Thursday, December 29, 2011

እውነትም ፍቅር ትቀዘቅዛለች!


ሩቅ ሳንሄድ ኢትዮጵያ ውስጥ እስላሙ በክርስትያኑ ላይ «የአላሁአክባር» ዘመቻውን በደንብ እያስፋፋው ስለመገኘቱ ከታች ባለው ርእስ የተመለከተው የቪዲዮ ምስል ማሳያ ነው። እራሱ ክርስቲያን ነኝ የሚለው ኦርቶዶክሱ እርስ በእርሱ እየተባላ፣ እየተካሰሰ፣ የአሸናፊነት ከበሮ ለመደለቅ በአንድ ወገን ሲኖዶሱ እርስ በእርስ፣ በሌላ ወገን ማኅበረ ቅዱሳንና ደጋፊዎቹ በእነ በጋሻው ላይ የተያዘ የሞት ሽረት ትንቅንቅ፣ በእስልምናው በራሱ የሱኒና የሐነፊ ሽኩቻ በመጨረሻው ዘመን የተነገረው ትንቢት እየደረሰ ይሆን? ያስብላል። «ሕዝብ በሕዝብ ላይ መንግሥትም በመንግሥት ላይ ይነሣልና፥ ራብም ቸነፈርም የምድርም መናወጥ በልዩ ልዩ ስፍራ ይሆናል» ማቴ 24፣7ከሁሉ የሚገርመውና ትንቢቱን በትክክል የሚያረጋግጥልን ነገር ክርስቶስ በተወለደበት ቤተልሔም መቅደስ የፈረንጆቹ ገና በሁለት ወገን ጦርነት ደምቆ መዋሉ ነው። ኳኳታና የሰው ግንባር ፍንዳታ በተሰማበት አዲስ ዜማ በቤተክርስቲያኑ ውስጥ ክርስቲያን ቀርቶ አረሚ የማያደርገውን ፈጽመው አክብረው ዋሉ። እውነትም «ከዓመፃም ብዛት የተነሣ የብዙ ሰዎች ፍቅር ትቀዘቅዛለች» ማቴ24፣12 ያለው ደርሷል። ግሪኮችና አርመኖች ተፈጣፈጡ!!



Wednesday, December 28, 2011

የኢየሱስ ክርስቶስ አስታራቂነትና አምላክነት

«ክርስቶስ ማለት በቁሙ ወደአማርኛ የተገለበጠው የግሪኩ(ጽርእ)ቃል «Χριστός»«ክሪስቶሽ ሲሆን ትርጉሙም «የተቀባ» ማለት ነው። መቀባት « χριστῷ» የሚለውን ብቻውን የሚያመለክተው ከሌላ መቀበልን ሲሆን «ክርስቶስ» የሚለው ቃል ግን የቅብእ ባለቤትነትንና የመቀባት ግብርን አያይዞ የሚጠራ ስም ነው። (ኢሳ 45፣1) ይመልከቱ። «ክርስቶስ» በእብራይስጡ «המשיח» ሀመሺያኽ ቅቡእ፣ የተቀባ ሲሆን ግእዙ «መሲህ» በሚለው ይተካዋል። የቤተክርስቲያን ሊቃውንትም «የክርስቶስን መቀባት ወይም ቅቡእ መሆን ለማመልከት ሲያስተምሩ «አብ ቀባኢ፣ ወልድ ተቀባኢ፣ መንፈስ ቅዱስ ቅብእ» በማለት ይገልጻሉ። በእርግጥ ይህ ትምሕርተ መለኰት ሰፊና ጥልቅ እንደመሆኑ መጠን በዚህ ዙሪያ የተነሱ ትምህርቶችና ክርክሮች ብዙ ሲያምሱ ቆይቷል፣ ዛሬም ቢሆን ጨርሶ የጠፋ ስለመሆኑ የሚታወቅ ነገር የለም። እኛም ያንን ላለመድገም እንደመንደርደሪያ ይህንን ያህል ካልን ወደተነሳንለት ዓላማ እናምራ!
«ክርስቶስ» የተቀባ ማለት ነው ብለናል። እንደዚሁ ሁሉ «ኢየሱስ» የሚለውን ስንመለከት የእብራይስጡ «ישוע» የሹአ ሲሆን ትርጉሙም «መድኃኒት» ማለት ነው። ግሪኩም «Ιησούς» መድኃኒት፣( ማዳን)፣ አዳኝ የሚለውን ትርጉም ይሰጣል። ከዚህ የተነሳ «ኢየሱስ ክርስቶስ» ማለት «የተቀባ፣ቅቡእ እና መድኃኒት፣ አዳኝ» የሆነ ማለት ነው። ይህንን የስም ትርጉም ካገኘን ለሚቀጥሉት ሃሳቦቻችን መረዳት መጠነኛ ግንዛቤ ጨብጠናል ማለት ነው።
የሚቀባው ማነው? የሚቀባውስ ለምንድነው?
እነዚህን ነገሮች አጥርቶ ማወቅ የብሉይ ኪዳን አስተምህሮዎችን መመርመር ግድ ይላል። ያንንም ማድረግ አስፈላጊ የሚሆነው «ስለመሲሁ» ክርስቶስነት ላይ በሚነሱ ልዩ ልዩ አመለካከቶች ከብዥታ የወጣ እይታ እንዲኖረን ይረዳናል።
ሙሉውን ጽሁፍ ለማንበብ........>>>(እዚህ ላይ ይጫኑ

Thursday, December 22, 2011

መጋቤ ሀዲስ በጋሻው ደሳለኝ የአራዳውን ምድብ ችሎት በመሳጭ ስብከቱ አስደመመ


ጽሁፉን በፒዲኤፍ ማንበብ ከፈለጉ ........>>>To read in PDF click here


ታህሣሥ 9 ቀን 2004 ዓ.ም በዋለው የአራዳው ምድብ ችሎት የዐቃቤ ሕግ አንደኛ ምሥክር ሆኖ የቀረበው መጋቤ ሀዲስ በጋሻው ደሳለኝ ችሎቱን ፍጹም ወደ ሆነ መንፈሳዊ ድባብ ለውጦ አስተምሮ መውጣቱን የዜና ምንጮቻችን አረጋገጠዋል፡፡ ዘመድኩን በቀለ በግሉ አርማጌዶን ቁጥር አንድ እና ቁጥር ሁለት ሲዲና ቪሲዲ በማሠራጨት እና የተሳሳተ መልዕክት በማስተላለፍ ምዕመናንን በማወናበዱና በወንድሞች ላይ የስም ማጥፋት ዘመቻ በመክፈቱ በአራዳው ምድብ ችሎት ላይ ክስ የተመሠረተበት ሲሆን እርሱ ራሱ የ"ማኅበረ ቅዱሳን" አባል የሆነ ጠበቃ አቁሞ ለመከላከል ሞክሯል፡፡ በዚሁ ዕለት ከቀኑ 8፡00 ሰዓት እስከ 10፡25 በቆየው የክርክር ሂደት የዘመድኩን ጠበቃ የተልፈሰፈሰ መስቀለኛ ጥያቄ ለማቅረብ ሞክሮ በታዳሚው ሲሳቅበት እንደዋለ እነዚሁ ምንጮቻችን አስታውቀዋል፡፡

ጠበቃው ባቀረበው መስቀለኛ ጥያቄ ቤተክርስቲያንን "አሮጊቷ ሣራ" ብለህ ተሳድበሃል፤ ታዲያ ቤተክርስቲያንን በምንፍቅና ጥለው ከሄዱት ከእነ አባ ዮናስ በምን ትለያለህ? ብሎ የጠየቀው ሲሆን፣ መጋቤ ሀዲስ በጋሻው በሰጠው ምላሽ፣ እናታችን ሣራ በዕድሜ ብታረጅም፣ እግዚአብሔር አከበራት፤ ልጆችን ሰጣት፡፡ እኔም፣ ጥንታዊት ቤተክርስቲያናችን በአሁኑ ሰዓት በማገልገል ላይ ያሉትን ወንድሞችና እህቶች አገልጋዮችን አፍርታለች ነው ያልኩት፡፡ የእኛ ሣራ ልጆችን ወልዳለች፤ የእነ አባ ዮናስ ሣራ ግን ስለመወለዷ አይታወቅም፤ በዚህ እንለያለን በማለት መመለሱ ታውቋል፡፡

መጋቤ ሀዲስ በመቀጠል የቀረበለት ጥያቄ፣ ራስህን በራስህ ሰባኪ አድርገሃል፤ የቤተክርስቲያን ትምህርት ሳይኖርህ ታስተምራለህ፤ ለመሆኑ ዲቁናውን ማን ሰጠህ? መጋቤ ሀዲስ የሚለውንስ ማዕረግ ከወዴት አገኘኸው? የሚል ነበር፡፡ እርሱም በበኩሉ ሲመልስ፣ ዲቁናውን የተቀበልኩት ከብፁዕ አቡነ በርተለሜዎስ የቀድሞው የሲዳማ፣ ጌዴኦ፣ አማሮና ቡርጂ ዞኖችና ልዩ ወረዳዎች ሀገረ ስብከት ሊቀጳጳስ ነው፡፡ የስብከት መምህርነት ኮርስም ተከታትዬ የተሰጠኝ የምሥክር ወረቀት አለኝ፡፡ የመጋቤ ሀዲስነት ማዕረጉንም ሰባ ሺህ ያህል ሕዝብ ባለበት የሰጡኝ ብፁዕ አቡነ ፋኑኤል በዚያን ወቅት የሀገረ ስብከቱ ሊቀጳጳስ ናቸው፡፡

መምህር በጋሻው ሌላው የቀረበለት ጥያቄ የእኛ ጌታ ተኝቶ ይገዛል ብለሃል፡፡ ይህ አባባልህ ልክ ነው? የሚል ነበር፡፡ እርሱም ሲመልስ ታዲያ ይሄ ምን ስሕተት አለው? ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከደቀመዛሙርቱ ጋር በጀልባ ሲጓዝ፣ ተኝቶ ነበርና ማዕበሉ በተነሳ ጊዜ ሲቀሰቅሱት፣ እምነት የጎደላችሁ ስለምንድርነው አላላቸውም? በከርሰ መቃብር ሦስት መዓልትና ሦስት ሌሊት ባደረበት ወቅት ዓለምን አልገዛም? ጌታችን፣ አምላካችን በሰው አስተሳሰብ የተኛ ፣ የሞተ ቢመስልም እርሱ ግን ሁሉንም በኃይሉ ይጠብቅ ነበር፤ በማለት መልሷል፡፡ መጋቤ ሀዲስ በጋሻው ሌሎችንም ተጨማሪ ማብራሪያዎችን የሰጠ ሲሆን፣ እርሱ ጥያቄዎችን በሚመልስበት ወቅት ሁሉም ከመመሰጡ የተነሳ የችሎቱ ሂደት ስብከተ ወንጌል አዳራሽ እስከሚመስል ደርሶ እንደነበር በስፍራው የነበሩ እማኞች ገልጸዋል፡፡

Wednesday, December 14, 2011

ማደናገር ይቁም! የሰንበት ት/ቤቶች ማ/መ ድረገጽ


«ADOBE OF GOD»በሚል ርእስ የክርስቶስ ኢየሱስን የማዳን ስራ የሚያጥላላና ፍጹም ክህደት የተሞላበት ፊልም ኢትዮጵያ ውስጥ ሊሰራ እንደነበር በባለፈው ወር የወጡ መረጃዎች ያመለክታሉ። በእርግጥም ከ75% በላይ ሕዝብ ክርስትናን በአንድም በሌላ ምክንያት ተቀብሎ የሚኖርና በአብዛኛውም ይህንኑ የእለት ከእለቱ መመሪያ አድርጎ በሚቀበል ሀገር ላይ ይህንን መሰሉን ፊልም መስራት መርገም ካልሆነ በረከት ያመጣል፣ ተብሎ አይታሰብም። ክርስቶስን ለማዋረድ መፈለግ ከክርስቶስ ማንነት ላይ አንዳች የሚያጎለው ነገር ባይኖርም
«የማያምኑ ቢኖሩ አለማመናቸው የእግዚአብሔርን ታማኝነት ያስቀራልን?» ሮሜ 3፣3 እንዳለው ክርስቶስ ዛሬም፣ ነገም ያው እሱ መሆኑ ሳይጎድል አምልኰና ክብር በሚገባው ቦታ ተሳልቆና ክህደት ሲተካ ግን የረድዔትና የበረከት እጁን ላለመቀበል በፈለግነው ልክ የዚህ ዓለም ገዢን ማስተናገድ በመሆኑ ሊያስደነግጠን እንደሚገባ ለአፍታ መዘናጋት የለብንም። ይህንን ድርጊት ለምእመናንና ምእመናት በማዳረስ በመረጃው ላይ የወል ግንዛቤ ወስዶ አቋማችንን ለሚመለከተው ለማድረስ ሚዲያዎች ሰፊ ዘገባቸውን ሰጥተው ሰርተዋል። ይህ ሊመሰገን የሚገባው መንፈሳዊ ተግባር ነው። ይሁን እንጂ አንዳንዶች ራሳቸውን የዚህ ጥረትና ትግል ዋነኛ አካል አድርገው የኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ማእከላዊ ጽ/ቤት ግን «ፊልሙ እንዲሰራ ፈቅዷል» በማለት ድካምና ጥረቱን ውሃ በመቸለስ ከችግሩ ጎን ለጎን የችግሩ ዋነኛ ምህዋር እንደነበር ለማሳየት መሞከራቸው አስገራሚ ሆኗል። ከነዚህም መካከል የማኅበረ ቅዱሳኑ ሌላኛው እጅ የ«ደጀሰላም» ድረገጽ ከለጠፈው በኋላ ቤተክህነቱን የወነጀለበትን ጽሁፍ ያውርድ እንጂ ወንድሙ የሆነው «አንድ አድርገን» ለማንበብ ይህን ይጫኑ
እስካሁን ያስነብበናል። «ማኅበረ ቅዱሳን የቤተክህነት እዳ» በተሰኘው መጽሐፍ እንደተጠቆመው «እንቁ» መጽሔት የማኅበረ ቅዱሳን የእጅ አዙር መጽሔት መሆኑን ለመረዳት ብንችል ሁሉም በአንዴ ተቀባብለው ቤተክህነቱን ያለስራው ስም ሰጥተው «ADOBE OF GOD» ለተሰኘው የክህደት ፊልም ትብብሩን ሰጥቷል ሲሉ መጻፋቸው ካንድ ወንዝ መቀዳታቸውን እንደሚነግሩን እንገነዘባለን። የቤተክህነቱ ሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ነገሩ እጅግ ቢያስመርረው በድረገጹ ለተባለው ፊልም ከታቃውሞ ውጪ ድጋፍ አለመስጠቱን አስነብቦናል።
ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ

Friday, December 9, 2011

የጳጳሳት ጆሮ የተነፈገው የአዲስ አበባ ካህናት ጩኸት!


የጳጳሳት ጆሮ የተነፈገው የካህናት ጩኸት(to read in PDF click here)

ከደጀብርሃን፣

የአዲስ አበባ ሀ/ስብከት የገንዘብና የንብረት ዘረፋ ሀገር ያወቀው፣ፀሐይ የሞቀው ጉዳይ ነው። ኰሌጅ፣ ሙአለ ህጻናት፣ አውቶቡስ፣ ታክሲ፣ ሆቴል፣የተለያየ ደረጃ ያላቸው ህንጻዎች፣ ሱቆች፣ የሚከራዩ አፓርትማዎች፣ የቤትና የንግድ መኪናዎች ያላቸውን አስተዳዳሪዎች፣ ፀሐፊዎች፣ ሂሳብ ሹሞች፣ የቁጥጥር ሠራተኞች፣ገንዘብ ያዢዎችና ንብረት ክፍሎችን ማየት እንግዳ ነገር አይደለም። ይህንን ሁሉ ሀብት ሲያጋብሱ የቀድሞ ደመወዛቸው ቢበዛ የአስተዳዳሪው ከአንድ ሺህ አምስት መቶ ብር የሚበልጥ አልነበረም። የሌሎቹ ደግሞ ሺህ ብር ባልገባ ደመወዝ ነበር ይህንን ሁሉ ሃብት ማፍራት የቻሉት። የዘረፋ ቁንጮ እንደሆነ የሚነገርለትና አውቶቡስ፣ ት/ቤት፣ ትልቅ ህንጻ እንዳለው የሚነገርለት (ሊቀ ሊቃውንት)አባ እዝራ የሚባለው የሽማግሌ ማፊያ ለዚህ የሚጠቀስ አብነት ነው። ሊቀሊቃውንት ብላ ቤተክርስቲያን የምትጠራው ጡቷን ምጎ፣ ምጎ አጥንቷን ስላወጣው እውቀቱ ይሆን? ይህንን እንግዲህ እውቅና የሰጠው ሲኖዶስ የሚባለው የአባቶቹ ማኅበር ያውቃል። ሌሎቹንም የዘረፋ ሊቀ ሊቃውንት በስምና በአድራሻ ማንሳት ይቻላል። የሚያሳዝነው ግን ንቡረ እድ አባ ገ/ማርያም ገ/ሥላሴን ከአዲስ አበባ ሀ/ስብከት ሥራ አስኪያጅነት ለማስነሳት የዘመቻው ፊት አውራሪዎች እነዚህ የቤተክርስቲያንን ሀብት እያገላበጡ የሚዘርፉ የቀን ጅቦች መሆናቸው ነው። ከማሳዘን አልፎ የሚገርመው ንቡረ እድ አባ ገ/ማርያም የቀን ጅቦቹን አፍ የዘጉት በየትኛውም የቤተክርስቲያን ገንዘብና የንብረት ቆጠራ ላይ አስተዳዳሪው፣ ፀሐፊውና ሂሳብ ሹሙ እጃቸውን ሳያስገቡ ቁጭ ብለው እንዲመለከቱና አገልጋይ ካህናቱ ብቻ በአንድነት ቆጥረው የተገኘውን ገንዘብ በሞዴል 64፣ የገባውን ንብረት በሞዴል 19 ገቢ አድርገው በግልጽ መጠበቅና ማስጠበቅ መቻላቸውን ሲኖዶስ የሚባለው ስብስብ እያወቀ ወይም ማወቅ ሲገባው ለዘራፊዎቹ ጩኸት ምላሽ በመስጠት ባለፈው ጉባዔ ሥራ አስኪያጁን ከቦታው እንዲነሱ አድርጓል።
ከ5 ሚሊዮን ያላለፈውን ለጳጳሳት ደመወዝና ሥራ ማስኬጃ ፈሰስ የሚደረገውን የጠቅላይ ቤተክህነት ገቢ ወደ 27 ሚሊዮን ከፍ ስላደረጉላቸው ሽልማት መስጠቱ ይቅርና ይህንን አጠናክረህ ቀጥል ማለት አቅቷቸው እንደጥፋተኛ ሰው የልማቱን አባት ለቦታው አትሆንም ብሎ ማንሳት ሲኖዶስ በእውነት በመንፈስ ቅዱስ የሚመራ ነው? የሚያስብል ነገር ነው። የአባ ገ/ማርያምን መነሳት የሚሹ ወገኖች(ፓትርያርኩን ጨምሮ) የዝውውር ጥያቄ ውድቅ ሊያስደርግ የሚችል ተግባር ለማየት ሲኖዶስ የሚባለው ክፍል በመንፈሳዊነት ደረጃ ይቅርና በመስማትና በማሽተት እንዴት ሳይረዳው ቀረ? ይልቁንም ጊዜውን በአባ ሠረቀ ጉዳይ ላይ የማኅበረ ቅዱሳንን ውክልና በማስፈጸም መጠመዱን ስራዬ ብሎ ዋለ እንጂ!! እውነትም የመንፈስ ቅዱስ ጉባዔ!!!!!!!
ከታች የቀረበው በሰዓታቱ፣በማኅሌቱ፣በቅዳሴው፣በፍትሃቱ ሌሊትና ቀን እየጮሁ ቤተሰቦቻቸውን የሚያስተዳድሩ ካህናት ጩኸትና ትዳር አንፈልግም፣ እኛ መንኩሰናል፣ እያሉ ግን ብዙውን ጊዜያቸውን ሽቶ የተለወሰ ቀሚሳቸውን አስረዝመው፣ ወለተማርያም፣ወልደ ማርያም እያሉ የመበለት ቤቶችን የሚበዘብዙ አስተዳዳሪዎች መካከል የተደረገው የአቤቱታ ክርክርና ከላይ እስከታች ረዳት የሌለውን ካህን ድምጽ የሚያሳይ ነውና መልካም ንባብ ይሁንልዎ!! ኅሊናዎትም ፍርዱን ይስጥ!!ከታች ያለውን ተጭነው ያንብቡ!(http://dejebirhan.blogspot.com)

Thursday, December 8, 2011

መጽሐፈ ሰዓታት ምን ይላል?

                               መጽሐፈ ሰዓታት.............to read in PDF click here





«ሰዓሊ ለነ ሰንበተ ክርስቲያን ቅድስት፣
ለውሉደ ሰብእ መድኃኒት፣
ወእስከ ለዓለም ሰፋኒት» ትርጉም--ለሰው ልጆች መድኃኒትና እስከዘለዓለም ገዢ የሆንሽ፣ የክርስቲያን ሰንበት ሆይ ለምኝልን ማለት ነው።
ሰንበተ ክርስቲያን የተባለችው ዕለት ለሰው ልጆች መድኃኒት በመሆኗ እንዲሁም እስከዓለም ፍጻሜ የሰው ልጆች ገዢ ስለሆነች እንድታማልደን እንጠይቃት ማለቱን መጽሐፈ ሰዓታት ይጠቁመናል።
እዚህ ላይ ጥቂት ጥያቄዎችን እናንሳ።
1/ሰንበተ ክርስቲያን የምትባለው ምናልባትም ዕለተ እሁድ ናት። ሐዲስ ኪዳን ግእዙ «ወበእሁድ ሰንበት መጽአት ማርያም መግደላዊት ኀበ መቃብር»ዮሐ20፣1 «ማርያም መግደላዊት ወደመቃብር በሳምንቱ መጀመሪያ ቀን መጣች»ይላል። ምንም እንኳን የእብራይስጡም ሆነ የጽርዑ መጽሐፍ ቅዱስ እሁድ ሰንበት የሚል ቃል ባይዝም እሁድ ብለው ያስቀመጡትን የግእዝ ተርጓሚዎች ተከትለን ብንሄድ እሁድ የተባለችው ቀን---
ሀ/እንዴት ሆና ነው የሰው ሁሉ ገዢ የምትሆነው?
ለ/ እሁድ በምን አፏ ነው የምልጃ ቃልን የምታሰማው?
ሐ/ እሷስ ከማነው የምታማልደን?
ሐ/ከሳምንቱ እለታት የተለየች ናት ካልን የጌታ እለታት ያልሆኑት የትኞቹ ናቸው?
መ/ድርሳነ ሰንበት የተሰኘው መጽሐፍ «ሰንበት» ማለት ኢየሱስ ክርስቶስ ነው ይለናል። ታዲያ ሰንበት የተባለው መድኃኔዓለም ያማልደናል ማለታቸው ነው?
2/ አስታራቂና አማላጅ የሆነችው እለተ ሰንበት ስለመሆኗ የተቀመጠ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ማስረጃ ምንድነው?
ሐዋርያው ጳውሎስ ለገላትያ ሰዎች ወንጌልን ከሰበከላቸው በኋላ ወደቀደመው ከንቱ የሆነ አምልኰ ሲመለሱ ተመልክቶ እንዲህ ብሎ ነበር።
«ነገር ግን በዚያን ጊዜ እግዚአብሔርን ሳታውቁ በባሕርያቸው አማልክት ለማይሆኑ ባሪያዎች ሆናችሁ ተገዛችሁ» ገላ 4፣8
እንደዚሁ ሁሉ እለተ እሁድ እግዚአብሔር ከቀናት እንደአንዱ የሰራት መሆኗ ተረስቶ ልክ አማልክት ወደመሆን የተቀየረች ይመስል አስታርቂን፣አማልጂን ማለት ጳውሎስ በባህሪያቸው አማልክት ለማይሆኑ ባሪያዎች ሆናችሁ የተገዛችሁ ነበረ ያለውን ቃል እኛ ዛሬም እየፈጸምን መገኘታንን ያሳያል።

Wednesday, December 7, 2011

የጴንጤ መዝሙር ያዳመጠስ?

የበጋሻው ግጥም ስህተት የለውም!
በጋሻው ደሳለኝን በተመለከተ አንዴ ጻድቅ ነው፣ አንዴ ደግሞ ኀጥእ ነው እንደሚለው ማኅበረ ቅዱሳንና ልሳኖቹ በሆኑት ደጀሰላም፣ አንድ አድርገን  በመሳሰሉት እንደሚናገሩት ኀጥኡን ለመኮነን ወይም ጻድቁን ለማጽደቅ የኛ ድርሻ ስላልሆነ እንዲሁም  ቃለእግዚአብሔር አይፈቅድልንምና በዚህ ዙሪያ የምንለው ነገር አይኖርም።
ሁለተኛው ደጀሰላም የሆነው «አንድ አድርገን» የበጋሻውን ከሀዲነት የሚገልጽ የግጥምና የመዝሙር ቅንብር በማቅረብ ለማጋለጥ ሞክሯል። እስኪ በዚያ ላይ ተንተርሰን ጥቂት ሃሳብ እንስጥ። ለፍርድ ያመች ዘንድ ግጥሙን ለማሳያነት በጥቂቱ ኮፒ አድርገነዋል።

የፕሮቴስታት                                                                  የኦርቶዶክስ
ካልባረከኝ አለቅህም ካልባረከኝ አለቅህም-                      ካልባረከኝ አለቅህም ካልባረከኝ አለቅህም
 አምላኬ ነህ ለዘላለም                                                 -አምላኬ ነህ ለዘላለም
ጌታዬ ነህ ለዘላለም                                                       ጌታዬ ነህ ለዘላለም
ለብቻዬ ልኖር ፈቃድህ ከሆነ                                           ሊነጋ ሲጀምር ሰማዮ ሲቀላ
ሌላው አይገደኝም ህይወቴ ከዳነ                                      ወዴት እሔዳለው ነፍሴ እንዲህ ዝላ
ሲሆን እስከ ንጋት ልታገልህና                                           እያለቀስሁ ሁሉ እከተልሀለሁ
ስደደኝ ጌታዬ ሆይ ሕይወቴን ባርክና                                   እጅህን ዘርጋልኝ በረከት እሻለሁ
በመንበርከክ ብዛት በጸሎት ትግል                                        ለብቻዬ ልኖር ፈቃድህ ከሆነ
ፈቃድህ ከሆነ ጉልበቴ ይዛል                                               ሌላውን አልሻም ሕይወቴ ከዳነ
እያለቀስኩ ሁሉ እከተልሀለሁ                                           ሲሆን እስከ ንጋትታግለሃልና ል                                                                              
እጅህን ዘርጋልኝ በረከት እሻለሁ                                       ስደደኝ ጌታዬ ሕይወቴን ባርክና

የግጥሙን መመሳሰል ወደኋላ ላይ እናቆየውና የሚታየውን እውነት ኢአመክንዮያዊ (fallacy)በመስጠት በጋሻውን ከሃዲ ለማድረግ የተሞከረበትን ስነ ሞገት እንመርምር።

Monday, December 5, 2011

ይከራከሩኛል!


                 ይከራከሩኛል
ይከራከሩኛል፣ እየተጋገዙ
በከንቱ ላይረቱኝ፣ አምላክን ሳይዙ።
እንዳገሩ ልማድ- ለተማረ ዳኛ፣
ቅጣት ይገዋል-ይህ ደፋር አፈኛ፣
ብሎ ፈረደብኝ- የወንጌል ምቀኛ።
ክርስቲያን የሆነ-ሲኖር በዓለም፣
መመርመር ነው እንጂ- ክፉና መልካም።
እውነት እስኪገለጽ አጥብቆ መድከም፣
እንዲሁ ቢያከፉት- የወንድምን ስም፣
እጅጉን ነውር ነው-ጌታ አይወደውም።
ማርያምን ጻድቃንን-አይወድም ያሉት፣
በምቀኝነት ነው- ስሜን ለማክፋት።
በክስ ቢጠይቁኝ- ስለሃይማኖት፣