Sunday, July 29, 2012

እነሆ በደጅ ቆሜ አንኳኳለሁ!


እግዚአብሔር ይወድሃል! በየትኛውም ሁኔታ ውስጥ እያለህ መግቦቱን ያልከለከለህ ስለሚወድህ ብቻ ነው። ሰዎች በኃጢአት ውስጥ ስንኳ እያለን ዝም የሚለን በሕይወት እንድንኖር ጊዜ የመስጠት ፍቅሩ ነው። ማንም እንዲጠፋ አይፈልግም።  ወይኑ የሚያፈራው መራራ መሆኑን እያወቀ እንኳን ወይኑን ቶሎ አይነቅለውም። ወይኑን ይንከባከባል። ጣፋጭ ፍሬ እንዲያፈራ ይጠብቀዋል። ነገር ግን ወይኑ በተደረገለትና በተሰጠው ነገር ሁሉ ፍሬያማ መሆን ካልቻለ «ለወይኔ ያላደረግሁለት፥ ከዚህ ሌላ አደርግለት ዘንድ የሚገባኝ ምንድር ነው? ወይንን ያፈራል ብዬ ስትማመን ስለ ምን ሆምጣጣ ፍሬ አፈራ?» ብሎ የወይኑ ባለቤት መራራውን ወይን ይነቅለዋል። የመራራው ወይን መጨረሻም እጣ ፈንታ መራራ ይሆናል።
   እናም ወንድሜ ሆይ! መግቦቱን፤ ፍቅሩንና ትእግስቱን እንድናውቅለት እግዚአብሔር ይፈልጋል። በፍቅርና በምሕረት እንጂ በኃይልና በማስገደድ የሚገዛን እንዳልሆነም እንድንረዳ ይሻል። «በሰው ገመድ በፍቅርም እስራት ሳብኋቸው፤ ለእነርሱም ቀምበርን ከጫንቃቸው ላይ እንደሚያነሣ ሆንሁ፥ ድርቆሽም ጣልሁላቸው» እንዳለው  የሚስበን በፍቅሩ እስራት፤ ከሸክምም ነጻ በማውጣት፤ መግቦቱን በፍቅር እንጂ በማስገደድ አይደለም። ሆሴዕ 11፤4
ወንድሜ ሆይ፤ በሰውነታችን የወይን ተክል፤ መንፈስ ቅዱስን ብናስመርረው ከበረሃ ላይ ወድቀው እንደቀሩት ዐመጸኞች፤ የዐመጻ ዋጋችንን መቀበላችን አይቀርም።  ዐመጽን እንድንጸየፍ፤ ጽድቅን እንድንወድቅ አማራጭ የለው ምርጫችን ነው። ዐመጽን ጠላሁ፤ ጽድቅንም ወደድሁ ብሎን የለ! ዐመጽን ልንጠላ፤ ጽድቅንም ልንወድ ይገባል።
ጥያቄው መቼ? የሚል ይሆናል። መልሱንም  በቃሉ ይናገራል።  «የመዳን ቀን አሁን ነው» ያለው ሐዋርያው ለመዳን ፈልገው፤ ጩኸታቸውን ለማሰማት ለተነሱ የመራራ ነፍስ ባለቤቶች ሁሉ ነው። «በተወደደ ሰዓት ሰማሁህ በመዳንም ቀን ረዳሁህ ይላልና፤ እነሆ፥ የተወደደው ሰዓት አሁን ነው፤ እነሆ፥ የመዳን ቀን አሁን ነው» 2ኛ ቆሮ 2፤6
ከዐመጻ ለመውጣት በእግዚአብሔር ዘንድ የተወደደው ሰዓት፤ ኃጢአትን ለመተው ውሳኔ ባሳለፍንበት ቅጽበት ነው። በዚያም በመዳን ቀን ረዳሁህ የሚል አስተማማኝ ኃይል ይሰጠናል። ሰዓቱም አሁንና አሁን ብቻ ነው።
ምናልባት ተዘጋጅተንበትና ጊዜ ሰጥተን ሁኔዎችን  ካመቻቸን በኋላ ቢሆንስ? የሚል አስተሳሰብ ሊኖር ይችላል። ይሁን እንጂ «ቀን የሚያመጣውን ምን እንደ ሆነ አታውቅምና ነገ በሚሆነው አትመካ» እንደተባለው ነገ የእኛ ቀን ስለመሆኑ ቀናቶቹን በእጃችን የያዝናቸው ስላይደለ በሌለን ነገር ላይ ተስፋ እናደርግ ዘንድ የተገባ አይደለም። የእኛ ቀንና የተሰጠን ተስፋ አሁን ያለንባት የሕይወት ጊዜ ብቻ ናት። እሷም ብትሆን «ሕይወታችሁ ምንድር ነው? ጥቂት ጊዜ ታይቶ ኋላ እንደሚጠፋ እንፋሎት ናችሁና» ያዕ 4፤14  ተብሎ ስለተጻፈ እንኳን ለነገው ቀን ከጥቂት ጊዜ በኋላ በሕይወታችን ላይ ለሚመጣው ነገር የምናውቀው ምንም የለም። እናም መራራው ወይናችን የሚነቀለው ቀን ከመድረሱ በፊት በየትኛውም ሁኔታ ውስጥ ሳለን ለመገበን አምላክ ጣፋጭ ለመሆን አሁኑኑ እንሠራ!!  «እናንተ ደግሞ እንደ ሕያዋን ድንጋዮች ሆናችሁ፥ በኢየሱስ ክርስቶስ ለእግዚአብሔር ደስ የሚያሰኝ መንፈሳዊ መሥዋዕትን ታቀርቡ ዘንድ ቅዱሳን ካህናት እንድትሆኑ መንፈሳዊ ቤት ለመሆን ተሠሩ»
ከኃጢአት በመውጣት መንፈሳዊ ቤት ለመሆን የምንሠራው በቁርጠኝነት እንጂ በጠባይ፤ በቀጠሮና በመለሳለስ አይደለም። ያልጀገነ ተዋጊ ጠላቱን ሊያሸንፍ እንደማይችል ሁሉ ጠላትም ድል ለማድረግና በኃጢአት ምርኰ ይዞ ለማቆየት አይለሳለስምና ኃጢአትን በመተውና በመዳን መካከል ድርድር የለም። ጠላታችን በጀግንነት ካልተዋጋነው በስተቀር ካለማመደን ኃጢአት ውስጥ በነጻና በፍላጎት አያሰናብተንም። ጠላት ምን ጊዜም ጠላት ነው። እናም ውጊያችን መራራና ጠንካራ መሆኑን አውቀን መግጠም ይገባናል። በእኛና በጠላታችን መካከል ያለው ልዩነት ጠላታችን ውሱን ማንነት ያለው፤ ከኃይል በቀር ሥልጣኑን  የተቀማ ሲሆን በእኛ ዘንድ ያለው ሰይፍ ግን ሁሉን በእጁ የያዘ የፈጣሪ ኃይል፤ የሁሉ ገዢና አስገኚ፤ የዘላለማዊ ሥልጣን ባለቤት በመሆኑ የውጊያው አሸናፊነታችን በምክንያትና በሁኔታ ላይ ያልተወሰነ፤ እርግጠኛና አስተማማኝ ነው። ግን ይህንን ኃይል እንዴት መታጠቅ እንደምንችል፤ መቼ መታጠቅ እንዲገባንና እንዴት መጠቀም እንዳለብን ብዙዎቻችን እውቀቱ የለንም። ይህ አስተማማኝ አሸናፊነት እያለው የሰው ልጅ ሁሉ በኃጢአት የሚሸነፈው ታዲያ ለምንድነው?
እንደ ጳውሎስ ቁርጠኛና አሁኑኑ ወደውጊያው ለመግባት የሚወስን ጀግና መሆን ባለመቻሉ የሰው ልጅ ለሚሸነፍለት ኃጢአት ተሸንፎ ይኖራል። ጳውሎስ ለእግዚአብሔር ቀንቶ ክርስቲያኖችን ለማሳደድና ወኅኒ ለመወርወር እንኳን ቅንጣት አላመነታም።  ከኢየሩሳሌም ተነስቶ 217 ኪሎ ሜትር በእግሩ ወደ ደማስቆ ለመጓዝ ቅሌን ጨርቄን አላለም።  የጳውሎስ ጉዞ የክርስቶስን ቤት ለማፍረስ ቢሆንም እንደቁርጠኛ ውሳኔውን ግን ለእግዚአብሔር ከታሰረለት ፍቅር የተነሳ ነበር። ለእግዚአብሔር ፍቅር ጠላትን የሚዋጋ ጊዜ መፍጀት እንደሌለበት  ያመላከተ ሆኗል። ጳውሎስ በመንገዱ ላይ ያጋጠመው ብርቱ ኃይል ከእርሱ የሚበልጥ በመሆኑም  «አንተ ማነህ?» ማለቱም የጀግንነቱ ልክ መገለጫ ነበር። እግዚአብሔርም ራሳቸውን ለእርሱ የሰጡትን እንደዚህ ዓይነቶቹን ሰዎች ይወዳል። ጀግናን ማን ይጠላል?

Saturday, July 28, 2012

የሃይማኖታችን ሊቀ ካህናት


የጽሁፉ ባለቤት ገ/እግዚአብሔር ኪደ ይባላል። በአፍቃሬ ማኅበረ ቅዱሳን ብሎጎች ላይ ጽሁፉን በማቅረብ ይታወቃል። በፌስ ቡክ ገጹ ከሰጠን መረጃ ተነስተን ብሎጉ ላይ ካሰፈራቸው ጽሁፎች ውስጥ ይህንን ጽሁፉን መርጠነዋል። ጽሁፉ መጽሐፍ ቅዱሳዊ መሠረት ያለው፤ በቀደምት አበው አስተምህሮ ላይ የቆመ፤ በዘመናችን ውስጥ የሚታዩትን ብዙ የመዳኛ መንገዶች ውድቅ ያደረገ፤ የኢየሱስ ሊቀ ካህንነት በሌሎች ድካም በሚያሸንፋቸው ያልተተካ መሆኑን፤ ማዳኑ ፍጹምና ወደእሱ ለሚመጡት ሁሉ እስከ ዓለም ፍጻሜ እንደሚሰራ፤ በመሃላ የተሾመው ሊቀ ካህን «እኔ የበጎች በር (ደጅ) ነኝ» ይላልና ወደዚህ በር እንግባ እያለ ይነግረናል። ከዚህ እውነተኛው በር ውጪ ሌላ በር የለም።  ወደዚህ በር መሿለኪያ ወይም ውስጥ ለውስጥ መንገድ የለም። በመሃላ የተሾመ ሌላ ሊቀ ካህን የለም። «አንኳኩ ይከፈትላችኋል» ወዳለው የሕይወት ቃል እንድንቀርብ የሚናገረውን ይህንን ጽሁፍ መርጠነዋልና ካካፈለን ነገር እኛም አካፍለናችኋል።

    በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!

 በክፍል ሁለት ትምህርታችን ሊቀ ካህናችን ኢየሱስ ክርስቶስ እንደ እግዚአብሔር ሥርዓት ከሰዎች ተመርጠው ከሚሾሙት የብሉይ ኪዳን ሊቀ ካህናት ፍጹም የሚለይባቸውን ነጥቦች ማሳየት ጀምረን ነበር፡፡ የሚምር ነው፤ የታመነ ነው፤ በሰማያት ያለፈ ነው፤ በድካማችን የሚራራልን ነው ብለን አራት ነጥቦችን አይተናል፡፡ ለዛሬም እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ ካቆምንበት እንቀጥላለን፡፡ ቢችሉ አስቀድመው ይጸልዩ!

1. በመሐላ የተሾመ ሊቀ ካህናት ነው፡፡ 

 መሐላ የማይለወጥ ነገርን ያመለክታል፡፡ አንድ ሰው ይህን አላደርግም እንዲህም አላደርግም ብሎ ከማለ የነገሩን ሓቅነት ያመለክታል፡፡ሰዎች ከእነርሱ በሚበልጠው (ሎሌ በጌታው፣ ገረድ በእመቤቷ፣ ደቀ መዝሙር በመምህሩ፣ ልጅ በአባቱ) ይምላሉና ለማስረዳትም የሆነው መሓላ የሙግት (የክርክር የጸብ) ሁሉ ፍጻሜ ይሆናል፤ ስለዚህም እግዚአብሔር የተስፋውን ቃል ለሚወርሱ ፈቃዱ እንደማይለወጥ አብልጦ (አብዝቶ) ሊያሳያቸው ስለ ፈቀደ እግዚአብሔር ሊዋሽ (ሊፈርስ፣ ሊታበል) በማይቻል በሁለት  በማይለወጥ ነገር በፊታችን ያለውን ተስፋ ለመያዝ ለሸሸን ለእኛ ብርቱ መጽናናት ይሆንልን ዘንድ በመሐላ (በሥጋዌው) በመካከል ገባ፤ ይህም ተስፋ እንደ ነፍስ መልሕቅ አለን (ተስፋችንን አጽንተን ለያዝን ለእኛ ልቡናችን እንዳይነዋወጥ እንደ ወደብ የሚያጸናን ፍጹም ደስታ አለን) እርሱም እርግጥና ጽኑ የሆነ ወደ መጋረጃውም ውስጥ የገባ (እንደ መልከ ጼዴቅ ባለ ሹመት ተሹሞ ወደ ውሳጤ መንጦላዕት የገባ የዘላለም አስታራቅያችን ፊተውራርያችን ኢየሱስ ክርስቶስ) ነውእንዲል /ዕብ.616-19/፡፡ እንግዲያውስ ከሌዋውያን ክህነት በሚበልጥ ክህነት፣ እንደ መልከ ጼዴቅ ክህነት ዘላለማዊ በሆነ ክህነት የተሾመ ሊቀ ካህናት አለን፡፡ የዘመነ ብሉይ ሊቃነ ካህናት ምንም እንኳን በእግዚአብሔር ጥሪ የተመረጡ ቢሆኑም አገልግሎታቸው ጊዜአዊ ስለ ነበረ ያለ መሓላ የተሾሙ ነበሩና፡፡ ኢየሱስ ክርስቶስ ግን ከኦሪት ለምትበልጥ ለወንጌል መምህር ለመንግሥተ ሰማይም አስታራቂ ሆኖአልና በመሓላ የተሾመ ዘላለማዊ ሊቀ ካህናት ነው፡፡ ሐዋርያውም ስለዚሁ ሲናገር እንዲህ አለ፡- “እነርሱም ያለ መሓላ ካህናት ሆነዋልና፤ እርሱ ግን፡- ጌታ፡- አንተ እንደ መልከጼዴቅ ሹመት ለዘላለም ካህን ነህ ብሎ ማለ አይጸጸትም ብሎ በተናገረለት ከመሓላ ጋር ካህን ሆኖአልና ያለ መሓላ ካህን እንዳልሆነ መጠን እንዲሁ ኢየሱስ ለሚሻል ኪዳን ዋስ ሆኖአል” /ዕብ.720-22/፡፡ በዚህም ኦሪት ሥርየተ ኃጢአትን ማሰጠት ስላልቻለች እንደተሻረች ወንጌል ግን ማዳን ስለቻለች፣ ሥርየተ ኃጢአትን ማሰጠት ስለቻለች ሕልፈት ሽረት እንደሌለባት አወቅን፤ ተረዳን፡፡ ካህኑም አገልግሎቱም እንደዚሁ፡፡ ለምን ቢሉ ያለ መሓላ ከተሾሙት የብሉይ ኪዳን ሊቃነ ካህናት ይልቅ በመሓላ የተሾመ ሊቀ ካህናት ወልደ አብ ወልደ ማርያም ኢየሱስ ይበልጣልና፡፡  

Thursday, July 26, 2012

የግንቦቱ ሲኖዶስ ካወገዛቸው ግለሰቦች መካከል ሦስቱ ውግዘቱን በመቃወም ጠቅላይ ቤተክህነቱን ይግባኝ ጠየቁ

ክፍል 2

የዲያቆን አግዛቸው ተፈራ አቤቱታ
ምንጭ፤ አባ ሰላማ ድረ ገጽ

ህልውናውንና የሚመራውን መንፈስ ቅዱስን ወደጎን ትቶ ለማኅበረ ቅዱሳን በማደር በህሊና፣ በታሪክና በእግዚአብሔር ፊት አሳፋሪ ስህተት የፈጸመው የግንቦቱ ሲኖዶስ ስብሰባ እፎይ ብዬ ተቀመጥኩ ለማለት ቢሞክርም፣ እፎይ የማያሰኙ አቤቱታዎች እየቀረቡበት መሆኑን ከዚህ ቀደም ገልጸናል፡፡ እስካሁን ድረስ ባለን መረጃ ዲያቆን አሸናፊ፣ ዲያቆን አግዛቸው እና መምህር ጽጌ አቤት ያሉ ሲሆን፣ አቤቱታቸውን ሰምቶ ችግራችሁ ምንድን ነው ብሎ ሊያነጋግራቸው የቻለ አካል ይኑር አይኑር እስካሁን የታወቀ ነገር የለም፡፡ ባለፈው ጊዜ የዲ/ አሸናፊን አቤቱታ አቅርበንላችሁ ነበር፡፡ አሁን ደግሞ የዲ/ አግዛቸውን አቤቱታ እናቀርባለን፡፡ ሙሉውን የዲያቆን አግዛቸውን ደብዳቤ ከዚህ ጽሑፍ በታች ያገኙታል . . .
/ አግዛቸው ተፈራ እስካሁን ድረስ 4 መጻህፍትን የጻፈ ሲሆን፣ እነርሱም፦ የተቀበረ መክሊት፣ ጥላና አካል፣ የለውጥ ያለህ!!! አልተሳሳትንምን? የተሰኙ ናቸው፡፡ የተቀበረ መክሊት የተሰኘው የመጀመሪያው መጽሐፍ ብዙዎችን ያነቃ ወደ እግዚአብሔር እውነት እንዲደርሱ የረዳ እና የተቀበረውን መክሊት ፍለጋ ተግተው እንዲቆፍሩ ያነሳሳ መጽሐፍ ነው፡፡ የተቀበረውን እውነት እውነቱን የሸፈነውን ሐሰትና ለስሕተት መግቢያ ከሆኑት በሮች ዋናውን የአተረጓጎም ችግር የሚያሳየው ይህ መጽሐፍ፣ አሁንም ድረስ በርካታ የአብነት ትምህርት መምህራንና ተማሪዎች፣ የመንፈሳዊ ኮሌጅ ተማሪዎችና ምዕመናን እንደ ጥሩ ምንጭ ኮለል ያለውን እውነት የሚቀዱበት መጽሐፍ ሆኖ እያገለገለ ይገኛል፡፡
ጥላና አካል የተሰኘው ሁለተኛው መጽሐፍም ብሉይ ኪዳንንና ሐዲስ ኪዳንን በማነጻጸር በኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን እያታየ ያለውን ከፊል ኦሪታዊ ሥርአትን የሚገመግም፣ ብሉይ ኪዳን የአዲሱ ኪዳን ጥላና ምሳሌ እንደሆነና አማናዊውና አካሉ አዲስ ኪዳንም ለዚህ ዘመን ዋና ነገር መሆኑን የሚያብራራ መጽሐፍ ነው፡፡ ከብሉይ ኪዳን ዋና ዋና የሆኑ ነገሮችን ነቅሶ በማውጣት በሐዲስ ኪዳን ያላቸውን ትርጉም የሚያብራራ ሲሆን፣ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን የሚታዩ አንዳንድ የብሉይ ኪዳንን ስም የያዙ ንዋያተ ቅድሳትና ልምምዶች መጽሐፍ ቅዱሳዊ አለመሆናቸውን ያሳያል፡፡ በአሁኑ ሰዓት መጽሐፉ በገበያ ላይ የሌለ ሲሆን ብዙዎች እየፈለጉት እንደሚገኝ ለማወቅ ተችሏል፡፡
ዲያቆኑ ከጻፋቸው መጻሕፍት ሁሉ በገጽ ብዛት ከፍተኛውን ደረጃ የያዘው የለውጥ ያለህ!!! የተባለው መጽሀፉ አሁንም በገበያ ላይ የሚገኝ ሲሆን፣ እንደእነዚህ ላሉት መጻሕፍት የማስታወቂያ ሰራተኛ ሆኖ እያገለገለ ያለው ማኅበረ ቅዱሳን፣ ባለፈው አመት የግንዛቤ ማስጨበጫ በሚል በከፈተው ዘመቻ መጽሐፉን በቪዲዮ እያሳየ እንዳታነቡ የሚል መልዕክት ካስተላለፈ ወዲህ በከፍተኛ ደረጃ እየተሸጠ እንደሚገኝ ለማወቅ ተችሏል፡፡
አያ ዘባርቄ ምሕረተ አብ እውነትን በማዛባት በታቦት ላይ «አልተሳሳትንም» በሚል ርእስ የሰጠው ትምህርት «አልተሳሳትንምንየሚል መጽሐፍን ወልዷል፡፡ መጽሐፉ / አግዛቸው ስለ ታቦት ምሕረተ አብ በደመ ነፍስ ለገበያ በሚስማማ መልኩ እንደቸረቸረው ሳይሆን መጽሐፍ ቅዱስ የሚለውንና በታሪክ የተመዘገበውን እውነት ያብራራበትና የምህረተ አብን ውትፍትፍስብከትምበድንቅ ብዕር የተቸበት መጽሐፍ ነው፡፡ በምሕረተ አብ ደንባራ በቅሎ ተጭነው ሲጓዙ የነበሩና የሌሎች ምዕመናንን ጥያቄ የመለሰ መጽሐፍ መሆኑን ያነበቡ ሁሉ የሚመሰክሩት እውነት ነው፡፡ ጥላና አካል እና አልተሳሳትንምን? የተሰኙት መጻሕፍት ከገበያ ፈጽሞ የጠፉ ሲሆን ፈላጊያቸው ብዙ ሰው ሆኖ ሳለ ደራሲው ለምን መልሶ እንደማያሳትማቸው ጥያቄ ሆኖብናልና በማሳተሙ ላይ ቢያስብብበት ጠቃሚ ነው እንላለን፡፡
እነዚህን መጻሕፍት የጻፈውና ተጠርቶ ሳይጠየቅ የተወገዘው / አግዛቸው የተላለፈበትን ውግዘት በመቃወም ለጠቅላይ ቤተ ክህነት አቤት ያለ ሲሆን፣ የጻፈው ደብዳቤ በዮሐንስ ወንጌል ላይ ያለውን «ህጋችን አስቀድሞ ከእርሱ ሳይሰማ ምንስ እንዳደረገ ሳያውቅ በሰው ይፈርዳልን?” (ዮሐ. 751)» የሚለውን ጥቅስ በማስቀደም ይጀምራል፡፡ በመቀጠልም በቤተክርስቲያን ያሳለፈውን ጊዜ በአጭሩ ያስቀኛል፡፡ ይህም ማኅበረ ቅዱሳን እስካሁን ድረስ ስለእርሱ ጭሮ ጭሮ ሊያገኝ ያልቻለውንና እያዛባ ያቀረበውን አስተካክሎ ያቀረበ ነው፡፡

ማህበረ ቅዱሳን እና የወደፊት እቅዱ!

ሐምሌ 19 2004 .. ዐውደ ምሕረት/www.awdemihret.blogspot.com) (ይህን ጽሁፍ ያገኘነው ፌስቡክ ላይ ነው። ጸሀፊው ራሱንማህበሩ ውስጥ ሆነን የማህበሩን አደጋ ገልጠን የጠቆምን የቁርጥ ቀን የቤተክርስቲያን ልጆችሲል ይገልጻል። ጸሃፊው አለኝ በሚላቸው መረጃዎች መሰረት ጽሁፉን አዘጋጅቷል። የማኅበሩን የኑፋቄ ትምህርት ጨምሮ ጊዜ የምጠብቅላቸው ሌሎች መረጃዎች አሉኝ የሚለው ጸሐፊ እንደ ውስጥ አዋቂ የማኅበሩ እቅዶች እነዚህ ናቸው ሲል ይነግረናል። እንደ ጸሐፊው እምነት ማኅበሩ ከቤተክርስቲያን ተገንጥሎ እስከ መውጣት የጨከነራዕይያለው ነው። ለዚህም የሚረዳውን ጥናት የጨረሰ ሲሆን ተጨማሪ ጥናቶችን ለማድረግ ግብጽ ድረስ ሰው ልኳል ይለናል። በብሎጋችን እንዲወጡላችሁ የምትፈልጉዋቸው ጽሁፎች ካሉዋችሁ awdemihret@live.com ብላችሁ ብትልኩልን ይደርሰናል።  መልካም ንባብ)

ማህበረ ቅዱሳን ሁለት አይነት እቅድ አለው። አንደኛው ቤተክርስቲያኒቱን መቆጣጠር ሲሆን አሱ ካልተሳካ ደግሞ ሁለተኛውን ማለትም ሂደቶችን አይቶ በቂ የሚለውን አቅም ከገነባ በኃላ ወደፊት ተገንጥሎ የመውጣት ድብቅ ራዕይ አለው፡፡ ሁለተኛው አላማውም በቤተክርስቲያን ላይ አደጋ ለመፍጠርና አባላቱን ይዞ የራሱን ቤተ እምነት መመስረት ሲሆን ጉዞውን 40 በመቶ አድርሷል፡፡ ይህን እቅዱን ለማሳካት የተጠና እስትራቴጂ አዘጋጅቶ ተግባር ላይ አውሏል፡፡

 ከእቅዶቹ ዋና ዋናዎቹ እንደሚከተሉት ይቀርባሉ
1- ወደፊት ማህበሩ ቤተክርሰቲያኒቱን ከተቆጣጣረ ወይም ደግሞ ከተገነጠለ የራሱ አገልጋዮችን ብቻ መጠቀም ስለሚፈልግ ለሚገነጥለው ቤተ እምነት አገልጋይ እንዲሆኑ ካህናትንና መነኮሳትን በገዳማትና በአብነት /ቤቶች በጥንቃቄ ማሰልጠን እንዲቻል ከፍተኛ በጀት መድቧል፡፡ ይህን ስውር ተልእኮ ሊቃነ ጳጳሳቱ ነቅተው እንዳያስቆሙት በዘዴና በጥንቃቄ መያዝ
2- ጵጵስና ለቀሳውስት እንዲሰጥ በቅ/ሲኖዶስ ግፊት እንዲያደርጉ የማህበሩ አባላት የሆኑ ጥቂት ጳጳሳትን ማሳመን በዚህ ጉዳይ ጥናት እንዲሰሩ ስንታየሁ የተባሉ አንድ ቄስ ግብጽ ሃገር ተልከዋል፡፡
3- በቅዱስ ሲኖዶስ ውስጥ የማህበሩን አላማ በስውር የሚያስፈጽሙ ጳጳሳት እንዲሾሙ ማህበሩ መነኮሳትን መልምሎ በምርጫው ግዜ አባቶች ድምጽ እንዲሰጣቸው በየቤታቸው እየዞሩ የማግባባት ስራ መስራት፡፡ ማግባባቱ ለሃገረስብከታቸው እስከ ሁለት መቶ ብር በጀት ድጎማ ማድረግን፣ በግል እጅ መንሻ ማዘጋጀትን በአንዳንድ በልማት እቅዶቻቸው ውስጥ የማማከር ድጋፍ ማድረግን ይጨምራል፡፡ ለቤተክርስቲያን ቢጠቅሙም ለማህበሩ አካሄድ ግን አደገኛ ናቸው ያሏቸው አባቶች እንዳይሾሙ አባላት በሆኑ ጥቂት አባቶች በኩል መታገልና በቅዱስ ሲኖዶስ ስብሰባ ወቅት በእያንዳንዱ ሊቃነ ጳጳሳት ማረፊያ ተሰሚ የሆኑ አባላትንና አንዳንድ ባለጸጎችን በመላክ የማሳመን ስራን መስራት፡፡ እንቢ ያሉትን ማስፈራራት
4- የማህበሩን አካሄድ ትክክል አይደለም መታየት አለበት የሚሉ ጳጳሳትን ሰባኪያንን የአስተዳደር ሰዎችንና የመንግስት አካላትን ህዝቡ እንዲጠላቸው መናፍቃን ሆነዋል ተወግዘዋል ሌላ ተልእኮ አላቸው ወዘተ የመሳሰሉትን ቀለሞች በመቀባት ሃይላቸውን ለማድክም መሞከር፡፡ ይህን በአሜሪካና በአውሮጳ በገንዘብ የሚደግፍ ኮሚቴ በነያሬድ /መድህን በነዳንኤል ክብረት በነህብረት የሺጥላ በነፋንቱ ወልዴ በነዶ/ መስፍን የተቋቋመ ሲሆን ኮሚቴው የማህሩን የጥፋት አላማ የሚያደናቅፉትን ሁሉ አስፈላጊው እርምጃ እንዲወሰድባቸው በፋይናንስ መደጎም ሲሆን በስውር ሲዲ እያዘጋጁ መበተን፣ ስብሰባ እያዘጋጁ ባለጠጎችን ቤተክርስቲያን ልትፈርስ ስለሆነ እንድረስላት ገንዘባችሁን ስጡን በማለት የማህበሩን አቅም ማደራጀት፣
5- ለጥምቀት ምንጣፍ የሚያነጥፉ የዋህ ወጣቶችን ቀስ ብሎ ወደ ማህበሩ በማስገባት ቤተክርስቲያን አደጋ ላይ ነች ድረሱላት በማለት የአመጽ ትምህርታቸውን አስተምሮ ወደ ነውጥ እንቅስቃሴ እንዲገቡ በማድረግ ተጨማሪ ሃይል እንዲሆኑ ማሰልጠን፣
6- በአዲስ አበባ እና በመላው ኢትዮጵያ በሚገኙ የሰንበት /ቤቶች ሰርጎ መግባትና የማህበሩን መሰረት ማስፋት ካልተቻለ በየአጥቢአው ቢሮ በመክፈት ሰንበት ትምህርት ቤቶችን መበጥበጥ እና ማፈራረስ
7- በመንግስት ፖለቲካ ውስጥ የሚደረገውን ጣልቃ ገብነት በተጠና ሁኔታ ማጠናከር ይህም በሃገር ውስጥ ያሉ አባላት መንግስት እንዳይመታቸው የቤተክርስቲያኑን ጉዳይ ትኩረት አድርገው እንዲሰሩ በውጭ ያሉት ግን የተለያዩ ሚዲያዎችን እየተጠቀሙ መንግስትን እንዲቃወሙ ተደርጎ እስትራቴጂው ተቀርጿል፡፡ ደጀ ሰላም፣ አንድ አድርገን፣ደቂቀ ናቡቴ፣ savewaldeba, ecadforum … የተባሉትን ድረ ገጾች በመጠቀም ጸረ ሰላም ቅስቀሳዎችን ማጠናከር ፡፡
8- ማህበረ ቅዱሳንን ራሱን ችሎ እንዲወጣ የገንዘብ አቅሙን ቋሚ በሆነ ሁኔታ ማጠናከር ይህም የማህበሩን ህንጻ መገንባት፣የቤተክርስቲያን ልጆች በተለይ መንግስት ሰራተኞች ለቤተክርስቲያናቸው ሳይሆን ለማህበሩ አስራት አንዲከፍሉ ማድረግ፣ በተለያዩ ቦታዎች የንግድ ተቋማትን መመስረት፣ አንድ ባንክ በአባላቱ አክስዮን (እንቅስቃሴው ተጀምሯል።) መክፈት ወዘተ
9- በቤተክርስቲያን መድረኮችና በግል ሚዲያዎች ላይ የህዝብን ሰላም የሚያውክ የጽንፈኝነት ቅስቀሳ ማጠናከር፡፡ ይህን እንዲመሩ የተወሰኑ መምህራንን መድቦ ጽንፈኝነትን በሃይማኖት ቤተሰቦች ላይ ሽብርን እና ቅራኔን በሃማኖቶች መካከል የማስፋት ስራን አጠናክሮ መቀጠል፣ እንዲሁም በአንዳንድ የአዲስ አበባ፣ ድሬዳዋ፣ አዳማ፣ ባህር ዳር፣ መቀሌ፣ ጎንደር፣ አርባ ምንጭ፣ደሴ፣ በአውሮፓ አሜሪካ የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ ባሉ ትላልቅ አብያተክርስቲያናት ያሉ መምህራንን በጥቅም በመደለል በቤተክርስቲያን መድረክ ማህበሩን ማስተዋወቅ ችግር ተፈጥሯል፣ ቤተክርስቲያን መሪ የላትም ሲኖዶሱ የሞተ ነው መንግስት ቤተክርስቲያንን እየገደለ ነው እያሉ ሁከት በመፍጠር ህዝቡ እንዲታወክ ቤተክቲያንን እንዲሰለችና እረኞቹን ከበጎቹ ነጥለው ወደ አዲሱ ቤተእምነታቸው እንዲቀላቀሉ መሳብ

10- ቤተክርስቲያን በራሷ እንዳትተማመን በስነ ልቦና ጦርነት ማሽመድመድ ይህም ጠንከረው የሚሰሩ ሰባኪዎቿንና ሰራተኞቿን በሃይማኖት ስም ከስሶ በማዳከም ፈሪ እንድትሆን ማድረግ ዝም ማሰኘት፡፡ ልጆቿን በየአሉበት ፈልጋ እንዳታስተምር ባገኘችው አጋጣሚ ሁሉ ሰብካ ወደ በረቷ መስብሰብ እንዳትችልማከላከል የንስሃ አባቶች እንኳ ልጆቻቸውን በየቤታው ሄደው እንዳያስተምሩ፣ በቤተክርስቲያን ግቢ የሚደረጉ ጉባኤዎችን የመናፍቃን እጅ አሉባቸውና ምእመናን እንዳይሄዱ ቅስቀሳ ማድረግ፣ማህበረ ቅዱሳን ከጠራው ጉባኤ ውጭ ሌሎቹ የተሳሳቱ አድርጎ ማቅረብ፣ መዝሙር እንዳይዘመር፣ ሰባኪዎችን ሁሉ ሰው እንዲፈራቸው፣ ከፍተኛ ቅስቀሳ በማድረግ ቤተክርስቲያን ዝም እንድትል እና ሌሎች እንዲቀድሟት ለማድረግ አባቶችንም ስርአት ተጣሰ ህግ ፈረሰ ብለው በማደናገር ለክፉ ተልኮአቸው ተባባሪ እንዲሆኑ ማድረግ።

Tuesday, July 24, 2012

አቢሲኒያ የሚለውን ስም ከእኛ ይልቅ ነጮቹ ይጠቀሙበታል!


የዛሬዋ ኢትዮጵያ በአንድ ወቅት ታላቅ ሀገር እንደነበረች ታሪክ ይናገራል።  በግዛት ስፋት፤ በጦር ኃይል ብዛት፤ በሥነ ሕንጻና በሥነ ጽሁፍ ገናና ሆና መቆየቷን የሚናገሩ ብዙ የታሪክ ድርሳናት አሉ። በእርግጥ ብዙዎቹም ድርሳናት የተጻፉትና በሰነድነትም የሚገኙት በውጪው ዓለም ነው። አቢሲኒያ የሚለው ስም የትመጣነት ለታሪክ ሀተታ ይቆየንና ኢትዮጵያ የሚለው / ጥቁር መልክ/ ስያሜ ከመሰጠቱ በፊት አቢሲኒያ የምትባለው ሀገራችንን ታሪክ አብዛኛው የምናውቀው « የኢትዮጵያ የቀድሞ ስም» የሚለውን ጥሪ ብቻ ነው። ግፋ ቢልም «አቢሲኒያ ባንክን» !!!
ታሪካዊነቱን የሚገልጽ መታሰቢያ ዩኒቨርሲቲ፤ የጎዳና ስም፤ ሆስፒታል ወይም ሌላ ተመሳሳይ መጠሪያ እስከምናውቀው ድረስ የለንም። ምናልባት ያልሰማነው ካለ ይታረማል። ታሪክና ቅርስ ለአንድ ሀገር ሕዝብ ማኅበራዊና መንፈሳዊ ማንነት ወሳኝ ነው።  በዘመናት ያለፈባቸውን የጥንካሬና የድክመት ጉዞዎቹን ይቃኝበታል። መጻዒውንም ያማትርበታል።
እስራኤሎች ታሪካቸውን እየጻፉ ለመጪው ትውልድ የሚያኖሩላቸው ጸሐፊያን በየዘመኑ ነበራቸው። በሕይወታቸው ያለፈውን፤ ያደረጉትንና የተደረገላቸውን እየከተቡ ያኖሩ ነበር።
1ኛ ነገ 43
«ጸሐፊዎቹም የሴባ ልጆች ኤልያፍና አኪያ፥ ታሪክ ጸሐፊም የአሒሉድ ልጅ ኢዮሣፍጥ»
የእያንዳንዱ ነጋሲ ታሪክና ሥራ እየተጻፈም ይቀመጥ ነበር። ይህም ለልጅ ልጆች የሚቀመጥ ውርስ ነበርና ነው።
1ኛ ነገ 1532
በእስራኤል ነገሥታት ታሪክ መጽሐፍ የተጻፈ አይደለምን?
እኛ ለዚህ አልታደልንም።

 እንኳን እንደዚህ ዓይነት ታሪክ ጽፈን ለማቆየት ይቅርና በዘልማድ  ስለምናውቀው «አቢሲኒያ» ስለሚለው የሀገራችን ስም መታሰቢያ የሚሆን ነገር የለንም። ይሁን እንጂ ፈረንጆቹ በመጽሐፍ ቅዱስ «ኩሽ» በታሪክ አቢሲኒያ፤ በመጠሪያ ደግሞ ዛሬ ኢትዮጵያ ስለምትባለው ሀገራችን የእምነት፤ የጀግንነት፤የታሪክ፤ የቅርስና የመልክዓ ምድር ወዘተ ሰፊ ጥናት አድርገዋል። መጻሕፍትንም ጽፈዋል።
ፈረንሳዊው የታሪክ ጸሐፊ  ጂን ክሪስቶፍ ሩፊን/Jean-Christophe Rufin/ ዘ አቢሲኒያን፤ ሳሙኤል ጆንሰን፤ ጀምስ ብሩስ፤ሪቻርድ በርተን፤ ኢቭሊን  ዎግ፣ ዴርቭላ መርፊ፤ ሲልቪያ ፓንክረስት፤ ኸርበት ቪቪያን፤  ሮማን ፕሮቼስካ ፤ ጆንስ እና ኤልሳቤጥ/ መጽሐፉን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ /  ወዘተ እና ሌሎች ብዙዎች ጸሐፊያን ስለአቢሲኒያ ጽፈዋል።

 ይህንኑ ገናናውን የአቢሲኒያን ታሪክ ተከትሎና ከጥቁር ምድር ቀዳሚ የክርስትና ሀገር ኢትዮጵያ በመሆኗም ጭምር አሜሪካውን ጥቁሮች ቤተክርስቲያኖቻቸውን ጭምር በምድረ አሜሪካ ውስጥ በአቢሲኒያ ስያሜ ይጠሩ ነበር።  ኮሎራዶ በ516ኛው ክሬስትሞር ጎዳና ላይ የሚገኘው የአቢሲኒያውያን ክርስቲያኖች ቤተክርስቲያን፤  ኒውዮርክ በምእራብ 138ኛው ጎዳና ላይ በ1808 የታነጸው የአቢሲኒያውያን መጥምቅ ቤተክርስቲያን፤ 1828 ዓ/ም በ75 ኒው በሪ ጎዳና የተመሰረተው የፖርት ላንድ አቢሲኒያውያን ቤተክርስቲያን፤ እዚው ፖርት ላንድ የሚገኘው የአቢሲኒያውያን የመሰብሰቢያ አዳራሽ፤  ከብዙ በጥቂቱ የሚጠቀሱ በኢትዮጵያ የቀድሞ ስም በአቢሲኒያ ስም የተጠሩ የአሜሪካ ጥቁሮች የታሪክና እምነት ስያሜ መጠሪያዎች ነበሩ። ዛሬም በዚሁ ስም እየተጠሩበት ይገኛሉ። ብዙዎቹም እናት ምድራችን በሚሏት አቢሲኒያ /ኢትዮጵያ/ ተገኝተው ታሪኳን ቅርሷን፤ ክብሯን ሁሉ በአካል ለማየት ችለዋል። ያ ሁሉ ዝናና ታሪክ ተንኮታኩቶ የድሆች መናኸሪያ፤ የስደተኞች መፍለቂያ መሆኗን ሲያዩ ምን ብለው ይሆን?
አብያተ ክርስቲያኖቻቸውን በአቢሲኒያ ስም ከመጥራት ባሻገር አቢሲኒያን በተለያየ ዘመናት የረገጡ ነጮች ከምድረ አቢሲኒያ ድመት፤ ውሻ፤ ፈረስ፤ ድብ፤ አሳማ፣ እጽዋት በመውሰድ በሀገራቸው አራብተዋል፤ አዳቅለዋል።  
ዛሬ በአሜሪካ የአቢሲኒያ ድመት፤ ውሻ፤ ፈረስ ወዘተ በስም ተለይቶና ተመርጦ የሚገዛበት ትልቅ  ስም ነው። እንዲያውም ተፈላጊ መለያ ነው።
የአበሻ ውሾች ቁጡዎችና ኃይለኞች፤ ድመቶቹ አይጥ አዳኞች፤ ፈረሶቹ የጦር ሜዳ ዘመቻ ጋላቢዎች ስለነበሩ እየወሰዱ ተዳቅለዋል። ሳንዲያጎ በሚገኘው ግዙፉ የእንስሳት ፓርክ ውስጥ ከኢትዮጵያ የተወሰዱ አእዋፍና አሞራዎች አሉ። የአቢሲኒያ ድመቶች ማደቀያ ማኅበር ራሱን ችሎ በአሜሪካና በእንግሊዝ የተቋቋመ ነው።  እንስሳዎቹም በአቢሲኒያ ስም እስከዛሬ ይጠራሉ።
ከታች የሚታዩት ስእሎች በ«አቢሲኒያ» ስም ከሚጠሩ መካከል ጥቂቶቹ  ናቸው።

Sunday, July 22, 2012

ለማኅበረ ቅዱሳን ፍርሀት የሆነው ጉባኤ አርድዕት በጥሩ ሁኔታ እየተንቀሳቀሰ መሆኑ ታወቀ።


ብዙ ጊዜ ስለማኅበረ ቅዱሳን በሚቀርቡ ጽሁፎች ላይ አስተያየት የሚሰጡ የማኅበሩ አቀንቃኞች የሚያዩን  ስለማኅበሩ ጭፍን አመለካከት እንዳለንና ሥራውን ሁሉ እንደምናቃወም አድርገውን ነው። ይሁን እንጂ ማኅበሩ እንደማኅበር የሰዎች እንጂ የቅዱሳን መላእክት ስብስብ ባለመሆኑ በጉዞው ውስጥ መልካምም ይሁን መጥፎ ሰውኛ ድክመቶች የሚገለጽበት መሆኑን ሁሉም አምኖ እንዲቀበልና ጥንካሬው ለቤተክርስቲያን ጠቃሚ እንደሚሆን ሁሉ ድክመቱም አሉታዊ ተጽእኖ እንደሚያመጣ በመገንዘብ ራሱን እንዲያይ፤ እኛም ማን መሆኑን በማወቅ የተሻለ ግንዛቤ ይዘን እንደባህሪው  የበኩላችንን ድርሻ እንድንወጣ ነው። ለስህተት ትምህርቶችን የአዞ እንባ አፍሳሽነት፤ የሁሉን አውቃለሁና ጠበቃ ነኝ ባይነት መጥፎ ዐመል፤ የእኔ ላቡካው፤ እኔው ልጋግረው ግብዝነት፤ ከቤተክርስቲያኗ ኪስ ወደራስ ጓዳ የመሰብሰብ አባዜ፤ የሰላይ፤ የመቺ፤ የአሳዳጅና የፈራጅ ቡድን የማዋቀር ሲሲሊያዊ አካሄዱን ነቅሰን በማውጣት ይህን፤ ይህን ስትሰራ ቆይተሃል፤ ይህን ይህንንም እየሰራህ ትገኛለህ፤ መረጃዎቻችንም እነዚህ ናቸውና ከተነቃብህ እራስህን አርም፤ አስተካክል ወይም ቢያንስ ራስህን እስኪ  ጠይቅና ከሚወራው ውስጥ የትኛው እውነትና የትኛውስ ስም ማጥፋት ነው ብለህ ፈትሽ በማለት ለማሳሰብ ነው።  እኔ ቅዱስ እንጂ ስህተት የማይጎበኘኝ ነኝ ማለት ሲያበዛ ደግሞ አንተ ፈሪሳዊ ሆነህ ሳለ መጸብሐዊው አይጸድቅም የምትል ግብዝ ነህና መንገዳችንን አትዝጋ፤ የናቡከደነጾር የህልም ሀውልት ስለሆንክ ከተራራው የሚወርደው ዐለት ይፈጭሃልና ግዙፍነትህን አይተህ አትመካ እንለዋለን። ሌላውም  እንዲያይ የእስከዛሬ ማንነቱን ገልጠን ለሌሎች እናሳያለን። በዚህም ሥራችን ብዙዎች ራሳቸውን እንዲጠይቁ፤ የሚባለውን እውነትነት እንዲመረምሩ አድርገናል። በዚህም የመረጃ ስርጭትና ማንነቱን የመግለጽ ሥራችን ግምገማቸውን ወስደው ራሳቸውን ከማኅበሩ ክፉ ስራ ያገለሉ ብዙዎች ናቸው። ተሸፍኖ የነበረባቸውን የማኅበሩን ማደንዘዢያ መርፌ ነቅለው ከድንዛዜ ወጥተው፤ እስከዛሬ የት ነበርኩ? ያሉና ራሳቸውን የጠየቁ ብዙዎች ናቸው። ከዚህ በታች ያለውም የማኅበረ ቅዱሳን አቀንቃኝ ብሎጎች ማጭበርበርና የነፍስ ውጪ፤ ነፍስ ግቢ ውሸት ማሳያ ቀርቧልና  ሄዳችሁ ብሎጎቹን አንብባችሁ ከታች በቀረበው መረጃዎች ላይ ተመርኩዛችሁ ማቅ ማን መሆኑን ተመልከቱ! ሁሌም ውሸት! ውሸት! ውሸት! አቤት ማቅ?
ምንጫችን፤ ዓውደ ምሕረት ብሎግ፤

  •     ሊቀ ሥዩማን ኃይለ ጊዮርጊስ መኪና አልተቀማም
  •     ጉባኤ አርድእት ስብሰባ እንዳይሰበሰብ አልታገደም
  •     መንግስት ለማኅበረ ቅዱሳን የሰጠውን ማስጠንቀቂያ ማንም አልሰማም በማለት ወደ ጉባኤ አርድዕት ለማዞር ሞክረዋል
የማኅበረ ቅዱሳን ብሎጎች በተለመደው ዋሾ ባህሪያቸው ያልሆነውን ሆነ እያሉ መዘገብን ቀጥለውበታል፡፡ ስለጉባኤ አርድዕት በመፈራረቅ በሰሩት ዜናም ገና በመደራጀት ላይ ያለውን ጉባኤ ተፈረካከሰ ተልፈሰፈሰ ሄደ ተመለሰ እያሉ የጅል ምኞታቸውን ይነግሩን ይዘዋል፡፡ ሊቀ ሥዩማን ኃይለጊዮርጊስም በጠቅላይ ቤተክህነቱ ምክትል ሥራ አስኪያጅ አቶ ተስፋዬ ፊርማ መኪናው ስለተበላሸ ቅያሪ መኪና እንዲሰጠው የትብብር ደብዳቤ እንደተፃፈለት እያወቁ  ደብዳቤውን ከኛ በቀር ማንም አያገኘውም በማለት ተበላሽቶ ወደ ጋራዥ የገባውን መኪና ተቀማ በማለት ዘግበዋል፡፡
እነዚህ የማኅበሩ የውሸት ቃል አቀባይ የሆኑ ደጀ ሰላምና አንድ አድርገን የተባሉት ብሎጎች በጉዳዩ ላይ እርስ በእርሳቸው እንኳ መስማማት አቅቷቸዋል። ዋሽቶ ስምምነት የት አለና? ደጀ ሰላም ኃይለጊዮርጊስ መኪና የተቀማው በአቡነ ጳውሎስ ትዕዛዝ ነው ብላ ጀምራ ወደ ታች ወደ ወረድ ሲባል ደግሞ በምክትል ስራ አስኪያጁ በተስፋዬ ነው በማለት ራስዋን ተጣልታ ዘግባለች። አንድ አድርገን ደግሞ በምክትል ሥራ አስኪያጁ አቶ ተስፋዬ ነው ትላለች።
እውነታው ግን ሌላ ነው በምክትል ሥራ አስኪያጁ አቶ ተስፋዬ ፊርማ ተፈርሞ የወጣው ደብዳቤ እንደሚያስረዳው የኃይለጊዮርጊስ መኪና በብልሽት መቆምዋን እና እንዲያውም ተለዋጭ መኪና እንዲፈለግለት ልማትና ክርስቲያናዊ መምሪያን የሚጠይቅ ነው።
 ደብዳቤውን ለማንበብ ( እዚህ ይጫኑ )

Friday, July 20, 2012

የአዲስ አበባ ሃገረ ስብከት ማኅበረ ቅዱሳን በስራዬ ጣልቃ እየገባ ስላስቸገረ አደብ ይያዝልኝ አለ

(ሐምሌ 13 2004 ዓ.ም. ፣አውደ ምህረት/www.awdemihret.blogspot.com)ማኅበረ ቅዱሳን በማን አለብኝነት ወዋቅራዊ አሰራርን በመጣስ በአዲስ አበባ ሃገረ ስብከት ሥራ ላይ ጣልቃ በመግባት በስሩ የሚገኙ ገዳማትንና አድባራትን ሰበካ ጉባኤ ስብሰባ እየጠራ በቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠውን ከሶስተኛ ወገን የሚገናኝበትን መመሪያ እየጣሰ ይገኛል ሲል የአዲስ አበባ ሃገረ ስብከት አስታወቀ፡፡ ለተጻፈው ደብዳቤ ( እዚህ ይጫኑ )
ይህ የመዋቅር ጥሰት አግባብ ያልሆነ ስለሆነ ሃገረ ስብከቱ “…ማኅበሩ በሃገረ ስብከታችን ጣልቃ እየገባ የሚያስተላልፋቸውን ጥሪዎችና የመዋቅር ጥሰቶች እንዲያቆም…”የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት አካሄዱን የሚያተካክልበት መመሪያ እንዲሰጥልን እናሳስባለን ብሏል፡፡
ከፅንሰቱ ጀምሮ አመጽ በቀል የሆነው ማኅበር እኔ ያልጣድኩት ድስት አያስፈልግም እያለ በተለያየ ሥራዎች ላይ ጣልቃ በመግባት ለቤተክርስቲን የሚጠቅም ሥራ ከመስራት ይልቅ የማኅበሩን ገጽታ በመገንባት ሥራ ላይ ተጠምዶ ይገኛል፡፡  ህዝብ ወደ እግዚአብሔር እውነት የሚደርስበትን መንገድ ከማመቻቸት ይልቅ ቤተክርስቲያን ያለህዝብም ቢሆን በማኅበሩ ቁጥጥር ሥር የምትውልበትን ስራ በመስራት ላይ ያለው ማኅበር ባልተፈቀደለት የስራ መስኮች እየገባ በማን አለብኝነት እየበጠበጠ ነው፡፡
ደፋሩ ማኅበር ለመምሪያዎች ከተለያዩ አካለት የሚመጡ በየስልጠና ጥሪዎችን መምሪያዎች ውስጥ ባሉ ሰዎቹ አማካኝነት ደብዳቤ እያስከፈተ መምሪያው ሳያውቅ በመምሪው ስም ስልጠናዎችን የማኅበሩ ሰዎች እንዲወስዱ እያስደረገ መሆኑ ሲታወቅ ከዚህ በፊት እንዲህ ያለ ሁኔታ ሲከሰት ከማዘን ያለፈ ተቃውሞ ሳይሰማ ቀርቶ ነበር፡፡ ይህም የልብ ልብ እየሰጠው በሃገረ ስብከቶችና በአጠቃላይ በቤተክኅነቱ ስራዎች ላይ ጣልቃ በመግባት ማኅበረ ቅዱሳን ወይም ሞት ፉከራን እያሰማ ይገኛል፡፡
እንደ አንድ አለሌ ሽፍታ የተወሰኑ እበላ ባይ ጳጳሳትን ማስገበሩ የልብ ልብ እየተሰማው ምንስ ባደርግ ምን እሆናለሁ ያሻኝን ሰርቼ ወጥቼ እገባለሁ እያለ በአንድ መጠምሻ ጎረምሳ ስሜት የሚንቀሳቀስ ማኅበር መሆኑ ለቤተክርሰቲኒቱ አደጋ እየሆነ መምጣቱን ያሳያል፡፡
የቤተክርሰቲያንን ክፍተት ለመሙላትና አደጋዋን ለመቅረፍ በሚል አባባይ ቃል የታገዘው የማኅበሩ አካሄድ ግቡ ቤተክርስቲኒቱን በማኅበሩ መተዳደሪ ደንብ እንድትመራ ማድረግ ሲሆን ዶግማዋም ቀኖናዋም ማኅበሩ እንዲሆን የሚያስገድድ አካሄድ እየተከተለ መሆኑ የአደባባይ ሚሥጢር ሆኗል፡፡
የአንድ ተቋም ትክክለኛነት ከሚለካበት መንገድ አንዱ ህጋዊ መዋቅሮችን አክብሮ መንቀሳቀስ መቻሉ ነው፡፡ ያለ ሕጋዊ መዋቅር ህግ እና እውነት የበላይነት ይዘው መቀጠል የማይችሉ መሆናቸው እውነት ነው፡፡ ማኅበረ ቅዱሳን ግን ህግ የት እንዳለ የሚያስታውሰው ሌሎችን ለመምቻ የሚጠቅመው ከሆነ ብቻ ነው፡፡ የማኅበሩን ፍላጎት ለማስጠበቅ  ግን እስካዋጣው ድረስ በህጋዊ አሰራር እሱም ካላዋጣ የወንጀል ድርጊቶችን ጨምሮ የትኛውንም ህገ ወጥ አካሄድ ለመጠቀም ወደ ኋላ የማይል ድርጅት መሆኑን እስካሁን ያሉት ተሞክሮዎቹ ያስረዳሉ፡፡