መንፈሳዊነት ዛሬ በታሪክ ብቻ በነበር የምናወሳው የሩቅ ዘመን ትዝታችን ሆኖ መቅረቱ ሁላችንንም ሊያንገበግበን ይገባል፡፡ አውሮፓውያን እና አሜሪካውያን ዛሬ ለደረሱበት እጅግ ለመጠቀ ሥልጣኔ፣ የአስተሳሰብ ምጥቀት፣ ፖለቲካዊ፣ ማኅበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ እድገቶች እና ለውጦች ትልቅ መሠረት የጣሉ በሃይማኖት ተቋማቶቻቸው የነበሩ ጥልቅ አሳቢዎች እና ተመራማሪዎች እንደ ነበሩ የታሪክ ድርሳናት ይመሰክራሉ፡፡
በአውሮፓውያኑ ዘንድ ስለ ኢትዮጵያ ጥንታዊ ሥልጣኔ፣ ታሪክ፣ ቋንቋ፣ ቅርስ፣ ፍልስፍና፣ ኪነ ህንፃ እና ኪነ ጥበብ በሰፊው እንዲጠና በመካከለኛው ዘመን የነበሩ ኢትዮጵያውን መነኮሳት እና ሊቃውንት በተለይ በአውሮፓ ለኢትዮጵያ ጥናት እና ምርምር መከፈት ምክንያት መሆናቸውን ታሪካችን ያወሳል፡፡ በተለይ አባ ጎርጎሪዎስ ዘመካነ ሥላሴ የተባሉት መነኩሴ ጀርመናዊውን ሉዶልፍን የግዕዝን ቋንቋ፣ የሀገራችን እና የኢትዮጵያን ቤተ ክርስቲያን ታሪክ በማስተማር በመካከለኛው ዘመን በአውሮፓ ምድር የኢትዮጵያ ጥናት እንዲጀመር በቀደምትነት መሠረትን የጣሉ  ኢትዮጵያዊ ሊቅ እንደሆኑ የሀገር ውስጥም ሆኑ የውጭ ሀገር ምሁራን ይመሰክራሉ፡፡
በእነዚህ ኢትዮጵያውያን መነኮሳትና ሊቃውንት በአውሮፓ የተጀመረው ጥናት እስከ አሁን ዘመን ድረስ ቀጥሎ በአውሮፓና በሰሜን አሜሪካ ትላልቅ ዩኒቨርስቲዎች፣ የጥናት እና ምርምር ማእከሎች በኢትዮጵያ ጥንታዊ ቋንቋ በሆነው በግዕዝ፣ በሀገሪቱ የረጅም ዘመን ታሪክ እና ሥልጣኔ ዙሪያ ሰፋ ያለ ጥናት በማካሄድ ላይ ናቸው፡፡ ለአብነትም ያህል በፈረንሳይ፣ በኢጣሊያን ፍሎረንስ እና ኔፕልስ ዩኒቨርስቲዎች፣ በጀርመን ሀምቡርግ ዩኒቨርስቲ፣ በለንደን School of Oriental and African Studies እና በአሜሪካ በሚገኙ ታላላቅ ዩኒቨርስቲዎች በጥንታዊው የኢትዮጵያ ቋንቋ በግዕዝ እና በሀገራችን ጥንታዊ ሥልጣኔ እና ታሪክ፣ ባሕል እና ቅርስ ዙሪያ ጥናቶች ይደረጋሉ፡፡
እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ በአብዛኛው በኢትዮጵያ ዙሪያ ጥናት እና ምርምር የሚያካሂዱ የውጭ ሀገር ምሁራን መሆናቸው ቀስ በቀስ እየተለወጠ ቢገኝም እኛ ኢትዮጵያውያን በዓለም አቀፍ ደረጃ ስለ እራሳችን በጥናት እና በምርምር በተደገፈ ሁኔታ በልበ ሙሉነት ለመናገርም ሆነ በተለያዩ ቋንቋዎች የዳጎሱ የጥናት መጻሕፍቶችን በማቅረብ ረገድ ገና ብዙ የሚቀረን ይመስለኛል፡፡ ምናልባትም የዚህ የማኅበረ ቅዱሳን የምርምር እና የጥናት ማእከል በየዓመቱ የሚያዘጋጀው የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ጥናት ዓመታዊ ጉባኤም በከፊል የዚህ ቁጭት እና ቅናት ውጤት የወለደው ነው ለማለት የሚቻል ይመስለኛል፡፡
የጥናት እና ምርምር ፋይዳውን የተረዱ የቤተ ክርስቲያኒቱ ፍሬዎች የሆኑ እና በተለያዩ የትምህርት መስክ እስከ ፒ ኤች ዲ የተማሩ ልጆቿ ጥረት ለአራተኛ ጊዜ በማኅበረ ቅዱሳን የምርምር እና ጥናት ማእከል የተዘጋጀው አራተኛው የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ጥናት ጉባኤ፣ በጥናት እና በምርምር በመታገዝ በቤተ ክርስቲያናችን ያሉትን ችግሮች በሚገባ አጥንቶ በቤተ ክርስቲያንም ሆነ ተያያዥ በሆኑ፣ በወቅታዊ የሀገራችን ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ ጉዳዮች ላይ መፍትሔ ለማፈላለግ የበኩሉን ድርሻ ለማበርከት በሚል ከአራት ዓመታት በፊት የተጀመረ ጉባኤ መሆኑን የማኅበረ ቅዱሳን ሰብሳቢ የሆኑት ቀሲስ ዶ/ር ሙሉጌታ ሥዩም በመክፈቻ ንግግራቸው ገልጸዋል፡፡
ለአራተኛ ጊዜ በሀገር አቀፍ ደረጃ ለሁለት ቀናት በተደረገው የኢትዮጵያ ቤተ-ክርስቲያን የጥናት ጉባኤ ላይ በቀረቡት የጥናት ወረቀቶች እና ከተሳታፊያን በተነሱ ጥያቄዎች፣ አስተያየቶች እና ውይይቶች ዙሪያ መጠነኛ የሆነ አጭር ደሰሳ በማድረግ ይህችን አጠር ያለች ጹሑፍ ለአንባቢያን ለማቅረብ ወደድሁ፡፡
ይህ ጹሑፍ እግረ መንገዱንም በተለይ በማኅበረ ቅዱሳን እና ከማኅበረ ቅዱሳን በተቃራኒ በቆሙ ማኅበራት እና ግለሰቦች ደጋግመው ማኅበረ ቅዱሳንን ስለሚከሱበት፡- ‹‹ማኅበሩ የወንጌል ጠላት ነው፣ ማኅበረ ቅዱሳን የፖለቲካ ድ/ት ነው፣ ማኅበሩ በመንፈሳዊነት መጋረጃ ጀርባ የለየለት ዘራፊ እና ነጋዴ ሆኗል፣ ቤተ ክርስቲያኒቱ ላለፉት ሃያ ዓመታት ለገባችበት ቀውስ በከፊልም ቢሆን የማኅበሩ ተጠያቂ ነው…ወዘተ፡፡›› በማለት ማኅበሩን የሚከሱትን ቡድኖችንም ሆነ ግለሰቦች በሩቅ ቆመው ከመካሰስ እና እርስ በርስ ከመፈራረድ ይልቅ በቤተ ክርስቲያንም ሆነ በማኅበረ ቅዱሳን በኩል አሉ የሚሏቸውን ችግሮች እና ትዝብታቸውን በተጨባጭ መረጃ፣ በጥናት እና በምርምር በማስደገፍ ማቅረብ ቢችሉ እንዴት መልካም በሆነ ነበር፡፡ እንዲሁም በእንዲህ ዓይነቶቹ እና በተመሳሳይ የጥናት ጉባኤ መድረኮች ላይ በመገናኘት፣ በመቀራረብ እና በግልጽ በመነጋገር ልዩነቶችን አሰውግዶ በአንድነት መሥራት የሚቻልበት መንገድ እንዲኖር በሚል በቅንነት መንፈስ ያቀርብኩት ደሰሳ እንደሆነ ከወዲሁ ለአንባቢዎቼ በአክብሮት ለመግለጽ እወዳለሁ፡፡
በዚህ አራተኛው የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ጥናት ጉባኤ ላይ ከቀረቡት እና በጨርፍታ ዳሰሳ ላደርግባቸው ከመርጥኳቸው የጥናት ወረቀቶች መካከል በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የፕሬስ ባልደረባ፣ የታሪክ ምሁር እና ተመራማሪ እንዲሁም በሀገራችን በሚታተሙ ፖለቲካዊ፣ ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና የታሪክ ነክ መጽሐፎች ላይ ሰፊ እና ጥልቅ የሆኑ ዳሰሳዎችን (Book Reviews and Critics) በማድረግ የሚታወቀው አቶ ብርሃኑ ደቦጭ፡-

‹‹የማኅበረ ቅዱሳን የኅትመት ውጤቶች በቤተ ክርስቲያን እና በሀገራዊ አጀንዳዎች ላይ ያላቸውን የአዘጋገብ ሂደት›› በተመለከተ ባቀረቡት የጥናት ወረቀት ላይ በተለይ በስምዓ ጽድቅ ጋዜጣ ርዕሰ አንቀጾች፣ ዜናዎች እና ሐተታዎች ላይ አጥኚው ሰፋ ያለ ትንታኔ ለመስጠት ሞክረዋል፡፡ ጋዜጣዋ በቅዱስ ሲኖዶስ ስብሰባዎች፣ ሂደቶች እና ውሳኔዎች ላይ፣ በሃይማኖታዊ ግጭቶች መንስኤዎች ዙሪያ፣ ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ማኅበራዊ በሆኑ ወቅታዊ እና ሀገራዊ አጀንዳዎች ላይ የሚወጡ ዘገባዎች በአብዛኛው ፍርሃት የሚንጸባረቅባቸው ቢሆኑም ስምዓ ጽድቅ ጋዜጣ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ያሉትን ችግሮች በማሳየት ረገድ አዎንታዊ ሚና እንዳላት ጠቁመዋል፡፡ ነገር ግን ተግባራዊ የሚሆን መፍትሔን በማቅረብ ረገድ ግን ጋዜጣዋ ድካም እንደሚታይባት ገልጸዋል፡፡
አቶ ብርሃኑ ባቀረቡት የጥናት ወረቀት ላይ አንድ የቤተ ክርስቲያኒቱ ሊቃውንት እና በቅርስ ጥናት እና ጥበቃ የሥራ ባልደረባ የሆኑ ሰው በሰጡት አስተያየት፡- ‹‹ስምዓ ጽድቅ ጋዜጣ እንደ ስሟ እውነትን በመናገር ረገድ ብዙም የተዋጣላት አይደለችም፡፡›› የማኅበረ ቅዱሳን ኅትመት ውጤቶች፡- ‹‹የቤተ ክርስቲያን ዋና ተልእኮ የሆነው ወንጌልን ገሸሽ ያደረጉና የወንጌሉ ዐቢይ መልእክት እውነት፣ መንገድ እና ሕይወት የሆነውን ኢየሱስ ክርስቶስን በሚገባ የማይገልጽ ነው በሚል አስተያየታቸውን አጠናክረዋል፡፡›› በሌላ በኩል ደግሞ ሌሎች አስተያየት ሰጪዎች፡- ‹‹የማኅበረ ቅዱሳን የኅትመት ውጤቶች በቅዱስ ሲኖዶስ ስብሰባዎች እና ውሳኔዎች ላይ እንዲሁም ሀገራዊ በሆኑ ወቅታዊ እና አንገብጋቢ ፖለቲካዊ አጀንዳዎች ላይ ግልፅነት እና ተጠያቂነት የሚያንሰው ነው ሲሉ…›› ሌሎች በግል ያነጋገርኳቸው ተሳታፊዎች ደግሞ በዋነኝነት፡-
‹‹በቤ/ን እና በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ የማኅበረ ቅዱሳን የኅትመት ውጤቶች መንፈሳዊ ወኔ እና ድፍረት የሚጎድለው አዘጋገብ እንደ ሚንጸባረቅበት…›› አስተያየታቸውን ሰጥተውኛል፡፡ 

Sunday, September 16, 2012

«ሰምና ወርቅ»


 ከካሳሁን ዓለሙ ድረ ገጽ ተመርጦ የተወሰደ ቅኔ፤
*********************
እንኳን ደኅና ገባህ ከሄድክበት አገር፣

ጠላቶችህ ሁሉ ይቅር ብለው ነበር፡፡

***************

‹ትግራይ› አይደለም ወይ መለስ ትውልድህ፣

የጁ ነው በማለት የደበደቡህ፡፡
*****************

‹መለስ ዜናዊ› ታላቅ መስፍን፣

ነበሩ ሲሉ ባገራችን፣

እንዲያ ሳያጡ ሰገነት፣

ምነው አደሩ ፈረስ ቤት፣

ሞከሩት እንጂ አልኖሩም፣

ከዳሞት አልቀሩም፡፡

***************
በዓለ ድባብ ንጉሥ ባለ ጥና አቡን፣

እየዞሩ ፈቷት አገራችንን፡፡
****************

አሁን ምን ያደርጋል ሱሰኛ መሆን፣

ብዙ ቤት ፈረሰ ትላንት በዚያ ቡን፡፡
***************

ይድናል እያልን ዓይን ዓይኑን ስናይ፣

እንዲያ እንደፈራነው እውነት ሞተ ወይ?
************

የዛሬ ዘመን ወዳጅም፣

ከሽሕ አንድ አይገኝም፣

አንቱ ብትለው ይኮራል፡

አንተ ያልከው ግን ይኖራል፡፡
*********

አሻግሬ ባይ መንገዱን፣

ኧረ ሰው ምናምን፡፡
************
ተስቦ ገብቶ ከቤቴ፣

አልወጣ ካለኝ ዓመቴ፡፡
**************

ወደ አደባባይ ወጥተህ፣

ከባላጋራህ ተሟግተህ፣

ክርክር ገጥመህ ወደ ማታ፣

ዓለም አፈር ነው ስትረታ፡፡
***************
‹ዋልድባ› ወርጄ ቀስሼ፣

ልብሰ ተክህኖ ለብሼ፣

ታዩኛላችሁ እኔን

ነገ ገብቼ ሣጥን፡፡
**************

ክፉ ቢናገር ተቆጥቶ፣

ጠላትህ ደሙ ፈልቶ፤

እሱም እንዳንተ ሰው ነው

ኧረ ተው ሰብቀህ አትውጋው፡፡

Friday, September 14, 2012

ከተማን በመግዛትህ ሁሉን እገዛለሁ አትበል!


ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ፣ ምእራፍ ከተባለ መፅሄት ጋር ያደረጉትቃለመጠይቅ፣
           በጣም የሚወዱትን መዝሙር ይንገሩኝ?
           አቶ ኃ/ማርያም፡- ‹‹እኔም እንደ ዳዊት ጨርቄን ልጣልልህ›› የሚለውን
           ጉባዔ ገብተው ሲያመልኩ ግን እንደ ባለሥልጣን የፕሮቶኮል ነገር አለ፡፡ የጥበቃ ጉዳይ አለ፡፡ ሌላም ሌላም፡፡ ይሄን ሁሉ ረስተው በነጻነት ለማምለክ አይቸገሩም?
አቶ ኃ/ማርያም፡ ምንም አልቸገርም፡፡ ጉባዔ ውስጥ ካለሁ እኔ ስለ ራሴ ጨርሶ አላስብም፡፡ እነ ንጉሥ ዳዊት በእግዚአብሔር ፊት ጨርቃቸውን ጥለው ያመልኩ ነበር፡፡ እኔስ የማመልከው እግዚአብሔር ፊት እንደሆንኩ እንጂ የማስበው ሌላ ነገር አላስብም ማልቀስ ካለብኝ አለቅሳለሁ፣ መንበርከክ ካለብኝ እንበረከካለሁ፡፡ ጌታ ሁን ያለኝን ሁሉ ለመሆን ዝግጁ ሆኜ ነው የማመልከው፡፡
ልጆችዎ በቤተክርስቲያን ውስጥ የመክሊት (የአገልግሎት) ሥራ ውስጥ ሲሳተፉ ይታያል፡፡ የእከሌ ልጅ ነኝ እኮ ብለው ሳይኩራሩ ወንድሞችና እህቶች የጠጡባቸውን የሻይ ብርጭቆዎች እየዞሩ ሲለቅሙ እንዳየ ወንድሜ ፍጹም ነግሮኛል፡፡ በቤት ውስጥ ምን ብለው ቢያስተምሯቸው ነው?
አቶ ኃ/ማርያም፡- እኔም ባለቤቴም ቤት ውስጥ ሁሉም የምንነግራቸው ነገር እኛ ጋር ምንም እንደሌለ እኛ ምንም እንዳልሆንን ሀብታችን ኢየሱስ እንደሆነ የማወርሳቸውም አምላኬን እግዚአብሔርን ብቻ እንደሆነ ነው የምንነግራቸው፡፡ አንተ የራስህ መኪና እንኳን የለህም፡፡ ቤት የለህም፣ አሁን እናንተ አንድ ነገር ብትሆኑ እኛ ምን አለን? ሲሉኝ እንኳን የምመልስላቸው መልስ የለንም ግን መኪና አጥተን እናውቃለን ወይ? ቤትስ አጥተን ማደሪያ አጥተን እናውቃለን ወይ? መኪና ብገዛም ቤት ቢኖረንም የእኛ አይደለም፡፡ ሁሉንም ትተነው ነው የምናልፈው፡፡ ሀብታችን ጌታ ብቻ ነው እላቸዋለሁ፡፡ በአገልግሎት እንዲበረቱም እንመክራቸዋለን፡፡
ለአገልግሎትና የክርስቶስን አካል ለማነጽ ልዩ ልዩ ጸጋ ይሰጣል፡፡ ለእርሶ የተሰጦት የጸጋ ዓይነት ምንድነው?
አቶ ኃ/ማርያም፡ እንግዲህ ጥሪ የተለያየ ነው፡፡ ሁላችንም መሰዊያ ላይ ቆመን አንሰብክም፡፡ እኔን ደግሞ የሰጠኝ የሚመስለኝ ጸጋ ሕዝብን እና አገርን በመልካም አስተዳደር ማገልገል ነው፡፡ ስለዚህ ለእኔ ሥራዬ ስራ ብቻ ሳይሆን አገልግሎትም ጭምር ነው ብዬ የተቀበልኩት፡፡
አቶ ኃ/ማርያም ጠዋት ከመኝታዎ ስንት ሰዓት ይነሳሉ?
አቶ ኃ/ማርያም፡/ሳቅ ብለው/ መመለስ አለብኝ እኔ ሁልጊዜ ከእንቅልፌ ምነሳው ከለሊቱ 11 ሰዓት ነው፡፡ ጉዞ፣ እንደዚህ አይነቱ ነገር ካልረበሸኝ በስተቀር 11 ሰዓት እነሳለሁ፡፡ ከ11 ሰዓት እስከ 12 ድረስ የፀሎት ጊዜዬ ነው፡፡ ከ12 እስከ 12፡30 ትንሽ ‹‹ኤክሰርሳይስ›› (ስፖርት እሰራለሁ፡፡ በቀሪው ጊዜ የዕለቱን የቢሮ ስራ አዘጋጅቼ 1፡30 አካባቢ ወደ ቢሮዬ እሄዳለሁ፡፡
አዘውትረው የሚጸልዩባቸው ጉዳዮች አሉ ካሉ ቢያስታውቁን?
አቶ ኃ/ማርያም፡እኔ ዘወትር በአራት ርዕሰ ጉዳዮች ላይ እጸልያለሁ፡፡ አንደኛ ሰላምና በረከት ለዚህች አገር እንዲበዛ እጸልያሁ፡፡ ለመሪዎቿ፣ ለመንግሥት፣ ባለሥልጣናት ጥበብና ማስተዋልን እንዲሰጥ እጸልያሁ፡፡ ሁሉም ሃይማኖቶች ያለ አድልዎ እና ልዩነት በእኩልነት እና በመቻቻል እንዲኖሩ እመኛለሁ፡፡ ሁለተኛ የእግዚአብሔር ቃል ‹‹ሰው ሁሉ ወደ መዳን እንዲመጣ›› ይላል፡፡ ስለዚህ ሰው ሁሉ እንዲድን እጸልያለሁ፡፡ ይህ የእግዚአብሔር ፈቃድ ነውና፡፡ ሶስተኛ እናቴ አልዳነችምና ለወላጅ እናቴ በተለይ እጸልያለሁ፡፡ አራተኛ ለልጆቼና ለቤተሰቤ ዘወትር እጸልያለሁ፡፡
እንደው በግልጽ ለመጠየቅ ያህል ወደ ሥልጣን ሲመጡ አብረው የሚመጡና ለመሥራትም የሚመቹ የኃጢአት ፈተናዎች ይኖራሉ፡፡ እርስዎ እስካሁን ድረስ የገጠምዎትን ፈተና በምን መንገድ አልፈውታል?
አቶ ኃ/ማርያም፡ የእውነት ለመናገር እስካሁን እግዚአብሔር ረድቶኛል፡፡ በፈተናዎቹ አልፌአለሁ እላለሁ፡፡ ይሄን ከልቤ ነው የምልህ፡፡ ንጉሥ ዳዊት የተከበረ በእግዚአብሔር ዘንድም የተወደደ በብዙ ነገር በጣም የተመሰገነ ንጉሥ ነበር፡፡ እስራኤልን የሚመስል ትልቅ ሕዝብ መግዛት የቻለ ዳዊት ግን ራሱን መግዛት አልቻለም ነበር፡፡ ለዚህ ነው መጽሐፍ ቅዱስ ከተማን ከመግዛት ይልቅ ራስን መግዛት ይበልጣል ያለው፡፡ ነገር ግን መጽሐፉ የሚመክረው ራስን ቤተሰብን መግዛት እንድንችል ነው፡፡ አለ አይደል ከተማን በመግዛትህ ሁሉን እገዛለሁ አትበል፡፡ አንዳንድ ጊዜ ውስጣዊ ሰብዓዊ ውድቀት ሊኖርብህ እንደሚችል አስበህ ጥንቃቄ አድርግ፡፡ ጥንቃቄ ይጠብቅሃል አይደል የሚለው መጽሐፍ ቅዱስ፣ ዝሙት ሊያታልህ ይችላል፡፡ ዝሙት እንዳይጥልህ ጥንቃቄ አድርግ፡፡ የሥጋ ምኞት፣ ገንዘብ ፍቅርና የዓይን አምሮት የሚባሉት አይደሉም ሰውን የሚጥሉት፡፡ ስለዚህ ከተማን የገዛ ሰው፣ በተለይ እነዚህ ሶስት ነገሮች ላይ መጠንቀቅ አለበት፡፡ እኛ ኢህአዴጎች ስኳር ነው የምንለው፡፡ ስኳሩ እንዳያታልልህ ጥንቃቄ መደረግ አለበት ነው ሀሳቡ፡፡ ፓርቲዬን በጣም የምወድበት ትልቁ ምክንያት ሙስናን፣ ያለ አግባብ፣ ጥቅም ለማግኘት የሚደረግን ጥረት ፓርቲዬ የኪራይ ሰብሳቢ አመለካከት የሚላቸው በሙሉ መጽሐፍ ቅዱስ ላይ የተወገዙ ናቸው፡፡ እነዚህ መሰረታዊ መርሆች ከመጽሐፍ ቅዱስ አስተምህሮት ጋር ይጣጣሙልኛል፡፡ አይቃረኑም፡፡ ስለዚህ ሙስና፣ አላስፈላጊ ጥቅማጥቅሞች፣ ውሸት ውስጥ ሳትገባ ሕዝብን ማገልገል አለብህ ስለሚል የኔ ፓርቲ እነዚህን መርሆዎች ስለሚያራምድ ይህ ደግሞ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ስለሆነ በጣም ደስ ብሎኝ ነው የምሰራው፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ ላይ አንተ ራስህ ከእግዚአብሔር ጋር ንስሐ በመግባት የምትፈታው ነገር ከተገኘ ተገምግመህ እንድትስተካከል ይሆናል ወይም ደግሞ ልትባረርም ትችላለህ፡፡ ስለዚህ ፓርቲዬ በዚህ ጉዳይ ላይ በጣም በጣም ጠንካራ አቋም አለው፡፡ እና በዚህ ዓይነት ነው፡፡
የሚጸጸቱበትን ውሳኔ አስተላልፈው ያውቃሉ?

Thursday, September 13, 2012

«ጉድ ሳይሰማ መስከረም አይጠባም!»

«እናንተ ብትገቡበት አያቅታችሁም፤በቤተ ክህነት አጽናኝም አሸባሪም መኖሩን የተናገሩት» አባ  ኤልሳዕ የደቡብ ጎንደር ሊቀ ጳጳስ

«ማኅበረ ቅዱሳን ቅዱስ ሲኖዶስን በዙሪያው ኾኖ የሚጠብቅ፣ የቅዱስ ሲኖዶሱን ውሳኔዎች በማስፈጸም ረገድም ቋሚ ተጠሪ ነው»
አባ ማትያስ የካናዳ ሊቀ ጳጳስ
«የቅድስት ቤተ ክርስቲያን አንድነት እንዳይናጋ “በወርድም በቁመትም መሥራቱን” አጠናክሮ እንዲቀጥል» አባ ገብርኤል የሃዋሳ ሊቀ ጳጳስ
«ማኅበሩን መደገፍ ቤተ ክርስቲያንን ማገልገል እንደኾነ» ቄስ ኃ/ሥላሴ ዓለማየሁ
ከ40 ሚሊዮን ተከታዮች በላይ ያሏትን ቤተክርስቲያን ከመንበረ ፓትርያርክ እስከ የገጠሪቱ አጥቢያ ቤተክርስቲያን ድረስ የመምራትና የማስተዳደር ሥልጣን የተረከቡ ሊቃነ ጳጳሳት ከቤተክርስቲያኒቱ የምእመናን ማኅበር አንዱ አባል ለሆነው ለማኅበረ ቅዱሳን ይህን ያህል «ተቀመጥ በወንበሬ፤ ተናገር በከንፈሬ» ዲስኩር ለማሰማት መድረሳቸው በእርግጥም የቤተክርስቲያኒቱ መሪዎች እግዚአብሔርን ተስፋ ከማድረግ ወርደው፤ መንፈስ ቅዱስን አጋዥና መሪ ከማድረግ ወጥተው፤ ማኅበረ ቅዱሳን የቤተክርስቲያኒቱ መንፈስ ቅዱስ ስለሆንክ አንተ ምራን ከሚሉበት ደረጃ መድረሳቸው አሳዛኝም ፤አሳፋሪም ነው።
አባ ኤልሳዕ የደቡብ ጎንደር ሊ ቀጳጳስ በሁለቱ ሲኖዶስ መካከል ያለውን ቅራኔ ለመፍታት ማኅበረ ቅዱሳን ቢገባበት ምንም የሚያቅተው እንደሌለ መናገራቸው ሲሰማ በእርግጥ እኒህ አባት በመንፈስ ቅዱስ ኃይል ይመራሉ? ብለን እንድንጠይቅ እንገደዳለን። የ21 ዓመቱ ክፍፍል ሊያበቃ ያልቻለው ለካ፤ በሥጋዊ መንፈስ እየተመሩና የመንፈስ ቅዱስን ኃይል ታምነው እንዳልነበረ ከማሳየቱም በላይ ዛሬም ከዚያው ስህተታቸው ሳይላቀቁ ማኅበረ ቅዱሳንን ለማስቀደም መድፈራቸውን ስንመለከት ቤተክርስቲያኒቱ የምትመራው በእነማን እንደሆነ ቁልጭ ብሎ ይታየናል።  «እናንተ ብትገቡበት አያቅታችሁም» ማለታቸው የሚያሳየው እስከዛሬ የዘገውም ማኅበረ ቅዱሳን በእርቁ ውስጥ የማሸማገል ሚናውን ስላልተወጣ ነው ማለታቸው ነው። ሲኖዶሱ ደካማና ለእርቁ መፈጸም አቅም የሌለው በመሆኑ እስካሁን የመዘግየቱ ምክንያት እንዲህ ከተገለጸላቸው ታዲያ ለምን ማኅበረ ቅዱሳንን የሲኖዶሱ የእርቁ ቋሚ ተጠሪ አድርገው በመሾም ቶሎ እንዲፋጠን ያላደረጉ? በዚያውም ደግሞ በሲኖዶስ ጉባዔ ላይ እንደፓርላማ ደንብ በአጋር ድርጅትነት ወንበር የማይሰጡት?
ማኅበረ ቅዱሳን የራሱ የሆነ  የአጭርና የረጅም ጊዜ እቅድ ያለው ድርጅት ነው። በዚህ ስውርና ግልጽ የዓላማዎቹ ጉዞ ላይ የሚቀበሉትን እስከነጉድፋቸው ተሸክሞ ለመጓዝ የማይጠየፍ፤ የማይቀበሉትን ደግሞ ምንም እንኳን ንጹሐን ቢሆኑ አራግፎ ለመጣል ጥቂት የማያቅማማ ድርጅት እንደመሆኑ መጠን እነ አቡነ ኤልሳዕን የመሳሰሉ ታማኞች  «አንተ ስላልገባህ እኛ አቅቶናል» የሚል ድምጸት ያለውን ቃል ቢናገሩለት ማን መሆናቸውን ከሚያሳዩ በስተቀር ስለማኅበረ ቅዱሳን ሁሉን አዋቂነትና የመፍትሄ ቁልፍነት መናገራቸው ማንንም አያሳምንም።
ሌላው አባትም ገና ከወደ ካናዳ ብቅ ከማለታቸው «እስመ አልቦ ነገር ዘይሰዓኖ ለማኅበረ ቅዱሳን» የሚል ትርጉም ያለውን ቃል ሲናገሩ መስማት ለጆሮ ይቀፋል። እሳቸው የተናገሩት ነው ተብሎ በደጀ ሰላም የሠፈረውን ይህን ቃል መዝኑት።
«ማኅበረ ቅዱሳን ቅዱስ ሲኖዶስን በዙሪያው ኾኖ የሚጠብቅ፣ የቅዱስ ሲኖዶሱን ውሳኔዎች በማስፈጸም ረገድም ቋሚ ተጠሪ ነው»
ማኅበረ ቅዱሳን እውነት የሚታዘዝ ሆኖ ከሆነ ይታዘዛል፤ ይላካል፤ የሲኖዶሱን ትእዛዝ ተግባራዊ ለማድረግ ሲጠሩት አቤት፤ ሲልኩት ወዴት ይላል ብሎ ታዛዥነቱን መግለጽ አንድ ነገር ነው። ነገር ግን ማኅበረ ቅዱሳን፤ ቅዱስ ሲኖዶስን በዙሪያው ኾኖ ይጠብቀዋል ማለት ማኅበረ ቅዱሳን እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ኾኗል ማለት ነው።  ቅዱስ ሲኖዶስ ዙሪያውን ሆኖ የሚጠብቀው መንፈስ ቅዱስ ነው ወይስ ማኅበረ ቅዱሳን? የሲኖዶሱ አባል አባ ማትያስ ግን ሲኖዶሱ ዙሪያውን ሆኖ የሚጠብቀው ማኅበረ ቅዱሳን ነው ሲሉ በግልጽ መናገራቸው ማኅበረ ቅዱሳን ሁሉን ማድረግ እንደሚችል የማወጃቸው ነገር አስገራሚ ነው። ሲኖዶሱ በምን ዓይነት ሰዎች እንደተሞላ ከማሳየት አልፎ ፓትርያርክነቱን ለማግኘት ስለማኅበረ ቅዱሳን ታላቅነት መማል ፤ መገዘት የግድ ሆኗል ማለት ይቻላል።
አባ ማትያስ የሲኖዶሱ ጠባቂ ማኅበረ ቅዱሳንን ከማድረጋቸውም በላይ የሲኖዶሱን ውሳኔዎች ለማስፈጸም የሲኖዶስ ቋሚ ተጠሪ መሆኑንም አያይዘው አውጀውልናል። አሁን እንግዲህ ማኅበረ ቅዱሳን ከማኅበር ጣሪያ በላይ ወጥቷል። ከእንግዲህ ማኅበረ ቅዱሳን ድስት ያላጠለቀ ሲኖዶስ ነው ማለት ነው። በንግግር መሳት ካልቀረ እንደእነ አቡነ ማትያስ ጭልጥ ብሎ መንጎድ እግዚአብሔር ሲኖዶስን ይጠብቃል፤ ሥራውን ሁሉ ያከናውናል እስኪባል ድረስ የሲኖዶስ ጣዖት ሆኖ ማኅበረ ቅዱሳን ይቀጥላል ማለት ነው።
እነሱው በሰጡህ ፈቃድ መሠረት የሲኖዶስ ጠባቂ ማኅበረ ቅዱሳን ሆይ እነዚህን ጳጳሳት ጠብቅ፤ ከፍ ከፍም አድርጋቸው!!! እንላለን።
ሌላው ሊቀ ጳጳስ ደግሞ አባ ገብርኤል ናቸው። በመሠረቱ አባ ገብርኤል ከሲኖዶሱ ይልቅ በማኅበረ ቅዱሳን እንደሚታመኑና እንደሚመኩ ይታወቃል። አባ ገብርኤል ወደ ምድረ አሜሪካ ኰብልለው በመሄድ ኢህአዴግ ይውደም፤ አባ ጳውሎስ ይውረዱ በማለት የፖለቲካ ሰልፍ ሲመሩ እንደነበሩ መረጃዎቻችን ያሳያሉ። ከዚያም በድርድር ይሁን በእርቅ ለጊዜው በማይታወቀው ምክንያት ግሪን ካርዳቸውን ይዘው ወደ አዲስ አበባ በሁለት ዜግነት መግባታቸውን ደግሞ አየን። በእርግጥ ሰው ከስህተቱ ቢታረም አያስገርምም። አባ ገብርኤልን ስንመለከት ከስህተት የሚማሩ አይመስሉም። ዛሬ ደግሞ የዳቦ ስሙን ላወጡለት ማኅበር እንዲህ ሲሉ ይደመጣሉ።
«የቅድስት ቤተ ክርስቲያን አንድነት እንዳይናጋ “በወርድም በቁመትም መሥራቱን አጠናክሮ እንዲቀጥል»  ማኅበረ ቅዱሳን ያስፈልጋል ይሉናል።ኧረ ለመሆኑ  የቤተክርስቲያኒቱ አንድነት እንዳይናጋ፤ በወርዷም፤ በቁመቷም ለመስራት አልነበረም እንዴ አባ ገብርኤል ጵጵስና የተሾሙት?  በተሰጣቸው ጵጵስና መስራት ካቃታቸው ለሰጠቻቸው ቤተክርስቲያን መመለስ እንጂ ቤተክርስቲያንን እንዲመራ ውክልና ለሌለው ማኅበር ከወርድ እስከቁመቷ እንዲያዝባት እነሱ ደግሞ በተራቸው አሳልፈው እንዴት ይሰጣሉ?
ሲኖዶሱ ከመንበረ ፓትርያርክ አንስቶ እስከ ገጠሪቱ የሳር ክዳን አጥቢያ ድረስ መዋቅሩን የዘረጋው በወርዷም፤ በቁመቷም ለመሥራት አይደለም እንዴ?   አባ ገብርኤል ግን ያቃተቸው ይመስላል። ይልቁንም እኛ ስራውን ሁሉ ለማኅበረ ቅዱሳን እናስረክብና በወርዷም፤ በቁመቷም እሱው ይዘዝባት እያሉ አዋጅ ማስነገር ይዘዋል። አባ ገብርኤልስ የሌላ ሀገር ዜግነት ስላላቸው ነገር ዓለሙ መበላሸቱን ሲያዩ እብስ ብለው ወደ ጥንት የሰልፍ ሀገራቸው አሜሪካ ሊሄዱ ይችላሉ! ማኅበረ ቅዱሳን እንኳን በወርድ በቁመቷ፤ አንዲት ጋት በቤተክርስቲያን ላይ የማዘዝ መብት የለውም የሚሉ የቤተክርስቲያን ልጆችንስ ጅቡ ማኅበር ይዋጣቸው ማለት ነው?
እስከሚገባን ድረስ የቤተክርስቲያኒቱ ራስ እግዚአብሔር ነው። አንዳንድ ጳጳሳት ጠባቂያችን ማኅበረ ቅዱሳን ቢሉም እስከሚገባን ድረስ የሲኖዶሱ ጠባቂ መንፈስ ቅዱስ ነው። እግዚአብሔርን ራስ አድርጎ ሲኖዶሱ በመንፈስ ቅዱስ ኃይልና መገለጥ ቤተክርስቲያንን በወርድና በቁመቷ ይመራታል እንላለን። ከእነ አባ ገብርኤል የተገኘው አዲስ ግኝት ግን በወርድና በቁመቷ ለመሥራት ሥልጣኑ የማኅበረ ቅዱሳን ሆኗል። አባ ገብርኤል ፓትርያርክነቷ ተወርውራ እኔ ጋር ትደርሳለች ብለው አስበው ይሆን?
አንድ ጊዜ ሥልጣናቸው ተገፎ አቶ ኢያሱ የተባሉ፤ ሌላ ጊዜ ደግመው ኮብልለው የፖለቲካ ሰልፍ ሲመሩ የነበረ፤ በኋላም ተመልሰው የወደዷቸውን ጸረ ኢህአዴጎችን ከአሜሪካ ከድተው ፤ የጠሉትን ኢህአዴግን ወደው፤ የጽዋውን ማኅበር ማኅበረ ቅዱሳንን አነግሳለሁ እያሉ በአደባባይ በማወጅ የተጠመዱና በአንድ ቦታ በአንድ ቃል የማይረጉ አባ፤  እንኳን ፓትርያርክ ሊመረጡ ለእጩነትም ሊቀርቡ ተገቢ አይደለም። መጽሐፍ  «በዲያብሎስ ነቀፋና ወጥመድም እንዳይወድቅ፥ በውጭ ካሉት ሰዎች ደግሞ መልካም ምስክር ሊኖረው ይገባዋል» ይላልና። አባ ገብርኤል ለምንም ሹመት የሚበቁ አይደሉም እንላለን። « ሆያ ሆዬ ጉዴ ፤ብሯን ብሯን ይላል ሆዴ» እንደሚሉት የሆያ ሆዬ ጫወታ የእሳቸውም ሆድ ቁንጮዋን መጨበጥ ስለሆነ ሆዳቸውን እየቆረጠ እንዳይቸገሩ ቁርጣቸውን ማሳወቅ ተገቢ ነው።

Tuesday, September 11, 2012

በአዲሱ ዓመት አዲስ ሰው እንሁን!


ለነፍሳችን እረፍትን የሰጠን እግዚአብሔር የታመነ ነው። ይሁን እንጂ ይህንን የነፍስ እረፍት ባለማግኘታችን በረከትና የኃጢአት ሥርየት ፍለጋ ከቦታ ቦታ የምንዞር ኢትዮጵያውያን ስፍር ቁጥር የለንም። ዘመናቱን እያፈራረቀ መግቦቱን ያላቋረጠ እግዚአብሔር ከሊቅ እስከ ደቂቅ ያለውን እነሆ ይመግባል። ነገር ግን ሚሊዮኖች ኢትዮጵያውያን የእለት እንጀራችንን ከእርዳታ ለጋሽ ሀገራት ምጽዋት በመጠበቅ የወፍ ጫጩት ከመሰልን ዓመታት አለፈን። ገሚሶቻችንም ምጽዋቱ ሲቀንስ፤ እድሜና ሆዳችን በማደጉ ረሃብና ጠኔ ከሚገለን የበረሃው ሃሩር ያቅልጠን፤ የባሕሩ ዓሳ ይብላን እያልን ዳቦ ፍለጋ መንጎዳችን ቀጥሏል።
እንግዲህ በነፍሳችን በረከት፤ ቃል ኪዳን፤ ሥርየት፤ ምሕረት፤ እረፍትና መድኃኒት መፈለግ ከጀመርን፤ ለሥጋችንም ዳቦ፤ ለእርዛታችን እራፊ መሻታችን ማብቂያ አለማግኘቱ የሚጠቁመን ነገር በእኛ በቃል ተቀባዮቹና በቃል ሰጪው በእግዚአብሔር መሃከል የሆነ ችግር አለ ማለት ይቻላል። እግዚአብሔር ለነፍስ እረፍትን ለሥጋ መግቦቱን ስለመስጠቱ ከተማመንን ከዚህ ስጦታ የኛው ድርሻ የጎደለው ለምንድነው? ብለን መጠየቁ ተገቢ ነው።
መጽሐፍ እንደሚለው በእርሱ የሚታመኑ ሁሉ ሕያው ቃሉን እየታመኑ ይህንን ለማለት ይደፍራሉ። «ነፍሳችን እግዚአብሔርን ተስፋ ታደርገዋለች፥ ረዳታችንና መጠጊያችን እርሱ ነውና» መዝ 3320
ይሁን እንጂ ለነፍስ እረፍት የሚሰጠው እግዚአብሔር ያጎደለው ነገር ያለ ይመስል ኢትዮጵያውያን የነፍስ እረፍት ፍለጋ ሀገሪቱን ስናስስ እድሜአችንን ኖረናል። ዛሬም ፍለጋችን እነሆ አላቋረጠም። መሻታችንን ከምንፈልግበት ቦታ ደርሰን በማግኘት የረካነው ስንቶቻችን እንሆን? ብዙዎች ግን ዛሬም ተስፋው እንደሞላ ሰው ረክቶ ከመቀመጥ ይልቅ የተሻለ መተማመኛና እረፍት ፍለጋ ላይ ናቸው። በረከት፤ ምሕረት፤ ሥርየት፤ ቃል ኪዳን፤ አስተማማኝ ቃል ፍለጋ፤ ፍለጋ.........ግን መገኛው የት ይሆን?
እስካሁን አስተማማኝ ነገር ላለመገኘቱ እለታዊ ሕይወታችን ግን ይመሰክርብናል። እኛም አላረፍንም፤ ሀገራችንም ከችግር አላረፈችም።
መዝሙረኛው እንዳለው «ነፍሳችን በመሬት ላይ ተጐሳቍላለችና፥ ሆዳችንም ወደ ምድር ተጣብቃለች» መዝ 4425 እንዳለው እየሆነብን መሆኑ እርግጥ ነው።
ሚሊዮኖች በሀገራቸው ባለው ነገር ተስፋ በመቁረጣቸው ተሰደዋል። ወለተ ማርያም ከድጃ፤ አመተ ማርያም ፋጡማ ወዘተ እየተባሉ የማያውቁትን እምነት እምነታቸው አድርገው ለባርነትና ከሰው በታች ለሆነ ኑሮ እራሳቸውን በመሸጥ የሚኖሩትን ብዙ ሺዎችን ስናይ እግዚአብሔር ተስፋችን ባርኮታል ማለት እጅግ ይከብዳል። እኛ እንደምንለው፤ እውነት ኢትዮጵያ ሀገረ እግዚአብሔር ከሆነች የተሰጠው አጸፋ እንዲህ ዓይነት ፈተና ሊሆን ይገባው ነበር? ወይስ እግዚአብሔር ስለሚወደን እኛን ለመከራ አሳልፎ በመስጠት ሊፈትነን ስለፈለገ ይሆን?
ይህንን ቃል ለመቀበል ያስቸግራል። እየተራበ፤ ያስራበኝ እግዚአብሔር ስለሚወደኝ ነው የሚል ሰው እግዚአብሔርን አያውቀውም፤ አለበለዚያም እግዚአብሔር ቃሉን ለሚጠብቁ አጠግባችኋለሁ ካለው እኛን የሚበድልበትን ምክንያት ሊያሳየን የግድ ይሆናል።
እውነታው ግን እግዚአብሔር ቃሉን እንደሰው አይለዋውጥምና ለሚታዘዙት በረከትን፤ ለሚቃወሙት ቁጣን እንደሚሰድ ስለምናውቅ ራሳቸውን እየደለሉና ሕጉን ሳይጠብቁ እኛ ሀገረ እግዚአብሔር ነን የሚሉቱን አስመሳዮች አንቀበላቸውም።
ረሃብ፤ እርዛት፤ ህመምና ሞት ለሰው ልጆች ከእግዚአብሔር የተሰጡ ገጸ በረከቶች አይደሉም። ሰው ራሱ በራሱ ላይ ወዶና ፈቅዶ ያመጣቸውና የሚያመጣቸው ጉድለቶች ስለመሆናቸው ቃሉ ይናገራልና።
«ለስሜ ክብር ትሰጡ ዘንድ ባትሰሙ፥ በልባችሁም ባታደርጉት፥ ይላል የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር፥ እርግማን እሰድድባችኋለሁ፥ በረከታችሁንም እረግማታለሁ አሁንም በልባችሁ አላደረጋችሁትምና እኔ ረግሜአታለሁ» ሚል 22


Saturday, September 8, 2012

እውነቱ የቱ ነው?

መነሻ ሃሳብ «ገመና ዘ81ዱ» መጽሐፍ

ርእስ፤  እውነቱ የቱ ነው?
    
 ሀተታ፤
በኦርቶዶክሳውያን  ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ውስጥ ከታች ጀምሮ እስከላይኛው እርከን ድረስ ያለው ሰው ስህተት ይኖርብናል ወይም ልንሳሳት እንችላለን ብሎ የሚያስብ ማግኘት አዳጋች ነው። በክርስቶስ ደም የተመሰረተችው ቤተክርስቲያን ፍጽምትና ንጽሕት መሆኗን በመቀበል እንዳለ መሪውና ተመሪው ራሱንም በዚያው ዓይን እያየ እኛ ፍጹማንና ንጹሐን ነን በሚል ከለላ ስር ራሱን በማስጠለል፤ ስህተትን አምኖ ለመቀበል አይፈልግም። የስህተት አስተምህሮ አለ፤ በእግዚአብሔር ቃል ሲመረመር አደጋው የከፋ ነው፤ የክፉ መንፈስ አሰራር ወደማወቅ እንዳንደርስ ቃሉን በክሏል ሲባል የሚሰጠው ምላሽ፤ 2000 ሺህ ዘመን የኖረችን ቤተክርስቲያን ዛሬ የተነሱ አፍቃሬ ተሐድሶ መናፍቃን ሊያርሟትና ሊበርዟት ይፈልጋሉ በማለት ታፔላ መለጠፍ ይቀናቸዋል። የስም ታፔላ መለጠፍ ብቻ ሳይሆን ሽልማት የሚያሰጥ ቢሆን ኖሮ የተመረጡና ለመስማት የሚዘገንኑ ስድቦችና ዛቻዎች ይዥጎደጎዳሉ።
በእርግጥ የክርስቶስ ቤተክርስቲያን ፍጽምትና ንጽሕት መሆኗ አያጠራጥርም። ምክንያቱም የመሠረታት በዓለቱ ላይ በፈሰሰው ደሙ ነውና። ይህ እውነት ቢሆንም በክርስቶስ ቤተክርስቲያን ውስጥ አባል ሆነው የሚኖሩት የአዳም ልጆች መሆናቸውንም በመዘንጋት የቤተክርስቲያኗን መንፈስና ባህርይ እንዳለ ወደሰዋዊ ማንነት በመውሰድ እኛ ፍጹማንና ንጹሐን ነን በማለት ከስህተት አልባነት የቤተክርስቲያን ማንነት ጋር ራስን መቁጠር ትኩረት የሚያሻው መሆኑን ልናሰምርበት ይገባል። በእርግጥም የተጠራነው ፍጽምት በሆነች ቤተክርስቲያን ውስጥ ፍጹማን እንድንሆን ነው። ነገር ግን ሰው ከተፈጠረበት ማንነት የተነሳ በፍጽምቷ ቤተክርስቲያን ውስጥ ፍጹም ሆኖ መኖር የሚችል ማንነት የለውም።
ለዚህ ጥሩ ምሳሌ ሊሆኑን የሚችሉት የገላትያ ሰዎች ማንነት ነው። የገላትያ ሰዎች በክርስቶስ አዳኝነት አምነው ወደ ሕይወት መንገድ የተመለሱ ሕዝቦች ነበሩ። ፍጽምትና ንጽሕት በሆነች የክርስቶስ ቤተክርስቲያን ተጨምረው የቆዩ ሆነው ሳለ ሰብአዊ ማንነታቸው አሸንፎአቸው ወደስህተት መንገድ በመግባታቸው በሐዋርያው ጳውሎስ እጅግ የተወቀሱ ሕዝቦች ሆነዋል።
«የማታስተውሉ የገላትያ ሰዎች ሆይ፥ በዓይናችሁ ፊት ኢየሱስ ክርስቶስ እንደ ተሰቀለ ሆኖ ተሥሎ ነበር፤ ለእውነት እንዳትታዘዙ አዚም ያደረገባችሁ ማን ነው?» ገላ 3፤1
ክርስቶስ ኢየሱስ በፊታቸው የተሰቀለ ሆኖ በእምነት ይታያቸው የነበሩት ሕዝቦች ከዚያ የቅድስና ማንነት ወርደውና እውነትን በመተው፤ የጠላት አዚም የወረደባቸው  ሕዝቦች እስከመሆን መድረሳቸውን ሲናገር እናያለን። ሥራቸውን ሁሉ በመንፈስ ቅዱስ ኃይል የጀመሩ ሆነው ሳለ ቁልቁል ተመልሰው የሥጋን ሃሳብና እውቀት ወደማመን መመለሳቸው በእርግጥም አሳዛኝ የሰው ልጆች ማንነት ማሳያዎች እንደሆኑ የሚያስገነዝበን  ነገር ነው።
«እንዲህን የማታስተውሉ ናችሁ? በመንፈስ ጀምራችሁ አሁን በሥጋ ትፈጽማላችሁን?» ገላ 3፤3 ይላል።

 እንግዲህ ክርስቲያኖች ፍጽምትና ንጽሕት በሆነች ቤተክርስቲያን ውስጥ በመንፈስ ቅዱስ ኃይል እምነታቸውን ሊጀምሩ ይችላሉ። ይሁን እንጂ ይህንን ፍጽምና ወደአለማወቅ መመለስም ሊታይባቸው ይችላል። ምን ጊዜም ቢሆን የስህተት መንፈስ አገልግሎቱ፤ የእውነቱን መንፈስ ከሰው ልቡና ላይ በመውሰድ ወደስህተት መንገድ መምራት ስለሆነ በቅድስት ቤተክርስቲያን ውስጥ ባሉ ሰዎች ውስጥ የስህተት አስተምህሮ እንደሚገባ እናረጋግጣለን።
ብዙዎች የአብያተ ክርስቲያናት አባላት በክርስቶስ ፍቅር ላይ ጸንተው ከመቆም ይልቅ ወደ ምድራውያንና ሰማያውያን ፍጥረቶች ፍቅራቸውን ስለለወጡ የሕይወት መንገድን ስተው መገኘታቸው እውነት ነው።
ጳውሎስ ጢሞቴዎስ ልጁን ወደ ተሰሎንቄ የላከበት ዋናው ምክንያትም ተሰሎንቄዎች  ከእምነት ጽናታቸው ወደኋላ እንዳይመለሱ በመንፈስ ያበረታታቸው ዘንድ ነበር። ምክንያቱም ፈታኝ የምንጊዜም አዚሙን የሚያፈሰው  የአማኞችን ልቡና በማደንዘዝ ወደ አልሆነ አቅጣጫ መመለስ  ሥራው ስለሆነ ከዚህ ፈታኝ ይጠበቁ ዘንድ እንደላከላቸው ቅዱሱ ወንጌል ይነግረናል።
«ስለዚህ እኔ ደግሞ ወደ ፊት እታገሥ ዘንድ ባልተቻለኝ ጊዜ። ፈታኝ ምናልባት ፈትኖአቸዋል ድካማችንም ከንቱ ሆኖአል ብዬ እምነታችሁን ለማወቅ ላክሁ» 1ኛ ተሰ 3፤5
ከከሳቴ ብርሃን አባ ሰላማ ወዲህ ወደ ኢትዮጵያ መጥተዋል ተብለው የሚጠሩ መነኮሳት በዋሻና በፍርክታ ገዳም መስርተው ሰው ሁሉ ወደዚያው እንዲከትም ከማድረግ ውጪ ሀገር ላገር ዞረው፤ እንደሐዋርያቱ ወንጌል ላልበራለት ሕዝብ ወንጌልን ስለማስተማራቸው የሚታወቅ ነገር የለም። ወንጌል ለሕዝቡ የበራ ቢሆንማ ኖሮ እስከዛሬ በዛፍ ስር ቡና የሚደፉ፤ ደም የሚያፈሱ፤ቅቤ የሚቀቡ፤በጨሌ፤ ቆሌና የቤት ጣጣ አምልኮ ሰርጾባቸው የሚኖሩ ባልኖሩ ነበር።  እምነት አለን፤ አውቀናል የሚሉት እንኳን እስከፕሮቴስታንት መምጣት ድረስ መጽሐፍ ቅዱስን አያውቁትም። ደረትን ነፍቶ ኦርቶዶክሳዊ ስለመሆን አረጋጋጭ ከሆኑት ከድርሳናት ውጪ መጽሐፍ ቅዱስን ይዞ መገኘት በራሱ ኮትልኳል ወይም ጰንጥጧል የሚያሰኝ በመሆኑ ይዞ መገኘት ያሳፍር ነበር። ይህ በእድሜአችን ያየነው እውነት ነው። አንዳንዶች «ሳያዩ የሚያምኑ ብጹአን ናቸው» የሚለውን ቃል ጠምዝዘው ራሳቸው ለመሸንገያነት በመጠቀም አንድም ሐዋርያ ሳይመጣ ያመንን ስለሆንን ቃሉ እኛን ኢትዮጵያውያንን ያመለከታል ለማለት ቢፈልጉም የሐዋርያ ወይም የሰባኪ አለመምጣት እንደ ጉዳት እንጂ እንደጠቃሚ ነገር መቁጠር አለማወቃችንን የሚያሳይ ነው። መጽሐፍ የሚለን እውነት ይህንን ነው።
«እንግዲህ ያላመኑበትን እንዴት አድርገው ይጠሩታል? ባልሰሙትስ እንዴት ያምናሉ? ያለ ሰባኪስ እንዴት ይሰማሉ?» ሮሜ 10፤14
እንደዚሁ ሁሉ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን እውነተኛ ወንጌል በማስተማርና ሕዝቡን ከክርስቶስ ወንጌል ጋር በማስማማት እንዲኖር ለማድረግ እስከሞት ድረስ ከታገለው ከአባ እስጢፋኖስ በቀር ግብጻውያንም ጳጳሳት የሰሩት የወንጌል አገልግሎት አልነበረም። ወንጌል ሥራው በግጻዌ ምድቡ በጥቅስ ደረጃ በየሥርዓተ ቅዳሴው ላይ ተመርጦ ከሚነበብ ውጪ ከተአምረ ማርያምና ከድርሳናት እኩል መድረክ አልነበረውም። አቡነ ቴዎፍሎስ የወንጌልን አስፈላጊነት በማመን አዳሪ ት/ቤቶችን በማጠናከር፤ ሰንበት ት/ቤቶች በማቋቋምና በቃለ ዓዋዲ እንዲደነገግ እስኪያደርጉ ድረስ አብያተ ክርስቲያናት በግእዝ ቀድሰው፤ በግእዝ አንብበው፤ ለዓለመ ዓለም ካሉ በኋላ እግዚኦ መኀረነ ክርስቶስ እንበል 12 ጊዜ ብለው ጣት ከማስቆጠር ባለፈ ህዝቡ ወንጌልን እንደማያውቅ ጠንቅቀን እናውቃለን።
 እንዲያውም ወንጌል እቃ ግምጃ ቤት ገብቶ የሸረሪት፤ የአቧራና የአይጥ ቀለብ ሲሆን በአንጻሩ ልፋፈ ጽድቅ በየአንገት ላይ የሚንጠለጠል ክቡር መጽሐፍ ሆኖ ለዘመናት ኖሯል። ዛሬም እስከመቃብር ድረስ አብሮ የሚወርድ፤ ክቡር አዳኝ መጽሐፍ ሆኖ መቆጠሩን አላቋረጠም። የዲቁናም ይሁን የቅስና ማእርግ የሚሰጠው ሥርዓተ ቅዳሴውንና ኩሳኩሱን ከመልክዓ መልክዑ ጋር መሸምደዱ እንጂ ወንጌልን ተንትኖ ሕይወት የሚገኝበትን ቃል ማስተማር ስለሚችል አይደለም።  
ከዚህ በታች የምናቀርባቸው መጽሐፍ ቅዱሳችን በምንለው መጽሐፍ ውስጥ የሚገኙ ስህተቶች፤ ነገር ግን እውነት እንደሆኑ ቆጥረን የምንከራከርላቸው ሲሆኑ ችግሩን እንደችግር ያለመቁጠራችን ዋና ምክንያት ከላይ በሀተታ እንደዘረዘርነው አንድም እኛ ፍጽምትና ንጽሕት በሆነች ቤተክርስቲያን ውስጥ ያለን ስህተት አልባዎች ነን ከማለት የመነጨ ሰውኛ ማንነትን ካለመቀበል ችግር፤ አንድም- ክርስቶስ ከፊታቸው ተስሎ የነበሩት ገላትያውያን እንደሆኑት የሆነ አዚም አደንዝዞን እውነትን ለመቀበል ባለመፈለግ፤ አለያም ሳያዩ የሚያምኑ……በሚለው የሽንገላ ቃላት ተሸውደን እውነተኛውን የክርስቶስ ወንጌል የሚሰብክ እንዲኖረን ባለመፈለግ ራሳችንን ስናሞኝ በመኖራችን ይሆናል።

 የስህተት ትምህርት አስረጂዎች፤
ብዙውን ጊዜ «ከእውነተኛ የወንጌል አስተማሪዎች እጦት የተነሳ» /ከአስተማሪዎች እጦት የተነሳ አላልኩም/ ሕዝቡ እስካሁን ለወንጌል ቃል አዲስ በመሆኑ አሳማኝ መልስ መስጠት ስለማይችል እንደችግር መፍቻ መፍትሄ የሚጠቀምበት መንገድ በመሳደብ፤በማሳደድ፤በማሽሟጧጥ፤ በመደባደብ ብሎም በመግደል  ልዩ ለሆነ ሃሳብ ሁሉ ምላሽ ሲሰጥ ቆይቷል። አሁንም ይህ አድራጎት አላቋረጠም። ከዚህ በታች ለሚቀርቡ አስረጂዎች ምላሽ መስጠት የሚችል አንድም ሰው እንደሌለ እርግጠኞች ስንሆን የሚሳደብ ወይም የሚያንቋሽሽ ክርስቲያኖችን ግን በሺህዎች እንጠብቃለን። 
  • 1/ ስለታቦተ ጽዮን ትረካ፤
  • 1,1  ስለታቦተ ጽዮን አመጣጥ ታሪክ የሚናገረውን  «ክብረ ነገሥት» የተባለውን መጽሐፍ ማኅበረ ቅዱሳን ውሸታም ብሎታል።
ማኅበረ ቅዱሳን ትውፊትንና ባህልን፤ ልምድንና አምልኰትን ለይቶ የማያውቅ የጅምላ እምነት አራማጅ መሆኑ ሲታወቅ፤ ራሱ እገዛበታለሁ የሚለውን ትውፊት ሲሽር እንጂ ሌሎች ሲሽሩ ዓይኑ ደም የሚለብስ አስቸጋሪ ድርጅት ነው። እንደሚታወቀው ግራሃም ሐንኰክ የተባለ እንግሊዛዊ ምሁር /The sign of the seal/ በሚል ርእስ እ/ኤ/አ በ1992 ዓ/ም ያሳተመውን መጽሐፍ ይህ የትውፊት ጠበቃ ነኝ የሚለው የጅምላ እምነት አራማጅ ማኅበር፤ /ታቦተ ጽዮንን ፍለጋ/ በሚል ርእስ በጌታቸው ተስፋዬ አስተርጉሞ ያሳተመው መጽሐፍ  እንደሚተርከው ታቦተ ጽዮን በንጉሥ ሰሎሞን ዘመን በልጁ ኢትዮጵያዊ ንጉሥ በቀዳማዊ ምኒልክ እጅ ሳይሆን ወደኢትዮጵያ የመጣው በግብጽ ኤሌፋንታይን አቋርጦ ከዓመታት ቆይታ በኋላ የዓባይን ሸለቆ ተከትሎ ቀስ በቀስ በጣና አድርጎ ነው የገባው በማለት ይናገራል። ስለዚህ «ክብረ ነገሥት» ስለታቦተ ጽዮን አመጣጥ የሚተርከው የእነ ቀዳማዊ ምኒልክ ታሪክ በውሸታምነቱ ተመዝግቧል ማለት ነው። ማኅበረ ቅዱሳን የታቦተ ጽዮንን አመጣጥ በግራሃም ሃንኰክ አተራረክ መሰረት የሚያምን ከሆነ ክብረ ነገሥትን ትረካ ዋጋ ቢስ ያደርገዋል። የሚገርመው አንድም የሊቃውንት ጉባዔ ይሁን የጳጳሳቱ ዓለም የክብረ ነገሥትን ትረካ የሚቃወመውን የማኅበረ ቅዱሳን እትም መጽሐፍ ሲያወግዝ ወይም ታሪካችንን አፋልሷል ሲል አልተሰማም። ስለዚህ የክብረ ነገሥትን ውሸታምነት አጽድቆታል ወይም የማኅበረ ቅዱሳንን የትርጉም አተራረክ ለመከላከል አቅም አጥቷል። ከዚህ አንጻር ስለታቦተ ጽዮን አመጣጥ የሚናገር የተለያየ ሃሳብ በቤተክርስቲያኗ ውስጥ ስላለ እውነተኛው የትኛው እንደሆነ ለጊዜው አይታወቅም ማለት ነው። 

  • 1,2/ ታቦተ ጽዮን ወደኢትዮጵያ አልመጣችም በማለት መጽሐፈ እዝራ ካልዕ ይናገራል።
ከላይ እንዳስቀመጥነው ማኅበረ ቅዱሳን ክብረ ነገሥትን ውሸታም በማለት በግብጽ በረሃ አድርጋ ነው ታቦተ ጽዮን የመጣችው የሚለውን የግራሃም ሃንኰክን መጽሐፍ ለተከታዮቹ ሲያከፋፍል የምንረዳው ሁለት የተለያየ የአመጣጥ ትረካ መኖሩን ነበር። ይሁን እንጂ ሰማንያ አሀዱ በተባለው መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በመጽሐፈ እዝራ ካልዕ ምዕራፍ 1 ቁጥር 54 ላይ እንዲህ በማለት ከላይ የቀረቡትን ሃሳቦች ሁሉ ውድቅ በማድረግ ታቦተ ጽዮን ወደኢትዮጵያ እንደመጣች ሳይሆን ወደባቢሎን መሄዷን በግልጽ ይናገራል።
«እግዚአብሔርን የሚያገለግሉበትን ንዋየ ቅድሳቱንና ጥቃቅኑንና ታላላቁን ዕቃ ሁሉ የእግዚአብሔር ማደሪያ ታቦትንም፤ ከቤተመንግሥት ዕቃ ቤት ያለውን ሣጥኑንም ሁሉ ማርከው ወደ ባቢሎን ወሰዱ» እዝራ ካልዕ 1፤54
ናቡከደነጾር ከ634-562 ዓ/ዓ የነበረ የባቢሎን ንጉሥ ሲሆን እርስ በእርሳቸው ያልተስማሙት የክብረ ነገሥትና የታቦተ ጽዮንን ፍለጋ መጻሕፍት ትረካ ውድቅ በማድረግ ወደ ባቢሎን ማርኰ ስለመውሰዱ ሰማንያ ወአሀዱ የተባለው መጽሐፍ ቅዱስ አፖክሪፋ መናገሩ ነገሩን ሁሉ መያዣ መጨበጪያ የሌለው አድርጎታል። አሁን እንግዲህ ሊነሳ የተገባው ጥያቄ፤
  • ·         ክብረ ነገሥት የተባለው መጽሐፍ ነው ትክክል?
  • ·         ታቦተ ጽዮንን ፍለጋ የተባለው መጽሐፍ ትረካ ነው ትክክል? ወይስ
  • ·         የለም! ሁለቱም የሚሉት ትክክል አይደለም፤ ታቦቱ ወደባቢሎን በምርኰ ተወስዷል የሚለው የመጽሐፈ እዝራ ካልዕ ቃል ነው ትክክል?